en
Feedback
ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር ወደ ግሸን ላሊበላ ቁልቢ ገብርኤል እና ሌሎች ገዳማት ጉዞ እናዘጋጃለን

ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር ወደ ግሸን ላሊበላ ቁልቢ ገብርኤል እና ሌሎች ገዳማት ጉዞ እናዘጋጃለን

Open in Telegram

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ስርዓት እና ደንብ የተከተለ ሃይማኖታዊ መልእክት እሚተላለፍበት ነው ሃይማኖት እንደ አባቶቻችን ቴክኖሎጂ እንደዘመናችን! ተጠቅመን የገዳማት ታሪክ ወቅታዊ የቤ/ክ መልዕክት እና መረጃ የምንለዋወጥበት ቃለ እግዚአብሔር የምንማርበት ነ የአባቶቻችን ትምህርት እናስተምራለን ፤ ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን ፤ የተማርናት ፤ ሃይማኖት ይህች ናት:: እንኖርባታለን

Show more
579
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ታላቁ አባት የጸሎት ሰው እና የፈውስ ሀብት የነበራቸው ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ሰላማ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በአዲስ አበባ ሃሌሉያ ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ መስከረም 18 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የብፁዕነታቸውን ሽኝት መርሐ ግብር በተመለከተ በቋሚ ሲኖዶስ እንደተወሰነ ዝርዝሩን  የምናሳውቅ ይሆናል። የብፁዕነታቸው ቡረከት ይደርብን ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇                 •➢ ሼር // SHARE

​​✞ እሰይ እልል በሉ ✞ እሰይ እልል በሉ ተገኘ መስቀሉ ✞ (፪) የጥል ግድግዳ - አበባ -የፈረሰበት -አበባ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር -አበባ -የታረቀበት -አበባ የእግዚአብሔር ልጅ  - አበባ -የነገሰበት -አበባ የሞት አበጋዝ - አበባ -የወደቀበት- አበባ         አዝ = = = = = = አይሁድ በቅናት -አበባ -መስቀሉን ቀብረው - አበባ ቢከድኑት እንኳን - አበባ -በቆሻሻቸው - አበባ ጌታን መቃወም - ስለማይችሉ - አበባ ይኸው ተገኘ - አበባ -ወጣ መስቀሉ አበባ         አዝ = = = = = = ደጉ ኪራኮስ - አበባ -ሽማግሌው -አበባ እሌኒን መራ - አበባ - በደመራው  - አበባ ጌታ በሱ ላይ - አበባ - በመሰቀሉ - አበባ ጢሱ ሰገደ - አበባ - ወደ መስቀሉ - አበባ         አዝ = = = = = = የእምነት ምልክት - አበባ  - መስቀል ነውና - አበባ ተራራው ሜዳ - አበባ  - ሆነ እንደገና  - አበባ እንደ ተነሳው - አበባ  -ጌታ እንደቃሉ  - አበባ ከጉድጓድ ወጣ - አበባ - እፀ መስቀሉ - አበባ         አዝ = = = = = = እኛም በመስቀል - አበባ -እንመካለን - አበባ በእግዚአብሔር ጥበብ - አበባ -መች እናፍራለን - አበባ ሞኝነት እንኳን - አበባ -ቢሆን ለዓለም - አበባ ኃይል እፀ ወይን ነው - አበባ - ለዘላለም - አበባ         አዝ = = = = = = ግድግዳው ፈርሷል -- አበባ -  የልዩነቱ - አበባ ምድርና ሰማይ - አበባ - ሆኑ እንደ ጥንቱ - አበባ ነፍስና ስጋ - አበባ - በሱ ታርቀዋል - አበባ ሕዝብና አሕዛብ -አበባ - ወንድም ሆነዋል - አበባ

ከባለፈዉ የቀጠለ የመፅሐፍ ቅዱስ ስሞች  #ክፍል 2 1 ባሮክ ፡ ብሩክ ማለት ነዉ 2 ሮቤል፦እነሆ ወንድ ልጅ ማለት ነው። 3 ኤርምያስ፦እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል ማለት ነው። 4 ሮብዓም፦ሕዝብ ይብዛ ማለት ነው። 5 ማራናታ፦ጌታ ሆይ ና ማለት ነው። 6 ቤቴል፦የእግዚአብሔር ቤት ማለት ነው። 7 ቄርሎስ፦የተመረጠ ምርጥ ማለት ነው። 8 እስጢፋኖስ፦አክሊል ማለት ነው። 9 ሳውል/ሳኦል፦ከእግዚአብሔር የተለመነ ማለት ነው። 10 ሴዴቅያስ፦የእግዚአብሔር ጽድቅ ማለት ነው። 11 ፊቅጦር፦ኀዘኔን አራቀልኝ ማለት ነው። 12 ንፍታሌም፦ታጋይ የሚታገል ማለት ነው። 13 ዮርዳኖስ፦ወራጅ ውሃ ማለት ነው። 14 ዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው። 15 ገነት፦የአትክልት ስፍራ ማለት ነው። 16 ፊልድልፍያ፦የወንድማማች ፍቅር ማለት ነው። 17 ዲና፦ፈረደ ማለት ነው። 18 ማኑሄ፦እረፍት ማለት ነው። 19 መልሕቅ፦ከብረት የተሠራ የመርከብ ማቆሚያ 20 ራማ፦ከፍታ ማለት ነው። 21ቴዎድሮስ፦የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው። 22 ፊላታዎስ፦የአምላክ ወዳጅ ማለት ነው። 23 ሕርያቆስ፦ኅሩይ ምርጥ ማለት ነው። 24 ፊልጶስ፦ወንድም ወዳጅ ማለት ነው። 25 ቶማስ፦ፀሐይ ማለት ነው። 26 ታዴዎስ፦እሸቱ ማለት ነው።(ግብራዊ ትርጓሜ) 27 ማትያስ፦ፀሐይ ወይም ምትክ ማለት ነው። 28 ቀሌምንጦስ፦ግንብ ማለት ነው። 29 አቤል፦በግ ወይም ደመና ማለት ነው። 30 ኖኅ፦ደስታ ማለት ነው። 31 ሴም፦ተሾመ ማለት ነው። 32 ይሥሐቅ፦ደስታ አንድም ይሳቅ ማለት ነው። 33 ሙሴ፦የውሃ ልጅ ማለት ነው 34 አሮን፦የእግዚአብሔር ተራራ ማለት ነው። 35 ጌዴዎን፦እግዚአብሔር ኃያል ነው ማለት ነው። 36 እሴይ፦ዋጋየ ማለት ነው። 37 አሚናዳብ፦መንፈስቅዱስ ማለት ነው። 38 ዳዊት፦የተወደደ ልበ አምላክ ማለት ነው፣ 39 ዕንባቆም፦ጠቢብ አዋቂ አስተዋይ ማለት ነው። 40 ሄኤሜን፦ምኞቴን አገኘሁ ማለት ነው። 41 አሞጽ፦እግዚአብሔር ጽኑ ነው ማለት ነው፣ 42 ዮናስ፦ርግብ ማለት ነው። 43 ሐጌ፦የእግዚአብሔር መልእክተኛ ማለት ነው። 44 ራኄል፦በግዕት ማለት ነው። 45 ዕዝራ፦ረዳቴ ማለት ነው። 46 ሔርሜላ፦ከክብር ዘመድ የተገኘች ማለት ነው። 47 መርቆሬዎስ፦የአባት ወዳጅ ማለት ነው። 48 ኤጲፋንዮስ፦ምስጢር ገላጭ ማለት ነው። 49 ሜሮን፦የተባረከ ሽቱ ማለት ነው። 50 ሱላማጢስ፦ሰላማዊት ማለት ነው። 51 ሶምሶን፦ፀሐይ ማለት ነው። 52 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ ማለት ነው። 53 ማርታ፦እመቤት ማለት ነው። 54 ሊዲያ፦ፈራሂተ እግዚአብሔር ማለት ነው። 55 ኤፍሬም፦ፍሬያማ ፍሬው ማለት ነው። 56 ኤፍራታ፦ክብርት የተከበረች ማለት ነው። 57 ታዴዎስ፦ተወዳጅ ወይም ፍቁር ማለት ነው።(ቃላዊ ትርጓሜው) 58 ኢየሩሳሌም፦የሰላም ሀገር ማለት ነው። 59 ሄኖስ፦ሰው ማለት ነው። 60 ሰሎሜ፦ሰላም ማለት ነው። ማስታወሻ፦ከላይ ከጻፍኳቸው ውስጥ አንዳንድ ስሞች ከ81ዱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የማይገኙ ከሌሎች የታሪክ እና የገድል መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ስሞች መሆናቸውን ማሳወቅ እፈልጋለሁ።             

