en
Feedback
SILTI SECONDARY SCHOOL. Offical page (Kibet)

SILTI SECONDARY SCHOOL. Offical page (Kibet)

Open in Telegram

"Eduction is the most powerful weapon to change the world " "Madiba"

Show more
378
Subscribers
+124 hours
+47 days
+2830 days
Posts Archive
ለስልጢ 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2016 ዓ.ም 12ተኛ ክፍል ላጠናቀቃችሁ ተማሪዎች በሙሉ ዶክመንት መውሰድ የምትችሉት ከቀን 13/12/2016 ዓ.ም ጀምሮ የመደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ እስከ ሚጀመርበት ሲሆን በምዝገባ ወቅት የማናስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን ። ት/ቤቱ

በክልሉ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከወሰዱ መደበኛ ተማሪዎች ውስጥ 44 ከመቶ የሚሆኑት የማለፊያ ነጥብ አስመዝግበዋል- 101 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ደግሞ ሙሉ ተማሪዎችን አሳልፈዋል- አቶ አንተነህ ፍቃዱ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን በ1509 ትምህርት ቤቶች ለፈተና ከተቀመጡ 110 ሺህ 772 መደበኛ ተማሪዎች ውስጥ 44 ከመቶ የሚሆኑት የማለፊያ ነጥብ በማስመዝገብ ማለፋቸውን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ ገለጹ። አቶ አንተነህ በጉዳዩ ዙሪያ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ከእነዚህ አጠቃላይ ተማሪዎች ውስጥ 110 ሺህ 772 በመደበኛ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 48ሺህ 728 የሚሆኑት 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል። 101 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ደግሞ ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል ሲሉ ገልጸዋል። በክልሉ በአጠቃላይ በሁሉም መርሃ ግብሮች 112 ሺህ 689 ተማሪዎች የክልል አቀፍ ፈተናውን ወስደው እንደነበርም አስታውቀዋል። በመደበኛ መርሃ ግብር ከተፈተኑ 58 ሺህ 978 ሴት ተማሪዎች ውስጥ 24 ሺህ 792 ወይም 42 ከመቶ እንዲሁም 51 ሺህ 794 ወንድ ተማሪዎች ውስጥ 23 ሺህ 931 ወይም 46 ነጥብ 2 ከመቶ የሚሆኑት ፈተናውን አልፈዋል ብለዋል። አምና በ2015 የትምህርት ዘመን ያለፉ ተማሪዎች መጠን 18 ነጥብ 5 ከመቶ ብቻ ነበር ያሉት አቶ አንተነህ ዘንድሮ ውጤትን ለማሻሻል የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ እንዳደረጉ ጠቁመዋል። በተለይም ደግሞ ኩረጃን በማስቀረት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የተደረጉ የቱቶሪያል፣ የትምህርት አመራሮች ስልጠናና የሞዴል ፈተናዎች ለዚህ ስኬት መገኘት አስተዋጽኦው ከፍተኛ ነበር ብለዋል። ውጤቱ የሚያበረታታ፣ የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሳ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አንተነህ ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት፣ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ለትምህርቱ ሴክተር በሰጡት ልዩ ድጋፍ፣ የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬና ሌሎችም አመራሮችና ህብረተሰቡ እንዲሁም የሆሳዕና ትምህርት ኮሌጅ መምህራንና አመራሮች ሊመሰገኑ እንደሚገባ ተናግረዋል ። አማካይ የማለፊያ ነጥቡ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ መሆኑን ያነሱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ለአካል ጉዳተኞች ደግሞ 45 ከመቶ እንደሆነ አብራርተዋል ። እንደ አጠቃላይ ሲታይ ደግሞ ከግል ተፈታኞች 40 ከመቶ፣ ከማታ 19 ከመቶ እና ከርቀት 28 ከመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል ። አጠቃላይ ለተመዘገበው አመርቂ ውጤት የትምህርት ፖሊሲ ማሻሻያውና የአዲሱ ስርኣተ ትምህርት በቁርጠኝነት መተግበር ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው አቶ አንተነህ አብራርተዋል። ተማሪዎች መለያ ቁጥራቸውን https://ce.ministry.et/ ሊንክ በማስገባት ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል ። ነሐሴ 3/2016 ዓ.ም

