en
Feedback
Arada Subcity Small Taxpayers Branch Office CS

Arada Subcity Small Taxpayers Branch Office CS

Open in Telegram

Forms Rules & Regulations

Show more
Ethiopia12 814The category is not specified
827
Subscribers
+224 hours
+137 days
+4930 days
Posts Archive
ለቅ/ፅ/ቤታችን ግብር ከፋዮች በሙሉ ነባር ግብር ከፋዮችን ከብሄራዊ መታወቂያ /ፋይዳ ሲስተም ጋር /የማቀናጀቱ ስራ እየተሰራ ስለሆነ ብሄራዊ መታወቂያ እያወጣቹ መታቹ እንድታቀናጁ እናሳውቃለን።

ለአራዳ ክፍለ ከተማ ለደረጃ ሀ እና ለ ግብር ከፋዮች ባላቹ ደረጃ መሰረት የቴሌግራም ገፆች ስለተከፈተ ከስር በተገለፀው መሰረት በደረጃቹ እንድትቀላቀሉ እንጋብዛለን። ደረጃ ሀ— @Aradakk_Revenue ደረጃ ለ— @Arada_Revenue

የንግድ_ስራ_ገቢ_ግብር_ማስታወቂያ_ቅጽ.docx1.40 KB

ታክስ ከፋይ ማሳወቅ ያለበት ለውጥ ማንኛውም ለታክስ ከፋይነት የተመዘገበ ሰው ስም ወይንም የሚከተሉት ዝርዝር ጉዳዮች ለውጥ ሲደረግባቸው ታክስ ከፋዩ በ30 ቀናት ውስጥ በጽሑፍ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡ ለውጦቹም፡- ▶️ በንግድ ድርጅቱ ስያሜ ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ በድርጅቱ ስም የተመዘገበ:- i. ቋሚ የንግድ ሥራ፣ የቢሮ እና የመኖሪያ አድራሻ ለውጥ፤ ii. በማምረቻ ቦታ ወይም ታክስ ከፋዩ በሚጠቀምበት መጋዘን ላይ የተደረገ የአድራሻ ለውጥ፤ iii.በፖስታ ወይም በመደበኛ እና በተንቀሳቃሽ ሰልክ፣ ፋክስ ወይም ኢ-ሜል አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ በዋነኛ የሥራ እንቅስቃሴው ወይም በቅርንጫፍ ወይም በንግድ ሥራው ዘርፍ ወይም መስክ ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ በድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ ወይም የመመስረቻ ጽሑፍ ወይም የሽርክና ስምምነት ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ በአክሲዮን ባለድርሻ አባላት ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ በድርጅቱ ወይም በታክስ እንደራሴው የባንክ ሂሳብ ወይም የባንክ ቅርንጫፍ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ የኤሌክትሮኒክስ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ በተመዘገበና በተከፈለ ካፒታል ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ የንግድ ሥራውን በከፊል ወይም በሙሉ በማቋረጥ ወይም በሽያጭ ወይም በስጦታ በማስተላለፍ ወይም በመለወጥ ወይም በዋስትና በማስያዝ በድርጅቱ ላይ የተደረጉ ለውጦች፤ ▶️ በንግድ ሥራ ወኪል ወይም የታክስ እንደራሴ ላይ የተደረገ ለውጥ፤ ▶️ የአክሲዮን ትርፍ ድርሻ ለካፒታል ማሳደጊያ ሲውል፤ ▶️ የገቢ ምንጭ መቋረጡን ወይም መሻሻልን በተመለከተ፤ *️⃣ የቤት ወይም የህንፃ ወይም የመጋዘን ኪራይ ውል ሲቋረጥ ወይም ሲሻሻል፤ *️⃣ በተሽከርካሪ ወይም በኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ወይም ሌሎች የካፒታል ወይም የንግድ ሥራ እቃዎች ላይ የተደረገ የኪራይ ውል መቋረጥ ወይም መሻሻል፤ *️⃣ በራሱ ገቢ የሚያስታውቅ ተቀጣሪ ሥራውን ሲለቅ ወይም ሲቀይር ወይም የደመወዝ ለውጥ ሲኖር፤ *️⃣ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴውን በጊዜያዊነት ወይም በቋሚነት ሲያቋርጥ ወይም ሲያሻሽል፤ ▶️ የታክስ ከፋዩ ሠራተኛ ሲጨምር ወይም ሲቀንስ ወይም የሠራተኞች የደመወዝ ለውጥ ሲያደርግ፤

REVISION_2_ESIC_JUly_09_2011_DIRECTIVE_NO_17_2011doc_1.pdf3.07 MB

የተጨማሪ እሴት ታክስ በሶስት ወር ስታሳውቁ ለነበራችሁ ግብር ከፋዮች በሙሉ ከዘህ በፊት የተጨማሪ እሴት ታክስ በሶስት ወር ስታሳውቁ ለነበራችሁ አዲስ እና ነባር ግብር ከፋዮች ከሀምሌ 1/11/2016 ጀምሮ በየወሩ የተጨማሪ እሴት ታክስ  መሳዋቅ  ያለባችሁ መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡

ቀን 12/11/2016                               ማስታወቂያ ለቅ/ጽ/ቤት ግብር ከፋዩች በሙሉ   አጠቃላይ የሰራተኛ ስብሰባ ስለአለ በቀን 13/11/2016 ዓ/ም አገልግሎት የማንሰጥ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

አዲሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ

ARADA.xlsx0.83 KB

ለቅርንጫፍ  ጽ/ቤታችን ግብር ከፋዩች በሙሉ ከ2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የግብር ከፋዮች ደረጃ ምደባ በአዲስ መልክ እየተሰራ በመሆኑ የግብር ማሳወቂያ የቅርንጫፍ ፅ/ቤት ለውጥ ተደረጓል። ስለሆነም ስማችሁ ከዚህ በታች  የተገለጻችሁ ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓ/ም ግብራችሁን የምታሳዉቁት በተዛወራችሁበት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መሆኑን እየገለጽን የተዛወራችሁበት ቅ/ጽ/ቤት ከዚህ በታች በዝርዝር ተቀምጧል።   ከሰላምታ ጋር