"አልጠቅምም አትበል" #በቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ ስለ ሌሎች መዳን ከማይጨነቅ ክርስቲያን በላይ ሰነፍ ሰው የለም፡፡ ወዳጄ “እኔ ድኻ ነኝና ይህን ማድረግ አልችልም” የምትል አትኹን፤ ባለ ኹለት ዲናሯ ሴት ትወቅስሃለችና፡፡ ዳግመኛም “ወርቅም ብርም የለኝም” ብሎ የተናገረ ጴጥሮስ ይወቅሰሃልና፡፡ "ምናምንቴ ነኝ" አትበል፤ እንዲህ ስትል ምናምንቴዎቹ ሐዋርያት እንዳይሰሙህ! "እኔ በሽተኛ ነኝ" አትበል፤ በሽተኛው ጢሞቲዎስ ይታዘብሃልና፡፡ ፈጽመህ “እኔ ሌሎች ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ማምጣት አይሆንልኝም” አትበል፡፡ በእውነት ክርስቲያን ከኾንክ ይህን ከማድረግ ይልቅ አለማድረጉ ይከብዳልና፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ እንድትኾን አድርጎ ፈጥሮሃልና ተፈጥሮህን መካድ አይቻልህም፡፡ ክርስቲያን በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ወንድሞቹ ብርሃኑን ከሚከለክል ይልቅ ፀሐይ ብርሃኗን ብትከለክል ይቀላልና ስለዚህ አልጠቅምም አትበል፡፡ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇                 •➢ ሼር // SHARE     

እንኳን አደረሳችሁ ተወዳጇ እና ተናፋቂዋ ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም ደረሰች እግዚአብሔር ቢፈቅድ ነገሮች ጥሩ ከሆኑ ከመስከረም 17 እስከ መስከረም 24 ጥሩ ቆይታ የማይረሳ ትዝታ ሆኖ ያልፋል በመንፋሳዊ ህይወት ደግሞ ከፈጣሪ ጋር ከመስቀሉ ጋር ተጣብቀን እምናሳልፍበት ግዜ ይሆናል ባለን ውሱን ቦታ ብቻ ምዝገባ ጀምረናል ። የጉዞ መነሻ እና መመዝገቢያ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን (መርካቶ)

