Official Fenote Loza Media
Open in Telegram
ይሄ መንፈሳዊ ቻናል በፍኖተ ሎዛ ሰንበት ት/ቤት ምዕመናንን ለማስተማርና ጠንካራ መንፈሳዊ ህይወት እንዲኖራቸው ለማድረግ የተከፈተ ሲሆን ሰብስክራብ በማድረግ እና ለሌሎች ቻናሉን በማጋራት የመንፈሳዊ ቤተሰባችን አባል ይሁኑ ። አብረን በመንፈሳዊነት እንድናድግ ፣ እንድንማር እንዲሁም እንድናዉቅ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ጋብዘኖታል።
Show more1 211
Subscribers
-124 hours
-27 days
-330 days
Posts Archive
🌺✨ እንኳን አደረሳችሁ✨🌺ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር- እግዚአብሔር የሰራት ቀን ይህች ናት (መዝ 117(118)፡24) ይህች ዕለት በበሽታ ዅሉ ላይ በሰው ልጆች ቁስል ላይም የተሾመ ፈታሄ ማህጸን ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ የስሙ ትርጓሜ ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር መሐሪ፣ ቅን የዋህ ማለት የሆነ የቅዱስ ሩፋኤል በአለ ሢመቱ፣ የቅዳሴ ቤቱም የሚከበርባት ዕለት ናት። (ጦቢት ፲፪፥፲፭) ዳግመኛም በዚህች ዕለት አስማንድዮስ የተባለ ጋኔን በወለተ ራጉኤል ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ቢያሰቃያት ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስጨንቆ አስወጥቶላታል (ጦቢት ፫፥፰-፲፯)፡፡ የጦቢትን ዓይንም አብርቶ ለልጁ ለጦቢያም መልካም ትዳርን ያበጀለት በዚህች ዕለት ነው። ይህች ዕለት ከዕለታት ተለይታ የተመረጠች ናት። የሰማይ ደጆች የሚከፈቱባት መላእክት የሚወጡባት የሚወርዱባት ጸሎት ልመናችንንም የሚያሳርጉባት የእግዚአብሔር አምላካችንን ቸርነት ምህረትን የሚያወርዱባት ዕለት ናት። ቀላያተ ማያትም የሚባረኩበት ለእያንዳንዱ ለሚያምንም ሁሉ የስጋም የነፍስም ድኅነት የሚያገኝባት ዕለት ናት።
የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ ቅዱስ ሩፋኤል(ጦቢት ፲፪፥፲፭) ለሀገራችን ለምድራችን ቸርነት ምህረትን ያድርግልን። በአዲሱንም ዓመት ባርኮ ይስጠን።ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ TikTok | Instagram | YouTube ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
+9
✨✨በትላንትናው እለት ፍሎተ ሎዛ ለሁለት ወር በትጋት ቃለ እግዚአብሔርን ያስተማረቻቸውን ልጆቿን አስመረቀች✨✨
በህጻናት ምርቃት ወቅት የተነሱ ማስታወሻ ፎቶዎች📸✨
🌸አማኑኤል ይቅር ባይ ነው🌸
አማኑኤል ይቅር ባይ ነው ፍቅር
ምሕረት ከቦት በሰማያት የሚኖር
እያመመው አባቱን እየጠራ
አይቻለሁ ለሚገድሉት ሲራራ
አዝአይምረኝም አትበሉ ጨካኝ ንጉስ አይደለም ደሙ ብቻ ያነጻናል ከኃጢአታችን ዘላለም እንደ ሞላ ጅረት ፈሶ ምድራችንን አጥለቅልቋል የእርሱ ምሕረት ኃይል ሆኖት ስንቱ ከሞት አፈትልኳል
አዝየጨለመው እየነጋ የተሻለ ቀን ይመጣል በፍቅሩ ጦር ሳይወጋ ማን ከሞት ፊት ሮጦ ያመልጣል ይን ክፋ ቀን በድል አልፈን እንደ ዋርካ የሰፋነው ነውርን ሁሉ በሚከድን በሞተልን በኢየሱስ ነው
አዝየእርሱን ፍቅር የሚያሸንፍ አንዳች ኃጢአት የለምና ወደ ጌታ ለመመለስ አንዳች እንኳን እንዳትፈራ ሀገራችን በሰማይ ነው የሚወድቅ የለም የሚረሳ ሰማያትን እንወርሳለን ከበጉ ደም የተነሳ
አዝወዳጅ አለን አንድ ብቻ በሰማይም በምድርም ስሙ ኢየሱስ የተባለ ሰውን ሁሉ የሚያፈቅር ከመቃብር በላይ ሆኖ ፍቅሩ ዓለምን አስገረመ ይህን ሁሉ ጎስቋላ ሰው በትከሻው ተሸከመ ዘማሪ እዝራ ኃይለ ሚካኤል
የመጽሐፍ ዳሰሳ📚
