cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ANEL MUSLIM

አሠላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ ውድ የቻናሌ ቤተሠቦች በዚህ ቻናል ላይ ➬እስላማዊ መረጃዎች ➬እስላማዊ ታሪኮችን ➬ሶሒህ የሆኑ ሀዲሶች ➬ፒክቸሮችን ያገኛሉ!!! ስለ ቻናሉ ሀሠሳብ ፣አስተያየት ካላቹ inbox፦ @ABD_Buna👈 መወያያ ግሩፕ ፦ https://t.me/ISLAMICgroup11 ላይ ያገኙናል፡፡ ANEL MUSLIM

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
202
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ጥቂት ስለ አሕመዲን ጀበል ንግግር‼ ========================== ✍ ሰሞኑን አሕባሾችና መሰሎቻቸው አሕመዲን ጀበል ነቢያችንን ﷺ «ሰለምቴ ናቸው ብሏል!» ብለው ከልክ በላይ ሲያስጮኹ ነበር። ቪድዮውን እኔም ተመልክቸዋለሁ። ነገር ግን በቀጥታ ንግግሩን ወስዶ ወደ ብይን ከመግባት ይልቅ ትንሽ በተን አድርጎ መመልከት ቢቻል ያ ሁሉ ጩኸት አያስፈልግም ነበር። «ሰለምቴ» ማለት ምን ማለት ነው? በኛ አማርኛ በብዛት የምናውቀው የሰለምቴ ትርጉም ሙስሊም ያልነበረ ሰው ሲሰልም ነው። ነገር ግን አሕመዲን ጀበል ይህን ቃል የተጠቀመው ወሕይ በነቢያችን ላይ ከወረደላቸው በኋላ ለወረደው ወሕይ እጅ ሰጥተው በመቀበል የሰለሙ ሰለምቴዎች ማለት ፈልጎ ከሆነ ልክ ነው። ነቢያችን ﷺ በርሳቸው ላይ ወሕይ ከመውረዱ በፊት ሙስሊም ናቸው። ከወረደም በኋላ ሙስሊም ናቸው። እስልምና በርሳቸው የተጀመረ ሳይሆን ከጥንት ከጠዋቱ የተጀመረ ነው። ወሕይ ሳይወርድላቸው በፊት በየትኛውም የሽርክ ክብረ በዓል ላይ የማይገኙ፣ ራሳቸውን ወደ ጛሩ-ል-ሒራእ በማግለል አላህን በብቸኝነት የሚያመልኩ፣ ቀጥ ባለችው የነቢዩ-ል'ሏህ ኢብራሂም መንገድ ላይ የነበሩ አላህ በተፈጥሮ በሚያድለን ንጹሕ የአንድ አምላክ መኖር እሳቤ ላይ ያሉ ነበሩ። ወሕይ ሲወርድላቸው ደግሞ ያ አንድ አምላክ ላወረደው ዝርዝር ትእዛዝ የመጀመሪያው ተገዥ የሆኑ (እጁ የሰጡ፣ የሰለሙ) ነበሩ። ለዛም ነው አላህ ቁርኣን ላይ እንዲህ ይላል፦ (قُلْ إِنَّ صَلَاتِي وَنُسُكِي وَمَحْيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ لَا شَرِيكَ لَهُ ۖ وَبِذَٰلِكَ أُمِرْتُ وَأَنَا أَوَّلُ الْمُسْلِمِينَ) "«ስግደቴ፣ መገዛቴም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ነው» በል፡፡ «ለእርሱ ተጋሪ የለውም፡፡ በዚህም (በማጥራት) ታዘዝኩ፡፡ እኔም #የሙስሊሞች_መጀመሪያ_ነኝ» (በል)፡፡" [አል-አንዓም: 162–163] «የሙስሊሞች_መጀመሪያ_ነኝ!» ማለታቸው በርሳቸው ላይ በወረደው የአላህ ቃል የመጀመሪያው አማኝ መሆናቸውን ለመግለፅ እንጂ፤ አዲስ እየሰለሙ መሆናቸውን ወይም ከርሳቸው በፊት ሌላ ሙስሊም የሌለ መሆኑን አያመላክትም። ቀታዳም «ከዚህ ኡማ» ለማለት መሆኑን አስፍሯል። وقوله : ( وأنا أول المسلمين ) قال قتادة : أي من هذه الأمة . وهو كما قال ، فإن جميع الأنبياء قبله كلهم كانت دعوتهم إلى الإسلام ، وأصله عبادة الله وحده لا شريك له! √ በአጭሩ ከርሳቸው በፊት የነበረና ቁርኣን ሲወርድ በህይዎት ያልነበረ ሰው ሙስሊም አይደለም አይባልም። እርሱ በህይዎት በነበረበት ዘመን በተላከው ነቢይ ሸሪዓህ በትክክል ከተመራ ሙስሊም ነው። ነቢያቶች ዲናቸው አንድ ነው። የሚለያየው ሸሪዓቸው ነው። ለዛም ነው ራሳቸው ዉዱ ነቢይ ﷺ  " نحن معاشر الأنبياء أولاد علات ديننا واحد "  «እኛ የነቢያት ስብስብ የጣውንት ልጆች ነን፤ ዲናችን አንድ ነው።» ማለታቸው። ሸሪዓቸው ግን ይለያያል። አንዱ ሌላውን የሚሽርባቸው ህግጋት አሉ። ከርሳቸው በኋላ ግን የርሳቸው ሸሪዓህ በማንም አይሻርም። لا تنسخ أبد الآبدين ، ولا تزال قائمة منصورة ، وأعلامها مشهورة إلى قيام الساعة! ነገሩን ከዚህ አንፃር ማየት እየተቻለ፤ ይህቺን አጋጣሚ አገኘን መስሏቸው ተሳሳተ ካሉት በላይ ሲያቀጣጥሉት ነበር። ከነርሱ አልፈው ለሙስሊም ጠል ዲያቆንም አሳልፈው ሰጡት። አሁን ይሄ ዲያቆን ይሄንን አጀንዳ የፖሰተው የእውነት ለነቢያችን ﷺ የሚቆረቆር መስሏችሁ ነው? ለጊዜው ባትረዱንም ይህ ሰውና መሰሎቹ እናንተንም አይወዷችሁ። ለማንኛውም አላህን መፍራት መልካም ነው። የእውነት ተሳስቶ ቢሆን እንኳ ሸሪዓውን ባማከለ መልኩ ከስህተቱ እርሱም ሆነ ንግግሩን የሰማ ሰው እንዲታረም ታስቦ እርማት ይሰጣል እንጂ በስድብና በእልህ ይባስ ሰውን ለሌላ ወንጀል መገፋፋት ሸሪዓችን አይፈቅድም። የቱንም ያክል ብንነታረክ በምንጠላውም ሰው ላይ ቢሆን ድንበር ማለፍ አያስፈልግም። ነገ አላህ ፊት መቆም አለ። ያንን ቀን እንፍራ! ሰዎች ሲሳሳቱ ለመተቸት ስንል ደስ ሊለን አይገባም። እስኪሳሳቱ በጉጉት የምንጠብቅ መሆንም የለብንም። አላህ ሁላችንንም ወደሚወደው ነገር ሁሉ ይምራን። አላህ አዕለም https://t.me/islamawihabeshawi
Show all...
ANEL MUSLIM

አሠላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ ውድ የቻናሌ ቤተሠቦች በዚህ ቻናል ላይ ➬እስላማዊ መረጃዎች ➬እስላማዊ ታሪኮችን ➬ሶሒህ የሆኑ ሀዲሶች ➬ፒክቸሮችን ያገኛሉ!!! ስለ ቻናሉ ሀሠሳብ ፣አስተያየት ካላቹ inbox፦ @ABD_Buna👈 መወያያ ግሩፕ ፦

https://t.me/ISLAMICgroup11

ላይ ያገኙናል፡፡ ANEL MUSLIM

"ሌባው" የመስጅድ ኢማም ================= ባልና ሚስት ከረመዷን ወራት ባንዱ በሰፈራቸው የሚገኝ መስጂድ ኢማም የሆኑትን ሸይኽ ለፊጥራ ጋበዟቸው። ኢማሙም ግብዣውን በክብር ተቀበሉ። የቤቱ እማወራ የምግብ ማዕዱን ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ እያለች ሳለ ገንዘቧን ጠረጴዛው ላይ ጥላ ወደ ኩሽና አመራች። ፊጥራው ተጠናቀቀ። ኢማሙም ሄዱ። ሚስት ገንዘቧ እንደጠፋ አስተዋለች። «ገንዘቡን የሰረቀው ማን ነው?» ተብሎ አይጠየቅ ነገር ባልና ሚስት ልጆች የሏቸውም። በወቅቱ ወደቤት የመጡት የመስጂዱ ኢማም ብቻ ናቸው። ውስጧ በጥርጣሬ ተናጠ። ታሪኩን ለባለቤቷ አጫወተችው። የመስጂዱን ኢማም እንዲያማክራቸውና ጉዳዩን እንዲያረጋግጥ ጠየቀችው። «ኧረ ነውር ነው ፤ ባይሆን ከኢማሙ ጋር የፈጠርነውን ግንኙነት አቋርጠን ፋይሉን እንዘጋለን እንጂ እንዲህ አይነት ጥያቄ ማንሳት የማይታሰብ ነው» በማለት መለሰላት። ያም ቢሆን ባለቤቷ ኢማሙን ተከትሎ ሶላት ላለመስገድ ወሰነ። ቀናት በንፋስ ፍጥነት ከነፉ። ቀጣዩ ረመዷን ገባ። ባል ከሚስቱ ጋር ተቀመጠ። «እንግዲህ የእዝነት እና የይቅርታ ወር ስለገባ ያለፈውን መርሳት አለብን። እንደምታውቂው ኢማሙም ቤተሰብ የላቸውም። ስለዚህ ዘንድሮም ቢሆን ፊጥራ ልንጋብዛቸው ይገባል» በማለት ሚስቱን ሹክ አላት። ሚስት ለአፍታ ዝም ካለች በኋላ «በሃሳብህ እስማማለሁ፤ ነገር ግን የማስቀምጠው ቅድመ ሁኔታ ይኖራል። እርሱም የባለፈው ዓመት ረመዷን ላይ ስለተሰረቀው ገንዘብ ጉዳይ በግልጽ እንድታወሩ እፈልጋለሁ» አለችው። እርሱም ባቀረበችው ሃሳብ ተስማማ። የመስጅዱ ኢማም ግብዣውን ተቀብለው ከቤት መጡ። ፊጥራውን ከጨረሱ በኋላ የቤቱ አባወራ ጉዳዩን በይፋ አነሳው። ስለ ገንዘቡ ሁኔታ በቀጥታ ጠየቃቸው። ከፍተኛ የሀፍረት ስሜት ተሰማቸው። እንባቸው በጉንጮቻቸው ላይ ተንኳለለ። ካቀረቀሩበት ቀና አሉ። አይኖቻቸው የእንባ ቋጠሯቸውን እንደፈቱ ነው። ሚስት ፈጠን ብላ « ኢማም ሆይ! ምን ሆነው ነው የሚያለቅሱት ?» በማለት ጠየቀቻቸው። «አዎ! ገንዘቡን ያነሳሁት እኔ ነኝ። ያስቀመጥኩትም የመጽሃፍት መደርደሪያው ላይ ከተቀመጠው ብቸኛ ቁርኣን ውስጥ ነው። እንባዬ የፈሰሰውም ረመዷንን ጨምሮ ለ 365 ቀናት ያህል የአላህን መጽሃፍ ገልጣችሁ አንድ ፊደል እንኳ አለመቅራታችሁ ገርሞኝ ነው» በማለት ምላሽ ሰጡ። በዚህ ጊዜ የቤቱ አባወራ በፍጥነት መደርደሪያው ላይ ወደተቀመጠው ቁርኣን አመራ። ገንዘቡንም የቁርኣኑ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ምዕራፍ መሃል ላይ ተቀመጦ አገኘው። ሚስት እንባዋ ግድቡን ጥሶ ፈሰሰ። ኢማሙን በክፉ በመጠርጠሯም ይቅርታ ጠየቀቻቸው። «ልጄ ሆይ! እኔ ደካማ የአላህ ባሪያ ነኝ፤ ይልቅ አመቱን ሙሉ ቁርኣኑን ችላ በማለትሽ ይቅርታና ምህረት ከአላህ ጠይቂ» በማለት መከሯት። እኛስ መቼ ይሆን ለመጨረሻ ጊዜ የአላህን ቃል ከፍተን ያነበብነው? ነፍሳችንን ሳንዋሽ እውነቱን ለራሳችን እንገረው❗ ወገኖቼ የአላህ ቃል እየጠራን ቢሆንም ችላ ብለነዋል። #ውዶቼ ካነበብኩት ላካፍላቹ ብዬ ነው! እንደምትማሩበት ተስፋ አረጋለው! https://t.me/islamawihabeshawi
Show all...
ANEL MUSLIM

አሠላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ ውድ የቻናሌ ቤተሠቦች በዚህ ቻናል ላይ ➬እስላማዊ መረጃዎች ➬እስላማዊ ታሪኮችን ➬ሶሒህ የሆኑ ሀዲሶች ➬ፒክቸሮችን ያገኛሉ!!! ስለ ቻናሉ ሀሠሳብ ፣አስተያየት ካላቹ inbox፦ @ABD_Buna👈 መወያያ ግሩፕ ፦

https://t.me/ISLAMICgroup11

ላይ ያገኙናል፡፡ ANEL MUSLIM

Photo unavailableShow in Telegram
"ሐጂ" ዑመርንና ዶ/ር ጀይላንን በዚህ ፖለቲካው በተወሳሰበበት ዘመን የመጅሊስ መሪ ማድረግ እነርሱንም ኡማውንም ማስቸገር ነው። ይልቁንም ወደሚመጥናቸው የፈታዋ ኮሚቴ መግባታቸው ደረጃቸውን ከፍ ማድረግ ነው። ከጀርባቸው ያለ ሰው እንደፈለገ ሊሾፍራቸው ሲፈልግ ወደ ስልጣን ካልተመለሳችሁ ብሎ ካስገደዳቸው ልንቃወምላቸውና ከጎናቸው በመቆም አጋርነታችንን ልናሳይ ይገባል። https://t.me/islamawihabeshawi
Show all...

Repost from N/a
ሙፍቲ ሀጅ ኡመር እድሪስ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ''እርምጃ እንወስዳለን ሴቱም ወንዱም ተነስ '' ብለዋል። ለማንኛውም እኛም እስከ ዛሬ ዳርዳር ስንለው የነበረውን ጉዳይ ይፋ እናደርጋለን። በሙስሊሙ መካከል ማንኛውም ችግር ቢፈጠር የመጀመሪያው ተጠያቂ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና መንግስታቸው ነው ። ምክኒያቱም ሙፍቲ ሀጅ ኡመር እድሪስ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ከኢድ በኋላ በነበረ ስብሰባ ላይ በይፋ ገልጸዋል። ''መጅሊሱ ለሁለት መከፈል አለበት። አለበለዚያ በሙስሊሙ መካከል ደ'''ም ይ*ፋሰሳል ብለው በይፋ ፊት ለፊት ተናግረዋል። ኡስታዝ ሙሀመድ ሙስጠፋም ይሄን ጉዳይ በተመለከተ ከቀናት በፊት በይፋ ገልጿል። በዚህ ፕሮግራም ላይ ኡለማዎች፣ኡስታዞች ጭምር ተሳታፊ ነበሩ። ኋላ ችግር ከተፈጠረ በኋላ ትርጉም የለውም። በዚህ ዝግጅት ላይ ተሳታፊ የነበራችሁ ኡለማዎች እና ኡስታዞች ሁሉ ያያችሁትን አይታችኋል። ህዝበ ሙስሊሙን ለስልጣን ሲባል ማንም ይሁን ማን እርስ በርስ እንዲያጫርስ አንፈቅድለትም። ልክ እንደ 1987 ኢህአዴግ እንዳደረገው ብልጽግናም እደግመዋለሁ ብሎ አስቦ ከሆነ የማይሆን ቅዠት ነው ።
Show all...
ሙፍቲ ሀጅ ኡመር እድሪስ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ''እርምጃ እንወስዳለን ሴቱም ወንዱም ተነስ '' ብለዋል። ለማንኛውም እኛም እስከ ዛሬ ዳርዳር ስንለው የነበረውን ጉዳይ ይፋ እናደርጋለን። በሙስሊሙ መካከል ማንኛውም ችግር ቢፈጠር የመጀመሪያው ተጠያቂ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና መንግስታቸው ነው ። ምክኒያቱም ሙፍቲ ሀጅ ኡመር እድሪስ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ከኢድ በኋላ በነበረ ስብሰባ ላይ በይፋ ገልጸዋል። ''መጅሊሱ ለሁለት መከፈል አለበት። አለበለዚያ በሙስሊሙ መካከል ደ'''ም ይ*ፋሰሳል ብለው በይፋ ፊት ለፊት ተናግረዋል። ኡስታዝ ሙሀመድ ሙስጠፋም ይሄን ጉዳይ በተመለከተ ከቀናት በፊት በይፋ ገልጿል። በዚህ ፕሮግራም ላይ ኡለማዎች፣ኡስታዞች ጭምር ተሳታፊ ነበሩ። ኋላ ችግር ከተፈጠረ በኋላ ትርጉም የለውም። በዚህ ዝግጅት ላይ ተሳታፊ የነበራችሁ ኡለማዎች እና ኡስታዞች ሁሉ ያያችሁትን አይታችኋል። ህዝበ ሙስሊሙን ለስልጣን ሲባል ማንም ይሁን ማን እርስ በርስ እንዲያጫርስ አንፈቅድለትም። ልክ እንደ 1987 ኢህአዴግ እንዳደረገው ብልጽግናም እደግመዋለሁ ብሎ አስቦ ከሆነ የማይሆን ቅዠት ነው ። @islamawihabeshawi @islamawihabeshawi
Show all...
አስቀድሜ የነገርኳችሁ የባንግላዲሹ ሸኽ ከተቀበሩ ከ 32 አመት በኋላ ነው ቀብራቸው በጎርፍ ተደርሞሶ እንደገና ሊቀበሩ ሲሉ የተነሳውን ፎቶ ተመልከቱ😱 ኢናሊላ ወኢና ኢላሂ ራጂኡን አላህ ሆይ ምን ይሳንሀል❤️ https://t.me/islamawihabeshawi https://t.me/islamawihabeshawi
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
........ የአይን ማረፍያ ቀልብ ሚሰርቅ ውበት ሰላም ተድላ እርጋታ የህሊና እረፍት ሙሉ ደስታ .... ሁሉም እዚህ ናቸው/ብቻ 🥰 فلسطيني💜 @palestine_history
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
#ፊዳከ_ሙፍቲ ይህው እዛ መንደር ሀገር ሙሉ ጀማ ወንበር በመራቡ በነጋ በጠባ ቢደገስ በአርሂቡ ሁሉም ካድሙኝ አለ ወጣ ከመደቡ ማን እንደ ደረጃው ይጎንበስ ከቀልቡ ቁጢጥ ብለዋል ሊቅና ጃሂሉ ያለ ወንበራቸው እየተካለቡ። *ማን በመሰረተው መጅሊስ ማን ሊመራ ወላሂ በአሸባሪዎችማ አንመራም ያረብ በዛሬው የተከበረ ምሽት ይሁንብህ ጠራርገህ አንሳልን! *መሀይሙን ጀይላን በኢብራሂም ቱፋ ማለት ጉልቻ ቢቀያየር እንደ ማለት ነው አለ ደሞ ምክትል ተብዬው ወላሂ ያሳዝናል ልጅ በአባቱ ካልወጣ ግመል ነው። #መጅሊሱን_አሸባሪ_እንዲመራው_አንፈቅድም! @islamawihabeshawi @islamawihabeshawi
Show all...
#ፊዳከ_ሙፍቲ ይህው እዛ መንደር ሀገር ሙሉ ጀማ ወንበር በመራቡ በነጋ በጠባ ቢደገስ በአርሂቡ ሁሉም ካድሙኝ አለ ወጣ ከመደቡ ማን እንደ ደረጃው ይጎንበስ ከቀልቡ ቁጢጥ ብለዋል ሊቅና ጃሂሉ ያለ ወንበራቸው እየተካለቡ። *ማን በመሰረተው መጅሊስ ማን ሊመራ ወላሂ በአሸባሪዎችማ አንመራም ያረብ በዛሬው የተከበረ ምሽት ይሁንብህ ጠራርገህ አንሳልን! *መሀይሙን ጀይላን በኢብራሂም ቱፋ ማለት ጉልቻ ቢቀያየር እንደ ማለት ነው አለ ደሞ ምክትል ተብዬው ወላሂ ያሳዝናል ልጅ በአባቱ ካልወጣ ግመል ነው። #መጅሊሱን_አሸባሪ_እንዲመራው_አንፈቅድም! @islamawihabeshawi @islamawihabeshawi
Show all...