#ሀምሌ_7_የአብርሃሙ_ሥላሴ እንኳን ለፈጣሪያችን ለቅድስት ሥላሴ አመታዊ በአል በሠላም አደረሠን አደረሳችሁ።በዚችም ቀን ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት /ቅድስት ሥላሴ/ በኦሪት መጽሐፍ እንደ ተጻፈ ወደ አብርሃም ቤት ገቡ ያቀረበላቸውንም ተመገቡ. የይስሐቅንም ልደት አበሠሩት ባረኩት አከበሩትም፡፡መጽሐፈ ስንክሳር ዘሐምሌ ሰባትሥላሴ ማለት በቅዱሳት መጻሕፍት መሠረት አንድ አምላክ በሦስት አካላት እንዳለ ለአበው ለነቢያትና ለሐዋርያት መገለጡን አምነን የምንማረው ትምህርት ነው፡፡ሥላሴ ማለት የግእዝ ቃል ሲሆን ሦስት፤ ሦስትነት ማለት ነው፡፡ የአንድ አምላክ በሦስትነት መገለጥን ለመረዳት በኦሪት ዘፍጥረት 1፡26 ላይ በተገለጠው መሠረት “እግዚአብሔርም አለ ሰውን በመልካችን እንደምሳሌችን እንፍጠር” ይላል ይህ አገላለጽ “እግዚአብሔርም አለ” ሲል አንድነትን (አንድነታቸውን) “እንፍጠር” ሲል ከአንድ በላይ (ሦስትነትን) መሆንን ያስረዳል፡፡በኦሪት ዘፍጥረት 3፡22 ላይ “አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ” የሚለው አገላለጽ ከአንድ በላይ መሆንን የሚያስረዳ ነው። በኦሪት ዘፍጥረት 11፡5-7 የተጠቀሰው “ኑ እንውረድ ቋንቋቸውን እንደባልቅ”በማለት ሥላሴ የተናገሩት ከአንድ በላይ (ሦስትነት) መሆንን የሚያመለክት ነው፡፡በኦሪት ዘፍጥረት18 ላይ ሥላሴ ለአብርሃም እንደተገጹለት የሚያስረዳ ሀሳብ የያዘ አገላለጽ ሲሆን ሥላሴ ለአብርሃም በመገለጻቸው አብርሃም ሥላሴን በእንግድነት አሰተናግዷል፡፡የሥላሴ ባለሟል መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ በእርግናው ጊዜ ልጅ እንደሚያገን ተበስሮለታል፡፡ ዘሩ እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደ ምድር አሸዋ እንደሚበዛ በሥላሴ ቃል ተገብቶለታል፡፡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚጠመቅበት ጊዜም የሥላሴ ምስጢር ተገልጧል፡፡ “እግዚአብሔር አብ የምወደው ልጄ ይህ ነው” ሲል እግዚአብሔር ወልድ ሲመጠቅ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ተገልጧል፡፡ ማቴ.3፡13 አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን ሂዱና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ ደቀመዛሙርቴ አድርጉ” ማቴ. 14፡28 ሲል ሦስትነት የሚገልጽ መልእክት አስተላልፏል፡፡ እንግዲህ ሥላሴ ስንል በስም በአካል፣ በግብር የተለዩ መሆናቸውን ያስረዳል፡፡ ይኸውም፡-የአካል ሦስትነት፡-አብ የራሱ መልክ፣ ገጽ፣ አካል አለው፡፡ወልድ የራሱ መልክ፣ ገጽ፣ አካል አለው፡፡መንፈስ ቅዱስ፡- የራሱ መልክ፣ ገጽ አካል አለው፡፡የስም ሦስትነት ስንል፡- የአንዱ ስም ለአንዱ የማይሆን አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ በመባል ይጠራሉ፡፡የግብር ሦስትነት ስንል፡- አብ ወላዲ፣ አስራጺ ሲሆን ወልድ ተወላዲ ነው የተወለደውም ከአብ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ሰራጺ ነው፡፡ የሰረጸውም ከአብ ነው፡፡የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት ለመረዳት በሥላሴ ፈቃድ መጻሕፍት እንዳስተማሩ ሊቃውንት እንደተረጉሙልን እንጂ ማንም በገዛ ፈቃዱ ተመራምሮ አይደርስበትም፡፡ በዓለ ሥላሴበዓላት የሰው ልጅ በእግዚአብሔር የተደረገለትን የቸርነት ሥራ በማሰብ ቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት ያደረጉትን ተጋድሎና ተአምራት በመስማትና በማሰማት የተደረገውን ድንቅ ነገር በመዘከር በደስታ የሚከበሩ ዕለታት ናቸው፡፡ “በቃለ አሜን ወበትፍስሕት ድምፁ እለ ይገብሩ በዓለ፡- በዓለ የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና የምስጋና ቃልአለው” እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ.41፡5 የበዓል መከበርን ያሳወቁት ሥላሴ ሲሆኑ፤ ሥላሴ ፍጥረታትን ስድስት ቀናት ፈጥረው ሰባተኛውን ቀን ቀዳሚትን አርፈውበታል፡፡ “በሰባተኛውም ቀን ከሥራው ሁሉ ዐረፈ፡፡ እግዚአብሔር ሰባተኛውን ቀን ባርከውም ቀድሰውም እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፏልና” ዘፍ.1፡1-3 እንዲልበዚህ መሠረትነት በዓል እንዲከበር የመደቡት ሥላሴ ሲሆኑ የመጀመሪያው የሥላሴ መታሰቢያና የበዓል አከባበር መጀመሪያ የሆነችው ቀዳሚት ናት፡፡ ☞የዛሬው ሐምሌ 7 ቀንም ሥላሴ በአብርሃም ቤት ገብተው ቸርነታቸውና ፍቅራቸውን የገለጹበት፣ አብርሃምን የባረኩትና ልጅ እንደሚወልድ፣ መጻዒው ሕይወቱን የነገሩት ዕለት ስለሆነ በዓሉን ስናዘክር ሥላሴን እናመሰግናለን፡፡ ቸርነታቸው፣ ፍቅራቸው፣ ትድግናቸው እንዳይለየን እንማጸናለን፡፡ የቅድስት ሥላሴ ቸርነት አይለየን፡፡

"…እመቤታችን ፍቅሯን በልቦናችን ጣዕሟን በአንደበታችን ያሳድርብን። ምልጃና ጸሎቷ ረድኤት በረከቷ ከሁላችን ጋር ይሁን። የአሥራት ሃገሯን ኢትዮጵያን በምልጃዋ ትጠብቅልን።
"…እመቤታችን ፍቅሯን በልቦናችን ጣዕሟን በአንደበታችን ያሳድርብን። ምልጃና ጸሎቷ ረድኤት በረከቷ ከሁላችን ጋር ይሁን። የአሥራት ሃገሯን ኢትዮጵያን በምልጃዋ ትጠብቅልን።