የኤፍራጥስ ወንዝክፍል ሁለት የመጽሐፉ መዋቅርና የአቀራረብ ዘይቤ መጽሐፉ በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች የተዋቀረ ሲሆን፣ በጠቅላላው ከ30 በላይ ጥልቀት ያላቸውን መጣጥፎችና የበዓላት ስብከቶችን አካቷል፦ ክፍል አንድ (መጣጥፎች)፦ በዚህ ክፍል ደራሲው መንፈሳዊ ሕይወትን፣ የትሕትናን ጥልቀት፣ የእግዚአብሔርን ፍርድ ምስጢር፣ የክብረ ክህነትን ክብርና የዘመኑን ቤተ ክርስቲያናዊና ማኅበራዊ ፈተናዎች የሚዳስሱ መጣጥፎችን አቅርቧል:: «የኤፍራጥስ ወንዝ»፣ «እግዚአብሔር እንዴት ይፈርዳል?»፣ «የካም ትውልድ»፣ «ደስ ይበላችሁ» እና «ጌታ ሆይ ይህን ውኃ ሥጠኝ» የሚሉት መጣጥፎች የዚህ ክፍል ጉልህ ማሳያዎች ናቸው:: ክፍል ሁለት (የበዓላት ስብከቶች)፦ በዚህ ክፍል ደግሞ ከልደት እስከ ደብረ ታቦር ያሉትን ዋና ዋና የቤተ ክርስቲያን በዓላት፣ ምስጢራትንና የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን መሠረት ያደረጉ ስብከቶች ቀርበዋል:: እያንዳንዱ ስብከት የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን ከታሪክ አጋጣሚዎች ባሻገር ጥልቅ መንፈሳዊና ምሳሌያዊ ትርጉማቸውን ይገልጣል:: በወፍ በረር ሁሉንም ምእራፍ እንመልከት:- 1)የኤፍራጥስ ወንዝ (የመጽሐፉ መግቢያና መነሻ) — ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ቅዱስ ኤፍሬምን «የቤተ ክርስቲያን የኤፍራጥስ ወንዝ» ብሎ የጠራበትን ምክንያትና የመጽሐፉን ዋና መንፈሳዊ ዓላማ ያብራራል። 2)የዕንባ አባት ቅዱስ ኤፍሬም — የቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊን የዕንባ ሕይወት፣ ጸሎትና ቀንና ሌሊት ስለ ኃጢአትና ስለ ቤተ ክርስቲያን የሚያነባውን ጥልቅ ቅዱስ ዕንባ ይተነትናል። ይቀጥላል... ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ TikTok | Instagram | YouTube ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
+9
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
የሐምሌ 16 የእናታችን የቅድስት ኪዳነ ምሕረት ንግስ ክብረ በዓል በአያት ጌቴሴማኒ ቅድስት ኪዳነምሕረት እና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ የተነሱ በሰዎች ፎቶዎች 📸
ነሐሴ 16 2018 ዓ/ም
ፍኖተ ሎዛ ሚዲያ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
+9
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
የሐምሌ 16 የእናታችን የቅድስት ኪዳነ ምሕረት ንግስ ክብረ በዓል በአያት ጌቴሴማኒ ቅድስት ኪዳነምሕረት እና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ የተነሱ በሰዎች ፎቶዎች 📸
ነሐሴ 16 2018 ዓ/ም
ፍኖተ ሎዛ ሚዲያ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
TikTok | Instagram | YouTube
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨"ሞት በጥር፤ ነሐሴ መቃብር"✨እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ይህ የፍኖተ ሎዛ ሚዲያ ነው!! እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በስልሳ አራት ዓመቷ በጥር ፳፩ ቀን ጌታችን መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ ከዚህ ዓለም ድካም ሊያሳርፋት ሲል፣ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁን? አለችው። ጌታችንም በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል ባላትም ጊዜ እመቤታችን "ሞቴስ ለእነሱ ቤዛ የሚሆን ከሆነ ይሁን" በማለት ዕረፍቷን በደስታ ተቀበለች። ሐዋርያት ሥጋዋን ሊቀብሩ ወደ ጌቴሰማኒ ሲወስዱ አይሁድ ስጋዋን ሊያቃጥሉ ተነሱ። ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ አጎበሩን ጨበጠ፤ መልአክ እጁን በሰይፍ ቢቆርጠውም፣ ተጸጽቶ ሲማጸናት ተፈወሰ። ከዚህ በኋላ ጌታ ሥጋዋን በደመና ነጥቆ ቅዱስ ዮሐንስን አስከትሎ በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖረው። ሐዋርያትም ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ነሐሴ ፩ ቀን ሱባዔ ጀመሩ። በሁለተኛው ሳምንት (ነሐሴ ፲፬) ጌታ ሥጋዋን ሰጥቷቸው ቀበሯት፤ በሦስተኛው ቀን (ነሐሴ ፲፮) እንደ ልጇ ተነሣች። ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ በደመና ሲመጣ እመቤታችን ስታርግ አገኛት። ሰበኗን ሰጥታው ሂዶ ለሐዋርያት እንዲነግራቸው ላከችው። ሰበኗንም ለበረከት ተካፈሉት። በሚቀጥለውም ዓመት ሐዋርያት ትንሣኤዋን ለማየት ደግመው ጾሙ፤ ነሐሴ ፲፮ ቀንም እመቤታችንን መንበር አድርጎ ጌታ እራሱ ቀድሶ አቆረባቸው።ቤተክርስቲያንም ይህንን መታሰቢያ አድርጋ በየዓመቱ ታከብረዋለች። 🌸የእመቤታችን ምልጃዋና በረከቷ አይለን🌸
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር
🌸 ማርያም አርጋለች 🌸
ማርያም አርጋለች ወደ ገነት/2/
የሰማይ መላእክት እያረጋጓት
እርሷም እንደ ልጇ ተነስታለች
አዝየአባቷን ዳዊት ትንቢት ልትፈፅም ወርቁን ተጎናፅፋ በቀኙ ልትቆም ወደ አምላክ ማደሪያ ወደ ሰማያት አረገለች በእልልታ ድንግል የእኛ እናት አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝሰማያት ይከፈት ደመናም ይዘርጋ ዝምታም አይኖርም እመ አምላክ አርጋ አንደበት ይከፈት ማርያምን ያመስግን ከዘላለም ጥፋት በምልጃዋ እንድንድን አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝየአምላክ ማደሪያ ቅዱስ ሥጋሽ አምላክን ያቀፉት እነዚያ እጆችሽ ሙስና መቃብር ይዞ አላስቀራቸው ተነስተዋል በክብር በእምነት አየናቸው አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝሐዋርያት አበው እንኳን ደስ አላችሁ በክብር አረገች ማርያም ሞገሳችሁ ወደ ዓለምም ውጡ ሰበኑዋን ይዛችሁ የድንግል እርገቷን ንገሩ ተግታችሁ አርጋለች ማርያም ተነስታለች ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
🌸✨እንኳን አደረሳችሁ✨🌸
+6
✨በአያት ጌቴ ሴማኒ ቅ/ኪዳነምሕረት እና ቅ/ገብርኤል ቤተ/ያን የደብረታቦር በዓል እንዲህ ባማረ መልኩ ተከብሯል።✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
TikTok | Instagram | YouTube
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
+5
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዛሬው ዕለት በሰንበት ትምህርት ቤታችን በነበረን ከአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ጋር የአንድነት የጸሎት መርሐግብር ላይ በሕብረት ዝማሬ ወቅት የተነሱ ፎቶዎች 📸
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨✨በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!✨✨
🔔 የፍቅር ማዕድ/አጋፔ እንቋደስ 🔔 ✨✨✨
📆 አርብ ነሐሴ 22 2018 ዓ.ም
⏰ ከ11:30 ጀምሮ
📻በዕለቱ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ ሻይ እና ቡና ፣ ዳቦና ቆሎ (የፍቅር ማዕድ) ፣ መንፈሳዊ ጨዋታዎች ይኖራሉ
⛪️ በአያት ጌቴሴማኒ ቅድስት ኪዳነምሕረት እና ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ፍኖተ ሎዛ ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ
📌የቲኬት ዋጋ :150 ብር ብቻ
በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ በመገኘት አልያም በቴሌብር 0978800327 መቁረጥ ይችላሉ።
ለበለጠ መረጃ: @K_anasimon
ኪነ ጥበብ ክፍል 📌📌ማሳሰቢያ፡ ያለን ውስን ቦታ በመሆኑ ቀድመው ቲኬቱን ይቁረጡ!!
