en
Feedback
SILTI SECONDARY SCHOOL. Offical page (Kibet)

SILTI SECONDARY SCHOOL. Offical page (Kibet)

Open in Telegram

"Eduction is the most powerful weapon to change the world " "Madiba"

Show more
378
Subscribers
+124 hours
+47 days
+2830 days
Posts Archive
አፍሪካ የ15 ሚሊየን መምህራን እጥረት አጋጥሟታል - ኅብረቱ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአኅጉሪቱ የ15 ሚሊየን መምህራን እጥረት ማጋጠሙን የአፍሪካ ኅብረት አስታውቋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የትምህርት፣ የሣይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር መሐመድ ባልሆሲን በሰጡት መግለጫ፥ የመምህራን እጥረቱ በአኅጉሪቱ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የተቀመጠውን በትምህርት የ2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት አኅጉሪቱ የተፈጠረውን ክፍተት ለማስተካከል ርምጃ እንድትወስድ ጠይቀዋል። የመምህራን እጥረቱን ለመሙላትና በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ኢንቨስት የሚደረገውን በአግባቡ ለመጠቀምም ጠንካራ ጥረቶች እንደሚያስፈልጉ አስረድተዋል፡፡ በአፍሪካ የመምህራን እጥረትን ለመፍታት፣ የትምህርት መሠረተ ልማቶችን ለማሻሻል፣ የዘላቂ ልማት ግቦችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ 90 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡ በአፍሪካ ያለው የትምህርት ሥርዓት የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግብ ዓለም አቀፍ ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

"ባካሄድነው ጥናት 90 በመቶ ተማሪ ኮራጅ መሆኑን ደርሰንበታል" #Ethiopia | በኢትዮጵያ የኩረጃ ደረጃ ምን ያህል ነው? ሀገርንስ ምን ያህል ይጎዳል? በሚል በ2004 በተደረገ ጥናት 90 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ኮራጅ መሆናቸው ተረጋግጧል ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአካቶ ትምህርት ክፍል ተመራማሪ የሆኑት አለማየሁ ተ/ማሪያም (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ተመራማሪው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዳጉ ፕሮግራም በነበራቸው ቆይታ፤ በቀደመው የትምህርት ሥርዓት የመመዘኛ ፈተናዎች የሚሰጡበት ሂደት ለኩረጃ ምቹ እንደነበሩ ተናገረዋል፡፡ ተማሪዎች በፈተና ወቅት የማያውቁትን ጥያቄ መልስ ከሌሎች ለመቅዳት ድሮም ይሞክሩ እንደነበር ገልጸው፤ አሁን ላይ ሥር ሰዶ በዘመቻ መል የሚካሄድ ሆኗል ሲሉ ነው የተናገሩት፡፡ ተማሪዎች ከትምህርቱ በበለጠ የኩረጃ መንገዶችን ያጠናሉ የሚሉት ተመራማሪው፤ በጥናቱ 27 የሚሆኑ የኩረጃ ዘዴዎች እንዳሉ ደርሰንበታል ብለዋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ወላጆች ልጆቻቸው እንዲያልፉ ከመፈለግ አንፃር እንዲሁም መምህራን፣ ርዕሰ መምህራን፣ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጭምር ለኩረጃው እገዛ እንደሚያደርጉ ይናገራሉ፡፡ ይህም ፈተናውን አልፈው ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች የሥብዕና ጉድለት እንደሚታይባቸው እዲሁም መሰረታዊ የሆነው መፃፍ እና ማንበብ ሲቸግራቸው እንመለከታለን ይላሉ፡፡ ተመራማሪው፤ ከፈተና አሰጣጥ በተጨማሪ ለግምት አጋላጭ የሆኑ የፈተና ዓይነቶችን ለማስተካከል መስራት እንደሚገባ አዲሱ የፈተና ሥርዓት ያመላከተ መሆኑንም ይናገራሉ፡፡ በተለይም የተጀመረው የበይነ በረብ (ኦን ላይን) ፈተና አሰጣጥ ሲጠናከር የተንሰራፋውን የኩረጃ መጠን በመቀነስ እና ተማሪዎችን በማብቃት ረገድ ላቅ ያለ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት፡፡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ከ700 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች ከሐምሌ 3 ጀምሮ እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ Via EBC

የ12ኛ_ክፍል_ናቹራል_ተማሪዎች_የዶርም_ድልደላ.xlsx0.78 KB

ቅዳሜ የተባለው ጉዞ ለእሁድ 2:00 ተቀይሯል መልክቱን ቴሌግራም ለማይከታተሉ መልክቱን በስልክ አድርሷቸው!!! የዶርም ምደባው እስካሁን አልደረሰንም እንደደረሰን እናሳውቃለን

የ12ተኛ_ናቹራል_ተማሪዎች_የመኪና_ምደባ.xlsx1.17 KB

ቅዳሜ የተባለው ጉዞ ለእሁድ 2:00 ተቀይሯል መልክቱን ቴሌግራም ለማይከታተሉ መልክቱን በስልክ አድርሷቸው!!! የዶርም ምደባው እስካሁን አልደረሰንም እንደደረሰን እናሳውቃለን

naturals naturals naturals ለ12ኛ ክፍል ናቹራል ተማሪዎች ሀሙስ ቀን 4/11/2016 ከጠዋቱ 4:00 ላይ በድጋሚ  ኦረንቴሽን ስለሚሰጥ በሰአቱ እንድትገኙ እያሳሰብን በዚህ ኦረንቴሽን ላይ ያልተገኘ ተማሪ ት/ቤቱ ከፈተናው የሚያግድ መሆኑን እናሳውቃለን!!!

for social 12th

2016 grade 12 Entrance Exam s Orientation Program for social students...

ለ12ኛ ክፍል ሶሻል ተማሪዎች ቅዳሜ ቀን 29/10/2016 ከጠዋቱ 4:00 ላይ በድጋሚ ኦረንቴሽን ስለሚሰጥ በሰአቱ እንድትገኙ እያሳሰብን በዚህ ኦረንቴሽን ላይ ያልተገኘ ተማሪ ት/ቤቱ ከፈተናው የሚያግድ መሆኑን እናሳውቃለን!!!

ተፈታኞች_በዩኒቨርሲቲ_የሚፈቀዱላቸው_እና_የተከለከሉ_ነገሮች_እንዲሁም_መብትና_ግዴታ.docx0.12 KB

+9
GEOGRAPHY ANSWER KEY.docx0.16 KB

+7
CHEMISTRY Model exam pdff.pdf2.27 KB

የ12ኛ ክፍል ኢንትራንስ ተፈታኞች ከታች የተያየዘውን ደክመንት በማየት ስትሪሙን ቼክ እንድታደርጉ እና አደሚሽን ነምበራችሁን በዛው እንድትይዙ ችግር ካለ መጥታቹህ ሪፖርት አድርጉ

kilil model.xlsx0.72 KB

የ12ተኛ ክልላዊ ሞዴል ፈተና የመፈተኛ ሩም ከታች በተያያዘው ዶክመንት ማየት ትችላላቹ