+ የዝምታ ጩኸት + እስራኤል ጭንቅ ላይ ናቸው:: ከባርነት ተላቅቀው ከግብፅ ከወጡና ጉዞ ከጀመሩ በኁዋላ ፈርኦን የለቀቀው ሕዝብ ጉልበት ቆጭቶት በቁጣ ነድዶ ሠራዊቱን አስከትቶ በፈጣን ሠረገላ እየጋለበ መጣባቸው:: ከፊታቸው ደግሞ የሚያስፈራ ባሕር ተደቅኖአል:: ሕዝቡ የፈረደበት ሙሴ ላይ ጮኹበት::  መጽሐፈ መቃብያን "ያንን ሁሉ ሕዝብ ሲጠብቅ ያልተበሳጨ ሙሴን አስበው" እንደሚል እንደ ሙሴ ትሑትና ታጋሽ መሪ ታይቶ አይታወቅም:: ልክ በዚያች ዛፍ ላይ እሳት ሲነድባት እንዳልተቃጠለች እስራኤላውያንም ሙሴ ላይ ለዓመታት ቢነዱም አላቃጠሉትም:: "በግብፅ መቃብር ጠፍቶ ልታስፈጀን ነው?" "ከሞት ባርነት በስንት ጣዕሙ?" እስራኤል በኤርትራ ባሕር ዳርቻ ሙሴን በቁጣ እየጮኹ አስጨነቁት:: መሪነት ከባድ ነው:: ያንን ሁሉ ድንቅ ነገር አድርጎ እግዚአብሔር ነፃ ሲያወጣቸው ሙሴ ለእነርሱ ቤዛ ሆኖ ተሹሞ ብዙ ዋጋ ከፍሎአል:: ውለታውን ረስተው አፋጠጡት:: "ሙሴም ለሕዝቡ፦ አትፍሩ፥ ዛሬ የምታዩአቸውን ግብፃውያንን ለዘላለም አታዩአቸውምና ቁሙ፥ ዛሬ ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ። እግዚአብሔር ስለ እናንተ ይዋጋል፥ እናንተም ዝም ትላላችሁ፡ አላቸው" ሙሴ ሕዝቡን ከጩኸታቸው ሲያረጋጋ ሳለ የእግዚአብሔር ድምፅ ወደ ሙሴ መጣ "ሙሴ ሆይ ለምን ትጮኽብኛለህ?" አለው:: ልብ አድርጉ የጮኸው ሕዝቡ ነው ሙሴ አረጋጋ እንጂ ቃል አልተናገረም:: ሆኖም ሙሴ አፉ ዝም ቢል ልቡ ይጮኽ ነበር:: ከእስራኤል ጩኸት ይልቅ የሙሴ ዝምታ እግዚአብሔር ጆሮ ደረሰ:: እግዚአብሔር ኤልያስ እንዳላገጠባቸው የአሕዛብ አማልክት በጩኸት ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለም:: በትዕቢትና አመፅ ከሞላበት ጩኸት ይልቅ በተሰበረ ልብ የሚቀርብ ዝምታ እግዚአብሔር ጋር ይጮኻል:: የእስራኤል ጩኸት ፍርሃት ይነዛል:: ልናልቅ ነው የሚል ሽብር ይፈጥራል:: የሙሴ ዝምታ ግን ባሕር ይከፍላል:: ጌታ ሆይ ጩኸታችን አልሆነልንም:: ዝምታችንን ሰምተህ ሀገራችንን ከከበባት ጥፋት ታደግልን:: የእኛ መጨቃጨቅና ጠብ ባሕር አይከፍልም:: የእኛ ጩኸት ከመነካከስ በቀር አያሻግርም:: በአርምሞ የሚለምኑህን በእኛ ፊት ዝም አሉ የምንላቸው በአንተ ፊት ግን የሚጮኹትን ሰምተህ ታደገን:: የኤርትራ ባሕር በዝምታ ተከፈለ:: እስከ ራማ የተሰማው ራሔል ስለ ልጆችዋ ያለቀሰችው ዕንባ ባሕር ከፈለ:: እመቤታችን ሆይ ስለ እኛ ስለልጆችሽ እባክሽን አልቅሺ:: የራሔል ዕንባ ራማ ከደረሰ የአንቺ ዕንባ የት ሊደርስ ነው? በየበረሃ እየወደቀ ስላለው ልጅሽ ስለሞተለት ወንድም እባክሽን ለምኚ:: በሙሴ በትር ባሕሩ ተከፈለ:: የኤርትራ ባሕር (ቀይ ባሕር [በግሪኩ erythos ማለት ቀይ ነው]) እጅግ ባለ ታሪክ ባሕር ነው:: ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ደረቅ ሆኖ ፀሐይ ያየውና ግማሽ ሚልየን የሚሆን ሕዝብ በመካከሉ ተራምዶ ያለፈበት ይህ ባሕር እንንደ ግድግዳ የቆመ ብቸኛው የዓለማችን ባሕር ነው:: በዚህ ባሕር እስራኤል ሲሻገሩ ፈርኦን ከነሠራዊቱ ሰጠመ:: በእግር የሔዱት የተሻገሩትን ባሕር በሠረገላ የሔዱት አቃታቸው:: የኤርትራ ባሕር ለእስራኤል ትንሣኤ ሲሆን ለፈርኦን ግን መቃብር ሆነ:: ፈርኦን ደንግጦ መመለስ የነበረበት ባሕሩ ሲከፈል ሲያይ ነበር:: ፈርኦንን ያደቆነ ሰይጣን ግን ባሕር መካከል ሳያቀስስ አልለቀቀውም:: እግዚአብሔር ማን ነው? ብሎ ነበር በዚያ ባሕር ተዋወቀው:: እሱ ሲሰጥም እስራኤል በኩራት "እግዚአብሔር ማን ነው? " ለሚለው የፈርኦን ጥያቄ ከባሕር ማዶ ሆነው መልስ ሠጡ "እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው" አሉ:: እስራኤል በኤርትራ ባሕር መሻገራቸው የጥምቀት ምሳሌ ሆኖ "በባሕርና ደመና ተጠመቁ" ተብሎላቸዋል:: ፈርኦን ግን እስራኤል በተጠመቁበት ጠበል ውስጥ ሰጠመ:: የኤርትራን ባሕር ሲሻገሩ ከሙሴ ሌላ እስራኤልን ሲመራ የነበረ ጠባቂ ነበረ:: እርሱም የእስራኤል ጠባቂ (advocate of Israel) በመባል የሚታወቀው ቅዱስ ሚካኤል ነበር:: "በእስራኤልም ሠራዊት ፊት ይሄድ የነበረው የእግዚአብሔር መልአክ ፈቀቅ ብሎ በኋላቸው ሄደ፤ የደመናውም ዓምድ ከፊታቸው ፈቀቅ ብሎ በኋላቸው ቆመ" ዘጸ 14:19 እንዲል ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ቀን በደመና ሌሊት በብርሃን ዐምድ እየተመሰለ በመንገድ መራቸው:: ኢትዮጵያውያን ያለነው ከባሕሩ ዳርቻ ላይ ነው:: ሁሉም መሻገር ይፈልጋል:: ከእኛ መካከል እንደ ፈርኦን ሰጥሞ የሚቀር ይኖራል:: እንደ እስራኤል የሚሻገር ይኖራል: :  ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ለእኛም ድረስልን:: ይህንን ክፉ ዘመን በክንፎችህ አሻግረን:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ኅዳር 12 2013 ዓ ም ድሬደዋ ኢትዮጵያ ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!

ማህበራችን ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር የዛሬ ዓመት በዚህ ታላቅ በዓል ላይ ጉዞ በማዘጋጀት በቦታው ተገኝቶ ነበር ድንቅ ማንም ሊያመልጠው የማይገባ በዓል ነበር ዘንድሮ በትዝታ ወደዋላ የቅዱስ
+2
ማህበራችን ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር የዛሬ ዓመት በዚህ ታላቅ በዓል ላይ ጉዞ በማዘጋጀት በቦታው ተገኝቶ ነበር ድንቅ ማንም ሊያመልጠው የማይገባ በዓል ነበር ዘንድሮ በትዝታ ወደዋላ የቅዱስ ላልይበላ የእረፍት መታሰቢያና የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብረ ሮሐ ቅዱስ ላልይበላ ገዳም እየተከበረ ነው። ባለፈው ዓመት አረጋዊው አባት ብጹእ አቡነ ቄርሎስ ተገኝተው ነበር ዘንድሮ ደግሞ በበዓሉ ላይ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የከምባታ፣ ሀድያ፣ ስልጤና የደቡብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን በተገኙበት በድምቀት እየተከበረ ነው።

እንኳን ለገናናው መላክ ለቅዱስ ሚኪኤል በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ ከክፉ ነገሮች ሁሉ ይጠብቃችሁ ።
እንኳን ለገናናው መላክ ለቅዱስ ሚኪኤል በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ ከክፉ ነገሮች ሁሉ ይጠብቃችሁ ።