መልካም ዜና ! 43,500 የመንግስት የሥራ ቅጥር ለሥራ ፈላጊዎች የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ የገጠርና የከተማ ቀበሌዎች ውስጥ የግብርና ናሙና ቆጠራ ያከናውናል፡ ፡ስለሆነም በቀበሌው የሚሰማሩ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ የሚያሟሉ መረጃ ሰብሳቢዎችን አወዳድሮ በኮንትራት መቅጠር ይፈልጋል። በዚህም መሰረት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በኩል በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት(ሌበር ማርኬት ፖርታል- E-LMIS) በመጠቀም ከመላ የሀገሪቱ ክፍሎች 43,500 ሰራተኛ ይፈለጋል። ስለሆነም በዚህ የሥራ እድል ተጠቃሚ ለመሆን lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ አንድ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር ይዛችሁ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። የሥራ መደቡ መጠሪያ፡- የስታቲስቲክስ መረጃ ሰብሳቢ 1 ብዛት፡- 43,500 ፆታ ፡- ጾታ አይለይም የሥራ መደቡ ዓላማ ፡-ጥራቱን የጠበቀ የገጠር/ከተማ የቤተሰብ/ባለይዞታ የግብርና መረጃ መሰብሰብ እና ወደ ሰርቨር መላክ አሁኑኑ ሊንኩን ይጫኑና ይመዝገቡ: https://lmis.gov.et

#የደመወዝ_ጭማሪ " ታች ላለው የመንግስት ሠራተኛ 300 እጥፍ ደመወዙን ጨምረናል " - ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሾለ መንግሥት ሠራተኛ የደመወዝ ጭማሪ ምን ተባለ ? ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር። በዚህ ማብራሪያቸው በሪፎርሙ በዋጋ ንረት ምክንያት ሊጎዱ ይችላሉ / ሪፎርሙ በትሩን ሊያሳርፍባቸው ይችላል ተብሎ ከተለዩት የመንግሥት ሠራተኞች ዋነኞቹ ናቸው ብለዋል። በመሆኑም ዝቅተኛ  የሆነ ወርሃዊ ደመወዝ ለሚበሉት ሠራተኞች ከፍተኛ የደመወዝ ማሻሻያ ይደረጋል ሲሉ ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፦ " መንግሥት በወር 1,500 ብር የሚበላ ሠራተኛ አለው። የአሁኑ ደመወዝ ማሻሻያ ከ90 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ሃብት ጠይቆናል። ለዚህ ምን አይነት መንገድ ተከተልን ታች ያለው 1,500 ብር የሚበላው የመንግስት ሠራተኛ 300 እጥፍ ደመወዙን ጨምረናል። ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ አይታወቅም። ላይ ያለው ከ25 ሺህ በላይ ያለውን ለጊዜው ታገሰን አልነው። ደመወዝ የጨመርነው ታች ለሚጎዱት ይሄ ሪፎርም ለሚጎዳቸው ሰዎች በርከት ያለ ሃብት ጨምረን ትንሽ ሻል ሻል ያለና ለተወሰነ ጊዜ ጫናውን ለሚቋቋሙት አቆየን  ይበቃቸዋል ማለት አይደለም እነሱም ቢሆኑ ፤ በንጽጽር ግን በጣም እያለቀሰ የሚያድረውን ሠራተኛ ማገዝ አለብን ነው። ተሿሚዎች ብዙ ላያገኙ ይችላሉ። ታች ግን አድርገናል። " #TikvahEthiopia @tikvahethiopia

👉https://facebook.com/groups/192719114961039/ Join selti secondary official group in Facebook

#የግል_ዩኒቨርሲቲዎች_ዲግሪ_ማሳተም_ተከለከሉ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የግል ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ዲግሪ በማሳተም ለተማሪዎቻቸው መስጠት አይችሉም ተባለ፡፡ በግል ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የተማሩ ተማሪዎች ዲግሪ የሚታተምላቸው በትምህርት ሚኒስቴር በኩል እንደሆነም ተነግሯል፡፡ ይህንን ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ(ፕ/ር) ናቸው፡፡ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የግል_ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ለሚያስተምሯቸው ተማሪዎች ዲግሪ በራሳቸው ማተም እንዲያቆሙ የተናገሩት ሚኒስትሩ፤ ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎቹን ዲግሪ የማተም ስራ እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡ ፕ/ር ብርሀኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ‘’ሰኪውሪቲይ ፕሪንቲንግ’’ ብለው የጠሩት አዲስ የዲግሪ ህትመት አሰራር ይጀመራል ብለዋል፡፡ ይህም በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሩ ተማሪዎች ዲግሪን የማተም ስልጣን ለት/ት ሚኒስቴር ብቻ የሚሰጥ ነው ተብሏል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎቹን ዲግሪ የሚያትመው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ውጤት እና ተቋማቱ ለትምህርት ሚኒስቴር በላኩት የመረጃ ቋት(HEMIS) ተምርኩዞ እንደሆነም ሚኒስትሩ ሲናገሩ ሰምተናቸዋል፡፡ የትምህርት ተቋማቱ ላስተማሯቸው ተማሪዎች ለሚታተምላቸው ዲግሪ ህትመት ለትምህርት ሚኒስቴር ክፍያ ይፈፀማሉም ተብሏል፡፡ ይህ አሰራርም ተግባራዊ የሚደረገውም፤ በሀገሪቱ የሚታየው የሀሰት ዲግሪ(ፎርጅድ) ህትመት ለማስቆም ተብሎ እንደሆነ የትምህርት ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡(ሸገር ራዲዮ)

ዘንድሮ በተሰጠው የመውጫ ፈተና 22 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አንድም ተማሪ አላሳለፋም ተባለ የግል የከፍተኛ ተቋማት በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ካስፈተኗቸው ተማሪዎች መካከል ያሳለፋት 13 በመቶ እንደሆነ ተነግሯል። የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ አጠቃላይ ካስፈተኗቸው ተማሪዎች 58 በመቶ አሳልፈዋል ተብሏል። 202 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በዘንድሮ የመውጫ ፈተና ተማሪዎቻቸውን ቢያስፈትኑም 22ቶቹ አንድም ተማሪ ማሳለፍ እንዳልቻሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ(ኘ/ር) ተናግረዋል። ምንጭ -: EthioTube

የስልጢ ከፍተኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የWELLGO PROGRAM አካሄዱ..

ነፃ የOnline ስልጠና #ክፍያየለውም መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ 5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደርስ (5 million Ethiopian Coders) የተሰኘ ስልጠና አመቻችቷል። መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ “5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ” የተሰኘ አዲስ የስልጠና እድል አመቻችቷል። ይህ ኢኒሼቲቭ ከአይሲቲ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ኮርሶች ጥራቱና በጥልቅ ይዘቶች በሚታወቀው በኦዳሲቲ ፕላትፎርም (Udacity Platform) የፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስና ሌሎችም ከአይሲቲ ጋር የተገናኙ ኮርሶችን ከክፍያ ነፃ ማግኘት የሚያስችል ነው። ተማሪዎች እና መምህራን ያለምንም ወጪ በእነዚህ ኮርሶች በመመዝገብ ይህንን ልዩ የስልጠና እድል መጠቀም የሚችሉ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ውስጥ በመሳተፍና ችሎታቸውን በማጎልበት በአለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ ተወዳዳሪ መሆን ይችላሉ። በዚህ ስልጠና ተመዝግበውና የትምህርት ይዘቶቹን ተምረው ያጠናቀቁ ተሳታፊዎች በአለም አቀፍ ድርጅቶች እውቅና ያለው እና የስራ እድልን በእጅጉ ሊያሳድግ ከሚችለው Udacity የምስክር ወረቀት ያገኛሉ። ትምህርት ሚኒስቴር በስልጠናው እንዴት መመዝገብና መሳተፍ እንደሚቻል የሚያሳዩ መመሪያዎችን በጽሁፍና በቪዲዮ አዘጋጅቷል። ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎችና መምህራን ይሄንን በበዙ ክፍያ ይሰጥ የነበረን ስልጠና መመሪያውን ተከትሎ ብቻ በመመዝገብ በነጻ መሰልጠን ትችላላችሁ። የመመሪያውን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/-zSmhhD5qE4 ላይ በመግባት መመልከት የምትችሉ ሲሆን በምስል የተደገፈውን መመሪያም ከዚህ ፖስት ጋር አጋርተናል። ይሄንን ጠቃሚና ነጻ የስልጠና እድል ፍላጎቱ ላላቸውና የትምህርት ዝግጅታቸው ከዚህ ስልጠና ጋር ለሚገናኝ ጓደኞቻችሁ፣ ወዳጅ ፣ ቤተሰባችሁ እንዲሁም ተማሪዎችና መምህራን በማጋራት ተጨቃሚ እንዲሆኑ አድርጉ።

የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ከስራ ፈጠራ ባሻገር ለአገልግሎት ዘርፍ ኢንቨስትመንት መጎልበት ሚናው የጎላ ነው አዲስ አበባ፤ ሐምሌ16/2016(ኢዜአ)፦ የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ከስራ ፈጠራ ባሻገር ለአገልግሎት ዘርፍ ኢንቨስትመንት መጎልበት ሚናው የጎላ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ኢኒሼቲቭን በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል፡፡ ኢኒሼቲቩ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስና የኢትዮጵያ መንግስታት የሚተገበር ሲሆን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ 5 ሚሊዮን ወጣቶች በኦንላይን የኮዲንግ ስልጠና የሚወስዱበት ነው፡፡ ስልጠናውም በዋናነት በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስ እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ ከኢኒሼቲቩ ማስጀመሪያው በተጓዳኝ የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ላይ ትኩረት ያደረገ የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡ በውይይቱ ከተሳተፉት መካከል የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፤ ኢኒሼቲቩ የትምህርት ዘርፉ ብቁ ትውልድ ለመገንባት በሚያከናውነው ስራ ላይ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው አብራርተዋል፡፡ በተለይ ትውልዱ በንድፈ ሃሳብ የሚያገኛቸውን እውቀቶች በቀላሉ ወደ ተግባር እንዲለውጥ ምቹ እድል በመፍጠር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያስችላል ነው ያሉት፡፡ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል በበኩላቸው ቴክኖሎጂ ከስራ ፈጠራ ጋር የሚተሳሰር ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የወጣቶችን ዲጂታል አቅም ለመገንባት የተሰጠው ትኩረት ደግሞ ግብርናን ጨምሮ የተለያዩ መስኮችን ለማዘመን የተያዘውን ውጥን እውን ለማድረግ እንደሚያግዝ ነው የተናገሩት፡፡ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስትን ወክለው በፓናሉ የተሳተፉት አብዱልአዚዝ አልጃዝሪ በኢትዮጵያ የዲጂታል ቴክኖሎጂን እውን በማደረግ ረገድ ከፍተኛ የሆነ የአመራር ቁርጠኝነት መኖሩን አንደታዘቡ ተናግረዋል፡፡ ይህ ደግሞ በኢኒሼቲቩ የተያዙ ግቦች እንዲሳኩ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ ቴክኖሎጂ የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ በእጅጉ እየቀየረ ስለመሆኑ አንስተው፤ ከዚህ አኳያ ለዘርፉ ቅድሚያ መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡ የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ከ10 ዓመቱ መሪ የልማት አቅድ ጋር የሚጣጣም መሆኑን ያብራሩት ደግሞ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ በእቅዱ ላይ ዲጂታል ክህሎትን መሰረት ያደረገ የሰው ኃይል ልማት ትኩረት እንደተሰጠው ጠቅሰው፤ ኢኒሼቲቩም ይህን እውን በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢኒሼቲቩ በኢትዮጵያ ክህሎት ያለው የሰው ሃይልን በመገንባት ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በአገልግሎቱ ዘርፍ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡ የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ዘመናዊና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥን እውን ማድረግ መንግስት እያከናወነ ያለው የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ አካል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ የመንግስት ሰራተኞች ዲጂታል ክህሎት ማደግ እንዳለበት ጠቅሰው፤ ኢኒሼቲቩም የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያውን የሚያግዝ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