OLD 1990 ethiopan Music⏮⏪⏯⏭⏩🎶
Open in Telegram
ያፈቀረን ማፅናናት ለኛ ኖርማል ነው አያሳስብም😉 #Join ያርጉና ፈታ እያሉ በውብ የፍቅር ቃላቶች ይደመሙ😍 ዘፈን , ግጥም ,
Show more2 638
Subscribers
No data24 hours
-107 days
-2630 days
Posts Archive
አንዳንድ ሰዎች አስተሳሰባችንን ትተው ይምንለብሰው ልብስ እንደሚያዩት ሁሉ እኛም ጋር ትልቅ ችግር አለ
ስለ አስተሳሰባችን በጣም ፈጣን ነን ሁሉም ነገር በ አንዴ እንዲሆን እንፈልጋለን ፊታችን ላየ ያለውን ነገር ትተን ስለ እሩቁ እናስባለን ማለትም ሰው ሲያየን ትልቁን አይምሮ የኛን አስተሳሰብ ትቶ በትንሽ ብር የተገዛውን ልብስና ጫማ አንደሚያየው ሁሉ ማንንም ሰው ለመለየት ጊዜ ያስፈልገናል::
የሆነ ነገር ስንጀምርም እንደዛው ጊዜ ያስፈልገናል
ስለዚህ አጠገባችን ያለውን ዕድል ሆነ ሰው በትዕግስት ነው የሚለየው:: ሁሌም ቢሆንመታገስ ይልመድብን ባይ ነኝ ኪሩቤል
10/10/2014
@keruoo
••●◉ንፋልኝ አለችኝ🙊🙉🙈
----------------------------------
ከመሸ ቡሃላ ስልክ 📲 ደውላልኝ
እቤት ማንም የለም ቶሎ ድረስልኝ
ብላ ነገረችኝ...
በማራኪ ድምጿ እያማለለችኝ
ታክሲ ተሳፍሬ 🚗
እንደ ጀት በርሬ 🚀
ከቤቷ ደርሼ ቀና ብዬ ሳያት
በጣም ተኳኩላ እጅጉን አምሮባት
ፀጉሯን ተተኩሳ
ጭኗን የሚያሳይ አጭር ልብስ ለብሳ
ከንፈሯን በቀለም ቀብታ አለስልሳ
እጄን ይዛ ገብታ ከመኝታ ቤቷ
እፍረት ሳይሰማት አርጋኝ ከደረቷ
አጠገቧ አስቀምጣ እየዳበሰችኝ
እባክህን አንዴ ንፋልኝ አለችኝ....
.
በጇ ወደ ዋሽንት እየጠቆመችኝ።
🤣🤣😂😂😂😂
dirty mind matrebu 🙈🙈🤣
ከተመቻቹ ÷
#𝐑𝐞𝐚𝐜𝐭
#𝐂𝐨𝐦𝐦𝐞𝐧𝐭
#𝐬𝐡𝐚𝐫𝐞 🙏 🥀 ¶™
•────────────•🌐
📱ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!📱
መምጫዬ ሰአት ቀርባለች እና ንሰሃ ገብታችሁ ታጥባችሁ ጠብቁ ለ16 ሰው ላኩ በ3ቀናት ውስጥ እንጀራ ታገኛለህ ሳትልክ ብትቀር ግን ለ7አመት ልፋት ድካም ይሆንብሃል ብለዋል የገዳም አባቶች እኔም ተልኮልኝ ነዉ።
Repost from የ Al Nassr ደጋፊዎች በኢትዮጵያ
"ክርስቲያኖ ሮናልዶን ወደ ጦርነት ልትወስድ ትችላለህ እና እሱ ብቻውን ያሸንፍልሃል። ለሊዮኔል ሜሲ ሁሉንም የባርሴሎና የቡድን አጋሮቹን ማምጣት አለብህ።
የነገ ሟች የዛሬን ሟች ሲቀብር!!!
<<ዛሬ ደህና ሆነህ የምትታይ አንተ ግን የምትሞት ሰው ነህ!!!>> 1ኛ መቃ 33÷7
ሰፈራችን ጠንብቷል!!በመንደራችን የሚያልፍ ሁሉ አፊንጫው ይዞ እየተጠየፈን ነው ሚያልፈው።ነገሩ እኛም ግራ ቢገባን እንጂ መግቢያ መውጫ አጥተናል።መንደሩ አንዳች ጥንባት ተጠናውቶታል።በወይራ ጢስ የማይለቅ ግማ፤በእጣን የማይጠፋ ሽታ፤ሽቶ ቢነፋ አብሮ የሚሸት የሚቀረና ነገር መግቢያ መውጫ አሳጥቶናል....
አከባቢውን ብናስስም የሞተ እንስሳ አደለም ዝንቦች እራሱ ግማቱን ሸሽተው የጠፉ ይመስል ሰፈሩ ውስጥ እንግዳ ነገር አይታይም፡፡በጠዋቱ የመንደሩ ወጣት ራቅ ብሎ ካለ የድንጋይ ቁልል ላይ ተሰብስቦ ስለነገሩ ሲፈልጥ ደርሼ ተቀላቀልኩ...
እኔ ምለው የአቶ አያልነህ ዶሮወች ይሆኑ እንዴ??(አንዱ መላ ምቱን ጣል አደረገ
አረ እሳቸው ዶሮወቻቸው አልቀዋል የእቴ አቦዘነች አንቡላ ይሆናል እንጂ...