+  መልአኩ ነው +        ሰዓቱ ሌሊት ነው ፤ እንደ አጋጣሚ ሆኖ በዚያ ሌሊት መላው የቤተሰባችን አባል አምሽቶ እየተጫወተ ነው፡፡ ከዚህ የቤተሰብ ስብስብ መካከል ሳይገኝ የቀረው አንድ በወኅኒ ቤት የታሰረ ወንድማችን ብቻ ነበር፡፡ ድንገት ግን የጊቢው በር በተደጋጋሚ ተንኳኳና ሁላችንም ጨዋታችንን አቋረጥን፡፡ በሌሊት የሚያንኳኳው ማን ነው ? ሠራተኛችን ሮጣ ሔደች:: ወዲያው ግን በሩን ሳትከፍተው ተመልሳ እየሮጠች መጣች፡፡ በደስታ ሰክራ ‹‹የታሰረው ልጃችን በር ላይ ቆሟል!›› ብላ ተናገረች፡፡ "በድምፁ አወቅኩት!› እያለች ዘለለች፡፡ ከሁኔታዋ የተነሣ ‹አብደሻል እንዴ!?› አላት ቤተሰቡ ሁሉ፡፡ እስዋ ግን በእርግጠኝነት ተናገረች! በቀን የታሰረው ልጅ በሌሊት ተፈቶ መምጣቱ ፈጽሞ ሊታመንን የማይችል ነገር ነው፡፡ ቤተሰቡ ሁሉ የታሰረው ልጅ መጣ ብሎ አላመነም፡፡ ባይሆን የመንግሥት ወታደሮች የቀረነውን ሊወስዱን ይሆን? ማን ሊሆን ይችላል? ብሎ ተብሰለሰለ:: በመጨረሻም የሁሉም ግምት አንድ ነገር ላይ አረፈ:: ሁሉም ሰው በአንድ ድምፅ አንድ ቃል ተናገረ "መልአኩ ነው!"   መልአኩ የሰው ስም አይደለም:: ቤተሰቡ የተስማማው "ደጅ የቆመው የታሰረው ልጃችን ሳይሆን እሱን ለመጠበቅ ከእግዚአብሔር የተሠጠው ጠባቂ መልአኩ ይሆናል›› ብሎ ነበር፡፡ የበሩ መንኳኳት አሁንም ስላልቆመ ቤተሰቡ ግር ብሎ ወጣና ተቻኩሎ በሩን ከፈተ፡፡ በደጅ የቆመው ግን እንደተባለው የታሰረው ልጅ ራሱ ነበር፡፡ ሁሉም ተደሰተ!!!       ይህ ገጠመኝ በአሁን ዘመን የተፈጸመ ነው ብዬ ብናገር ማን ያምነኛል? እውነት በሌሊት የቤታችን በር ሲንኳኳ  መልአክ ነው ብለን እንገምታለን? ይህ ቤተሰብ ምን ዓይነት ቤተሰብ ነው? በብዙዎቻችን አእምሮ ውስጥ መጀመሪያ የሚመጣው ጥርጣሬ ‹ሌባ ሊገባ ይሆን?› የሚል ስለሚሆን ዱላ ፍለጋ እናማትራለን፡፡ ወይ ደግሞ ሌሊቱ ወደ መንጋቱ እየተቃረበ ከሆነ ‹‹የምን መርዶ ሊያረዱኝ ይሆን? የቱ ዘመዴ ሞቶ ይሆን?› የሚል ጭንቀት ይፈጠራል፡፡ ‹የሚያንኳኳው የእግዚአብሔርመልአክ ይሆናል› ብሎ የሚጠረጥር ሰው ግን በዚህ ዘመን ለማግኘት ያስቸግራል፡፡ እንዲህ ብሎ ግምቱን የሚናገር ሰው ከቤተሰባችንመካከል ቢገኝ እንኳን እንደ ዕብድ ልንቆጥረው እንችላለን፡፡ ታዲያ ይህን ገጠመኝ ከየት አመጣኸው ትሉኝ ከሆነ መልሱ ከመጽሐፍ ቅዱስ የሚል ነው፡፡       በሐዋርያት ዘመን ሔሮድስ የተባለው ንጉሥ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስን ወኅኒ ቤት ውስጥ ወርውሮት ነበር፡፡ የቀሩት ደቀመዛሙርትና ክርስቲያኖች በዚያ ሰሞን ሲጸልዩ ከርመዋል፡፡ በአንድ ሌሊት በማርቆስ እናት ቤት ውስጥ ተሰብስበው አምሽተው ነበር፡፡ ድንገት የቤቱ በር ሲንኳኳ ሮዴ የምትባል የቤት ሠራተኛ ደጁን ልትከፍት ወጣች፡፡ ማነው ብላ ስትሰማ የቆመው እስረኛው ቅዱስ ጴጥሮስ መሆኑን በድምፁ አወቀች፡፡ ደስታ ግራ ሲያጋባት በሩን መክፈትን ረስታ ወደ ውስጥ ሮጠችና ጴጥሮስ መምጣቱን ተናገረች፡፡ እነርሱ ግን አላመኑአትም፡፡ ጤንነቷን ተጠራጥረው ‹አብደሻል› አሏት፡፡ እርግጠኛ ሆና ተናገረች፡፡ እነርሱ ግን መልሰው ‹‹የቆመው ጴጥሮስ ሳይሆን መልአኩ ነው፡፡›› አሉ፡፡ ይደንቃል የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች እንዲህ በር ሲንኳኳ ‹መልአክ ነው› ብለው የሚገምቱ መንፈሳዊያን ነበሩ፡፡ (ሐዋ. 12፡12-15)       ቅዱሳንመላእክት እኛ የሰው ልጆች ከመፈጠራችን ቀድመው የተፈጠሩ ታላቅ ወንድሞቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም ምድርና የሰው ልጅ ሲፈጠር ደስ እያላቸው ‹‹እልል›› ይሉ ነበር፡፡ (ኢዮ. 38፡6) ቅዱሳን መላእክትን እግዚአብሔር ለእንዳንዳችን ጠባቂዎች አድርጎ ሠጥቶናል፡፡ ከክርስቶስ እግር ሥር ቁጭ ብለው የተማሩት ቅዱሳን ሐዋርያት ስለ መላእክት ጠባቂነት ጋር ይህን ያህል እምነት ከነበራቸው እኛም የመላእክቱን ጠባቂነት ማመን ለዚህ ዘመን ክርስቲያኖችም ምን ያህል ይገባን ይሆን? ቅዱሳን መላእክት በክርስትና ሕይወት ለሚኖርሰው ሁሉ የመላእክት ረዳትነት እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ለሁሉ ብርታት የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን በሥጋው ወራት በተያዘባት ምሽት ሲጸልይ ‹‹ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታው መልአክ ታየው›› ተብሎ ተጽፏል፡፡ (ሉቃ. 22፡43) ይህም ቀርበው አገለገሉት‹ለከ ኃይል› እያሉ አመሰገኑት ማለት ሲሆን ለእኛም የመላእክት ርዳታ አያስፈልገኝም እንዳንል የሚያስተምረን ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት በምድር የሚሆነውን ያውቃሉ:: (2 ሳሙ 14:20) በበደላችን ስንጸጸት "ኃጢአትህ ተሠረየችልህ" ይላሉ (ኢሳ 6:7) በክፋታችን ጸንተን ከቀጠልን ደግሞ "ይቅር አይሉም" (ዘጸ 23:20) ስለእኛ በእግዚአብሔር ፊት ቆመው "የማትምራቸው እስከ መቼ ነው?" ብለው ያማልዳሉ:: (ዘካ 1:12) ባለንበት ዘመን በዓለም ሁሉ በበሽታ የሚሠቃየው ብዙ ነው::  በሕመም ለሚሠቃየው ሁሉ "መልአክ ቢገኝለት እየራራለት [ለእግዚአብሔር] ፡— ቤዛ አግኝቻለሁና ወደ ጕድጓድ እንዳይወርድ አድነው፡ ቢለው፥ ሥጋው እንደ ሕፃን ሥጋ ይለመልማል፤ ወደ ጕብዝናውም ዘመን ይመለሳል" ኢዮ 33:23-25 ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ሰኔ ሚካኤል - 2007 ዓ ም የተጻፈ