"መከራ እግዚአብሔር እንደ ሐኪም ፈውስን የሚሰጥበት መድኃኒት እንጂ የሚቀጣበት ጅራፍ እንዳልሆነ እንረዳ።"
ሊቁ አውግስጢኖስ
መከራ ሁላችንም በስምምነት የምንሸሸውና የምንፈራው የሕይወታችን አካል ነው። ይህ ሽሽት ተፈጥሮአዊ ነገር ቢሆንም የሚደንቀው ነገር በድሮ ጊዜና በዘመናችን የተነሱ ፈላስፎች ሳይቀሩ የመከራን ጠቀሜታ መናገራቸው ነው። የሰው ልጅ በምቾት ሕይወት ውስጥ የተደበቀው አቅሙ በመከራ ጊዜ እንደሚገለጥና እንደሚጠነክር ይናገራሉ። ለክርስቲያን ግን መከራ ከዚህ የላቀ ጥቅም አለው። መከራ በዚህ ዓለም ምቾት ተዘፍቆ ይህችን ምድር እንደ ዘላቂ መኖርያው መጠበቅ ለሚፈልገው ሰው የዚህን አስተሳስብ ስህተትነት በታላቅ ድምጽ ትናገራለች። ለሰው ልጅ እውነተኛ ደስታና ሰላም በዚህ ዓለም እንደማይገኝ ትመሰክራለች። እግዚአብሔርም በመከራ መድኃኒትነት ይህችን ዓለም ቤታቸው ለማድረግ የሚጥሩ ነፍሳትን ይጠራል። ይህ ዓለም የጭንቀትና ችግር መፈራረቂያ የሆነበትም ሰው እውነትኛ ሰላምና እረፍትን ፍለጋ ከአምላኩ ጋር ይጣበቃል።
"Let us understand God is a physician and suffering is a medicine for salvation, not a punishment for damnation."
Augustine of Hippo
Suffering is the main taboo in our society that we all collectively agree to flee from. That is natural, as who would want to be in pain? But not only the christians but the atheistic philosophers of old times and now have agreed to the salvific effect of suffering. They have observed suffering has the capacity to reveal the true potential of a person otherwise hidden in the comfort zone of life. A christian agrees to this saying and more over derives another meaning to suffering. For the christian, suffering loudens the alarm letting one know that true comfort and happiness is not to be found on earth, as it doesn't exist. If one gets accustomed to a life of comfort here, one will inevitably believe it to be its true home. Thus, God, who has destined man for a greater dwelling than here, teaches him to pine after his true home by medicating him in suffering. The sufferer will then long after true rest as he is not finding it here, thus possessing true comfort in God through the process.
የቀጠለ....
የመናኞቹ መንገድ 📖
✨ ምዕራፍ አስራ ዘጠኝ፡ ስለ ጸሎት ✨
ክፍል ሦስትንቅአ ሕሊናን የሚለማመድ ሰው ምላሱን ብቻ ሳይሆን ውስጣዊ ማንነቱንም ወደ ጥልቅ በመግባት መፈተሽና መጠበቅ ይኖርበታል (ገላ 6፤1)፡፡ በንቅአት ሊጠበቁ የሚገባቸውን በውስጣቸውም የኃጢያት ትዝታዎችንና ሃሳቦችን የያዙ ሰፊ መዝገብ ቤቶችን ያገኛል፡፡ ጸሎትህን የሚረብሽ ትዝታን በመኮርኮር ለማስታወስ አትሞክር፤ ባለፉ ኃጢያቶች ውስጥ በመርመስመስ ወደትፋቱ እንደሚመለስ ውሻ አትሁን(ምሳ 26፤11)፡፡ ይህ የባላጋራህ ተወዳጅ መፋለሚያ ሲሆን ከርሱ ጋር ንግግር እንድትጀምር እንዲሁም ፈተናውን እንድትቀበለው የሚያደርግበት ቦታ ያንተ ሐሳብ እንደሆነ ተገንዝበህ የተለያዩ ፍላጎቶችን የሚያነሳሱ ትዝታዎችና ሐሳቦች ላይ ጊዜህን አታጥፋ፡፡ በምናብ ዓለም ውስጥ ጥርጥርና ጭንቀት እንዲሁም አመክንዮአዊ ንግግሮችና ምስክሮችን እና የማይጠቅሙ ጥያቄዎችን ከራስህ ከሚገኙ መልሶች ጋር የሚዘራበት ተመራጭ ቦታው ነውና እነዚህ ነገሮች ሲቀርቡህ በመዝሙረኛው ቃላት እናንተ ኃጢያተኞች ከእኔ ራቁ ብለህ አባራቸው(መዝ 119፤115)፡፡ ✨Chapter Nineteen : ON PRAYER✨
part threeBut it is not only the tongue that the person who practices the art of watchfulness must control. He must look to himself (Galatians 6:1) in every detail, and his care must extend to the depths of his being. Deep within he finds immeasurable store-rooms, where memories and thoughts and fantasies stir about and must be restrained. Do not stir up a memory that will cover your prayer with mud, do not root around in the soil of your old sins. Do not be like the dog that returneth to his vomit (Proverbs 26:11). Do not let your memory linger on private matters that can reawaken your desire or set your imagination going. The devil's favourite wrestling-place is precisely our imagination; through it he draws us to further intercourse with him, to consent and action. In your thought-world he sows doubt and worry, attempts at logical reasoning and proof, fruitless questions and self-found answers. Meet all such things with the words of the Psalm: Away from me ye wicked (Psalm 1 119:115).
