cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

💚💛❤️ ትዝብት😳 ኢትዮጵያ💚💛❤️

💚💛❤️ኢትዮጵያን እንታዘባለን ያየነውን የሰማነውን እንመሠክራለን እንታዘባለን💚💛❤️ #Join now # share 💚💛❤️ ትዝብት😳 ኢትዮጵያ💚💛❤️ @Ethiotzibt @Ethiotzibt @Ethiotzibt

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
3 304Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

❗️ሰበር ደብረብርሃን‼ ከሻሸመኔ የተነሱ 4 ግለሰቦች በቤት መኪና ደብረብርሀን ከደረሱ በኋላ አለም ገነት ሆቴል እንዳረፉ እንቅስቃሲያቸው ጥሩ አልነበረም እና ክትትል ሲደረግባቸው ቆይቶ በቁጥጥር ስር ውለዋል። በተያዙበት ወቅትም ለሽብር ተግባር የሚያገለግላቸውን፦ 1) ብዛት ያላቸው በተለያየ ስም የተመዘጉ የመታወቂያ ካርዶች 2) ሁለት ከፍተኛ መጠን ያላቸው ተቀጣጣይ ፈንጅ 3) የ925 ሺህ ብር የቡና ባንክ ቼክ 4) 925 ሺህ ብር ንግድ ባንክ በዛሬው እለት ትራንስፈር የተደረገ ሲሆን ጉዳዩ በፀጥታ ኃይሎች ተይዞ እየተመረመረ ነው። #Join now # share 💚💛❤️ ትዝብት😳 ኢትዮጵያ💚💛❤️ @Ethiotzibt @Ethiotzibt
Show all...
‼️ከስንት ማዋከብ በኋላ ተመልሰናል‼️ 💚💛❤️ ትዝብት😳 ኢትዮጵያ💚💛❤️ @Ethiotzibt @Ethiotzibt @Ethiotzibt
Show all...
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአብን አባላት የተሰጠ መግለጫ! * ይሄ የማን መግለጫ ነው ፋኖ ብሎ ለመጥራት የከበደው 🤫? በሕግ ማስከበር ስም የሚነሱ የሕዝብ ጥያቄዎችንና ጠያቂዎችን የማጥፋትና ሕዝባችንን አንገት የማስደፋት እንቅስቃሴ አጥብቀን እንቃወማለን! (በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) የሕዝብ ተወካይ አባላት የተሰጠ መግለጫ፤) * ባለፉት አራት ዓመታት በሕዝባችን ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚደርስበት ሁሉንአቀፍ ማንነትን መሰረት ያደረገ ጅምላ ጭፍጨፋ፣ መፈናቀል ቅርጹንና አድማሱን እያሰፋ ተባብሶ ቀጥሏል። ይባስ ብሎም ትሕነግ፣ የቤንሻንጉል ነጻ አውጭና ኦነግ ሸኔ የአማራን ሕዝብ ለማጥፋት ይፋዊ ጦርነት ከፍተው ሕዝባችን ኅልውናው አደጋ ላይ ወድቆ በጠላቶቹ ከበባ ሥር ይገኛል። እኛ የአብን የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላትም መንግስት ትንሹን መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣና የሕዝባችንን ደኅንነት እንዲያረጋግጥ ስንወተውት ቆይተናል። ሆኖም መንግስት ለማሳሰቢያችን ጀሮ ባለመስጠቱና ስጋታችንን ባለመጋራቱ ሕዝባችን ማንነትን መሰረት ላደረገ ጅምላ ጭፍጨፋ፣ መፈናቀልና ስደት ከመዳረጉም በላይ ከተሞቹና በዘመናት ሂደት ያፈራው ንብረት ወድሞ ለአካላዊና ሥነልቦናዊ ችግር ተጋልጦ ይገኛል። በዚህም ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ በአገር ውስጥ መፈናቀል ከዓለም ቀዳሚ እስከመሆን ደርሳለች፡፡ ይባስ ብሎም የዜጎችን ኹለንተናዊ ደኅንነት ማስጠበቅ፣ ሕግና ሥርዓትን ማንበርና የተሳለጠ አመራር መስጠት ያልቻለው መንግሥት ሕዝባችን በትሕነግና ምስለኔዎቹ ኅልውናው አደጋ ላይ በወደቀበት በአሁኑ ጊዜ በነቁ አማሮች ማለትም በአብን አባላትና አመራሮች፣ በፋኖ አባላትና አገራቸውንና ሕዝባቸውን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ባገለገሉ የጦር መኮነኖች ላይ ማንነትን መሰረት ባደረገ መልኩ የአፈና፣ የሕገ-ወጥ እስር እና የመንግስታዊ እገታ ሥራዎች ላይ መጠመዱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአብን የሕዝብ ተወካይ አባላትን አሳዝኖናል፡፡ መንግስት የሕዝባችንን ደኅንነት ለማረጋገጥና አገራዊ አንድነትን ለማንበር ከፖለቲካዊ ሴራ በጸዳ አኳኋን ሕግ ቢያስከብር እኛም ከመረጠን ሕዝብ ጋር ሆነን የምንደግፈው ቢሆንም አሁን እየተደረገ ያለው ግን ሕግ ማስከበር ሳይሆን በአማራ ሕዝብ የሚነሱ የሕዝብ ጥያቄዎችንና ጠያቂዎችን የማጥፋትና ሕዝባችንን አንገት የማስደፋት እንቅስቃሴ ነው። ይኼን ጉዳይ ለሕዝባችን ክብር ካለን ጽኑ ፍቅርና ታማኝነት የተነሳ በቸልታ የማንመለከተውና ከሕዝባችን ጋር ሆነን የምንታገለው ያደረ አማራ ጠል እሳቤ ነው። በመሆኑም እኛ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአብን የሕዝብ ተወካይ አባላት መንግስት በሕግ ማስከበር ስም እያደረገ ባለው መንግስታዊ እገታና አፈና አሳሳቢነት ላይ ከተወያዬን በኋላ፦ ፩. በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን አባላትና አመራሮች፣ በፋኖ አባላት፣ በሕጋዊ ታጣቂዎችና ወጣቶች እንዲሁም አገራቸውንና ሕዝባቸውን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ያገለገሉ የጦር መኮነኖችንና የጸጥታ አመራሮች ላይ የሚፈጸመው መንግስታዊ እገታና ስወራ በአስቸኳይ እንዲቆምና በዚህ ሰበብ በማንነታቸው ብቻ የታገቱ አካላትም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ እንጠይቃለን፡፡ ፪. መንግስት በሕዝባችን ላይ እየፈፀመ ያለው ማዋከብ የታወቀ ጠላት የሚያደርገው ዓይነት ሲሆን ማዋከቡ በአስቸኳይ የማይቆም ከሆነ አገርና ሕዝብ በጉጉት የሚጠብቀው የአገራዊ ምክክር ከወዲሁ እንዲጨናገፍ የሚያደርግ ውጤት የሚያስከትል መሆኑን አጥብቀን ለማሳሰብ እንወዳለን። ፫. ሕግ ማስከበርን ሰበብ በማድረግ የፌደራል የፀጥታ መዋቅር በሕገ መንግሥቱ ለክልልና ለፌድራል ተለይቶ የተሰጠውን ኃላፊነት እና ሚና በደፈጠጠ መልኩ ክልሉን በሕገ-ወጥ መንገድ ለመቆጣጠር የሚያደርገውን ሙከራ እንዲያቆም እና የክልሉ መንግስት በፌደራል መንግስቱ ለሚፈጸመው መንግስታዊ እገታና ስወራ ተባባሪ ከመሆን ወጥቶ የሕዝባችንን ሰላምና ደኅንነት እንዲያስከብር እየጠየቅን ጉዳዮቹን በሰላማዊ መንገድ በውይይት እንዲፈታ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ፬. በሕግ ማስከበር ሰበብ ከተሞችን የጦር አውድማ የማድረግና ንጹሐንን መግደል መንግስታዊ ሽብር በመሆኑ መንግስት የሚያደርገውን ይሄን ሕገወጥ የሽብር ሥራ በአስቸኳይ አቁሞ ሕዝባችንን በማወያዬት የሕዝብ ፍላጎቶችና ድምጾች እንዲሰሙ እንጠይቃለን፡፡ ፭. መላው አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆችም መሰል መንግስት በአማራ ሕዝብ ላይ ያወጀውን መንግስታዊ ሽብርና ጦርነት እንዲያቆም መንግስት ላይ ጫና እንድታሳድሩ ለአማራ ሕዝብ ያላቸሁን አጋርነትም በተግባር እንዲያሳዩ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ፮. መላው የአማራ ሕዝብ በዚህ ፈታኝ ወቅት ውስጣዊ አንድነቱን እንዲያጠናክር እየጠየቅን በአማራ ስም የተደራጃችሁ ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች፣ ወጣቶች፣ ምሁራንና መላው ሕዝባችን የአማራ ሕዝብ ላይ የተጋረጠውን የኅልውና አደጋና ከበባ በመቀልበስ ልጆቹን እንዲጠብቅ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ፣ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ! ግንቦት 12 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ
Show all...
