367
Subscribers
+124 hours
-2887 days
-27230 days
Posts Archive
+9
ቀን 06/01/17
በዛሬው እለት በትምህርት ቤታችን የ2017ዓም የመክፈቻ ፕሮግራም በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ በፕሮግራሙ ላይ የተማሪዎች የትውልድ ቅብብሎሽ ስራን አስመልክቶ የ፩ኛ እና ፰ኛ ክስል ተማሪዎች የችቦ ማብራት ፕሮግራም ተካሂዷል
ከዚህ በተጨማሪ የተማሪዎች የዲሲፕሊን መመሪያ ፣ የሂሳብና እንግሊዝኛ ትምህርት ውጤት ማሻሻል፣ እንዲሁም የአራትዮሽ ውል ስምምነት ጥቅም ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በእለቱ የወረዳ ት/ጽ/ቤት ሃላፊ፣ የወረዳ ዋና ስራ አስፈጻሚ በትምህርት ቤታችን በመገኘት ለተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክትና የወደፊት የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል ።
በግቢ በመገኘት የእለቱ ፕሮግራም ላይ በመሳተፍ ፣ ተማሪ በማወያየት፣ ግቢውን በማሳመር ለተሳተፋችሁ ለግቢያችን አካላት ፣ ለወረዳ ሱፐርቪፅን በድን ፣ ለጽ/ቤት ሃላፊያችን በሙሉ ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ውስጥ በሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች የ2017 ትምህርት ዘመን ነገ ሰኞ መስከረም 06/01/2017 ዓ.ም ይጀምራል ።
የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብረሀም ጎሳ ለ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን ከነገ ጀምሮ የ2017 የትምህርት ዘመን ሁሉም የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደቱን በይፋ ለማስጀመር ሙሉ ዝግጅቱ መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
አቶ አብረሀም ጨምረውም አጠቃላይ ሂደቱ ሰላማዊ መማር ማስተማር እንዲሆን አስፈላጊው ስራ የተሰራ በመሆኑ ወላጆች ያለምንም ስጋት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ገበታ መላክ ይኖርባቸዋል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈው አዲሱ የትምህርት ዘመን የሰላም ፣ በዘርፍ የላቀ ውጤት የሚመዘገብበት አመት እንዲሆን ተመኝተዋል።
መስከረም 5/2017 ዓ/ም
ውድ መምህራን እንኳን ለ2017ትምህርት ዘመን በሰላም አደረሰችሁ እያልኩ ጊዛዊ የክ/ጊዜ ድልድል እና የተማሪዎች ምደባ ለ06/01/2017 ወይይት ትኩረት እንድታደርጉ ይሁን። እናመሰግናለን ።
የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1 ሺህ 499ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት እንዲሆን ልባዊ ምኞታችን እናስተላልፋለን፡፡
ቀን 04/01/17ዓም
እንዴት ዋላችሁ ውድ መምህራን እና አስተዳደር ሰራተኞች በሙሉ
እንደሚታወቀው የ2017 ዓም የትምህርት ዘመን ትምህርት ማክሰኞ ይጀመራል ተብሎ እንደነበር ትላንት በነበረን ውይይት ላይ አንስተን ነበር ሆኖም የመውሊድ በአል እሁድ በመዋሉ ምክንያት ትምህርት ሰኞ በ06/01/17ዓም የሚጀመር በመሆኑ ሁሉም መ/ር እንዲሁም አስተዳደር ሰራተኞች በጠዋት መደበኛ ስራ ላይ እንድትገኙ በጥብቅ እንሳስባለን ።
ማሳሰቢያ:- መቅረትም ሆነ ማርፈድ ፈጽሞ የተከለከለ ነው
በእለቱ የተማሪዎች ውይይት በሁሉም የክፍል ደረጃ ይከናወናል
የተማሪዎች የመማሪያ ክፍል ድልድል ይከናወናል
በ03/01/2017 ዓ.ም በአበቦች ፍሬ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በ3 ሰነዶች ዙሪያ መምህራኖች, የአስተዳደር ሰራተኞች , ር/መምህራን , የት/ጽ/ቤት ባለሙያዎች እና የክ/ከተማ ሱፐርቫይዘሮች በተገኙበት ውይይት ተካህዷል::
በዕለቱ የተገኙ አካላት :
መምህራን ወ = 18 ሴ = 23 ድ = 41
የአ/ሰ ወ = 5 ሴ 12 ድ 17
ር/መራን ወ = 2 ሴ = 1 ድ 3
የወረዳ ባለሙያ ወ = 1 ሴ = 0 ድ 1
የአ/ከ/ክ/ከ ሱፐርቫዘር ወ = 1 ሴ = 0 ድ = 1