ሁሉም መደዳውን የተደረደሩ መንደርተኞችን ቤት እያሰላሰለ ሲያነሳ ሲጥል ድንገት ኦቾ ትዝ ብሎኝ ጥያቄዬን ሰነዘርኩ
እኔምለው ኦቾ የት ሔደ??ዛሬኮ ስላሴዎች ናቸው...
አይ የሱ ነገር አንዱ ፀበል ደሞ ጠፍቶ ይሆናል ወደማታ ብቅ ማለቱ አይቀርም ዝክሩን መቼስ አያልፋት ዛሬ ደሞ የአመት አደል?(አንደኛው በግድ የለሽነት መልሶልኝ ወደሞቀው ወሬ ሲሄድ እኔ ግን ኦቾ ላይ ሙጥኝ ብዬ በሀሳብ ጠፋሁ
ስሌላሴን ከሚሸጠው ኦቾሎኒ ላይ እየዘገነ እያደለ የሚዘክረውን የዋሁ ኦቾን ካየሁት ቆይቻለሁ።እርግጥ ስለሚታመም ድንገት እየተነሳ ፀበል የመሄድ ልምድ ስላለው መጥፋቱ ብርቅ አደለም፡፡ዲያቆን ነው፡፡ድሮ እንደውም ትዝ ይለኛል...የኔታ ከዘኬ
ቤት በፔስታል ቋጥረው እንዲያደርስ የላኩትን ምግብ መንገድ ላይ ቀምተነው በልተን የኔታ ሲጠይቁት''መንገድ ላይ ርቦኝ በላሁት''ያለበትን ቀን አረሳትም።ለኛ ብሎ እኮ ነው... የኔታም ስለሚወዱት አልተቆጡትም።ከዛ ወዲህ ኦቾ ልቤ ውስጥ ቀረ እናት እና አባቱ ከሰጡት ቀበሌ ቤት ውስጥ እየኖረ ኦቾሎኒ
እየሸጠ ነው ሚኖረው....እድሜ ልኩን ከአፍንጫው የሚፈሰው ደም አላስቀድስህ ቢለው እንጂ እንደሱም ያለ ሊቅ ዲያቆን አልነበረም።ሲያዜም ልብ ሳይሆን ነብስ ቀጥ የሚያደርግ ስርቅርቅ ድምፅ አለው እንደ ድምፁ መልኩም ሸጋ ነበር።
ከስላሴ ደብር የሱን ያህል ደሞዝተኛም አልነበረም... ግን ደሞ ህመምና አገልግሎቱ አልጣጣም ቢለው ለመኖር ሲል ቅዳሴውን ትቶት ወደ ንግዱ ገባ.
ደሞኮ እማማ ድማም አጠገብ ነው ሽታው ሚብሰው..
የሌላኛው ወጣት ድምፅ ከወሬወች ሁሉ መሀል ጆሮዬ ሲገባ ከሀሳቤ ብንን ብዬ ቆምኩ ቀድሞም ውስጤ ሲሰጋ የነበረው ነገር እንዳይሆን እየፈራሁ ነበር።ምክንያቱም ከእማማ ድማም ቤት አጠገብ ያለችው የኦቾ ደሳሳ ጎጆ ናት!! ኦቾ ደሞ ምንም ቢሆን በስላሴ ቀን ያውም በአመቱ ከደብሩም ከሰፈሩም ሊጠፋ አይችልም!!ሳላስበው እጄ እየተንቀጠቀጠ እንባዬ እርግፍ እርግፍ ሲል የተሰበሰቡት ወጣቶች አፈጠጡብኝ።እነሱም ከሀሳባቸው እየታገሉ እወነቱን መቀበል ስላልፈለጉ እንጂ የከነከናቸው ነገር እንዳለ ሁሉ...
ምን ሆነካል?? ምን ተፈጠረ??ምን አስበህ ነው???(በጥያቄ አፋጠጡኝ
ኦቾን ከነጋ አላያችሁትም!!ዛሬ ስላሴ ነው እና የት ሔደ ይባላል!??ፈራ ተባ እያልኩ ሳግ እያነቀኝ ጠየኩ
ይሄኔ ሁሉም ሳይነጋገር ብድግ ሲል ጀርባዬን ሰጥቼ እግሬን በእንባ አጀብ ወደ ኦቾ ቤት አሮጥኩት። ከኋላዬ የሚሽቀዳደም ብዙ ኮቴ ይሰማኛል ለወትሮዋ ተከፍታ ምትውለው የኦቾ ቤት ገርበብ ብላ ሳያት ደሞ ጩኸቴ እየበረታ እንደ እብድ እያደረገኝ በሩን በርግጄ ገባሁ።
ኦቾ ኦቾቾቾ ኦቾቾቾቾቾቾ
የሮጥኩበት ገልበቴ ከድቶኝ ተንበረከኩ ለመጮኽ አቅም አነሰኝ ለማልቀስ እንባ አነቀኝ ኦቾ ትንሽዬዋ ፍራሽ ላይ እንደተዘረጋ እጁን በዲያቆናት ወግ ለመግነዝ አመሣቅሎ የስሉስ ቅዱስን ስእል አቅፎ እስከወድያኛው አሸልቧል፡፡
ዲያቆኑ፤ምስኪኑ፤ታዛዡ፤ዝምተኛው፤ታታሪው፤ብቸኛው ኦቾ ጆሮ ጭው የሚያደርግ ለቅሶ እየተለቀሰለት እስከ ነብሱ ጥግ ድረስ የታመነባቸው ስላሴወች በሚከብሩበት ቀን ዝክራቸውን በሚዘክርበት ቀን አፈር ቀመሠ።
"በኑሯችን የምንታመን በሞታችን የማንከዳ ፍፁም የስላሴ ባርያወች
ያድርገን"