💚💛❤️መዳኛየ💚💛❤️
Show all...
❗️መንግስታዊ አፈናው ተጠናክሮ ቀጥሏል‼️ የአማራ ወጣቶች እና የመላው የአማራ ህዝብ ልሳን የሆኑት <<የአሻራ ሚዲያ እና የንስር ሚዲያ >>ጋዜጠኞች እና ሌሎች የሚዲያው አባላት በአፋኙ መንግስት በዛሬው ዕለት በስራ ላይ እያሉ ታፍነው ተወስደዋል ። ከእነዚህ መካከል አሻራ ሚዲያ የታሰሩት ጋዜጠኞችን ስም ዝርዝር ስንመለከት 1) ቀለሙ ገላጋይ አቅኔ የአሻራ ሚዲያ የካሜራ ባለሙያና ኤዲተር 2) ጋሻየ ንጉሴ ፈረደ ጋዜጠኛ 3) ጌትነት ያለው ጋዜጠኛ 4) ሀብታሙ መለሰ ጋዜጠኛ 5) ዳንኤል መስፍን የካሜራ ባለሙያና ኤዲተር ሲሆኑ የንስር ብሮድካስት የጋዜጠኞች ስም ዝርዝር እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል። # share 💚💛❤️ ትዝብት😳 ኢትዮጵያ💚💛❤️ @Ethiotzibt @Ethiotzibt @Ethiotzibt
Show all...
ፈንጂ 5 ሰዎችን ገደለ! በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ባቲ ከተማ ፈንጂ 5 ሰዎች መሞታቸውን የባቲ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ።የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ሰኢድ ለዶይቼ ቬሌ ዛሬ እንደነገሩት በቅርቡ ከህወሓት ጋር በነበረ ጦርነት ቡድኑ ጥሎት የሄደን ፈንጂ ትናንት አግኝተው ሲነካኩ በመፈንዳቱ በአካባቢው የነበሩ ሠዎችን ጨምሮ 5 ሠዎች ህይወታቸው አልፏል።እንደ አቶ መሐመድ ሌሎች 5 ሠዎች ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ ቆስለው በህክምና ላይ ናቸው።ጉዳቱ የደረሰባቸው ሠዎች ከህፃናት እስከ አዋቂ ያሉ እንደሆኑም ጨምረው ተናግረዋል።ሕብረተሰቡ ማነኛውንም ብረት ነገር ሲያገኝ ለፀጥታ አካላት ማሳየት እንጂ በራስ መነካካት ጉዳት ያመጣልም ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን ዶይቸ ቬሌ ዘግቧል።
Show all...
ከሳምንታት በፊት ነበር ኦነግ ሸኔ እንደለመደው ከተማ ለማቃጠልና ለመዝረፍ እንዲሁም ሴቶችና ህፃናትን ለመድፈር የአባይ ወንዝ ተሻግሮ በየጁቤ አድርጎ ምስራቅ ጎጃምን የጦር ቀጠና ለማድረግ ዕቅድ ይዞ ትንኮሳውን ጀመረ። ነገር ግን አካባቢው ላይ ባሉ ፋኖወች ቂጡን ተብሎ ፈርጥጦ ተመለሰ። በዚህም የተከፍትና የተናደዱት እነ አሮጊቶቹ ኦፌኮ፣ ኦነግና የኦሆዴድ ባለስልጣናት ፍኖ አሸባሪ ነው እያሉ መግለጫ በመግለጫ ቀወጡት። የአራት ኪሎ መንገዴ በፋኖ እንዳይደናቀፍብኝ ብላ የምትሰጋው ወያኔና በኦነግሸኔ ሽንፈትና የእቅዳቸው መክሸፍ የተናደዱት ኦፌኮና ኦነግ እንዱሁም የኦህዴድ ባለስልጣናት በአንድነት ተባብረው ፍኖ ሌባ ነው አሸባሪ ነው በማለት ፌደራሉ መንግስት ትጥቅ እንዲፈታ አራት ኪሎ ላይ ሲማፀኑ ቆይተዋል። ለዚህም ነው አብይ ከነግብረ አበሮቹ እነ ወያኔ ፣ኦነግ ሽኔ፣ ኦፌኮና የኦሆዴድ ባለስልጣናት እንዳየኮርፍት ትናንት ህዝብን ከሌባ ከዘራፊ ከተማ ከሚያወድም ሴትና ህፃናትን ከሚደፍር ክፍ አረመኔ አሸባሪ የታደገውን ፍኖን ሊያፍንና ትጥቅ ሊያስፈታ አፍኙን ቡድን የላከ። እውነታው ይሄ ነው። አለኝታህን መከታህን መዳኛህን ፍኖን የመጠበቅ ያንተ ግዴታ ምክንያቱ ደግሞ መጪው ጊዜ በጣም ከባድ ነውና።
Show all...