“#መንፈሳዊው_ገበሬ” (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) “አንድ ገበሬ ዘር መዝራት ስላለበት ብቻ እንዲሁ አይዘራም፡፡ አስቀድሞ መሬቱን ማረስ፣ ማለስለስ አለበት፡፡ ካረሰ ካለሰለሰ በኋላ ዘሩን ይዘራዋል፡፡ አሁንም ግን መዝራቱ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ የዘራውን ዘር አፈር ሊያለብሰው ይገባዋል፡፡ እንዲያ ካላደረገ ወፎች መጥተው ይለቅሙታልና፡፡ ልክ እንደዚሁ እኛ ክርስቲያኖችም በእኛ ላይ የተዘራውን ዘር (ቃለ እግዚአብሔር) በየጊዜው እንደ ገበሬው የማንከታተለው ከሆነ በአየር ላይ እንደተዘራ ዘር ይሆንብናል፡፡ ሰይጣን ይለቅምብናል፤ የራሳችን ስንፍና እንዲጠወልግ ያደርጓል፤ ፀሐይ ያደርቋል፤ ጐርፍ ይወስዷል፤ እሾክ አንቆ ይይዟል፡፡ ስለዚህ ዘር ዘርቶ ዞር ማለት አያስፈልግም ማለት ነው፡፡ በየጊዜው መኮትኮት፣ ወፎችን ማባረር፣ የበቀለ አረም ካለ ማረም፣ ጭንጫ የበዛበት አከባቢ ካለ የለሰለሰ አፈር መጨመር፣ በየጊዜው መከታተል፣ አጥር ማጠር፣ እንዲሁም ማንኛውም የተዘራውን እህል ሊያበላሹ የሚችሉ ነገሮችን ማስወገድ ያስፈልጋል፡፡ ምናልባት በሰብሉ እርሻ የገበሬው ትጋት ብቻ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም መሬቱ ግዑዝ ነገር ስለሆነ፡፡ በመንፈሳዊው እርሻ ግን እንዲህ አይደለም፡፡ ኃላፊነቱ የገበሬው ማለትም የመምህሩ ብቻ አይደለም፡፡ ከግማሽ ወይም ከዚያ በላይ የደቀመዝሙሩ (የምእመኑ) ኃላፊነት ነው፡፡ በርግጥ መምህሩ ዘሩን መዝራት አለበት፡፡ ነገር ግን ደቀ መዝሙሩ የተነገረውን ቃል ሁል ጊዜ መስማት ብቻ ሳይሆን ማድረግም አለበት፤ በግብር ፍሬ ማፍራት አለበት፤ የበቀሉ አረሞች ካሉ በየጊዜው መንቀል አለበት፡፡…የገበሬ ልጆች በሰብሉ መካከል የበቀለ አረም ካለ እንዲሁ ጫፍ ጫፉን ብቻ አይቈርጡትም፡፡ ከሥር ይነቅሉትና በመጨረሻም በእሳት ያቃጥሉታል እንጂ፡፡ በእኛ ላይ የበቀሉ አረሞችም (ጥርጥሮች፣ ክሕደቶች፣ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ማነቆ የሆኑብንን ነገሮች…) ከሥራቸው ነቅለን ልናቃጥላቸው ይገባናል። ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇                 •➢ ሼር // SHARE      🔸https://t.me/fenot2

የትዳር ሕይወት ማለት ሩቅ አገር ከአንድ ከመረጡት ሰው ጋር የሚያደርጉት የሕይወት ዘመን ጉዞ ነው። ጉዞ እንደ መኾኑ ዓቀበት አለው፤ ቁልቁለት አለው። አስደሳች ሜዳ አለው፤ አሳዛኝ ጉጻጉጽም አለው። መንገዱ የአስፓልት ሊኾን ይችላል፤ የፒስታም ሊኾን ይችላል። በጫማ ሊኾን ይችላል፤ እንደ አበበ ቢቂላ በባዶ እግርም ሊኾን ይችላል። በሰሐራ በረኻ አንድ ወንድና አንዲት ሴት የሚያደርጉት ጉዞ አድርጋችሁ ማሰብ ትችላላችሁ። በዚሁ መካከል አንዱ ከአንዱ መለያየትስ ይቅርና ቢኳረፉ ራሱ ምን ዓይነት ዋጋ ሊያስከፍል እንደሚችል አሰባችሁት?   ታዲያ ይህን ጉዞ ለመጓዝ ሳያስብበት የሚገባ ማን ሰነፍ ሰው ነው? ቀድሞ ስለ መንገዱ ከባድነትና ቀላልነት፣ አብሯት ስለምትሔደው ሴት ድካምና ጥንካሬ መረጃ ሳይኖረው (Orient ሳይደረግ) ድንገት ተነሥቶ የሚሔድ ታዲያ ማን ነው? እናስ? እናማ ከማግባትዎ በፊት ጉዞዎ እንዳይበላሽ አብዝተው ይድከሙ እንጂ ካገቡ በኋላ የተበላሹ ነገሮችን ለማስተካከል አይድከሙ። ስለ መንገዱና ሊገጥምዎት የሚችለውን ዕንቅፋት እንዴት ማስቀረትና ማለፍ እንዳለብዎት  አስቀድመው ይወቁ እንጂ ጉዞ ከጀመሩና ዕንቅፋት ሲገጥምዎትና ወድቀው ሲቆስሉ ስለ ማደናቀፊያ ድንጋዩ ለማወቅ አይጣሩ። (ገብረ እግዚአብሔር ኪደ) ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆችp

ዕርገተ ክርስቶስ!! ወንጌላዊው ሉቃስ እንደሚነግረን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያረገው ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ በ40ኛው ቀኑ ላይ ነው፡፡ በእነዚህ 40 ቀናት ውስጥም ብዙ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ እየተገለጠ ብዙ ምሥጢርና ሥርዓተ ሐዲስ አስተምሯቸዋል፡፡ የተማሩትን ሁሉ እንዲጠብቁ፣ ዓለምን ሁሉ በወንጌል መረብ እንዲያጠምዱ ትእዛዝ ሰጥቷቸዋል፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ዕለቱን ያላረገው ስለ ብዙ ምክንያት ነው፡፡ አንደኛውና ዋነኛው ግን ለደቀ መዛሙርቱ ትንሣኤውን ያረጋግጥላቸው ዘንድ ነው፡፡ ወንጌላዊው ሉቃስ “… ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው” የሚለውም ስለዚሁ ነውና /ሐዋ.1÷3/ የተወለደው፣ መከራ መስቀልን የተቀበለው፣ የሞተው እርሱ የተነሣው ነውና ይህን ያረጋግጥላቸውና ያሳያቸው ዘንድ 40 ቀን ቆየ አንድም ደቀ መዛሙርቱ በሞቱ ምክንያት ተስፋ ቆርጠው ነበርና ሙስና መቃብር ሳይገድበው እንደተናገረው እንደተነሣ ያጽናናቸው ዘንድ ቆየ፡፡ አንድም የትንሣኤ ክብር እንደምን እንደሆነ ያሳያቸው ዘንድ ቆየ፡፡ አንድም ሞት ከእንግዲህ ወዲህ አስፈሪነቱ እንደቀረ ያሳያቸው ዘንድ ቆየ፡፡ በእነዚህ 40 ቀናትም ሕያው ኾኖ መነሣቱን፣ እንዲዳስሱት በማድረግ እና በመሳሰሉት አረጋገጠላቸው፡፡ በጌታችን ዕርገት ያገኘነው ጥቅም በበደልነው በደል ምክንያት ለ5 ሺሕ 500 ዘመናት በእግረ አጋንንት ስንቀጠቀጥ ኖረናል፡፡ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኔዓለም በከበረ ደሙ ቤዛ ሲሆነን ግን ከጥንተ ጠላታችን ግዛት ከዲያብሎስ ማርኮናል፡፡ ወደ ጥንተ ተፈጥሯችን መልሶናል፡፡ ከኃጢአታችን ነጻ አውጥቶናል ዳግም ልጆቹ እንባል ዘንድ አድሎናል፡፡ የሰጠን ሥልጣን “ልጅ” መባል ብቻ እንዳልሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲያስተምርም፡- “…እርሱም (ከሰማያት ሁሉ በላይ የወጣው ክርስቶስ) አንዳንዶቹ ሐዋርያት ሌሎቹም ነቢያት ሌሎቹም ወንጌልን ሰባኪዎች ሌሎቹም እረኞችና አስተማሪዎች እንዲኾኑ ሰጠ” ብሏል /ኤፌ.4÷11/ ዳግመኛም “ምርኮ” የሚለው ቃል ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ ሲተረጉመው እንዲህ ይላል፡- ‹‹ከመስቀሉ ወደ ሲዖል በመውረዱ አዳነን በአባታቸው በአዳም በደል በሲዖል ተግዘው የነበሩ ጻድቃንን ፈታ ከሙታን ተለይቶ አስቀድሞ በተነሣ በእውነተኛ ትንሣኤውም አስነሣን የንስሐንም በር ከፈተልን›› /ሃይ.አበ. 36፡30/ ይኸውም ቃል ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር የተስማማ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማያት ያረገው ከዚህ ምርኮ በኋላ ነው፡፡እኛም በዚህ ቃል ጸንተን የቆየን እንደሆነ ዳግመኛም ወደዲያ ብሎ ከምርኮ ባንመለስ የሐዋርያትና የሌሎች ቅዱሳን ጸጋ እንደማይለየንአረጋግጦልናል፡፡ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደቱ፣ ጥምቀቱ፣ ሕማሙ፣ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱ፣ ድንገት የመጣ ሳይሆን አስቀድሞ በነቢያት ትንቢት የተነገረ ነው፡፡ መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊት ስለ ጌታችን ዕርገት ሲናገር፡- “ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን/ አምላክ በዕልልታ፣ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ ዓረገ ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ ለንጉሣችን ዘምሩ” ያለውም ስለዚሁ ነው፡፡ /መዝ 46 (47)፥5)/ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ለእርሷ ተብሎ በተተከለ ብርሃናዊ ደብተራ (ድንኳን) ነበረች። ሐዋርያቱን ካናገረ በኋላም ወደ እርሷ ሄደ፤ ምድር ተንቀጠቀጠች፡፡ ሁሉም ሰገዱለት ጌታ ወደ ሰማያዊ ሠረገላ ወጣ፡፡ ሊቃነ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በሚመርዋቸው እልፍ አእላፍ ሠራዊተ ሰማይ በኹሉም መዓዘናት በየመልካቸው በየነገዳቸው በየሥርዓታቸው ቆመው ነበር፡፡ ወዮ! በዚህ ዕለት የታየው ሰማያዊ ሰልፍ የሰው ልጅ ደካማ ቋንቋ ፈጽሞ ሊገልጸው አይችልም!!! ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት “ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን- አምላክ በዕልልታ፡ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ ዐረገ። ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ” የሚለን ይህን ግሩም ምሥጢር አይቶ ነው፡፡ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ያገኘነው በጌታችን ዕርገት ነው፡፡ በመኾኑም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች እንደተናገረው /ኤፌ. 2÷7/ በክርስቶስ በሰማያዊ ሥፍራ ተቀምጠናልና ሰማያዊ ግብራችንን ረስተን በምድራዊ ግብር ብቻ ልንያዝ አይገባንም፡፡ በክርስቶስ ያገኘነውን ክብር ድጋሚ ልናቆሽሸው አይገባንም፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ዘወትር በቅዳሴዋ “ላዕለ ይኩን ኅሊናክሙ በሰማይ የሀሉ ልብክሙ አእምሩ ኀበ ትቀውሙ ስምዑ ቃለ ጽድቅ ወአስምዑ ዜና ሰናይ” እያለች የምታሳስበንም ስለዚሁ ነው፡፡ በዓለ ዕርገት ከትንሣኤ በዓል በኋላ በ40ኛው ቀን ስለሚውል ሐሙስን አይለቅም፡፡ በዓለ ዕርገት ከዘጠኙ የጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ እንደመኾኑ መጠንም በኹሉም አብያተ ክርስቲያናት በቅዳሴ ይከበራል፡፡ ታቦቱ ባላቸው አብያተ ክርስቲያናትም ታቦቱ ወጥቶ በዑደት በድምቀት ይከበራል፡፡አንዳንድ ምእመናንም በዓለ ዕርገትን ምክንያት በማድረግ ጸበል ጸዲቅን በማድረግ ያከብሩታል፡፡ ይሁን እንጂ ብዙ ሰው ሌሎቹን የጌታችን አበይት በዓላትን እንደሚያከብረው ለበዓለ ዕርገት ትኩረት ሲሰጠው አይታይም፡፡ ይኸውም ልምድ እየሆነ የመጣ ጥሩ ያልሆነ ልማድ ነው፡፡ በመሆኑም በዓሉን እንደ ጥንቱ አባቶቻችን በድምቀት ልናከብረው ይገባል፡፡ ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

