en
Feedback
TMA (Traffic Management Authority)

TMA (Traffic Management Authority)

Open in Telegram

Work With Us / 'ከኛ ጋር ይስሩ'

Show more
6 664
Subscribers
-424 hours
+17 days
-3830 days
Posts Archive
የጥንቃቄ መልእክት ለአሽርካሪዎች‼️

የዛሬ ዷጉሜን 4 የህብር ቀን አስመልክቶ በህብር እና በወዳጅነት መንፈስ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን እና የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ባለስልጣን መካከል በተካሄደ የእግር ኳስ ግጥሚያ የአ
+3
የዛሬ ዷጉሜን 4 የህብር ቀን አስመልክቶ በህብር እና በወዳጅነት መንፈስ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን እና የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ባለስልጣን መካከል በተካሄደ የእግር ኳስ ግጥሚያ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የእግር ኳስ ቡድን በከፍተኛ የጎል ብልጫ አሸነፈ ። እንኳን ደስ አላችሁ! ስፖርት ለወዳጅነት! ለአንድነት!

በባለስልጣን መ/ቤቱ ጳጉሜን 3 የጽናት ቀን ተከበረ ***** (ት/ማ/ባ ጳጉሜን 3 /2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ጳጉሜን 3 የጽናት ቀንን የዋናው መ/ቤት እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች እንዲሁም በጎ ፈቃደኛ ትራፉክ አስተናባሪዎች በጋራ አክብረዋል፡፡ የጽናት ቀንን የሚከበረው የህዝብን ሰላምና ሁለንተናዊ እድገት መሳካት በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት የሚጠብቁ ጀግኖችን ለማክበር እንደሆነ መልእክቶች ተላልፈዋል፡፡ እንዲሁም ለሀገራቸውና ለህዝባቸው ሉዓላዊነትና አንድነት ሲሉ ውድ ህይወታቸውን ላጡ የመከላከያ እና የፖሊስ አባላቶችን በከፍተኛ አገራዊ ክብር የምናስባቸው እለት መሆነም ተጠቁሟል፡፡ እለቱን አስመልክቶም ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ /ዶ/ር ያስተላለፉትን መልእክት ለሰራተኛው በንባብ ቀርቧል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙርም በአንድነት ተዘምሯል፡፡

የጽናት ቀን ኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው በዚህ የጽናት ቀን፣ ለሀገረ-መንግሥታችን ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትን የጀግኖቻችንን ታሪካዊ መስዋዕትነት በከፍተኛ ሀገራዊ ክብር የምንዘክረው፡፡ ዛሬ ላይ ሀገራችን በራሷ ዕውቀትና በልጆቿ አቅም የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸውን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ ዘመናዊ የታጠቁ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን፣ ከባድ መሣሪያዎችንና መድፎችን፣ እንዲሁም ተተኳሽ ጥይቶችን በራሷ ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች ማምረት ችላለች፡፡ ይህ በራስ የመቆም አቅም፣ የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሀገራዊ ጽናታችንን በተጨባጭ ልማትና በጠንካራ የመጠበቅና የመከላከል አቅም እያረጋገጥን የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና እናጸናለን! #EthiopiaPrevails ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

‹ከካሜራ ጀርባ ያለው እውነታ!* *የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን* ************************ (ት/ማ/ባ ጳጉሜን 2/2018) በነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡20 ሰዓት ላይ በአራዳ ክፍለ ከተማ እናት ሕንፃ አካባቢ የተፈጠረውን ክስተት የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል በተመለከተ ተቋሙ ማጣራት እንደሚያደርግና የማጣራቱን ውጤት ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ቀደም ሲል ገልጾ ነበር። በዚህም መሠረት በተደረገው ማጣራት፣ በተጠቀሰው ሰዓትና ቦታ አንድ አሽከርካሪ የትራፊክ ሕግና ደንብን በመተላለፍ በተከለከለ ቦታ ተሽከርካሪውን አቁሞ እንደነበር ተረጋግጧል። በመሆኑም በሥራ ላይ የነበሩት የትራፊክ ቁጥጥር ባለሙያዎች ሕጉን ለማስከበር ተሽከርካሪውን እንዲያነሳና የመንጃ ፈቃዱን እንዲያስረክብ ሲጠይቁት፣ አሽከርካሪው በባለሙያዎቹ ላይ ስድብና ዛቻ ከማድረሱም በላይ በአካላዊ ኃይል በመጠቀም ገፍትሮና ደብድቦ በአካባቢው ሁከት ከፈጠረ በኋላ ከቦታው መሰወሩ ተረጋግጧል። ይህንንም ክስተት የሚያሳይ የሲሲቲቪ ምስል በአካባቢው ከሚገኘው የማኅበራዊ ዋስትና ሕንፃ የደኅንነት ቁጥጥር ካሜራ ተቀርጾ የነበረ ሲሆን፣ በይፋዊ ጥያቄ መሠረት ለተቋሙ የተሰጠው የኤሌክትሮኒክስ ማስረጃም በማጣራቱ ተካቷል። በመሆኑም ተቋሙ የተገኘውን ማስረጃ በማያያዝ በደንብ ተላላፊው አሽከርካሪ ላይ ተገቢው ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ በ2/13/2018 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ ለአራዳ ክፍለ ከተማ ጣይቱ ፖሊስ ጣቢያ ጥያቄ አቅርቧል። በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 441(1)(ሀ) መሠረት የመንግሥት ሠራተኛ የሥራ ግዴታውን እንዳይወጣ በዛቻ ወይም በኃይል የሚያደናቅፍ ድርጊት ሕጋዊ ተጠያቂነትን ያስከትላል። ሕግ አስከባሪዎች የግል ፍላጎትን ለማስፈጸም ሳይሆን፣ ሕግን፣ ሥርዓትንና የህዝብን ደኅንነት ለማስጠበቅ በሥራ ላይ የሚገኙ የመንግሥት ወኪሎች ናቸው። ስለሆነም በሥራ ላይ ያሉ የትራፊክ ቁጥጥር ባለሙያዎችን መስደብ፣ ማስፈራራት፣ መገፋት ወይም መደብደብ ተቋሙ በጥብቅ የሚያወግዘው ድርጊት ነው። የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ሁሉም አሽከርካሪዎች የትራፊክ ሕግና ደንብን በማክበር፣ ለትራፊክ ቁጥጥር ባለሙያዎች ተገቢውን ትብብር በማድረግና ከማንኛውም ዓይነት ስድብ፣ ዛቻና ጥቃት በመቆጠብ የመንገድ ደኅንነትና የሕግ ማስከበር ሥራን እንዲደግፉ ያሳስባል። *ሕግን ማክበር የሁላችንም ኃላፊነት* ነው። *የመንገድ ደኅንነት የጋራ ኃላፊነታችን ነው።*

የማንሰራራት ቀንን ምክኒያት በማድረግ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ነው። የአዲስ አመት መቀበያ የሆነችው ጳጉሜን ቀናት በተለያየ ስያሜዎች እየተከበሩ ሲሆን የዛሬው ጳጉሜን 2 ደግሞ በማንሰራራት ተሰይሟል። የአዲስ አበባ የማንሰራራት ማሳያ የሆነው የትራንስፖርት ዘርፍም ለከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ቀኑን እያከበረ ነው። ለግማሽ ቀን በሚቆየው ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የከተማ አውቶብስና የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ለደንበኞቻቸው መልካም የአዲስ አመት በመመኘት ጭምር እየተሳተፉ ነው። በቦሌ ሚሊኒየም አካባቢ የተሰጠውን ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በነጻ ትራንስፖርቱ 1.1 ሚሊየን የመዲናዋ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። የአዲስ አበባ የማንሰራራት ማሳያ ከሆኑ ልማቶች መካከልም የትራንስፖርት ዘርፉ ዋነኛው ነው ያሉት አቶ ዳኛቸው የአዲስ አበባን ዝማኔ የሚመጥኑ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማስፋፋት ዘርፉን ማንሰራራት ተችሏል ብለዋል። ምቹ መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋትና የዘመነ አገልግሎትም በዘርፉ መሻሻል ማሳየቱ ነው ምክትል ቢሮ ኃላፊው የገለጹት። #Ethiopia #addisababa

በኢምፒርያል እና ጎላጎል አካባቢዎች የመንገድ ደህንነት ማሻሻያ ተግባራት እየተከናወኑ ነወ ******************* (ት/ማ/ባ ጿጉሜ 2/2018) የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥና የከተማዋን የትራፍክ እንቅስቃሴ ለማሻሻል 24/7 እየሰራ ይገኛል። በዚህ መሠረት፣ በImperial Overpass እና ጎላጉል አካባቢ የመንገድ አካፋይ ጠርዝና የትራፊክ አቅጣጫ በግልጽ እንዲታይ እያደረገ ነዉ። በተለይም አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ የመንገድ ክፍልን ለማመላከት እና አሽከርካሪዎች ከተወሰነው የጉዞ መስመር እንዳይወጡ ለመርዳት Flexible Plastic Delineator Posts ተገጥመዋል። ይህ የመንገድ ደህንነት መሳሪያ ደልነተሮች በተለይ የOverpass መግቢያ አካባቢን በግልጽ እንዲለዩ በማድረግ አሽከርካሪዎች በተፈቀደው የትራፊክ አቅጣጫ እንዲጓዙ እና በተከለከለ ቦታ እንዳይዞሩ ያግዛሉ። በተለይም በሌሊትና በዝቅተኛ የእይታ ሁኔታ ወቅት በግልጽ የመንገድን መስመር በማመላከት ፣ ተገቢ ያልሆነ ቅስቃሴን እና ያልተፈቀደ የመንገድ መሻገርን በመከላከል በአከባቢ የትራፍክ አደጋን ለመቀነስና ተገቢ የሆነ የትራፍክ ፍሰት እንዲኖር የጐላ ሚና ይኖረዋል። እንደ ማሳሰቢያ ለአሽከርካሪዎችና ለመንገድ ተጠቃሚዎች በሙሉ፦ 1. የመንገድ ምልክቶችንና የትራፊክ መመሪያዎችን በማክበር የተፈቀደውን የጉዞ አቅጣጫ ብቻ ይከተሉ። 2. U-Turn ማድረግ ሲያስፈልግ ከOverpass ስር በTraffic Signal የሚመራውን የተፈቀደ የመዞሪያ ቦታ ብቻ ይጠቀሙ። 3. ያልተገባ እንቅስቃሴ በማድረግ በተተከለዉ መሰረት ልማት ላይ ጉዳት የሚያደርሱት ላይ አኣባቢዉ ባሉ ካሜራዎች 📹 በመታገዝ ተገቢዉ የእርምት እርምጃ ይወሰዳል። ነፃ የስልክ መስመር 696ን ይጠቀሙ

አሮጌውን ዓመት ሸኝተን፤ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ እገኛለን፡፡ አዲሱን ዓት በደስታ እና በፍቅር ለመቀበል ሁላችንም የመንገድ ደህንነት ደንቦችና ህጎችን በማክበር ከትራፊክ አደጋ እንጠበቅ፡፡ 🙏 ውብ
አሮጌውን ዓመት ሸኝተን፤ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ እገኛለን፡፡ አዲሱን ዓት በደስታ እና በፍቅር ለመቀበል ሁላችንም የመንገድ ደህንነት ደንቦችና ህጎችን በማክበር ከትራፊክ አደጋ እንጠበቅ፡፡ 🙏 ውብ ዋዜማ ብሩህ ወርሃ ጳጉሜ!💥 መልካም የማንሰራራት ዘመን ይሁንልን!😇 የአዲስ አበባ ትፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን!

የ"ጎቤ" እና "ሺኖዬ" ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው ከክረምት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገርን የሚያበስረው “የጎቤ” እና “ሺኖዬ”ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡፡ በኦ
+2
የ"ጎቤ" እና "ሺኖዬ" ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው ከክረምት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገርን የሚያበስረው “የጎቤ” እና “ሺኖዬ”ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡፡ በኦሮሞ ባህል ዘንድ የክረምቱን መውጣትና የጸደይ መዳረሻን ለማብሰር ከሚከናወኑ ባህላዊ ሥርዓቶች መካከል “የጎቤ” እና “ሺኖዬ” ጨዋታ ተጠቃሽ ነው። AMN

ጳጉሜን 1 የሚከበረውን “ የእመርታ ቀን” በማስመልከት የፎቶ አወደርዕይ በታላቅ ድምቀት ተከፈተ "የእመርታ ቀን" ምክንያት በማድረግ፣ የከተማችንን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ በሚያሳይ በዚህ አውደርዕይ
+1
ጳጉሜን 1 የሚከበረውን “ የእመርታ ቀን” በማስመልከት የፎቶ አወደርዕይ በታላቅ ድምቀት ተከፈተ "የእመርታ ቀን" ምክንያት በማድረግ፣ የከተማችንን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ በሚያሳይ በዚህ አውደርዕይ እና የፓናል ውይይት የዕለቱ የክብር እንግዳ የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር አቶ ባዮ ሽጉጤ በተገኙበት ተከፍቷል ፡፡ የክቡር እንግዳው በመክፈቻ ንግግራቸው “የገቢዎቻችን ማደግና የፋይናንስ ሥርዓታችን መጠናከር፣ በፕላንና በዲዛይን የታገዙ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች፣ በኢንዱስትሪና በአርሶ አደርና ከተማ ግብርና የታየው ምርታማነት፣ ከአካባቢ ጥበቃ ጋር ተጣጥሞ የልማት አካሄዳችን ዘላቂ የወደፊት ጉዞ ያመላክታል በማለት እነዚህ ውጤቶች መድረሻችን ሳይሆኑ ለአዲሱ የዕድገት ምዕራፍ መነሻ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል። አክለውም በከተማዋ የተመዘገቡት ስኬቶች የሀገሪቱን አጠቃላይ የእመርታ ጉዞ የሚያጠናክሩ በመሆናቸው ይህን በጎ ልምድ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ ተናግርዋል። በአራዳ ፓርክ በተከፈተው በዚህ አውደርዕይ እና የፓናል ውይይት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ ታላላቅ ከተማ አቀፍ ስኬቶችን የቀረበ ሲሆን ፤ የፕላንና ልማት ቢሮ፣ የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን፣ የኢንዱስትሪ ቢሮ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የዲዛይንና ግንባታ ቢሮ፣ የገቢዎች ቢሮ እና የፋይናንስ ቢሮ በጋራ በመሆን ያዘጋጁት እንደሆነ ተነግሯ

የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲ
የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

#የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በ24/7 የስራ ባህል የመንገድ ደህንነት ማሻሻያ እየሰራ ነዉ ****** (ት/ማ/ባ ነሀሴ 30/2018) የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ከመገናኛ ቦሌ መስመር ኢምፒርያል መንገድ ኦቨር ፓስ ላይ የመንገድ አካፋይ እየሰራ ይገኛል። የመነገድ ደህንነት ምህንድስና ዳይሬክተር ኢንጂነር መርጋ እንዳሉት ቀደም ሲል መንገዱ ለአሾከርካሪዎች ምቹ ባለመሆኑ ለደህንነት እኖ ፍሰት እንቅስቃሴ መሳለጥ በአሁኑ ወቅት ጥናት ላይ የተመሰረተ የመንገድ አካፋይ እነተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።