"…የዐቢይ አሕመድ አሊ መንግሥት ከክረምቱ የወያኔ ወረራ በፊት ከዐማራ ህዝብ ጋር ጦርነት መግጠም ፈልጓል። የሚገርመውና የሚደንቀው ነገር ግን በየትኛውም የዓለም ታሪክ ህዝብን ገጥሞ ያሸነፈ መንግሥት ታይቶም፣ ተሰምቶም፣ ኖሮም ያለማወቁ ነው። "…ከፊቱ ከፍተኛ የጦርነት ስጋት ያለበትን ህዝብ ከወዲሁ መሳሪያውን መግፈፍ፣ መሪዎቹን፣ አንቂዎቹን መሰወር፣ ማገት፣ መግደል ማለት ምን ማለት ይሆን? "…ህዝብ አይሸነፍም። ተሸንፎም አያውቅም‼️ 💚💛❤️ ትዝብት😳 ኢትዮጵያ💚💛❤️ @Ethiotzibt @Ethiotzibt @Ethiotzibt
Show all...
🩸ሰበር ዜና‼️ በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ ግድም ወረዳ ጀብውሃ አካባቢ አሸባሪው ኦነግ ሸኔ ወደ ሸዋሮቢት በፓትሮል ሲጓዙ በነበሩ የልዩ ኃይል አባላት ላይ ጥቃት ፈጸመ። በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ ግድም ወረዳ ጀብውሃ በሚገኙ የአማራ ልዩ ኃይል አባላት ላይ ከበባ በማድረግ አሸባሪው ኦነግ ሸኔ ጥቃት ፈጽሟል። ግንቦት 10/2014 በተፈጸመው ጥቃት አንድ የልዩ ኃይል አባል በመቁሰሉ ቁስለኛውን ይዘው በፓትሮ ወደ ሸዋሮቢት ሲጓዙ ተጨማሪ የደፈጣ ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል። በጥቃቱም የሶስት የልዩ ኃይል አባላት ህይወት አልፏል፤ መኪናውም በመገልበጡ የቆሰሉ ስለመኖራቸው ለአማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ) ከስፍራው የደረሰው መረጃ አመልክቷል። ስርዓተ ቀብራቸውም ግንቦት 11/2014 በሸዋሮቢት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን መፈጸሙ ተገልጧል። (አሚማ) 💚💛❤️ ትዝብት😳 ኢትዮጵያ💚💛❤️ @Ethiotzibt @Ethiotzibt @Ethiotzibt
Show all...
መንግስት አደብ መግዛትና የሰራውን ትልቅ ስተት በቶሎ ማረም ካልቻለ በኋላ የማይወጣው መቀመቅ ውስጥ ይቸነከራታል። ህዝብን እንደ አሸባሪ መፈረጅ ያከስራል እንጂ አያዋጣም። ጥላትን ለማስደሰት ሲባል ህዝብን መካድ ከነውርም በላይ ነውር ነው። እናተ እንደምትሉት ፍኖ ዘራፊ አሸባሪ ቢሆን ኖሮ ህዝቡ እንደዚህ ግልብጥ ብሎ ፍኖን አትንኩብኝ ባላለ ነበር። ፍኖ የሰራውን ገድል እንኳን ፌደራል መንግስቱ ወያኔም እንዴት እንደሚያንቀጠቅጣት ታውቀዋለች ነገር ግን መንግስት ላኮረፋት ቡድን መሸንገያ ይሆነኛል በማለት ባለውለታውን ክዶ ማሳደድ ተያይዞታል። ህዝብ ደግሞ ጋሻ መከታየን መዳኛየን ፋኖን አሳልፌ አልሰጥም በማለት የአደባባይ ትግል ጀምሯል። መካነ ሰላም፣ ሞጣ፣ አሁን ደግሞ ከላይ እንደሚታየው ግንደወይን ህዝባዊ እምቢተኘነቱ ቀጥሏል። 🩸ማፈንና ደብዛን ማጥፋት ለደርግም ሆነ ለወያኔ አልበጀም ከህዝብ ጋር ጦርነት የትም አያደርስም‼️
Show all...