በባንክ ከፍያ ፈጽሞ ቦታ ማስያዝ ይቻላላ ንግድ ባንክ 1000002727211 አባይ ባንክ 2022
በባንክ ከፍያ ፈጽሞ ቦታ ማስያዝ ይቻላላ ንግድ ባንክ 1000002727211 አባይ ባንክ 2022

በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው ዐብይ ኮሚቴ የተሰጠው መግለጫ <<በከፍተኛ ትዕግስት ስናልፋቸው የነበሩ አባቶች ዛሬም ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ቤተክርስቲያንን ሲገፉ በዝምታ የምናይበት ሂደት አይኖርም፡፡>> ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግርን ለመቅረፍ  በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው ዐብይ ኮሚቴ በኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደት ላይ መግለጫ አወጣ። በአለፉት ሁለት ሦስት ቀናት በአባቶች ዘንድ ውይይት ተደርጎበት ስምምነት ላይ ሳይደረስበት የቀረው የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደትን አስመልክቶ በተደረገው  ውይይት ላይ በአባቶች የተፈጠረው  የሐሳብ መከፋፈልና አለመግባባት ሁኔታ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ለኮሚቴው በእጅጉ እያሳሰበው ይገኛል ሲል ከ10 በላይ ማኅበራትን የወከለው ኮሚቴው በመግለጫው ጠቅሷል። በየጊዜው በሚነሱ ወሳኝ የቅድስት ቤተክርስቲያን አጀንዳዎች ውስጥ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ጀርባቸውን የሚሰጡ፣ በቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ዓለማዊ አጀንዳ የሚያራምዱና ከዛሬ ነገ የቤተክርስቲያንን ፍቅርና ምህረት ተረድተው ወደልባቸው ይመለሳሉ በማለት በከፍተኛ ትዕግስት ስናልፋቸው የነበሩ አባቶች ዛሬም ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ቤተክርስቲያንን ሲገፉ በዝምታ የምናይበት ሂደት አይኖርም ያለው ኮሚቴው በዚህ ታሪካዊ ወቅት ለቅድስት ቤተክርስቲያን መቆም ሲገባችሁ እየሰማችሁ እንዳልሰማችሁ ሆናችሁ በዝምታ የምትመለከቱ አባቶችም ሆነ ዋነኛ የችግሩ አካላት የሆናችሁ አባቶች በእግዚአብሔርም በታሪክም በእኛም በልጆቻችሁ የሚያስጠይቃችሁ መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን ሲል አፅንዖት ሰጥቷል። ቤተክርስቲያን ከማይጠፋ ዘር በክርስቶስ ደም የተመሠረተች እንጂ እንደ ፖለቲካ ምክር ቤት በዘር በጎሣ የተመሠረተች አይደለችም። ቤተክርስቲያን የሁሉም ለሁሉም ነች ያለው ዐብይ ኮሚቴው ዛሬ በወከባና በጫና ለተለየ ብሔርና ጎሣ ተለይቶ የኢጲስ ቆጶስ ሲመት ቢሰጥ ነገ በዚህ ሰበብ ቤተክርስቲያንን ለመከፋፈል ዘርና ቋንቋን መሠረት አድርጎ የሚከተለውን ጥያቄና በጥንታዊት  ሐዋርያዊት ዓለም አቀፋዊት አንዲት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተነጣጠረውን የፈተና እና የመከራ ማእበል መመለስም መዳኘትም ይከብዳል ብሏል። ይህን ጽንፍ የወጣ አጀንዳ በድምጽ ብልጫ በማስወሰን ሕገ ቤተ ክርስቲያንን እና ቀኖናን በመጣስ መፍትሔ የሚያመጡ መስሎአቸው የሚተጉ አባቶችም ቤተክርስቲያንን ወደማትወጣው መከራና ፈተና እየገፏት እንደሆነ ሊረዱት ይገባል ብለን እናምናለን። በዚህ መግለጫ ብፀዓን አባቶችንን በታላቅ ትህትና ዐቢይ ኮሚቴው ማሳሰብ የሚፈልገው ይህ አጀንዳ አስተዳደራዊ ሳይሆን ሃይማኖታዊ/ዶግማዊ እና ሥርዓታዊ/ቀኖናዊ አጀንዳ በመሆኑ በሕገ ቅድስት ቤተክርስቲያን አንቀፅ 19፡ 5፡ ሐ መሰረት በሙሉ ድምጽ እንጂ በድምፅ ብልጫ ስምምነት ተደርጎበት ውሳኔ ላይ ሊደረስ የማይገባው አጀንዳ መሆኑንም ኮሚቴው በሚገባ ያምናል፡፡ በተለይም ይህ አለመግባባት እየሰፋ መጥቶ ውሳኔው በድምጽ ብልጫ የሚደረግ ከሆነ ሕገ ቤተክርስቲያንን እና ቀኖና ጥሰትን ስለሚያመጣ፤ ውጤቱም በብፁዓን አባቶች መካከል ያለውን መከፋፈል አስፍቶ ቤተክርስቲያንን ወደ ከባድ ፈተና የሚያደርስ ጉዳይ በመሆኑ ብፁዓን አባቶች በፍፁም መከባበር፤ ምድራዊ እና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ፍጹም ጸያፍ እና የተወገዙ በሆኑ ጉዳዮች፣ዘርን፣ ቋንቋን፣ ጎጥን ፖለቲካን፣የግል ጥቅምንና ፍላጎትን ሳይሆን የረቂቃኑ እና ግዙፋኑ፤ የሰማያውያን እና የምድራውያን ልዩ ጉባኤ፤አንዲት የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቅድስት ቤተክርስቲያንን ማዕከል በማድረግ ብቻ አንድ ልብ አንድ ሐሳብ ሆናችሁ በእርጋታ በመነጋገር ለቅድስት ቤተክርስቲያን የሚጠቅም ውሳኔ በአንድ ድምፅ ሰጥታችሁ እንደምትወጡና የአሁኑንም ሆነ የሚመጣውንም ትውልድ የመከራ ቀንበር እንደምታቀሉ ባለሙሉ ተስፋ ነን፡፡ መግለጫው ከቅዱስ ሲኖዶስ የምንጠብሸው ውጤት በማለት ዐራት ነጥቦችን ዘርዝሯል። 0ቢይ ኮሚቴው በጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም. ከተከናወነው  ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሢመት ጋር በተያያዘ በቤተ ክርስቲያን ላይ የተጋረጠው አደጋ መነሻ አድርጎ የተቋቋመ ሲሆን ከ10 በላይ ማኅበራትን ማለትም ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት፣ ከነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የምዕመናን ኅብረት፣ ማኅበረ ቅዱሳን፣ ጴጥሮሳውያን ኀብረት፣ የጎልማሶች እና ወጣቶች ማኅበር፣ ከወልዳ ዳንዲ አቦቲ፣ ከደጆችሽ አይዘጉ ማኅበር፣ ከሕግ ባለሙያዎች እንዲሁም ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የተለያዩ መምሪያዎች የተወጣጣ ነው። (ማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን)