en
Feedback
ቅን ልቦች

ቅን ልቦች

Open in Telegram

ደግነት ለራስ ነው !! ❣❣ በፍቅር ከሆነ እንስማማለን❣❣ ለ አስተያየት @Tesfish2 @EgerKwasMeme @YehabeshaTiktok @ye90slijochfans ▶ YouTube 🔥 https://youtu.be/619clN81mFs

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
4 854
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት Join our telegram 👇🏻 https://t.me/+GSYm_Bw39Vk3ZGNk
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት Join our telegram 👇🏻 https://t.me/+GSYm_Bw39Vk3ZGNk

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፳፩~ ( 221) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 ወይዘሮ አትጠገብ እንዲሁ እየተብሰለሰለች ቁጭ ብላ የባጡን የቆጡን ከእንደገና ብቻዋን ስታወርድ ስትሰቅል የቀኗ ፅሐይ ጥላዋን እያጠላች እግሮቿን ወደ ምስራቅ ዘርግታ አንገቷን ወደ ምዕራብ አቅጣች እያሰገገች ነው። የሰውን ክፋት ገመና በብርሀኗ ስታጋልጥ ውላ በመጨረሻ በጨለማ ተረትታ ጉሟ ውስጥ ተሸጎጠች። አንድ የከፋው እና የናፈቀ ህፃን ተንደርድሮ የእናቱን ጡት ይዞ ጉያዋ ውስጥ እንደሚደበቀው ነው የጀንበሯ ቀይ ጉሙ ላይ አሸጓጎጧ። ይህን የምሽት የተፈጥሮ መስተጋብር ቆሞ ላስተዋለ ሰው ብዙ ነገር ይማራል። አንዳንድ ጊዜ በየዋህነትም ሊሆን ይችላል ወይም በጊዜው በማይሆን ስሜት የፈጠርነው ችግር አድጎ እኛ የምንደበቅበት እስክናጣ ድረስ ያደርገናል። ሰው ልክ እንደ ፅሐይ ይወጣል። እድሜው የፅሕይን አስራ ሁለት ስዐት ሲያክል ደግሞ ይመሽበታል። ከመሸ በኋላ ጠዋቱን ማግኘት ቢፈልግ አያገኝም በፀፀት ቢናውዝም በጭራሽ። ስለዚህ ሕይወታችንን በጥንቃቄና በብስለት መኖር ካልቻልን የምንጥላቸው የነገር ቃሎች እሾህ ሆነው በቅለው ሲወጉንና እርምጃችንን በሰቀቀን እንድንሞላው ያደርጉናል። ሰው የዘራውን ነው የሚያጭደው ማለት ጤፍ ከዘራ ጤፍ እንጅ ማሽላ አያጭድም እንደማለት ብቻ ሳይሆን መጥፎ ነገር ካደረግን ምላሻችን ሊሆን የሚችለው መጥፎ ነገር ነው ለማለት ነው። መቼም ነገር በምሳሌ ጠጅ በብርሌ ነውና የሚባለው። በሀሳብ ሰጥማ ስትነሳ የተቀደደው የጎዳዋ ጫፍ የእግር ጣቷን ጠልፎ ከእንደገና ወደቀች የጎዳዋ ቀዳዳ ውስጥ የገባችው ጣቷ ትንሽ ወለም ብሏት አመማትና ይዛት ተቀመጠች። በጣም ስላመማት ሕመሟን እንደምንም እየዋጠች ቀስ አድርጋ በባዶው እየነካካች ታሻት ጀመር። ወይዘሮ የአትጠጠገብን አኳኋን የተመለከተ በጭራሽ መጥፎ ነገርን መስራት አይደለም ለማሰብ እርም ያስብላል። ከልቧ ነው ብሶቷና ኃጢያቷ ገንፍሎ አይኗን በእንባ ያጠበው። *** ሁሉም ነገር ዝግጁ ሆኗል። ሮሃ ባንድ የተዘጋጀለትን ቦታ ቀድሞ ይዞ ዝግጅቱን አጠናቆ የፕሮግራሙን ቅደም ተከተል ብቻ ይጠባበቃሉ። ካሜራ ማኖቹ በየቦታውና መውጫ መግቢያው ካሜራቸውን አስቀምጠው እያንዳንዷን ነገር ይለቅማሉ። የሙሽሮቹ ስቴጅ በደንብ ዲኮር ተደርጓል። እንግዶች እና ጥሪ የተደረገላቸው ሰዎች ቀድመው ቦታ ቦታቸውን ይዘዋል። ድንኳኑ በሰዎች ተጥለቅልቋል በየ ድንኳኑ ኮሪደር የቀዳማዊና የሐምራዊ ፎቶ ተሰቅሎ ዙሪያው በዲም ላይት ይበራል ከፏቷቸው ስርም " የአቶ ቀዳማዊ ታረቀኝና የወይዘሪት ሐምራዊ ሱራፌል የጋብቻ ስነስርዓት"የሚል ወርቃማ ፅሁፍ ሰፍሮበታል። የሰርግ ፎቷቸውን የተመለከተ እንግዳ ሁሉ "እትፍ እትፍ ከአይን ያውጣችሁ! ትዳራችሁ በፍቅርና በረድኤት የተሞላ ይሁን!"ብሎ የማይመርቅ የለም። ጠጁ፣ጠላው፣ቢራው ወይኑ፣ውስኪው ሁሉም በአይነት በየጠረንጴዛው ተደርድሯል። ምግቡም በአይነት ከአትክልት እስከ ዶሮ አሩስቶው በአልጫም በቀይ ተሰርቶ በጎዶጓዳ ሳህን ተቀምጧል አንግዶችም በሰልፍ የሚፈልጉትን ምግብና መጠጥ እያነሱ ይስተናገዱ ጀመር። የምሳ ስነስርአቱ እየተካሄደ እያለ ሙሽራውን ይዘው ሚዜየዎቹና አጃቢዎቹ ወደ ሙሽሪት ጉዞ ሄዱ።ሆታውና ጭፈራው እንደ ጉድ እየኖጋ ጉዞ ሙሽሪት ጋ። ሙሽሪት ጋር የነበረው ድግስ አጀብም ለጉድ ነው። የሁለት ኃብታሞች ሰርግ በመባል የተሰየመው የአቶ ሙሉሰውና የአቶ ሱራፌል ሰርግ በብዙ ክዋኔዎች የተሻለ ና የተመሰገነ አቅርቦትና ድግስ ነው። ከብዙ እልህ አስጨራሽ ጭፈራና ጥያቄ በኋላ ወደ ሙሽሪት ክፍል ሚዜዎቹና ሙሽራው ገቡ። የሙሽሪት ሚዜዎች በተራቸው ደግሞ ሙሽራተውን ሸፍነው በጭፈራ የወንዱን ሚዜዎችን አደከሟቸው። ትዕይንቱ ደስ የሚልና የባህልን ይዘት የተላበሰ በመሆኑ በሁለቱም ወገኖች ምንም አይነት ቅሬታ አይፈጥርም። የሴቷ ሚዜዎችም በባህል መሠረት ነው የሚያደርጉት ወንዶቹም የሚጋፉት በደስታ ነው። ባህልና ወግ ለአንዲት ሀገር ምሰሶዎችና መሠረቶች ናቸው። ባህል ሐይማኖት ወግ የሌላት ሀገር ሀገር አትመስልም። የራሷ መገለጫ ሊኖራት ይገባል።አሁን በርካታ የአለም ሀገራት የራሳቸው ወግና ባህል የላቸውም። ለረጅም አመታት በቅኝ ግዛት የተያዙ ሀገሮችም ቋንቋቸውም ባህላቸውም ወጋቸውም በቅኚ ገዥዎች ሀሳብና ተፅዕኖ ጠፍቶ የሌላ ሀገር ወግና ባህል ለምደው እናያቸዋለን።ይህ እንዳይሆን ትልቅ መስዋዕትነት ለከፈሉ ጀግኖች አያትቻችን ይግባና እንዲህ ውብ በሆነ የባህል ትውፊት ትዳር ሲመሰረት ደግሞ በጥሩ ሁኔታ ያማረና ለየት ያለ ይሆናል። በሽማግሌዎችና በቄሶቹ መሀል ቃለ መሀላ ፈፅመው ምሳ ከበሉ በኋላ ወደ ሙሽራው ቤት ተመለሱ። "በሀዘንም በደስታ ጊዜም አብረው ሊሆኑ ላይለያዩ ሚስቱን ሊያከብር ሊንከባከብ እርሷም ባሏን ልትንከባከብ ልታከብ እስከ እድሜ ማብቂያቸው ላይለያዩ በአጋቢ ቄሳቸው ፊት ተማምለው ባልና ሚስተነታቸውን አሳወጁ።ቤተዘመዱም ለሙሽሮቹ ደስታ ወገቡን ፈትሾ በውዝዋዜ አጅበው እንኳን ደስ ያላችሁ የሚል መልዕክት በጭብጫቦና በእልልታ አስተላልፈው ሙሽሮቹን ወደ ወንዱ ቤት ለመሸኘት አንድ ላይ ግልብጥ ብለው ከድንኳኑ ወጡ። ሙሽሮቹን እየዞሩ ሚዜዎቹ ከጨፈሩ በኋላ ለሙሽሮቹ ወደ ተዘጋጀችው ቅንጡ መኪና ሙሽሮቹን አስገብተው ከፊታቸው በፒካፕ ካሜራ ማኖቹ እየቀረፁ አጃቢዎቹ መኪኖችን በሰልፍ ይቀርፁ ጀመር።አጃቢዎቹ መኪናቸውን በንፋፊት ለጣጥፈው በጋራ እየጨፈሩ ጉዟቸውን ወደ ደጃች ውቤ ሰፈር አደረጉ። ከቦሌ የተነሳው ሰርገኝ በፍላሚንጎ መስቀል አደባባይ አድርጎ በጊዮን አልፎ አንባሳደርን በመተው የቸርቸልን መንገድ አቅንተው ወደ ውቤ በረሃ ገቡ። የወንዱ ሙሽራ ቤተሰቦችም ሙሽሮቹ እስኪመጡ አሰፍስፈው እየጠበቁ ነበርና የመምጣታቸውን የመኪና ጡርንባ ሲሰሙ ሁሉም ነገር ጀመረ። ደጂው የሰርግ ሙዚቃ ከፍቶ ይዘፍኑ ጀመር። ሰርግ ብዙ ሰዎች ባይወዱም ነገር ግን አንዳንድ ወላጆች የልጃቸውን ሰርግ ከማየት በላይ ለእነሱ ድል የለም። ተመርቀው ከሚያይዋቸውና በሌላ የስራ መስኮት ዝነኛ ሆነው ከሚረኩት በላይ በልጆቻቸው ሰርግ ይረካሉ ፍፁም ደስተኛ ይሆናሉ። ብዙ የተለፋበትን ድግስም ዘመድ አዝማድ የሩቅ እንግዳ ተጋብዞ ሲሄድ ወላጆች ደስ ይሰኛሉ።ቀዳማዊና ሐምራዊ በዚህ ውብ የአሰራረግ ስነስርዓት ተድረው ኤርስ በእርስ ተዛምደው ወላጆች ከወላጆች በልጆቻቸው ደስታ ተደስተው ሰርጉን ቋጩ። ልጆቻቸውንም እስከወዲያኛው በልጅ የታጀበ ደስታ እንዲሆንላቸው መርቀው ወደ ቤታቸው አስገብተዋቸው። በነ ቀዳማዊ ቤት የተዘጋጀላቸውን ግብዣ ተጋብዘው ተሳስቀው ተጨዋውተው ሙሽሮቹን ጥሩ ጫጉላ እንዲሆንላቸው በመመኘት ተሰናብተዋቸው ወጡ። ቀዳማዊና ሐምራዊ ቤተሰቦቻቸውን ሸኝተው ተቃቅፈው ሶፋው ላይ ተቀመጡ። "የኔ ፍቅር ይቺን ቀን በተስፋና በትዕግስት ለአመታት ስጠብቃት ነበር አሁን ይሄን ቀን በሕይወቴ መቼም አልረሳውም። ይሄው እድሜ ልኬን ደስተኛ ሆኜ እንድኖር ፈጣሪዬን አንተን የልቤን ንጉስ ሰጥቶ አንግሶኛልና ሁሌም የእሱ አመስጋኝ ሆኜ እኖራለሁ"አለችና አይኑን ሳም አደረገችው። እሱ ዝም ብሎ በፍቅር ይመለከታት ነበር ዝምታው በቃል የማይሰፈር አስተያየቱ በምን የማይገለፅ የፍቅር አተያይ ነበር። @amba88 @ken_leboch

የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት Join our telegram 👇🏻 https://t.me/+GSYm_Bw39Vk3ZGNk
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት Join our telegram 👇🏻 https://t.me/+GSYm_Bw39Vk3ZGNk

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፳~ ( 220) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 #ራስ አምባ "እሱ ቅቤ ነው አንድ ጊዜ ተገፍቶ የወጣ"አለች አትጠገብ። የግንባሯ ቆዳ ተሸብሽቦ የፊት ፀጉሯ ውስጥ ተደብቋል። በንግግሯ ውስጥ ቁጭት ፀፀት እንደ ስምንት ወር ፅንስ ይገላበጣል። የተቆጠበ የተመጠነች ንግግር ነበረች። ሌላ አንድም ቃል አልተነፈሰችም። ከወትሮው ወጣ ያለ አነጋገር ነበር። ማለፊያ የእናቷ ቃል አጥንቷን ሰርስሮ ዘልቆት የገባው ይመስላል። "ምን ሆነሽ ነው እታተዬ እንደዚህ የምትይው?"አለች ማለፊያ የአትጠገብን ጉንጭ በእጆቿ እየዳበሰች። "እንዳይረፍድባችሁ ልጄ! እንደኔ የማትመልሱት ነገር እንዳይገጥማችሁ ፍጠኑ። እኔ ልጅ ሆኜ በማይሆን እልህ እናንተን እዚህ ገደል አብሬ አስገብቻችኋለሁ። እንግዲህ ለዚህ በደሌ በምድርም በሰማይም እቀጣበታለሁ። እናንተ ግን ጊዜ አላችሁ ንስሃ የምትገቡበት ኃጢያታችሁን በንስሃ የምታጥቡበት ጊዜው አሁን ነው። አሁን ቀዳማዊን እርሱት። እሱ እረስቶናል። የራሱን ቤተሰብም መስርቷል። ሊያገባ ነው። ሕይወቱ ውስጥ የለንም። እሱም እስከ ወዲያኛው ከበደላችን ጋሬ አስፈንጥሮናል። እውነት ምን ጊዜም እንደ ጉልጭማ ፍም እሳት ነች። የፈለገ ብታዳፍኗት እሳትነቷ እንደማይጠፋ ሁሉ እውነትም የፈለግነውን ያህል ብናዳፍናት አንድ ቀን ትወጣለች ግብረ መልሷም የከፋ ይሆናል። ስለዚህ አሁን ኤንደ እናትም በእድሜ እንደገፋ ሰውም የምመክራችሁ እስከዚህ እድሜያችሁ ድረስ ያሻችሁን ስታደርጉ ነበር። ከዚህ በኋላ ግን በተቻላችሁ መጠን ክፉ ላለመሆን ሞክሩ። ካልሆነ እንደ እኔ በደለኞች ሆናችሁ የሰይጣን መጫዎቻ ሆናችሁ ትኖራላችሁ። እዩ ውስጡ ንፁህ የሆነውን ልጅ እጣ ፈንታ ተመልከቱ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ። እኔና እናንተ ግን ያለንበትን አልነግራችሁም። በውል ጥሩ ምርት ከማያስገኝ አፈር ተቀምጠን አፈር እያነሳን ነው። ኑሯችን ሳይሻሻል እዛው ከአፈር ወደ አፈር ሆኗል። ልጆቼ አሁን የምናገራችሁ ነገር ምን አልባት አሁን አይገባችሁ ይሆናል። ምክንያቱም ገና ያልበረደ ወጣትነት ውስጣችሁ ላይ ነገር ግይ እናት ናችሁና ዘግይታችሁም ቢሆን ትረዱኛላችሁ። ግን ሲገባችሁ ምን ማድረግ እንዳለባችሁ ምክር ስትፈልጉ እኔን አታገኙኝም። ገመዜ ሳይቀድማችሁ ቅደሙት እያልኳችሁ ነው ስስቶቼ"አለች የአይኗ ጭራ ላይ የደረሰውን እምባዋን ወደ ውስጧ እየሳበች። ሁላቸውም የንዝ ቃል የሚሰሙ እስኪመስላቸው ድረስ የእናታቸውን ንግግር ሳያቋርጡ በጥሞና አዳመጧት። "እሺ እታተዬ አታስቢ በሚገባ ተረድተንሻል ነገር ግን አሁን ያልገባኝ ነገር ለምንድነው እንደዚህ በድንገት እንደዚህ አይነት ንግግር የምትናገሪው?"አለች አድና። ወይዘሮ አትጠገብ የጣራውን ቡጥር እየተመለከተች "ጥሩ ጠይቀሻል ልጄ። እንዲህ የምላችሁ ከዚህ በኋላ ለወንድማችሁ የነበራችሁን አመለካከት መቀየር አለባችሁ። ከዚህ በኋላ ለእሱ መጥፎ መሆን የለባችሁም። እንደውም በተቃራኒው ይቅርታ ብትጠይቁትና እሱም ይቅር ብኋችሁ ትንሾ ጊዜም ቢሆን የወንድምና የእህት ጊዜ ብታሳልፉ ብዬ ነው። በጣም ይጠቅማችኋል። ደግሞ ደግ ነው በእርግጠኝነት ይቅር ይላችኋል። ይቅር የማይል የእግዚአብሔር ሰው አይደለም።እስኪ ተመልከቱት ሙሉቀንን እንኳ ቀዳማዊ ከመጣ በኋላ ነው ኑሯቸው የተለወጠው። ያቺ የማትረባ እናቱ እንኳ በእኔ ልጅ እርዳታ የገዛላትን ቀሚስ ለብስ ቤተርኪያን ላይ ስታገኘኝ እንዴት እንድት እንደምትሆንብኝ። ሙሉቀንስ በአንድ በሬ አልነበር እንዴ የሚኖረው መቀናጆ ገብቶ። አሁን ግን እንደምታዩት ማንም የሌላቸውን አይነቶች በሬዎች ገዝቶ ጥንድ ጥንድ በሬ አለው። ኧረ ምኑ ቅጡ "ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ ማለፊያ አቋረጠቻትና "እና ሆን ብሎ እኛን ለማናደድ ብሎ እኮ ነው ይሄን ሁሉ ያደረገለት። እያ ደግሞ ይቅርታ ያደርግላችሀዠኋል ያልሺውን አልስማማበትም። ምክንያቱም መጥቶ ምን ምን አድርጎ እንደሄደና ምን እያሰበ እንደሆነ በደንብ እናውቃለን።በርግጥ እንደሱ የተማሪ ተንኮለኛ ላንሆን እንችላለን። ነገር ግን በጭራሽ እኛም ከእሱ የበለጥን ነን ሊሸውደን አይችልም"አለች እጇን እያወራጨች። ርብቃም "የማለፊያን ሀሳብ ሙሉ በሙሉ እስማማበታለሁ። እታተይ በርግጥ አሁን ላይ በዚህ እድሜሽ ፍራቻሽን ነውና የመከርሽን ምክርሽን ሰምተነዋል ተረዴተሻልንም ግን ይቅር ተባባሉ የሚለው ሀሳብ ማዘናጊያ ነው። ቀዳማዊ ያን ሁሉ አድርገነው ረስቶት ይቅርታ ብሎን ጥሩ ወንድምና እህት እንሆናለን ብዬ አላስብም"አለች። "እኔ ግን የእታተይን ሀሳብ እደግፋለን። እየውላችሁማ በደንብ አስቡት።እታተይ እንደለትው ይቅርታ ብንጠይቀው ይቅር ሊለን ይችላል። ደግሞ ከተማ ነው ያደገው ይቅርታ ከተጠየቀ ሁሉንም ነው የሚረሳው። ነገ ጠዋት በብዙ ነገሮች መገናኘታችን አይቀርም። ልጆቻችንም ከእኛ ክፋትንና ቂምን መውረስ የለባቸውም። ለልጆቻን ይህንን መተው የለብንም። ከአሁኑ ካልቆረጥነው የችግሩ ሰንኮፍ እያደገ ይሄዳል። ደግሞም ይቅር ብለን ብንጠይቅ እኛ እንጅ ሸክማችን የሚቀል እሱ የምንም የሚለው ነገር አይኖርም"በማለት የእናቷን ሀሳብ ደገፍ ከጎኗ መሆንዋን አስመሰከረች። ኤርስበርስ ሲጨቃጨቁ ቆዩ። የነ ማለፊያ እና እርብቃ ቡድንበጭራሽ ይቅርታ አንጠይቀውም ብለው አሻፈረኝ ሲሁ። የነ አድና ቡድን ደግሞ ሁሉንም እንተወው በማለት ለሁለት ተከፈሉ። "በሉ አሁን አትጨቃጨቁብኝ። በቃ እንደፈለጋችሁ እርስ በርስ ተጣልታችሁ ደግሞ መሳቂያ እንዳትሆኑ። "ፐ ከወለዱ አይቀር እንዲህ ነው እንጅ እነሙሉቀንን እኮ የአየር ትኬት የቆረጠላቸው ራሱ ነው። መቼም ትልቅ ሰርግ ቢሆን ነው መሬት አይንካችሁ ብሎ በአየር ያስወሰዳቸው"አለ አንድ የአካባቢው ነዋሪ "ልክ ብለሀል ጃል የሙሉቀንን ኑሮ እኮ በድንገት ነው ያሻሻለለት ሀሰማይ የመጣ ነው የሚመስለው። እንደዛ ለምኗን እየተንቆሻቆሸ እንዳላረሰ አሁን ግን ተጀንኗል"አለ ንቀት ባዘለ አነጋገር። "አንተው እሱ ከተሜ ከተሜ ሸቷል ተይየይ በኋበላማ ጭራሽ ጉዳችን ፈላ። ወጉ ሁሉ አየር ነው የሚሆነው።"አለ ሌላኛው የበግ ለምዱን እያስተካከለ። "አንተው የእሱን ጉራ ተወውና ግን ጥሩ ልይ ነው ድምጡ እኮ አይሰማም። እንደ ድህነቱ አይደለም ዝቅ ብሎ ነበር የሚሰራው። ፈጣሪ ያን ቆጥሮለት ነው አቦ እንዲህ አይነት ሲሳይ የሰጠው። ችግር የለም የሰራ ሰው እንኳ ያግኝ ቁጭ ብሎ ባቱን እያጠበ የሚውል ሞላጫ አይደል። ይጥራል ይለፋል። በያ ላይ ለእኩ ክፋት የለውም ደግ ነው። እንዲህ አይነት ሰው ደግሞ ማግኘቱ ደግነቱን ይጨምርለታል እንጅ አይቀንስበት።ምክንያቱም ማግኘትንም ማጣትንም በሚገባ ያውቀዋል"በማለት የሙሉቀንን ጥሩ ማግኘት ደገፈ። "ግን አንድ ቀንም አስበኸው ታውቃለህ ቀዳማዊ እንደይህ ይሆናል ብለህ?" "ኧረ በጭራሽ ጎድ እንደው አንዱ የከተማ ሰው ዱርዬ አርጎ ወያላ ይሆናል ነው እንጅ ብዬ ያሰብኩ እንደይህ ትልቅ ሰው ይሆናል ብዬ እንኳ በህልሜም አላሰብኩት እንኳን በውኔ" "አይ የጌታ ነገር እሱ እኮ ማንሳትም መጣልም ይችልበታል። እንደዛ መከራውን አይቶ እኛ ራሱ ይቺ ሴትዮ በእውነት ይሄን ልጅ ወልዳዋለች? ብለን እስክንጠይቅ ድረስ እንዳላሰብነው ከዛ ወጥቶ ይሄን ያህል ማረግ ሲያገኝ እኛስ እኛ ነን እንደ ው እነ ወይዘሮ አትጠገብ ምን ይሉ?" ብሎ በመገረም ጠየቀ። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፱~ ( 219 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 " መቸገር አልነበረባችሁም እኮ ሙሌ"አለ ቀዳማዊ። "ኧረ አይባልም። እዛ ብትዳር ጥሩ ነበር በደንብ እድርህ ነበር። ደግሞ አዝመራው ለጉድ ነበር የያዘው። ያመረትነው እህል ብዙ ነበር። ከምግቡ እስከ ሰላሱቱ ድረስ ተመርቶ ነበር።"አለና ሁለቱን አቁማዳ የነጭ ጤፍ ዱቄት ለወይዘሮ ሔዋን ሰጡ። ሌሎቹ ልጆች ደግሞ የጠላ ድፍድፉን ይዘው ተከተሉ። "እግዚኦ ይሄን ሁሉ ነገር ተሸክማችሁ?"አለችና ሔዋን ሙሉቀንናና ዳሳሽን ስማ በዝና እንደምታውቃቸው ነግራቸው ወደ ቤት አስገብታ አስቀመጠቻቸው። ቀዳማዊም አብሯቸው ተቀመጠ። ዳሳሽ ብድግ አለችና "እትዬ የሆነ በርሚል ነገር ይስጡኝ ጠላውን ልጥመቅ"አለች። "ኧረ ምነው ልጄ መጀመሪያ አረፍ በይ እንጅ አሁን አይደል ከመንገድ የመጣችሁት ትንሽማ አረፍ በሉ የሚጠጣም የሚበላም ቀማምሱ እስከዛው ተጫወቱ እኔ የሚበላ ይዤ ልምጣ ብላ ወጣች ቀዳማዊም ተከተላት "እንግዶቹን ትተኻቸው ለምን መጣህ?" "እነሱ እንግዳ አይደሉም ወንድሞቼ ናቸው ስለዚህ ለትንሽ ደቂቃ ብቻቸውን ብተዋቸው ምን ይሆናሉ ብለሽ ነው! እትዬዋ" "እሺ እንዳልክ በል ሳህንና ይሄን ይዘህ ሂድና አስይዛቸው እኔ ወጡን ይዤ እመጣለሁ" "እሺ "ብሎ ይዞ ወጣ እነ ሙሉቀን ምግብ በልተው በደንብ ከተስተናገዱ በኋላ ወደ ስራ ለመግባት ተነሱ "ምን ልትሰሩ ነው የምትነሱት?"አለ ቀዳማዊ "እህ አዴጌር ያለበት ቤት ስራ ይጠፋዋል ብለህ ነው? የተገኘውን መስራቴ ነውይ ዳሳሽም ጠላውን ትጥመቅ ወንጠፍትና ገለገይት አምጥተሻል አይደል?"አለ ሙሉቀን ወደ ዳሳሽ ዘወር ብሎ "አዎ የከተሜ ሰው መቼም በቢራና በጠጅ ነው የሚያደርገው ጠላ ከጠመቁ ዝልሉን እንጅ ይሄን የገብሱን አያውቁትም ብዬ ሁሉንም ይዣለሁ። እኔ ምፈልገው ጋን ወይም በርሚል ብቻ ነው። እሱን እንዲያመጡልኝ ንገራቸው"አለች ለቀዳማዊ "እሺ እንግዲህ ካልሽ!" አለና ለሔዋን ዳሳሽ የምትፈልገውን እንድታቀርብላት ነግሯት ከነ መልካሙ ጋር ሻይ ቡና ለማለት ወደ ውጭ ወጡ። "ቀዳማ እንደው ይቺ ሴትዮማ እናት ማለት አይደለች"አለ ሙሉቀን "ከእናትም ትበልጣለች ወንድሜ ሕይወቴን ምቹና ጣፋጭ ያደረገችልኝ ሴት ነች። ባለቤቷን ደግሞ ይበልጥ ብታየው ትገረማለህ?"አለ "ወትሮም እኮ እሚባለው እልፍ ሲሉት እልፍ ይገኛል ነው!"አለ መልካሙ(አቤል) "እውነት ነው። በእሱ እኔም አምናለሁ። ተመስገን በአንድ በኩል እንደዛ ባይሆኑብኝ ኑሮ ይሄን አለም አላየውም ነበር ብዬ አስባለሁ። እግዚአብሔር ሰዎችን የሚያስጨክነውም የሚያራራውም በምክንያት ነውና እኔ በበጎ ጎኑ አይቼዋለሁ"አለ ቀዳማዊ "ሙሽሪትን የሰርጉ ቀን ነው የምናያት ቀዳ?"አለ ሙሉቀን ወሬውንም ለመቀየር ያህል "አዎ እንግዲህ የእለቱ እለት ማየታችሁ ነው። ያውም ኤኮ መች ነው ምንተዋወቀው እያለችኝ ነበር። አሁን እንዳልደውልላት ከጓደኞቿ ጋር እየተዘገጃጀች ነው።" "ኧረ ችግር የለም ቀስ ብለን እንተዋወቃለን"አለ ሙሉቀን። "ለምንድነው ግን ዳግማዊን ያላመጣችሁት ሙሌ"አለ ቀዳማዊ "ልጅ ይዞ መንገድ ጥሩ አይደለም። በዛ ላይ አያቱ ልጄማ ከእኔ ጋር ነው ሚቆየው ብላ ከረሚላ እሰጥሀለሁ ስትለው እሺ ብሎ አልቀረም መሠለህ" "አይ ጥሩ አላደረጋችሁም ይዛችሁት መምጣት ነበረባችሁ ማርያምን"አለ ቀዳማዊ "ችግር የለም የሚመጣባቸው ገና ብዙ ጊዚያቶች አሉን ስለዚህ ብዙ ቅር አይበልህ *** "ልጄ ደከምሽ እኮ። ደግሞ ብዙ ነው ያመጣችሁት"አለች ሔዋን ለዳሳሽ ከልቧ እያዘነች። "ኧረ ይቺማ ምን አላት እትዬ አውራጅማ ብዙ ነበር የሚያዝ"አለች ዳሳሽ እየተቅለሰለሰች "አይ ይሄን ሁሉ ይዛችሁ ጭራሽ ትንሽ ነው? አይ ከበቂ በላይ ነው። የሚያግዝሽ እንዳልጠራ ይሄን አጠማመቅ የምትችል ሴት ያለች አይመስለኝም" "ኧረ ችግር የለም ይሄው እየጨረስኩ ነው። ትንሽ ነው የቀረኝ"አለች ለማስተባበል ነገር ግን አንድ ሙሉ ማዳበሪያ ድፍድፍ ነበር የቀረው። ግን ጉሹን ቅመሺው እስኪ እትዬ መወፈሩንና መቅጠኑን"አለችና በመቀነሻ ቀንሳ ሰጠቻት። ጥጥት አድርጊው ገብስ ነው። ጌሾ ትንሽ ነው ያለው" ሔዋን ጠጣችው። በጣም ይጥማል ጭልጥ አድርጋ ጠጣችና እቃውን ሰጠቻት " በጣም ጥሩ ነው። ከዚህ በላይ መወፈርም መቅጠንም ያለበት አይመስለኝም"አለች ሔዋን አፏን እየጠራረገች። "እሺ "አለችና ዳሳሽ መጥመቋን ቀጠለች። "እንዴት አይነት ግሩም የሆነ ጠላ ነው! እንዴት አድርጋ እንዳዘጋጀችው ብታይ"አለች ሔዋን ለሙሉሰው "እኔ ርኮ የወሎን ባህላዊ ጠላ በጣም ነው የምወድላቸው እስኪ ይዘሽልኝ ነይ ሔዋኔ "አለ ሙሉሰው። ሔዋንም ሂዳ አመጣችለት። "ይሄ ሰርግ በቃ እንደፈለግሽው ሆነልሽ። ኧረ እንደውም ከፈለግሽው በላይ ነው የሆነው ከመጠጥም ብዙ አይነት ሆነልሽ "አለ ሙሉሰው "እንዴታ የመጀመሪያ ሰርጌ እኮ ነው። ለቀጣዮቹ ልጆቼ ልምድም ይሆነኛል። በል እንዲጨመርልህ ከፈለክ ንገረኝ ወይም ሄደህ በሀይላንድ አስቀድተህ ጠጣ" ብላው ወጣች። ሙሉሰው የኮረፌውን አይን እያዬ "እንዲህ ነው እንጅ ሴትነት የቱባው ባለሞያ ሲሆን ይጥማል"እያለ እያጣጣመ ሳለ "እስኪ አባዬ እኔም ልጠጣ ስጠኝ"አለች ኤሊያና "አይሆንም ትሰክሪያለሽ "አለች ሔመን ድንገት ከመኝታ ቤቷ ብቅ ስትል ኤሊያና ከአባቷ ልትቀበል የነበረውን ኮረፌ በመመልከት "ሔሚዬ ይሄ እኮ አያሰክርም ቡቅሬ በይው ንፁህ ገብስ ነው። እና ማርማር ነው የሚለው ከፈለግሽ አንቺም ልትጠጪ ትችያለሽ"አለ። "እሺ አባዬ በርግጥ ከአንተ በላይ ለኤሊ አስቤ ሳይሆን እንዲሁ ከአፌ ስለመጣ ነው ይቅርታ"አለች ሔመን ሀዘኔታ በተሞላ አነጋገር። "ችግር የለም የኔ ማር እኔም የምፈልገው ይሄን ያህል ለእህትሽ እንድትጠነቀቂላትና እንድታስቢላት ነው። እናንተ እርስ በእርስ ስትዋደዱና ሰትተሳሰቡ ሁሉም ነገር ቀናና የተደላደለ ይሆናል። እርስበርስ መጠባበቅ አለባችሁ አንዳችሁ ለአንዳችሁ ምርኩዝ ነው መሆን ያለባችሁ። መቼም እኛ ለዘላለም አብረናችሁ አንኖርም"አለና ሙሉሰው ሁለቱንም አቅፎ ሳማቸው @amba88 @ken_leboch

የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት Join our telegram 👇🏻 https://t.me/+GSYm_Bw39Vk3ZGNk
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት Join our telegram 👇🏻 https://t.me/+GSYm_Bw39Vk3ZGNk

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፰~ ( 218 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 ከ ፫ ወራት በኋላ የሰርጉ ሽርጉድ እና ሆይሆይታ አንዱን ከአንዱ አያሰማማም። በሁሉም አቅጣጫ የተገጠሙት ሞንታርቦዎች የተከፈተውን የሰርግ ሙዚቃ እያስተጋቡ ነው። ሁሉም ሰው የስራ ድርሻውን እየተወጣ ይገኛል። ወንዶቹ በሬዎቹን አሳርደው ስጋውን እየከተፉ ነው። ሴቶቹ ጎላውን ጥደው መቁሎውን እያቁላሉ ያወራሉ። "እህ ምን የጎደለ ነገር አለ? የሚጠጣ ምን ይምጣላችሁ?" እያለች ሔዋን እየዞረች ሁሉንም ሰው እየጠየቀች እንደየፍላጎታቸው ታስተናግዳቸዋለች። የቤታቸው በር መሠረት ተደርጎ የተሰራው ድንኳን ረዝም እና ወደ ጎንም ሰፊ ነው። በእነ ፊደላዊት ፍላጎት መሠረት ሆቴል ሊሆን የነበረው ሰርግ በወይዘሮ ሔዋን እምቢታ ምክንያት ሰርጉ ቤት እንዲደረግ ሆኗል። የቀዳማዊን የሰርግ ወጪ የሸፈነው የሚሰራበት ድርጅት ነው። ምንም አይነት ወጪ አላወጣም ከልብስ ጀምሮ የሙሽራውንም የሙሽራይቱንም ልብስ ድርጅቱ ከአሜሪካ ገዝቶ ነው በስጦታ መልክ የሰጣቸው። **** "የኔ ፍቅር ከነገ ጀምሮ እኮ አብረን ልንኖር ነው!"አለች ሐምራዊ የደረቱን ፀጉር እየነካካች። "አብረን መኖር ከጀመርን እኮ ሦሥት ወር አለፈን"አለ ቀዳማዊ። "እሱ በእኛ ፈቃድ ነው። አሁን ደግሞ ቤተሰቦቻችን መርቀውን ከዛ በኋላ በቃ እንዲህ ጧትና ማታ ያለ ትዝታና ናፍቆት አብረን እንሆናለን" " ልክ ነሽ። ከአንቺ ርቆ መኖር ለእኔ ከባድ ነው። እነዚያ ወራቶች እንዴት ምዐተ ዓመት ሆነውብኝ እንደነበር ብታይ! "አለ ቀዳማዊ አይኖቹን የቤቱ ጣራው ላይ እየተከለ። "ግን ፍቅሬ ምን እንደምፈልግ ታውቃለህ?" "ምንድነው ምትፈልጊው?" "ከእንቅልፌ መንቃት ምፈልገው በእንጉርጉሮህ ነው። የኔ ጌታ አንተና ጊታርህ እኮ ስትገናኙ ማመን እስኪያቅተኝ ድረስ ነው ምታስገርመኝ" አለች ሐምራዊ በአግራሞት እጇን አገጯ ላይ አስደግፋ በስስት እየተመለከተችው "አንድ ጊዜ ብቻ አዳምጠሺኝ እንዲህ ማለት አይከብድም?"አለ ቀዳማዊ እንጦጦ ሄደው እያለ የተጫወተላትን አስታውሶ "ኧረ ባክህ አንድ ብቻ?"ብላ ሳቀችና የተጫወተላትን ቦታዎችና ስንት ጊዜ እንደሆነ አስታወሰችው። "በነገርሽ ላይ ትንፋሼን እንደ ፈለኩ የምለቀው በእሱ ነበር። በተለይ እነዛ ዘጠኝ አመታትን ጊታር ባይኖር ኖር ይበልጥ ይከብደኝ ነበር። እድሜ ለዶን ዊይሊያምስ በጆሮዬ ሙዚቃውን በጣቶቼ ደግሞ ጊታሩን ተለማምጄ ለዚህ በቃሁ። ጊታሩን እስክለማመድ ድረስ የካንትሪ ሙዚክን አዘወትር ነበር። ኦህ ዶን "አለ " የኔ ውድ ይህን ባውቅ ኖሮ እመጣልህ ነበርኮ"አለችና ሳመችው። "ቤተሰቦቻችን ለእኛ ሰርግ እንቅልፋቸውን አጥተው እየሰሩ ነው። አንቺ እና እኔ ደግሞ እዚህ አለማችንን እንቀጫለን"አለና ቀዳማዊ ሳም አድርጓት ከመኝታው ተነሳ። ሐምራዊም ጡቶቿን በብርድልብሱ ሸፍና የአልጋውን ራስጌ ተደገፈችና "ቀዳ አንድ ጊዜ ልብሶቼን ትሰጠኛለህ?"አለች "እሺ የኔ ፍቅር ከፈለግሽ ላለብስሽም ኤችላለሁ"ብሎ ሳቀ። "አቤት አቤት ወግ ወጉን ይዘኸዋል"አለች እያሾፈች። ቁም ሳጥኑን ከፈተና ካስመረጣት በኋላ የመረጠቻቸውን ልብሶች ሰጥቷት እሱ የሚለብሳቸውንም አውርዶ ለባብሶ "ፕሮግራምሽ ምንድን ነው?" "ቤት መሄድና ከሚዜዎቼ ጋር ተገናኝተን መነጋገር" "ጥሩ እኔም ቤት ሌሂድና የሚጎለውን ነገር ላሟላ።በዛውም ከራስ አምባ የሚመጡትን ሰዎች ተቀብዬ ማስተናገድ አለብኝ"አለ ቀዳማዊ "ምን ያህል ሰው ነው ከዛ የሚመጣው? ሙሉቀን እና ሌሎች የተወሰኑ ልጆች ናቸው ያን ያህል ብዙ አይደሉም" "ለምን አያንሱም?"ሐምራዊ ጠየቀች። "እንደሚያንሱ አውቃለሁ። ግን አንድ ጊዜ ሄደን የሆነ መልስ ነገር እናደርጋለን። የተወሰነች ድግስ ደግሰን እዛ ካለው ማህበረሰብና ዘመድ አዝማድ ጋር አስተዋውቅሻለሁ።ስለዚህ ሰርጋችን ራስ አምባም ጭምር ነው። የእዛ የሚበልጥ ይመስለኛል። የገጠርን ሰርግ በደንብ ታይዋለሽ!"አለ ቀዳማዊ "ደስ ይለኛል"አለችና በፈገግታ ትከሻዋን ወደ ላይ ሰበቀች። * እምባዎቿ ያለ ከልካይ በጉንጮቿ በኩል ቦይ ሰርተው ይፈሳሉ። በቀሚሷ ጫፍ አይኖቿን አሁንም አሁንም ብትጠርግም የእንባዋን ጎርፍ ግን ማቆም አልቻለችም። ማንም ሰው ሳያያት እንደ ልጅ ስቅስቅ ብላ ትመለከታለች። በጉም ተሸፍኖ ሊያለቅስ የደረሰው ሰማይ የመከራ ግፏን ሊሰፍርላት የተዘጋጀ ቁና መሰላት። ቀና ብላ መመልከት ፈራች። አንገቷን ቁልቁል ደፍታ "እንዴት ሰው በራሱ ልጅ ይሄን ያህል ይጨክናል"አለችና ያደረገቻቸውን ግፎች አንድ በአንድ ለራሷ ታስታውስ ጀመር። "ምን አሁን ብታለቅሺ ምን ትፈይጃለሽ? የፈሰሰ ውሃ አይታፈስ። በቃ ከእንግዲህ በማልቀስ የአይኖችሽን እድሜ ማሳጠር የለብሺም። ይልቅ ልጅሽ የቀጣሽን ያህል ፈጣሪ እንዳይቀጣሽ ነስሃ ገብተሽ ብታርፊ ነው የሚሻልሽ"አለች ወይዘሮ ጎዳዳ። ወይዘሮ አትጠገብ ልቧ ተሸበረ። ሆዷ በፍርሃት ነጎድጓድ ሲተራመስ ታወቃት። ውስጧ አሁኑኑ ብትሞች ይሻልሻል ይላት ጀመር። እንደምንም የውስጧን የሐሳብ ትርምስ ተቋቁማ መደቡ ላይ ጋደም ብላ እንቅልፍ ሸለብ አደረጋት። ወይዘሮ ጎዳዳ ነጠላዋን እስከላይ አልብሳት ወደ ውጪ ወጣች። "እባካችሁ ልጆች እርጅናና ፀፀት ለሁለት እያዳከሟት ነው። አይናችሁን ከእናታችሁ አትንቀሉ። ተንከባከቧት ፀፀቷን ማጥፋት ባትችሉ ጉድለቷን ትቀንሱታላችሁ። በእናንተ ፍቅር ትፅናናለች። ቀዳማዊ አንድ ጊዜ ከእሷ አምልጧል።መቼም ቢሆን እናቴ ብሎ እንደ እናንተ ሰፍ አይልላትም። የእናትነት ወጓንም አያውቀውም። ስለዚህ እናንተን በኋላ እንዳይቆጫችሁ በተራ በተራ ሆናችሁ እናታችሁን ጠብቁ ተንከባከቡ"ብላ ትታቸው ወጣች። * " ሙሉቀን ከሚስቱ ጋር ሆነው እንዲሁም መልካሙና አስችሎ ከአውሮፕላን ሲወርዱ ቀዳማዊ መኪና ይዞ ጠበቃቸው። የናፍቆታቸውን ያህል ተሳስመው መኪና ውስጥ ገብተው ወደ ቤት መሄድ ጀመሩ። "ጉዞ እንዴት ነበር?"አለ ቀዳማዊ በውስጥ ስፖኪዮ እያያቸው። "አንተው ነፍስ አስይዞ ጉዞ ነው ይሄ የአየሩ መንገድ"አለ ሙሉቀን ። ቀዳማዊ ሳቅ አለና "እና ከመኪና አይሻልም ሙሌ? አንደኛ ቶሎ ትደርሳለህ። አሁን ለምሳሌ አንድ ሰው ከራስ አምባ ተነስቶ ተከዜ ደርሶ ለመመለስ የሚፈጅበትን ስዐት አንተ በአውሮፕላን አዲስ አበባ ደርሰህበት ትመጣለህ ማለት ነው"ብሎ ትንሽዬ ማብራሪያ ጨመረለት። "እንዴታ እሱማ ልክ ነህይ ርንደው ግን በመስኮቱ አጮልቀህ ዝቅዝቁን ስታየው ያስፈራል"አለ ሙሉቀን። "ቆይ ዳሳሽስ?"አለ ቀዳማዊ ፈገግ ብሎ "እኔማ ወድጄዋለሁ ሸጋ ነው። በፊት ልጅ እያለን አንጋጠን ወደ ሰማይ የምናየውን ኢሮቢላ ገብቼበት ስመጣ ደስታ ነው የተሰማኝ"አለች። ቀዳማዊ ሁሉንም በየተራ እየጠየቀ በደንብ እየተጫዋወቱ ቤት አካባቢ ከተያዘላቸው ማረፊያ ክፍል አደረሷቸው እቃቸውን በማውጣት ሊያግዛቸው ቢፈልግም። ከበድ ከበድ ያሉ እቃዎችን ይዘው ስለነበር እዛው ዳስ አካባቢ ያሉ የሰፈር ልጆችን ጠርቶ አስወረዶ ሊያስገባው ሲል ሙሉቀን ፈጠን ብሎ "ይሄ ወደ ዳሱ የሚሄድ ነው። ይሄ ደግሞ ለወይዘሮ ሔዋን የሚሰጥ ነው"አለ ሙሉቀን። @amba88 @ken_leboch

የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት Join our telegram 👇🏻 https://t.me/+GSYm_Bw39Vk3ZGNk
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት Join our telegram 👇🏻 https://t.me/+GSYm_Bw39Vk3ZGNk

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፯~ ( 217 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 በዛ ላይ እዛ አሉ ከሚባሉ ባለሀብቶች ጋር እውቅና አለው። እውቅናው ደግሞ ለስራው መሳካት ጉልህ አስተዋፅኦ ይኖረዋል በጣም ትልቅ ስኬት ነው! ስለዚህ ከወዲሁ ይሂድና ለሰርጉም እየተዘጋጀ በዛው መዋቅሩን ይዘርጋ)አለ ሚስተር ፖል ዊስተን የድርጅቱን የቦርድ አባላት ጋር ተሰብስበው በሚነጋገሩበት ጊዜ። "But he should not be alone. If he goes there, he may be missed by his wife and family, so we need to send someone and a team to take the lead."(ግን ብቻውን መሆን የለበትም እሱ እዛ ከሄደ በባለቤቱም ሆነ በቤተሰቦቹ ሊሳነፍ ይችላል ስለዚህ ይሄን ጉዳይ በዋናነት የሚመራ አንድ ሰውና ቡድን መላክ ይኖርብናል።ቀዳማዊን እንደ አጋዥ ልናየው ነው የሚገባ) አለ ሌላኛው የቦርድ አባል። በዚህ ተስማምተው ስብሰባቸውን ጨርሰው ሚስተር ፖል ዊስተንም ቀዳማዊን ወደ ቢሮው በመጥራት አስደሳቹን ዜና ነገረው። ቀዳማዊም የሰማውን ነገር ማመን እስኪያቅተው ድረስ በጣም ደስ ተሰኝቶ ሚስተር ፖልንና ቲሙን አመስግኖ ቀጥታ ወደ ቢሮው አምርቶ ዜናውን ለሐምራዊ ሊነግራት ስልኩን አንስቶ "አሁን ብድውልላት ምን ሆነ ብላ ልታስብ ትችላለች። ምን አልባትም የእኔ የስራ ስዐቴ በዚህ ስዐት መሆኑንም ህትረሳ ትችላለች ስለዚህ ጠዋት ላይ እደውልላታለሁ"አለ ቀዳማዊ ስዐቱ በኢትዮጵያ ለሊት ዘጠኝ ስዐት በመሆኑ ***** "ፍቅር በሰው ልጅ ልብ ውስጥ ሆኖ እንደ ወርቅ ይፈተናል። ይነጠራል። እስከ መጨረሻው ድረስ ተስፋ የማይቆርጡ ልቦች ደግሞ የተፈተኑበትን ፍቅራቸውን ከፍ አድርገው ያሳያሉ። ለብዙዎች የአፍቃሪ ምሳሌ ሐምራዊ ነች። እሷ ያሳየችውን ፅናት ማንም አፍቃሪ ነኝ ባይ አላሳየውም። ይሄን ደግሞ እኔ መመስከር እችላለሁ። ልጄ ስለሆነች አይደለም "አለች ፊደላዊት። "በእርግጥ ልክ ነሽ ግን ደግሞ ሙሉለሙሉ እንደዛ ማለት አትችይም ከምናቃቸው ጋር እንጅ ከማናቃቸው ልጆች ጋር ማነፃፀሩ ይከብዳል"አለች ሜሮን የተባለችው አርቲስት ጓደኛዋ። ፊደላዊት ስለ ሐምራዊ ተጨማሪ ነገሮችን አንስታ አሁንም ሌጇ ብቸኛ አፍቃሪና የፅናት ተምሳሌት እንደሆነች ተናግራ ዝም አለች። ** "በጣም ነው ደስ የሚለው የኔ ፍቅር ይሄን ስለሰማሁ ደስ ብሎኛል። በጣም ሳስበው የነበረው ያንተ ስራ ጉዳይን ነበር"አለች ሐምራዊ ቅልል እያላት። "ይሄው በመጨረሻ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ እየሄዱ ነው"አለ። "ግን በጥሩ ሁኔታ በሄዱ ቁጥር እኔም ፍርሀቴ እየጨመረ ነው""ለምንድነው የምትፈሪው? የኔ ቆንጆ ፍርሀትን አሁን እዚህ ጋር ምን አመጣው!"አለ ቀዳማዊ እየደነገጠ። "እንጃ አላውቅም ዝም ብሎ ነው ፍርሃት ፍርሃት የሚለኝ" "እንዲህ ነው የደስታ ሕይወት ልትጀምሪው ስትይ "አለ ቀዳማዊ እየሳቀ። "እሺ ይሁንልን እስኪ" አለችና ተጨዋውተው በፍቅር ሲነጋገሩ ቆይተው ተለያዩ። ቀዳማዊ አሳሳቋንና አሳሳሟን እያስታወሰ ፈገግ ብሎ ከእንደገና ስለ ራስ አምባው ፕሮጀክት አሰበና በኋላ ላይ ወደ ራስ አምባ እንደሚደውል ለራሱ ቀጠሮ ይዞ ወደ ሌላኛው ስራው ተመለሰ። **** "እንግዲህ እኛ የቻልነውን አድርገናል። ስላልተሳካልን ሁለቱም የራሳቸውን ምርጫ መርጠዋል። አሁን የእኛ ድርሻ እነሱን መደገፍ ነው"አለች ሔዋን። ትዮቢስታ አንገቷን እንደደፋች "አንቺው የኔዋ እንኳ ወዳ የመረጠች አይመስለኝም። እንደው ብቻ አላውቅም ጤነኛ አልመስልሽ እያለችኝ ነው። እንጃ ብቻ" "ምነው ምን ሆነች?"ሔዋን ጠየቀች"ለእኛም አትነግረንም። ልንጠይቃት የሞክርን ጊዜም ትቆጣለች።አባቷም የሚያደርገው ጠፍቶት ዝም ብሎ ያያታል። እኔ ነኝ ትንሽ አሰንደ ጓደኛም እንደ እናትም እንደ እህትም ላወራት እየሞከርኩ ያለሁት።ብቻ እንዳናጣት እሰጋለሁ" "ኧረ የሰይጣን ጆሮ ይደፈን ምነው ትዮብ እንዲህ አይባልም። አይዞሽ ምንም አትሆንም። በርግጥ ስጋትሽ ይገባኛል። እናት መሆን በራሱ ትልቅ ሸክም ነው። ልጆቻችን የፈለገ ቢያድጉ ልጆቻችን ናቸው። ግን ደሐብ አስተዋይና ጎበዝ ልጅ ነች። ነገሮችን በእርጋታ ተመልክታ ስለምተወስን ምንም ነገር አይፈጠርም። ታሮስም አጠገቧ እስካለ ድረስ ምንም አትሆንም እመኝኝ!"አለች ሔዋን ትዮቢስታን ለማረጋጋት እየሞከረች። እዮሲያስ ሔዋንን በንዴት እየተመለከተ "የማትረባ አጓጉል ተስፋ ሰጥታ ልጄን አሰቃየችብኝ"አለና "ምንድንነው ይሄን ያህል ትርጉም የሌለው ወሬ ማውራት"አለና ሔዋን ተገላምጦ በነገር ወጋ አደረጋት። ሔዋን ዘወር ብላ ተመለከተችውና "በይ ልሂድ እየደወልኩ እጠይቅሻለሁ"አለችና ተሰናብታት ወጣች። "ከዚች ሴትዮ ጋር ምን ይሄን ያህል ያስወራሻል ትዮብ! በቃ ተያቸው ራቂያቸው እሷ ናት የማይሆን ቃል ገብታ ልጄን ለዚህ የዳረገቻት። ከዚህ በኋላ ላያት አልፈልግም "አለ እዮሲያስ እየተቆጣ "እሷ ምን ታድርግ የቻለችውን እኮ አድርጋለች እዮሲ። ቀዳማዊ እንቢ ብሏት ነው እንጅ እኮ የእሷን ፍላጎትማ አይተናል። በልጁ ድርጊት ደግሞ እሷን ልንወቅሳት አይገባም። ይህ ከእኛ የማይጠበቅ አስነዋሪ ባህሪ ነው"አለችና ትዮቢስታ ወደ ውጪ ወጣች። ሔዋን እየተብሰለሰለች ቤት ደረሰች። አሁንም አሁንም ትተነፍሳለች በተደጋጋሚ "ሆይ ሆይ" ትላለች። ሙሉሰው የሔዋንን ሁኔታ ዝም ብሎ ሲመለከት ከቆዬ በኋላ "ምን ሆነሽ ነው ሔዋኔ ዛሬ ልክ አይደለሽም?" "ኧረ ተወኝማ ሆድ ይፍጀው ነው የሚባለው እንደው ሰው እኮ ነገረኛ ነው በግድ ነገር ካልበላሁ ማለት? ሆሆይ ይገርማል"አለች ለራሷ "ለምን የሆንሽውንና የተፈጠረውን አትነግሪኝም ሔዋን እኔንም እኮ አስጨነቅሽኝ" "እዮሲያስ ነዋ። ይገርማሌ እኔ እንዲህ አይነት ሰው አይመስለኝም ነበር። ለካ የወረደ ሰው ነው" አለች ንዴቷን ለመቆጣጠር እየሞከረች።"ምን ብሎሽ ነው?""ምን የሆነ ነገር ቢልማ ይሻለኝ ነበር የእሱ እኮ የሚገርም ነው። ፊቱን እንዴት እንደዘፈዘፈብኝ ቢመታኝ ሁሉ ደስ ይለው ነበር"አለች ከንፈሯን እየነከሰች። "ያው ራስሽን በእነሱ ቦታ አድርገሽ አስቢው። የደሐብ እናት ሆነሽ አስቢው እኔም ላደርገው የምችለው የእዮሲያስን ድርጊት ነው። ስለዚህ ቀለል አድርጊው ወይዘሮ ሔዋን "አለ ሙሉሰው ብዙም ሳይጨንቀው። "ኧረ እኔ በጭራሽ እንደሱ አልሆንም!"አለች ሔዋን ከተቀመጠችበት እየተነሳች " አንቺ ትሆኛለሽ ማን አለ? አንቺማ ትዮቢስታን ነው የምትሆኚው እኔ ነኝ እዮሲያስን የምሆነው"አለ ፈገግ እያለ በሔዋን ሁኔታ። ሙሉሰው አንዳንድ ጊዜ ነገሮችን የማቅለል ባህሪ አለው። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፮~ ( 216) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 ገና ከመጣ አንድ ወር ሳይሞላው የሐምራዊ ናፍቆትና ፍቅር ሌት ተቀን እየመጣበት የተቸገረው ቀዳማዊ ወደ አለቃው በመሄድ ይዞት የነበረውን ጥያቄ ዘረገፈለት። "Mr. Paul Whiston, I want to talk to you about a personal matter. I have a fiancé and a fiancé. And I decided to date her. So I made a decision. To accept my wife's desire to live in her country, I must decide to leave this country and work in Ethiopia. And you set the direction that this organization will expand its reach by opening branches in African countries. And if you open a branch in Ethiopia in five months. I want to do my job with the responsibility you give me so I came to consult on this issue" (ሚስተር ፖል ዊስተን አንድ የግል ጉዳዬን ላጫውተዎት እፈልጋለሁ። አንዲት በቅርቡ የማገባት ፍቅረኛና እጮኛ አለችኝ። እና ከእርሷ ጋር በትዳር ለመጣመር ቀን ቆርጠን ነው የመጣሁት። ስለዚህ የወሰንኩት ውሳኔ አለ። የሚስቴን በሀገሯ የመኖር ፍላጎት ለመቀበል የግድ እኔ ከዚህ ሀገር መውጣትና ስራየን በኢትዮጵያ የመስራት ውሳኔ ላይ ደርሻለሁ። እና ይህ ድርጅት ደግሞ በአፍሪካ ሀገራት ቅርንጫፍ በመክፈት ተደራሽነቱን ያሰፋል የሚል አቅጣጫ አስቀምጣችሁ ነበር። እና በአምስት ወር ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ ቅርንጫፍ የምትከፍቱ ከሆነ። እኔ በምትሰጡኝ ሀላፊነት ስራየን መስራት እፈልጋለሁ ስለዚህ ይህን ጉዳይ ለማማከር ነው የመጣሁት)አለና ንግግሩን ገታ አድርጎ የሚስተር ፖልን ምላሽ ይጠብቅ ጀመር። "First of all, I would like to thank you for coming here to talk openly about your ideas. You never know how happy I will be to hear that. Thank you very much. We do not want to lose you. Our organization needs you. Therefore, we have the responsibility to make it possible for you to do so. I don't think it will last as long as you said. We are in talks with the Ethiopian government. And for the organization there, we definitely need you. "We know the language and the culture, so we will fix it and it won't last until then."(በቅድሚያ በግልፅ እዚህ ድረስ ስላለህ ሀሳብ ለመናገር ስለመጣህ ላመሰግንህ እወዳለሁ። ይህን ስለሰማሁ ምን ያህል ደስ እንዳለኝ አታውቅም በጣም አመሰግናለሁ። እኛ አንተን ማጣት አንፈልግም። ድርጅታችን አንተ ታስፈልገዋለህ። ስለዚህ አንተ በምትችልበት ቦታና አካባቢ ደግሞ የማመቻቸት ኃላፊነት የኛ ነው። እስከ አልከው ጊዜ የሚቆይ አይመስለኝም። ኦልረዲ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እየተነጋገርን ነው። እዛ ላለው ድርጅት ደግሞ በእርግጠኝነት አንተ ታስፈልገናለህ። ቋንቋውነና ባህሉን ከማወቅ ጀምሮ ስለዚህ እኛ እናስተካክላለን እስከዛም አይቆይም) ብሎት ተለያዩ። ቀዳማዊ በሚስተር ፖል የቅንነት መልስ እየተደሰተ ወደ ቢሮው ተመለሰ። ** ሐምራዊ ቀዳማዊ በተደጋጋሚ ደውሎ እንዳጣት አይታ እሷ ስትደውል ደግሞ ልታገኘው አልቻለችም። እንደዚህ በመሆን ለቀናት ሳይገናኙ ቀሩ። የሞከረችው በሙሉ አልሆንላት ሲል ያላት አንድ አማራጭ ቀዳማዊ በሚደውልላት ስዐት ተቀምጣ ሳትተኛ መጠበቅ ነው። እንደጠበቀችው ከምሽቱ ሰባት ስዐት ደወለ። በመጀመሪያ ጥሪ አነሳችው "የኔ ፍቅር ደህና ነሽ ደህና ነህ"ተባብለው ናፍቆታቸውን በስካይፒ ምስል እየተሳሳሙ ይወጡ ጀመር። በጣም ነው የናፈቅሽኝ እኔም በጣም የናፈከኝ"እየተባባሉ ስለ ሰርጉ ይነጋገሩ ጀመር። "በነገርሽ ላይ የኔ ፍቅር አለቃዬ ድርጅታቸው ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ለመክፈት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ ነግሮኛል" አለ ቀዳማዊ "ኡፍ የኔ ፍቅር እንዴት አይነት ዜና ነው የነገርከኝ። በጣም ነው ደስ የሚለው "ብላ አልጋዋ ላይ በደስታ ዘለለች። "በጣም እኔ ራሱ እንዴት ደስ እንዳለኝ። እለቃለሁ ስላቸው ያው ትንቅ ያካብዱብኛል ብዬ አስቤ ነበር። የፍቅር አምላክ ሁሉንም ነገር ቀና በቀና አደረገው" "በጣም ፍቅራችን እውነተኛ ስለሆነና መራራቅ እንደሌለብን ፈጣሪ ስላዬ ነው። ለዚህ ጥሩ ዜና ነገ በጠዋት ሄጄ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጧፌን አበራለሁ"አለች። "ጥሩ አብሪና ሌላም ነገር ለምኝ የኔ ፍቅር"አለ ቀዳማዊ "ሌላ ምን ልለምን አባት?" "ልጅ ነዋ የኔ ፍቅር ሌላ ምን ሊሆን ይችላል" "እሱንማ ቀድሜ ለምኛለሁ! ለዛውም አንተን የመሰለ ቆንጆ ወንድ ልጅ" አለች " አይ አይ እኔ የምፈልገው አንቺን የምትመስል ቆንጅዬ ሴት ልጅ ነው"አለ ቀዳማዊ "አይ አይሆንም። የመጀመሪያ ልጃችንማ ወንድ ነው መሆን ያለበት ለአንተም ለእኔም ጥሩ ጓደኛና ወንድም ይሆነናል"አለች ሐምራዊ "ልክ ነሽ የኔ ፍቅር እንዲሁ የምፈልገውን ያህል እንጅ እሱማ ወንድም ቢኖረን አልጠላም። በዛ ላይ ከአንቺ የተወለደ" "አንተስ ብትሆን ጥሩ አባት እንደምትሆን ምንም ጥርጥር የለኝም""በቃ ፍቅሬ መሞጋገሱን እንተወውና የት አካባቢ ብንኖር ደስ ይልሻል? እሱን እያሰብኩ ነበር" "ወደ አያት አካባቢ ቢሆን ጥሩ ነው። ራቅ ብለን ብንኖር ደስ ይለኛል"አለች ሐምራዊ "ለማንኛውም በደምብ አስቢበት "አለና ሌላ ወሬ አንስተው ተጨዋውተው ተሰነባበቱ * "We did not expect things to improve so quickly. Anyway, at least I didn't go down without explaining myself first. I have no doubt that it will make a better organization in the short term. He also recognizes the investors who are there. Recognition also contributes to the success of the project. What a great achievement! So let's go ahead and stretch the structure in preparation for the wedding"(በዚህ ፍጥነት ነገሮች ይስተካከላሉ የሚል ግምት አልነበረንም። ለማንኛውም በጣም ጥሩ አጋጣሚ ነው በተለይ ለኢንጂነር ቀዳማዊ ጥሩ አጋጣሚ ለእኛም መልካም እድል ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ የተሻለ ድርጅት እንደሚያደርገው ምንም ጥርጥር የለኝም። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፭~ ( 215 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 "እና እዚህ ሌትኖሩ ነዋ!"አለ ሱራፌል የሚጫወቱትን የወሬ ርዕስ በአንድ ጊዜ እየቀየረ። "አዎ አባቴ እኔ እዚሁ ነው መኖር የምፈልገው። ከኢትዮጵያ ውጪ መውጣት አልፈልግም። በእርግጥ የቀዳማዊ ምርጫም እዚሁ መኖር ነው" "ጥሩ በደንብ ተነጋግራችሁ አንዱን ከአንዱ መዝናችሁ። አንዱን ለመረጣችሁበት ምክንያታችሁን አስቀምጣችሁ ነው መወሰን። በኋላ አንቺ ነሽ አንተ ነህ መባባል የለባችሁም። በሰከነ መንፈስ ህናችሁ እያንዳንዱን ነገር አብጠርጥራችሁ ነው መነጋገርና ማውራት ያለባችሁ። ትዳር ላይ ትንሽዬ ክፍተት እንኳ ካለች ታሻክራችኋለች።ልዩነታችሁንም ሳታርቡት ልታሰፋው ትችላለች"አለ ሱራፌል። "ተዋቸው እንጅ ልጆቹ እንደፍላጎታቸው እንደሚመቻቸው እንደተስማሙበት ያድርጉ አታስፈራራቸው። ደግሞስ እኔና አንተ ይሄን ያህል መጀመሪያ ተነጋግረናል? እነሱም ቀስ እያሉ የሚያይቱን እና ጎደለ ያሉትን እየተነጋገሩበት ቢሄዱ ይሻላል እንጅ ከአሁኑ ሁሉንም ካላሰባችሁ ብሎ መምከር ይከብዳል"አለች ፊደላዊት የሱራፌልን ምክር ስታዳምጥ ከቆየች በኋላ "የዝንብ ወተት የሆንሽ ሴት አሁን ከሌጅና ከአባት ምክክር ምን ጥልቅ አደረገሽ"አለ ሱራፌል ።ፊደላዊት እየሳቀች። "እንዴት አያገባኝም መካሪው ለብዙ አመት የማውቀው ባሌ! ተመካሪዋ ደግሞ አምጬ የወለድኳት ልጄ"አለች። "ፐ ወገኛ ነሽ ወግ ወጉንስ ይዘሻል "አለና ሱራፌል "ብቻ እናትሽን ተያት ቁምነገር ላይ ውሃ ደፍታ ማቆርፈድ ትወዳለች። ከልብሽ ያዥው አሁን ላይ በፍቅር ውስጥ ስለምትሆኝ ምንም ነገር አይታይሽም። ሁሉም ነገር ስተገቢበት ቀላል ነው ስትኖሪበት ግን ይከብዳል"አለ "በዚህ ምክርህ ልጅቱ ሰርጉን እንዳትሰርዘው እፈራለሁ"አለችና ሳቀች ፊደላዊት። ሱራፌል ተነስቶ "አፍ አፌን የምትይኝ ለምንድነው? ሰው ልጁን ላይመክር ነው"አለና ከፊደላዊት ጋር መላፋት ጀመሩ። ሐምራዊ ሁለቱንም በስስትና በፈገግታ ትመለከታቸው ጀመር። ** "ጥሩ ውሳኔ ነው ልጄ ሁሉም ነገር ላይ ችክ ማለት ጥሩ አይደለም። በቃ እሱ የራሱን ሕይወት ጀምሯል። አንቺም የራስሽን ሕይወት ለመጀመር መወሰንሽ አስደስቶኛል"አለች ትዮቢስታ የደሐብን ፀጉር እያሻሸች። "በቃ ሊጋቡ ነው እማዬ?" ደሐብ አይኖቿ እምባ እያቀረሩ ጠየቀቻት። "አዎ ቀን ቆርጠዋል። እሱም የስራውን ሁኔታ ለማስተካከል እና ወደዚህ ለማስቀየር ነው የሄደው። ከሰርጉ በኋላ የሚሄድ አይመስለኝም" "ታውቂያለሽ ግን እማዬ ጅል ሆኜ ነው እንጅ መቼም አላጣውም ነበር። ከመጀመሪያው ጀምሮ አጠፋሁ። ኩራትና እልህ ልቤን ደፈኑት አሁን እንዲህ በፍቅሩ ልሰቃይ ያኔ በማን አለብኝነት ልቤ ደነደነ።ምን አለ ዝም ብዬ መበለጤን አምኜ ከእሱ ጎን ብሆን ኖሮ"በማለት ተቆጨች። "ልጄ ያለፈን ነገር ማስታውሰ ተገቢ አይደለም። ያ የመሳሳቻ እድሜሽ ነበር ተሳስተሻል። ግን ስህተትሽን መድገም የለብሽም ሁሌም የምልሽ ይሄን ነው። አሁን ያን ባደርግ ኖሮ እንዲህ ባስብ ኖሮ ብትይ ምንም የምትለውጪው ነገር የለም። ጊዜን መመለስ አይቻልምአይቻልም። በኋላ ደግሞ እንዳትፀፀች ይሄን ልጅ እንዳትጎጂው"አለች ትዮቢስታ። ደሐብ በጉንጮቿ የእንባ ዘለላዎቿ እየተንከባለሉ በአንገቷ ወርደው ጡቶቿ ውስጥ ተደበቁ። ጉንጯን በፍጥነት ጠራርጋ ካበሰች በኋላ "ልክ ነሽ እማዬ ታሮስን እንዳልጎዳው መጠንቀቅ አለብኝ"አለች ወደራሷ ተመልሳ። "ቆይ ታያለሽ ሰርግሽ አዲስ አበባ ላይ መነጋገሪያ እንዲሆን አድርጌ ነው የምደግሰው። በሚገርም ማዕረግ ነው የምድርሽ"አለች ትዮቢስታ ለደሐብ መፅናኛ ቢሆናት ብላ *** አሜሪካ ካሊፎርኒያ "Welcome Engineer kedamawi. We have interrupted our work by waiting for you. And we want you to try to fix it as soon as possible. We have protected our customers a lot. (እንኳን ደህና መጣህ ኢንጂነር ቀዳማዊ። አንተን በመጠበቅ ስራዎቻችንን አስተጓጉለናል። እና በተቻለህ መጠን ባጭር ጊዜ ውስጥ ለማስተካከል ብትሞክር ደስ ይለናል።ደንበኞቻችችንን ብዙ አስጠብቀናቸዋል)"አለ የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሚስተር ፖል ዊስተን "I know we have a lot of expectations and I want to work quickly and satisfy the needs of our customers. I believe I should spend more time enjoying it.(አውቃለሁ ብዙ እንዳስጠበቅናቸው እኔም በቶሎ በመስራት የደምበኞቻችንን ፍላጎት ማርካት ነው ግቤ እንደዛ ስለማስብ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማስተካከል እሰራለሁ። ተጨማሪ ጊዜ ቢሆን በመጠቀም ማስደሰት እንዳለብኝ አምናለሁ) አለና ቀዳማዊ ሰላምታ ሰጥቶት የሚሰሩ ዶክመንቶችን ይዞ ወጣ። ቀዳማዊ የተደራረቡበትን ስራዎች እየሰራ ስለመሸ ለሐምራዊ መደወሉን ርስት አደረገው። አምሽቶ ስለነበር የተኛው ጠዋት ከእንቅልፉ የቀሰቀሰችው ፅሐፊው ነበረች። "Did you spend the night working here, sir?" ( እዚሁ ስትሰራ አድረህ ነው ጌታዬ?) አለች በመደነቅ "Yes, there are too many jobs. Our customers may be upset because we do not keep our word. A large organization like ours should not create a gap with customers in this way. So somehow we have to sacrifice our sleep when we have to" (አዎ ስራዎች በጣም በጣም በዝተዋል። ደንበኞቻችን ደግሞ ቃላችንን ባለማክበራችን ቅር ሳይላተው አይቀርም። እንደኛ አይነት ትልቅ ድርጅት ደግሞ በዚህ መልኩ ከደንበኞች ጋር ክፍተት መፍጠር የለበትም። ስለዚህ እንደምንም እንቅልፌንም ቢሆን መስዋዕት አድርጌ ባለን ጊዜ ማድረስ ይኖርብናል) አለ ቀዳማዊ እጆቹን እያንጠራራ ከወንበሩ ተነሳና ስልኩን ይዞ ወደ መናፈሻው ወጥቶ አየር ለመቀበል እንዲሁም ቢሮውን እንድታስተካክል በመተው። የጠዋቱን ነፋሻማ አየር እየተቀበለ ሐምራዊን አሰበ። በዚህ ጊዜ ነበር እንዳላወራት ትዝ ያለው። የእጅ ስልኩን አውጥቶ እንደማያገኛት በማሰብ ግን ትንሽ የማግኘት ተስፋ ይዞ ደወለ። ሶስት ጊዜ ደውሎ ልታነሳ አልቻለችም። ተኝታ ይሆናል በሚል እሳቤ ስልኩን ዘግቶ እጆቹን የሱሪ ኪሱ ላይ አስገብቶ ቁልቁል ይመለከታል። የተወሰነ ውጪ ላይ ቆይቶ ቁርሱን ቢሮው ድረስ እንዲመጣ በማዘዝ ወደ ቢሮው ተመልሶ ስራ ጀመረ። ስራውን አክብሮ በመስራትና የስራ ዲሲፕሊን በመያዝ በተለያዩ የድርጅት ሀላፊዎቾና በአለቆቹ ተወዳጅነትን ያከበረው ቀዳማዊ ዛሬም የግል ሕይወቱን ለማስተካከል እና ከወዳጅ ዘመዶቹ ጋር ጥሩ ጊዜ ለማሳለፍ የተጠቀመውን የአንድ ወር የስራ ጊዜ ለማካካስ ሌት ተቀን የስራ ገበታው ላይ መገኘቱ ስራ ስለመውደዱ የሚያሳይ ትልቅ ማሳያ ስሀመሆኑ ማንም አይጠራጠርም። እንደሌሎቹ ኢትዮጵያውያን ከሌሎቹ የአገሩ ሰዎች ጋር ሳይቀር ለመገናኘት አያስብም። አሜሪካ ለእሱ የስራ ቢሮው ብቻ ነች። ይህንን የስራ ወዳድነቱን ታዲያ አለቆቹ በጣም ስለሚወዱለት ማንኛውንም የደሞዝ ጭማሪ እና ጥቅማጥቅም ይጨምሩለታል። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፬~ ( 214) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 "ሰምተኸኛል አይደል ታሮስ"አለች ደሐብ አይን አይኑን እየተመለከተች " አዎ በደንብ ሰምቼሻለሁ እንጅ የኔ ፍቅር " "እና ምንም አትናገርም? ዝም አልክኮ"አለች አንገቷን እያቅለሰለሰች "አይ በደንብ እያሰብኩ ስለሆነ ነው። የኔ ፍቅር አንቺን እንዴት ማስደሰት እንዳለብኝ ቀጣይ ሕይወታችን ምን መምሰል እንዳለበት ሁሉ ነው በዚች ቅፅበት ማለቴ እንጋባ ባልሽኝ ጊዜ ያሰብኩት"አለ ታሮስ በፈገግታ ታጅቦ "እንደዛ ከሆነ ጥሩ መጀመሪያ የሚቀድመውን አድርግና ከዛ የሚከተለውን አብረን አስበን እናደርጋለን"አለች። "እሱስ ልክ ነሽ የሚቀድመውን ይቀድማል ግን እንዲሁ ከደስታዬ ብዛት ሌላ የማስበው ቢጠፋብኝ ነው እንጅ"አለና ተንጠራርቶ አይኗን ሳማት። ታሮስ ደሐብ የተናገረችውን ነገር ከእንደገና ለራሱ ደገሞ እንደ ገደል ማሚቶ በጭንቅላቱ እያመላለሰ ቀጥታ ወደ ቤቱ ሄደ። የታሮስ እናት ከወትሮው በተለዬ በፈገግታ ታጅቦ ታሮስን እየተመለከተች ሳቅ አለችና "ልጄ ምን አግኝተህ ነው እንዲህ እንደፈንዲሻ ፍንድቅድቅ ያልከው?"አለች "እማዬ ከየት እንደምጀምርልሽ አላውቅም። ግን በቃ ምን ልበልሽ ደሐብ እኮ እንዳገባት ጠየቀችኝ" "እውነትክን ነው ልጄ?"አለች እሷም በዜናው ተገርማ "አዎ እማዬ!" የታሮስ እናት ግን ፊቷን ዘወር አደረገትና ራሷን ማዳመጥ ጀመረች። ዜናው ብዙም ምቾት የሰጣት አትመስልም! "እንዴት በዚህ ቅፅበት እሺ ልትልህ ቻለች ልጄ?" መልሳ ጠየቀችው። "እናቴ ደግሞ በዚህ ቅፅበት ሆነ ምን ሆነ ዋናው እሷ እንዳገባት እኔን መጠየቄ ነው። ይልቅ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ሽማግሌ እንድትልኩልኝ እፈልጋለሁ። በተቻለ ፍጥነት በቅርቡ እንዲያልቅ ነው የምፈልገው" አለ ታሮስ "እሺ ከአባትህ ጋር እናወራና መች ሽማግሌ እንደምንልክ እናሳውቅሀለን" ብላው ታሮስ ልብሱን ቀያይሮ ተመልሶ ወጣ። *** ቀዳማዊ አንዱን ርዕስ በሌላኛው ርዕስ እየለጠቀ የኢትዮጵያ ቆይታው ከወር በለጠ። በየቀኑ የስራ መልዕክቶች እየበዙበት መጥተዋል። የተወሰኑትን መመለስ ሲችል አብዝሀኛዎቹን ግን በአካል መሄድ ይጠበቅበታል። ይህንን የስራ ጫና ተቋቁሞ ና ለሰርጉ የሚሆኑ ነገሮችን ከቤተሰቦቹ ጋር እየተነጋገረ ቀናቶችን አሽቆጠረ። ሐምራዊ የቀዳማዊ መሄጃ ቀን እየቀረበ በሄደ ቁጥር ሆዷ እየተሸበረ ያለፉትን ዘጠኝ አመታት የምትደግም እየመሰላት በፍርሀት ተውጣለች። "የኔ ፍቅር አሁን የምሄደው እስከ እድሜ ማብቂያችን ድረስ የሚያቆየንን ስራ ለማጠናቀቅ ነው። እኔም እንደ አንቺ ነው የማሰማኝ ከአንቺ መለየቱን አልፈልግም። ስለዚህ ምንም አታሰቢ እሺ የኔ ፍቅር"እያለ ቢያፅናናትም እርሷ ግን ለጊዜው እሺ ትለውና ግን ደግሞ በየቀኑ ሳታገኘው ለወራት እንደምትቆይ ስታስብ ትረበሻለች። ይህንን ሁኔታዋን ሔዋን አይታ ከቀዳማዊ በተሰጣት አደራ መሠረት ከወዲህ ታባብላታለች። ቀዳማዊ ወደማይቀረው የአሜሪካ ጉዞ ሻንጣውን ማዘጋጀት ጀመረ። ሐምራዊ ቀኑን ሙሉ ቢሮ ሳትሄድ ከቀዳማዊ ጋር አለሟን ስትቀጭ ዋለች። ሔመንና ሐምራዊ ቀዳማዊን እስከ አየር መንገድ ድረስ ሸኙት። "ፍቅሬ በቶሎ ተመለስ እሺ የኔ ጌታ በጣም ነው የምትናፍቀኝ"አለችና ሐምራዊ ከንፈሩን ሳመችው።"ቀዳ ትናፍቀናለህ"አለችና ሔመን ተንጠራርታ አንገቱ ሳር ሳም አደረገችው። አቀፋትና ግንባሯን ሳማት "በቶሎ እመጣለሁ እሺ "አለ "እሱማ ወደህ ነው በግድ እንጅ የምትፈልገው ነገር ያለው በሙሉ እዚህ"ብላ ሳቅ አለችና ወደ ሐምራዊ ዞረች።ሐምራዊም በፈገግታ ተቀበለቻት። "ታውቂያለሽ በጣም እድለኛ ነሽ "አለች ሔመን ዝም ብለው ሲጓዙ ከቆዩ በኋላ "ልክ ነሽ እድለኛ ነኝ። ብዙዎች የሚያፈቅሩትን ሰው አያገኙም። የሚያፈቅሩትን ሰው የሚያገኙት ከብዙዎቹ የተወሰኑት ናቸው። እና ከነዛ ከተወሰኑት መሀል መሆኔ ደግሞ እድለኛ ያደርገኛል። ቀዳማዊን ከማግኘቴ በተጨማሪ ማለት ነው።"አለች ሐምራዊ "ልክ ነሽ ብዙዎቹ የመጀመሪያ ፍቅራቸውን ማገኝት አይችሉም። ወይ የሚያፈቅሩት ሰው ሌላ ያፈቅራል ወይም ደግሞ በሌላ ሰው ይቀደማሉ። ከሁለት በአንዱ ምክንያት ማግኘት ያቅታል"አለች ሔመን ፊቷን ወደ መስታውቱ አድርጋ ውጪ ውጩን እየተመለከተች። ሐምራዊ እንደመደንገጥም ልቧ እንደመፍራትም አለ። " ምነው ያጋጠመሽ ነገር አለ? ካለ ልትነግሪኝ ትችያለሽ። ጓደኛሽ መሆን እችላለሁ" አለች ሐምራዊ። ሔመን ሳቅ አለችና " ተይው ይሄንና ይልቅ አርክቴክቸር ስለሆነ እያጠናሁ ያለሁት በእሱ ትረጂኛለሽ። አንዳንድ ዲዛይኖችን ታሳይኛለሽ ትሰጭኛለሽ" "እሱ ችግር የለውም ቀላል ነው። እንዳልኩሽ ማውራት የምትፈልጊው ሰው ከፈለግሽ አለሁ እንደ ታላቅ እህቴሽ ወንም እንደ ጓደኛሽ ልትቆጥሪኝ ትችያለሽ"አለች ሐምራዊ። "እሺ አወራሻለሁ አመሰግናለሁ በጣም "አለች ሔመኔ። ሐምራዊ ሔመንን ቤት አውርዳት ከእንደገና ወደ ቦሌ ተመለሰች። የመኪናውን ቴፕ ድምፁን ትንሽ ጨምራ ዘፈኑን እየዘፈነች ቦሌ ቢሮዋ ጋር ደረሰች። **** ሔዋን ፍፁም ደስተኛ ሆናለች። "በጣም ደስ ብሎሻል አይደል እማዬ?"አለች ሔመን "በጣም እንጅ ልጄ እስኪ ተመልከች ይሄው ለወግ ለማዕረግ ደረስኩኮ። በተራዬ እኔም ልድር ነው። ከዚህ በላይ ደስታ ከየት ይመጣል የእሱ የሰርግ ድንኳን ሳይነሳ ደግሞ አንቺ ትደርሽልኛለሽ በቃ በየተራ አሸሸ ገዳሜ ማለት ነው እንጅ " "የእኔን እንኳ ተይው" "ምን ማለቴ የው ተይው?"ሔዋን ፊቷን በአንድ ጊዜ ጨለም አድርጋ የምትሰራውን ስራ አቆመችና ጠየቀቻት። "እማ ደግሞ ምን ያናድድሻል። እኔ ብዙ እቆያለሁ ተመርቄ እንደ ሐምራዊ የተወሰነ አመት ሰርቼ በደንብ ራሴን ስችል ከእናንተ ሀላፊነት ስወጣ ያን ጊዜ ነው ወደ ትዳር ሐሳብ የምገባው" "ይሄን ሁሉ እስክታደርጊማ እኔ አረጅብሻለሁ። ካረጀሁ ደግሞ ማን አዘጋጅቶ ይድርሻል? የመጀመሪያ ልጄንማ በራሴ በጉልበቴ ሰርቼ እራሴ ሁሉን ነገር አዘገጃጅቼ ነው የምድርሽ"አለች ሔዋን " እስኪ ፈጣሪ ለዛ ያብቃን ውዷ እናቴ ሲደርስ እንነጋገርበታለን ለጊዜው ግን የቀዳማዊ ጥሩ ሰርግ አለሽ ያው ሰርጉ ሆቴል ላይ ይሁን ካላለ" "ማለት ሆቴል ስትይ የምን ሆቴል ነው? ነው የነገረሽ ነገር አለ?" "አይ የለም ግን እንዳትደክሚ ብሎ ቢቀይረውስ ብዬ ነው" "አይ የሚባል ነገር የለም። ተነጋግረናል። ሰርጉ ቤት ነው የሚሆነው። ዘመድ አዝማድ ይጠራል። የእኔም የሙሉሰውም ዘመድ ብዙ ነው ስለዚህ ሆቴል ብሎ ነገር የለም። የሐምራዊ ወላጆችም ሆቴል የሚፈልጉ አይመስለኝም" "አይ በእነሱ እንኳ እርግጠኛ አትሁኝ ያለ ድካም ሁሉንም ነገር ማድረግ ስለሚፈልጉ እሱ እንኳ ሊፈልጉ ይችላሉ"አለች ሔመን። "እኔ ዙሮ ቤቴ እንጅ መደገስ የምፈልገው ሆቴል የሚባል ነገር አልፈልግም።"አለችና ሔዋው ስራ መስራቷን ቀጠለች። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፫~ ( 213 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 "ልጄ እንዴት ልታደርግ ነው ታዲያ የሐምራዊን ነገር?"አለች ሔዋን ቀጣይ በሚጠብቀው ነገር ላይ እንደ እናት ሀሳቡን ለመስማትና ይበጃል ይሻላል የምትለውን የእሷን ሀሳብም ለመጨመር " ያው ሁለት ሀሳቦች ነው ያሉኝ አንደኛው ወይ እሷን ይዞ መሄድ ወይም ደግሞ እኔ የአሜሪካ ስራዬን ትቼ እዚህ መቅረት። ነገር ግን ከነዚህ ከሁለቱም የተሻለ አንድ ሀሳብ አለ። እኔ የምሰራበት አለም አቀፍ ኮንስትራክሽን ድርጅት እንደመሆኑ በአፍሪካ ካሉ ሀገራት ጋር ስምምነት በመፍጠር በመንግሥት የሚመሩ ትልልቅ ኮንስትራክሽኖችን ለመያዝ እቅድ አለው። እና ከአፍሪካ ደግሞ የመጀመሪያ እቅዱ የሆነችው ሀገር ኢትዮጵያ ናት።ስለዚህ ኢትዮጵያ ላይ ቅርንጫፉን ከከፈተ ስራ አስኪያጅ እና ዋና ተደራዳሪ ሆኜ መቀመጫዬን ኢትዮጵያ ላይ አደርጋለሁ ማለት ነው"አለ ቀዳማዊ ለፕቶፑን ዘግቶ ሻንጣው ላይ እያስቀመጠ። "ውይ ይሄ ከሆነማ እንዴት ደስ ይላል። እኛም ካጠገባችን ብትሆንልን ምን ያህል ደስ ይለናል መሰለህ ልጄ" አለች ሔዋን ስስትና ጉጉት በታከለበት አነጋገር "እንግዲህ ሁሉንም ነገር የሚያስተካክለው ፈጣሪ ነውና እሱ ይርዳን እኛ የቻልነውን እናደርጋለን"አለ * በሽማግሌ ወግና ስርአት መሰረት ልጃችሁን ለልጃችን ለማለት የልጆቹን ፍቅር በቤተሰብ ፈቃድ ለማስባረክ የቀዳማዊ ሽማግሌዎች በተቀጣጠሩበት ቀንና ስአት ተገኝተዋል። ከብዙ እልህ አስጨራሽ ክርክር በኋላ እነ ፊደላዊት ተረትተው ሽማግሌዎቹ ሶፋው ላይ ተቀመጡ። እየተካሄደ ያለው ነገር አልገባት ብሎ አንድ ጊዜ ሽማግሌዎቹን ሌላ ጊዜ ደግሞ ሱራፌልን ትመለከታለች። "እንግዲህ በወግና በባህላችን በኢትዮጵያዊነት ስርአታችን መሠረት እዚህ ድረስ የመጣነው ልጃችሁን ወይዘሪት ሐምራዊን ለልጃችን ለማጨት ነው"አለ አንድ በእድሜ በስልሳዎቹ አጋማሽ ያለ ሽማግሌ። "አዎ የእነዚህን ወጣቶች ፍቅር ወደ ትዳር እንዲቀየር የወላጅ ምርቃትና እሽታ ያስፈልጋልና እነሆ ለሽምግልና ነው የመጣነው"አለ ዮፍታሔ። ሙሉሰው ሽማግሌ መረጣ ላይ በነበረበት ጊዜ ነበር አቶ ዮፍታሔንም በማማከርና እሱም አንድ ሽማግሌ እንዲሆን ሙሉሰው በጠየቀው መሠረት በደስታ ነዋ በማለት የቅንነት መልሱን የሰጠው። ፊደላዊት ግራ በመጋባት ውስጥ ሆና "ለመሆኑ ልጃችሁ ማነው ሽምግልና የመጣችሁለት ስለ ልጁስ የምትሉን ነገር ካለ"አለች ሱራፌል ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብሎ "አብረው ነው የሚሰሩት መሀንዲስ ነው!"አለ። ፊደላዊት ይበልጥ ግራ ተጋባች። እየተካሄደ ስላለው ነገር ተነስታ ሐምራዊን አትጠይቃት ነገር ሽማግሌን ትቶ መነሳት ነውር ነው።ብቻ ጨንቋት ራሷን እያሻሸች ሳለ "እንግዲህ ልጃችን በሙያው መሀንዲስ ነው። በሙያውም አንቱታን ያተረፈ ታታሪ ንቁ ሁልጊዜም አዲስ ነገርን መፍጠር የሚችል አለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ድርጅት አሜሪካ ውስጥ ነው የሚሰራው። በባህሪውም እጅግ በጣም ጥሩና አስተዋይ አርቆ አሳቢ ትዕግስተኛና ለእሱ ቅርብ ለሆኑ ሰዎች ደግሞ ያለ ምንም ማመንታት የሚኖር ነው። ኢንጂነር ቀዳማዊ ታረቀኝ ይባላል። ሱራፌል ከመቀመጫው ብድግ አለና ተነስቶ ከእንደገና ቁጭ አለ። "ማለት አልገባኝም። እናንተ የቀዳማዊ ታረቀኝ የአቶ ሔዋንና የአቶ ሙሉሰው ሽማግሌዎች ናችሁ?"አለ ባለማመን "አዎ ያወቃችሁን መስሎን ነበር እኮ"አለ ዮፍታሔ "አይ እኔ ለሌላ ሰው ነበር ሽምግልና ይመጣል የተባልኩት! ለዛ ነው "አለ ሱራፌል። "እንዴት ሆኖ እኛ በጭራሽ እናንተ እንደምትመጡ አላወኩም" በማለት እሱም በተራው ወደ ፊደላዊት ዞረ። ምንም አላውቅም በሚል አስተያየት ትከሻዋን ሰበቀች። "እሺ ለማንኛውም ሽምግልናውን ተቀብለናል"አለ ሱራፌል ሽማግሌዎቹ ተነስተው እጅ ነስተው ተዋወቁና ተቀመጡ። የሚበላም የሚጠጣም ከቀረበ በኋላ እየተመገቡ በደንብ ተግባብተው ቆይተው በኋላም እጅ ተነሳስተው አንተ ቅደም አንተ ቅደም ተባብለው ተለያዩ። ፊደላዊትና ሱራፌል ሽማግሌዎችን ከጊቢ መውጣታቸውን ከተመለከተ በኋላ ከ ፊደላዊት ጋር ተጠቃቅሰው ቀጥታ ወደ ሐምራዊ ክፍል አመሩ። "እስኪ ንገሪን እኛ መጫወቻዎችሽ ነን? እንዴት ግን አስችሎሽ ዝም አልሽ እንደዛ ስጨነቅ "አለ ሱራፌል በሀዘኔታ አንገቱን ሰበር አድርጎ እየተመለከታት። "እውነት አባዬ ልነግርህ ነበር። ግን ዛሬ እንደዚህ አትሆንም ነበር። ደግሞ እማዬንም አንተንም ነበር ሰርፕራይዝ ማድረግ የፈለኩት ስለዚህ ለሁለታችሁም አንዳንድ ነገር መደበቅ ነበረብኝ። አንተን ከቀዳማዊ ጋ እንደተታረቅን አለመንገር ለእማዬ ደግሞ ሽማግሌ እንደሚልክ አለመናገር። ስለዚህ አንተን እንዳትነግራት የዕለቱ ዕለት ታቃለች አልኩህ። እሷን ደግሞ እራሴ እነግረዋለሁ እንዳትነግሪው አልኳትና አንተን ሰርፕራይዝ አደረኩህ"አለች እየተፍለቀለቀች። "ተሳክቶልሻል የኔ ቆንጆ ልጅ። ዋናውና ትልቁ ነገር አንቺ ልጃችን ደስተኛ መሆንሽ ነው"አለና ሱራፌል ግንባሯን ስሟት ተነሳ። "መቼም ሌላ የቀረሽ ነገር የለም አይደል ውዴ?"አለችና ፊደላዊት ፈገግ እያለች ሱራፌልን ተከትላ ወጣች። ** የሽንፈት መራራ ፅዋ የተሸናፊውን ሕይወት በመጠኑም ቢሆን ይቀይረዋል። ደሐብም በቀዳማዊ ተገፍታ ታሮስ ላይ ወድቃለች። ታሮስ በጣም እንደሚያፈቅራት ብታውቅም እሷ ግን ብዙም ለእሱ ስሜት እንደሌላት ስታስብ የታሮስ ፍቅር ብቻ ምንም እንደማይፈይድ ትረዳለች። ፍቅር የሁለት ሰዎች ፍላጎትና መሳሳብ ድምር ውጤት ሲሆን ይበልጥ ትርጉም ይሰጣል። ከታሮስ ጋር ግንኙነት መጀመራቸው እፎይታን ቢሰጣትም ግን ልቧ ለመቼውም ከቀዳማዊ ላይርቅ የተስማማ ይመስል ታወላውላለች። "ግን ለማደርጋቸው ነገሮች ምናምን በጣም ይቅርታ። ምን አልባት አንተን ሊረብሽ እንደሚችል አውቃለሁ። ግን በቃ በቀላሉ እርሱን መርሳት ደግሞ አልችልም"አለች ደሐብ የታሮስን አይኖች እየተመለከተች። "እሱን ስሜት በደንብ አውቀዋለሁ። የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ። እኔ ምንጊዜም የምጥረው አንቺን ደስተኛ ለማድረግ ነው። ፈፅሞ እንዲከፋሽ አላደርግም"አለ ታሮስ አይኖቿን ትኩር ብሎ እየተመለከተ "አውቃለሁ ታሮስ አንተ ፍፁም ደስተኛ እንደምታደርገኝ ለዛም ነው ቀሪ ህይወቴን ከአንተ ጋር ለመኖር ከራሴ ጋር የተስማማሁት። እኔ ከዚህ በኋላ ለምንም ነገር አቅም የለኝም።ደክሞኛል እንደ ድሮው እኖደየ አመጣጡ መመለስ አልችልም። ለነዛ የዋህነትም ኩራትም ለተቀላቀለባቸው ንግግሮቼ በቃል በቃል ዋጋ ከፍያለሁ። አሁን ግን ያለፈውን ሁሉ ረስቼ ያለፈ ታሪኬ አካል የነበሩ ሰዎችንም ትቼ ወደ ፊት ከአዲሱ ሕይወቴ ጋር መቀጠል ነው የምፈልገው።ስለዚህ ሽማግሌ እንድትልክና ቶሎ ተጋብተን እንድንኖር እፈልጋለሁ"አለች ታሮስ ክው አለ። የሆነ መብረቅ አጠገቡ የወደቀ ያህል ስሜት። አደነጋገጡ የሚገርም ነው። በዛች ቅፅበት አለም ላይ እንደ ታሮስ እድለኛና ደስተኛ ሰው አልነበረም። አይበገሬው አይሸነፌው የደሐብ ማረፊያ ያጣ ልብ በመጨረሻ የታሮስ የልብ ዋርካ ላይ ተዘረረ። በሰከንድ ብዙ ቦታ ደርሰው የሚመለሱት አይኖቿ በእርጋታና በጥሞና በተመስጦ ፊት ለፊቷ የተቀመጠውን አፍቃሪዋን ብቻ ትመለከታለች። ይህን ሁኔታዋን ለሚመለከት ሰው ደሐብ በፍቅር የናወዘችለትን ወንድ የምትመለከት እንጅ የምታፈቅረውን ልጅ የምትረሳበት መሸሸጊያ ዋሻዋ እንደሆነ አይመስልም። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፪~ ( 212 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 "እንግዲህ ምንም ያህል ቢቆይም በመጨረሻ የሚያፈቅራትን ሴት ከራሱ አንደበት ነግሮኛል። ለአንተም ሊነግርህ ስለሚፈልግ አናግረው"አለች ሔዋን ሙሉሰውን። ሙሉሰውም ወዲያው ወደ ቀዳማዊ ማደሪያ ክፍል ገባና "እስኪ ለእናትህ የነገርካትን ነገር ለእኔም ንገረኝ ልጄ"አለና ሙሉሰው ወንበሩን ወደ አልጋው ጠጋ አድዴድጎ ተቀመጠ። ቀዳማዊ ሁሉንም የተፈጠረውን ነገርና የሚሰማውን ስሜት ሙሉ በሙሉ አንድም ነገር ሳያስቀር ነገረው። ሙሉሰው ቀዳማዊ ያለውን አንድም ነገር ሳይቀር ከሰማውና ከተግባቡ በኋላ "ያልከኝ ነገር በሙሉ እውነት ከሆነና በስሜትህ ጥርጣሬ ከሌለ እኔ ነገውኑ ሽማግሌ እልካለሁ እንዳታስብ። ይሄን በደስታ ነው የማደርገው። ስለዚህ አንተ ምንም ሀሳብ እንዳይገባህ"አለ ሙሉሰው "እሺ ጋሼ አመሰግናለሁ። በእሷ ሙሉ ለሙሉ እርግጠኛ ነኝ። በሐምራዊ ልብ እተማመናለሁ "አለ ቀዳማዊ ። ሙሉሰው በይሁንታ ራሱን እየነቀነቀ ከቀዳማዊ ክፍል ወጣና ሔዋን ጋር ሄደ። "ሔዋኔ እንደ ባህልና ወጋችን በዚህ ሳምንት መጨረሻ ወደ ሐምራዊ ወላጆች ሽማግሌ እንልካለን"አለ "በጣም ጥሩ የእሱም መሄጃው እየደረሰ ስለሆነ አንድ ነገር ላይ ደርሰው ቢሄድ ጥሩ ነው"አለች ሔዋንም ተነሳሽነቷ እየጨመረ። *** "እንደምን ዋልሽልኝ እርግቤ!" "ደህና ነኝ የኔ ፍቅር ምንም አልልም ደህና አድርገህ ነው ክንፌን የሰበርከው!"አለች ሐምራዊ ፈገግታ በፊቷ ላይ እየረበበ። ቀዳማዊ ፈገግ አለና "ይሄን ስብራትሽን የሚጠግን ነገር አያስፈልገውም ታዲያ?" "ያስፈልገዋል እንጅ እንዴት አያስፈልገውም! እናቴ የተቻላትን እያደረገች ነው። አሁን አንተ ነህ የቀረኸው!" "ጥሩ እሺ የእኔ ግን ይለያል። ስጋሽን ሳይሆን መንፈስሽን የሚጠግን ነገር ነው የምሰጥሽ" "ኧረ አታጓጓኝ ቀዳ ምንድን ነው ልትነግረኝ የፈለከው?" ሐምራዊ ተቁነጠነጠች ከአልጋዋ ልትነሳ ስትል አቅም ያንሳታል ከእንደገና ተመልሳ ትወሸቃለች። "ጋሼ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ሽማግሌ ይልካል!"አለ "ምን?"ሐምራዊ ባለማመን አፏን ከፍታ በእጇ ከደነችው። "አዎ የኔ እርግብ ሽማግሌ ሊልክ ነው ከዛ በኋላ ሚስቴ ትሆኛለሽ። ሕይወታችንንም በደስታና በፍቅር እንኖራለን" "ወይኔ ቀዳ ምን ያህል ደስ እንዳለኝ አታውቅም" "በደንብ አውቃለሁ እንጅ የኔ ቆንጆ " "እትዬ ሔዋን በቀላሉ እሺ ትላለች ብዬ አላሰብኩም ነበር። ቀኑን ሙሉ ስጨነቅ ሳስብ ነበር የዋልኩት" "እኔም እምቢ የምትለኝ መስሎኝ አንቺን የማትቀበለኝ መስሎኝ ሲበዛ በጣም ጨንቆኝ ነበር። ግን ተመስገን ፈጣሪ የሁለታችንንም ፍቅር አይቶ በልቧ ውስጥ አድሮ በፍቅር ፈቅዳለች" ሐምራዊ በሀሴት የምትይዘው የምትጨብጠው አጣች። ሀዘንና ና ያልተጠበቀደስታ የሚወልደው እንባን ነውና እንባን ወለደች። የአሁኑ ለቅሶዋ ያለፉትን የናፍቆት ሀዘን ጊዚያት የሚሸኝ የደስታ እንባ ነበር። የዛ ሁሉ ፅናቷ ዋጋ ነበር። ያልተኛቻቸውን ለሊቶች ያሳላፈቻቸውን የትዝታ መንገዶች ወደ ኋላ መለስ ብላ ትንሽ ቃኘችውና ራሷን እያወዛወዘች "ሽማግሌ ሊልክ ነው!"አለች ለራሷ። እንደ ልጅ አደረጋት። የልጅነት ፍቅሯን እስከ እድሜ ማብቂያዋ ድረስ አብራው ልትኖር መንገድ መጀመሩን ስታውቅ አለም ላይ እንደሷ ደስተኛ ያለ አልመስላት አለ። አይኖቿን ጨፍና ፈጣሪዬ የልቤን መሻት አይተህ ለአመታት የምፈልገውን ልጅ እንደሚያስፈልገኝ አውቀህ ፀሎቴን ሰምተኽኛልና ክብር ምስጋና ይግባህ" ብላ ፀሎቷን ሳትጨርስ ሰማዩ በነጎድጓድ ድምፅ ራደ። ከየት መጣ ያልተባለ ዝናብ በወጀብና በነፋስ ተቀላቅሎ ወረደ። ቀስ ብላ ከአሌጋዋ ተነስታ የበረንዳውን ሰፊ የመስኮት በር መጋረጃውን ከፍታ የሚወርዱትን የዝናብ ጠብታዎች ትመለከት ጀመር። አልፎ አልፎ በነፋስ ተፈናጥረው መስኮቱ ላይ ያረፉት የዝናብ እንክብሎች የሆነ ፊደል ፅፈዋል።ዙሪያውን በማይለይ ምስል ቀርፀውታል። ሐምራዊ ወደዚህ ምስል አይኖቿን አፍጥጣ ሳለ በሯ ተንኳኳ ደንግጣ ዘወር አለችና አልጋዋ ላይ ገብታ ተኛች። በሩ በድጋሚ ተንኳኳና ተከፈተ። አባቷ ነበር። ሱራፌል ወደ ሐምራዊ ጠጋ አለና "ደህና ዋልሽ ልዕልቴ"አለ "ደህና ነኝ አባዬ አንተ ደህና ነህ?" "እኔማ ምን እሆናለሁ ደህና ነኝ ልጄ! አንቺ ነሽ እንጅ አንድ ጊዜ አንዱ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሌላኛው እረፍት እየነሳሽ ልጄ የተረበሸችብኝ" "አይዞህ አባዬ በቅርብ ሁሉም ነገር ያልቃል። እኔም ድክም ብሎኛል። እና ይሄን አይቶ ፈጣሪ የሰጠኝን ሰው እቀበላለሁ" አለች ሐምራዊ "ምንድነው ይሄ ነገር እናትና ልጅ ደጋገማችሁብኝ ምን ልትይኝ እንደፈለግሽ በቀጥታ ንገሪኝ ልጄ "አለ ሱራፌል "ልልህ የፈለኩት አባዬ በቃ በቅርቡ እወስናለሁ። አንድ መሀንዲስ ካላገባሁሽ እያለ ጭቅጭቅ እያደረገኝ ስለሆነ እኔም በቃ እስከዚህ ድረስ ከመጣሁ ይበቃኛል ብዬ ጥያቄውን ልቀበለው ነው። በዚህ ሳምንት መጨረሻ ሽማግሌ ይልካል " አቶ ሱራፌል ሐምራዊን ትክ ብሎ ተመለከታትና "ግን በደንብ አስበሽበታል? በኋላ የሕይወት ዘመን የማይሽር ቁስል ሆኖ እንዳያሳክክሽ"አለ ማስጠንቀቂያ በሚመስል አነጋገር "ችግር የለም አባዬ የሚፀፅተኝን ውሳኔ አልወስንም። በዚህ እርግጠኛ መሆን ትችላለህ" "እሺ ድንገት እንደዚህ የወሰንሽው በቀዳማዊ ላይ ምን ሰምተሽ ነው? ከደሐብ ጋር ያላቸው ግንኙነት ጠነከረ? ወይስ ሌላ ነገር ተፈጠረ?" "በቃ አባዬ ምንም ነገር አትጠይቀኝ "አለችና "ግን ስለ ሽማግሌው ምናምን ለእናቴ እንዳትነግራት አደራ አባዬ"ለእሱ ችግር የለውም ግን የኔ ውድ ልጅ በድጋሚ ላሳስብሽ በድጋሚ አስቢበት"አለና ግንባሯን ስሟት ወጣ። ሐምራዊ ባለችበት እጆቿን ከፍ ዝቅ እያደረገች ጨፈረችና "ሁለታችሁንም ነው ምሰራላችሁ"አለች እየሳቀች። ሙሉሰውና ሔዋን ዝግጅታቸውን ከወዲሁ ጀምረዋል። ለሽምግልና የሚልኳቸውን ሽማግሌዎች ከመምረጥ ጀምሮ ሌሎች አበይት ክንዋኔዎችን በየ ቅደም ተከተላቸው በማስኬድ ላይ ናቸው። ለሽምግልና የሚላኩትን ሽማግሌዎች ወደ እነ አቶ ሱራፌል ቤት የሚሄዱበትን ቀን ተነግሯቸዋል። አቶ ሱራፌል ደግሞ ለፊደላዊት የሆኑ የሚመጡ እንግዶች እንዳሉበት በመናገር እንድትዘጋጅና ምግቦችን እንድታሰናዳ አሳውቋታል።አቶ ሱራፌል የሐምራዊ የመጨረሻ ውሳኔን እያብሰለሰለ ቀዳማዊን ለማግኘትም ዳድቶት ነበር ከእንደገና ለክብሩ በማሰብና የልጁን ውሳኔ ከማክበር አኳያ ትቶት ነው እንጅ። "ፍቅሬ ለአባዬ ምን እንዳልኩት ታውቃለህ?"አለች ሐምራዊ እየተፍለቀለቀች። ቀዳማዊ ከአሜሪካ የተላከለትን መልዐዕክት ከፍቶ እያነበበ "ደግሞ ምን አልሽው?"አለ "ለአባዬ አንተ ሽማግሌ እንደምትልክ አይደለም የነገርኩት የሆነ መሀንዲስ ላግባሽ ምናምን እያለኝ ነው። አልኩት። ስለ አንተ ቢጠይቀኝ በቃ ከዚህ በኋላ ይበቃኛል ደክሞኛል ምናምን ስለው በጣም እየከፋው ነገር ግን የእኔን ፍላጎት ለመቀበል ያህል ብቻ እሺ አለ። እማዬን ደግሞ ሽማግሌ እንደሚላክ አታውቅም። ስለዚህ ሽማግሌዎቹ ሲመጡ አንደኛ የምትደነግጠው እናቴ ናት። ሁለተኛ ደግሞ አባዬ ሽማግሌዎቹ ለማን ለመጠየቅ እንደመጡ ሲያውቅ። ከዛ በኋላ እኔ ሁለታቸውንም እያየሁ መሳቅ ነው"አለች ገና ከትዕይንቱ አስቀድማ እየሳቀች። "የሚገርም ሰርፕራይዝ ነው ያዘጋጀሽላቸው ውዴ። እኔንስ በምንድነው ሰርፕራይዝ የምታደርጊኝ?"አለ እየሳቀ። "አንተማ ሰርፕራይዝ ተደርገሀል ስጦታም ተሰጥቶሀል"አለች እየሳቀች። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲፩~ ( 211 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 ** "ልጄ አስከፋውህ እንዴ?"አለች ሔዋን......... ቀዳማዊ በሀሳብ የፊደላዊትን ንግግር እያስታወሰ ስለነበር ሔዋንን አልሰማትም። በእጇ ነካ አደረገችውና ከእንደገና ጠየቀችው።"አዬ አላዘንኩብሽም። ያው እንደ እናት ልጅሽን ጥሩ ካልሆነች ሴት እየጠበቅሽ እንደሆነና ጥሩ ሚስት እንዲኖረኝ ከማሰብ የመነጨ እንደሆነ በሚገባ እረዳለሁ። በዚህም በጣም ደስተኛ ነኝ። ግን እኔንም ልትሰሚኝ ይገባል። የእኔ ትክክለኛዋ ሴት ፈጣሪ የሰጠኝ ሐምራዊን ነው። እርሷ ናት ትክክለኛ የኔ አፍቃሪ። ቃሏንም በሚገባ ትጠብቃለች። ስለዚህ ምርጫ የሌለው ምርጫ እኔን ይጎዳኛል እንጅ አያስደስተኝም። አንቺ ሐምራዊን አልወዳትም ብትይኝ እና ከአንቺና ከእሷ ምረጥ ብትይኝ ምርጫዬ ግልፅ ነው አንቺን እናቴን ነው የምመርጠው። ግን ከዛ በኋላ ደስታ ከእኔ ይርቃል። ምክንያቱም የሐምራዊ አምላክ የየዋኋ ልጅ ፈጣሪ የልቧን ቅንነት አይቶ ዝም አይለኝም። የእኔ ደስታ ማጣት ደግሞ በኋላም ቢሆን አንቺን ይነካሻል። ምናለ ያንጊዜ ምረጥ ባልለው ብለሽ ትቆጫለሽ። ያ ቁጭትና ፀፀት ምንም እንደማይፈጥር ስታውቂ ደግሞ ይበልጥ በራስሽ ትናደጃለሽ። እኔ ይሄ ሁሉ እንዳይፈጠር ነው የምለምንሽ።ግዴለም አንቺ ብቻ እሺ በይኝ ከሐምራዊ ጋር ሆኜ ደስተኛ ባልሆን እንኳ ኃላፊነት አንቺ አይኖርብሽም በኩራት መጀመሪያውኑ ነግሬው ነበር ትያለሽ። እኔም እውነት ሐምራዊ የጠበኩትን ያህል ባህሪ ካላገኘሁ እናቴ ነግራኝ ነበር ብዬ ልቆጭ"ብሎ የቀኝ ጉልበቷን በሁለት እጆቹ ይዞ ጠየቃት። ወይዘሮ ሔዋን በጥሞና ስታዳምጠው ከቆየች በኋላ ዝም ብላ ተመለከተችው። የምታውቀው ቀዳማዊ አይደለም። መልሶቿን በመጠበቅ አይኖቹን አይኖቿ ላይ የርኅራኄ አስተያየቱን እያንከራተተ የአዎንታ መልሷን ይጠብቃል። ይሁንታዋን እሺታዋን ብቻ ከአንደበቷ እንዲወጣ እየተመኘ በፍርሀት ያያታል። ይሄን ሁሉ ነገሩን ወደ ውስጥ የሚዘልቁ አስተያየቱን ስታይ አሳዘናት። በፈገግታ አገጩን በሁለት እጇ ይዛ "በትክክል ተረድተኸኛል። ባትረዳኝ ኖሮ ለምን እንዳልወደድኳት እነግርህ ነበር። ነገር ግን አንተ በእኔ ቦታም በእሷ ቦታም በራስህ ቦታም ሆነህ ነገሩነሰ ለማስተዋል ሞክረሀል። ጥሩ የኔ ልጅ እኔም የምፈልገው ይሄን እይታህን ነው። አሁን ሙሉ በሙሉ ፈቃዴን ሰጥቼሀለሁ። ለአንተ ለልጄ ጥሩ ሚስት ከሆነችልኝ የኔ ቀላል ነው። ምክንያቱም አንተ ደስታ ስለሚገባህ ጥሩ ሕይወት ስለሚገባህ ነው። የእኔ ምኞትና ደስታ እሱ ነው ስለዚህ ይሄን ያህል ካመንክባት እኔ ከልብህ እውነት ጋር አልጣላም። ስለዚህ በደስታ ሐምራዊን የአንተ ሚስት ብቻ አድርጌ ሳይሆን እንደ አንተ እንደ ልጄ ላያት ቃል እገባልሀለሁ"አለች ሔዋን። ቀዳማዊ ሳቅ እያለ አለቀሰ። ወይዘሮ ሔዋንን አቀፋትና "በጣም አመሰግናለሁ እናቴ!" ብሎ የሚናገረው ነገር ጠፋበት ከደስታ ብዛቱ የተነሳ ጉንጯን ሊለቃት አልቻለም። "እንዴ ጨረስከው እኮ ጉንጬን ቀዳ "አለች ሔዋን እየሳቀች። ** "እኔ አልፈልገውም ለእኔ የሚሆን ሰው አይደለም። እንደውም ከእሱ ይልቅ ለታሮስ የተለዬ ስሜት የተሰማኝ መሰለኝ"አለች ደሐብ። "እሱማ እንዴት አይለይብሽ ለአመታት የሚያፈቅርሽን ሰው እንዴት ጎልቶ አይታይሽ ከነ ሙሉ እንከንሽ ባህሪሽ እኮ ነው የሚያፈቅርሽ። ሲጀመር የምታፈቅሪው ሰው እና የሚያፈቅርሽ ሰው ይለያያል። አሁን አንቺ ቀዳማዊን እንጅ ቀዳማዊ አንቺን አይንከባከብሽም ታሮስም አንቺን ይንከባከባል እንጅ አንቺ እሱን ኬር አታደርጊውም።ስለዚህ በዚህ ምክንያት ነው ለእሱ የተለዬ ስሜት ያለቦሽ "አለች ቤርሳቤህ። ደሐብ ግን ቀዳማዊ ከውስጧ ሙሉ ለሙሉ ስላልወጣ ስለ ለታሮስ በደንብ ስትናገር ስለ እሱ ያላትን ስሜት ትጠራጠራዋለች። በቀዳማዊ መገፋቷ አለመመረጧ አብከንክኗታል። ችላ ስላላት ምንም አይነት የመፈለግ ስሜት ስላላሳያት ተናዳለች። ይህን ሽንፈቷን ደግሞ መቀበል ተስኗት በእያንዳንዱ ቅፅበት ከሀሳቧ ከአንደበቷ ሊጠፋ አለመቻሉ ይበልጥ ያብከነክናታል። ወይዘሮ ትዮቢስታ ለደሐብ ምክርም ይሁን ሀሳብ መስጠት ትታለች።እንደፈለገች የምትፈልገውን ታድርግ ዞሮ የሚጠቅማትም የሚጎዳትም ሌላ ማንንም ሳይሆን ራሷኑ ነው በሚል እሳቤ በትዝብት ብቻ ነው የምታያት። የደሐብ ባህሪ ቀን በቀን እንደተቀየረባቸው ነው። ያሳደጓት ያብራካቸው ክፋይ ሁሉ አልመስል አለቻቸው። አቶ እዮሲያስ አንዳንድ ጊዜ ትክዝ ብሎ ያያትና "እንደው ልጄ ያገኘሽ ነገር ግን ምንድን ነው። በእኛ በወላጆችሽ እንዲህ የሚያደርግሽ ምንድነው "ብሎ መጠየቅ ሲጀምር። ሳትመልስለት ተነስታ ትሄዳለች። የደሐብን መንገድ እናትና አባቷ ቆመው እንዲመለከቱ ከማድረግ ውጪ ሌላ አማራጭ አልሰጠቻቸውም። የሆነ ነገር ሊሏት ሲፈልጉ የምትናገራቸው ንግግሮች ከእርሷ የማይጠበቁና እንደ ልጅ ያልሆኑ ስለሆኑ ዝምታን መርጠዋል።አንዳንድ ጊዜ ቤተሰብ የልጆችን መስመር ማስመር ሲሳነው ልጆች ደግሞ በተሰጣቸው ሜዳ ቦርቀው ሲጨርሱ ያ ሜዳ ሲሰለቻቸው ወደ ሜዳ ሰጪዎቹ ዞረው ሜዳ ራሳቸው እንጅ ማንም እንዳይሰጣቸው ሌላ ጫናና ያልተገባ ድርጊት ይፈፅማሉ። የሰፊው የወላጅ ችግር የልጆችን ነፃነት በምን መልኩ መጋፋት እና ማስጠበቅ እንደሚችሉ በግልፅ አለማወቃቸው ነው። **** ቀኑን ሙሉ ስለቀዳማዊ ውሎውና ከሔዋን ጋር ስለሚያደርጉት ንግግር እያሰበች ቀኑ መሽቷል። ፊደላዊት ሐምራዊን እየተንከባከበች እንደ እናት ሳትሆን እንደ እህትና የቅርብ ጓደኛ እየታዘዘቻት ነው የዋለችው። "ሐምራ ለእራት አትመጣም እንዴ?"አለ ሱራፌል ከወትሮው የራት ማዕድ በተለዬ መልኩ ሲያጣት። ፊደላዊት ፈገግ ብላ "ማዕዱ ያለ እሷ ቅር ቅር አለህ አይደል? ትንሽ አመም አድርጓት ነው። እራቷን እዛው ሰጥቻት ነው የመጣሁት"አለች ፊደላዊት "ምነው ምን ሆነች?"ሱራፌል በድጋሚ ጠየቀ "ያው አንዳንድ ጊዜ ሀሳብም ስራም ሲበዛ ራሳችንን ያመን የል እንደዛ ነው። ያን ያህል ከባድ አይደለም"አለች ፊደላዊት ነገሩን ቀለል በማድረግ። "እሺ ግን ምግብ ስጨርስ ሄጄ አያታለሁ። እኔምልሽ እንደው በዛ ልጅ ጉዳይ ምንም አዲስ ነገር የለም? ልጄን እኮ አቁሞ አስቀረብኝ"አለ ሱራፌል ቁጭት ባዘለ ሁኔታ ከንፈሩን እየነከሰ። "እንግዲህ በቅርቡ ሁሉም ነገር ይስተካከላል ብዬ አስባለሁ ወይ ተስፋዋ ይለመልማል ወይም ተስፋዋን ትቆርጣለች"አለች ፊደላዊት ምንም ሳይመስላት። ሱራፌል "ምንድነው ነው ያልሽው ተስፋዋን ትቆርጣለች ነው ያልሽው? ይሄ ምን ማለት ነው። እሱን እኮ ነው እኔ የማልፈልገው። ልጄ ተስፋ ስትቆርጥ ከማያት ብሞት ይሻላል።"ብሎ በንዴት ኮስተር ብሎ ተናገራት። "እኔ እንደዛ ማለቴ አይደለም። በጣም ይቅርታ የኔ ፍቅር። እኔ ልል የፈለኩት ይሄን አይደለም ቁርጧን አውቃ መጪ ጊዜዋን ትወስናለች ለማለት ያህል ነው"አለችና ለስለስ ብላ ተናገረች። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፲~ ( 210 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 ወይናቸውን እየጠጡ ስላለፉት ሕይወት እየተጫወቱ ሳለ ድንገት ሐምራዊ አይኖቿ እምባ አቅረው ወዲያው አለቀሰች። "በጣም ናፍቀኸኝ ነበር። በየቀኑ ሳላስብህ ውዬ አላድርም በቃ ንፍቅ ትለኛለህ"አለችና እያለቀሰች ሰውነቱን በሙሉ ትነካካዋለች። እሱ መሆኑን እየተጠራጠረች። "አሁን ያ ሁሉ አልፏል። ያለፉት ጊዜዎቻችንን የተሰቃየንባቸውን አመታቶች በፍቅር ለመካስ አብረን ነን። አሁን ደስታ እንጅ ሀዘን የለም ሳቅ እንጅ እንባ የለም አለና አቀፋት እሷም አቀፈችው። አይኖቿን ከአይኖቹ መንቀል ተሳናት። አልፎ አልፎ ደግሞ ታስለመልማቸዋለች። ቀዳማዊም በፍቅር ሲመለከታት ከቆዬ በኋላ እጁን ሰጥቷት ተነሱና ቆመው ይሳሳሙ ጀመር። የሁለታቸውም ትንፋሽ ሙቀት የክፍሉን ሁኔታ ቀየረው። አንገቷን እየሳመ ከጀርባ በኩል የተሸመቀቀውን የሸሚዟን ቁልፍ ከፍቶ አወለቀው። ቲሸርቱን አወለቀችለት። ሁለቱም ለየቅል ስራዎቻቸውን በፍጥነት አጠናቀው አልጋው ላይ ተያይዘው ገቡ። ሐምራ ልጅነቷን በፍቅር ለቀዳማዊ አስረከበች። ድንግልናዋን እርሷነቷን አሳልፋ ሰጠችው። አለቀሰች እምባዋንና እያበሰች የሚፈሳትን ደም ለማስቆም ሻወር ቤት ገባች። ቀዳማዊ ያወለቀውን የሐምራዊን ሸሚዝ አቅፎ ሳመው አይኖቹን ጭፍን አድርጎ አፍንጫው ስር አሽቀመጠው። ሐምራዊ ተጣጥባ ተመልሳ ክንፏ እንደተመታች እርግብ በስ ብላ ቀዳማዊ ጋር ልጥፍ አለች። "አመሰግናለሁ የኔ ፍቅር። ይሄን ክብር ስለሰጠሽኝ!"አለ ቀዳማዊ። ሐምራዊ ፈገግ ብላ "እኔ ነኝ የማመሰግነው። ለአንተ እንድሆን ስለተረዳኸኝ። አፈቅርሀለሁ ሕይወቴን ሙሉ"አለችና ከንፈሩን ትስምው ያዘች። ለረጅም ደቂቃ ሲሳሳሙ ከቆዩ በኋላ በድጋሚ ፍቅር ሰርተው ተቃቅፈው ተኙ። አመሻሽ ላይ ወይዘሮ ፊደላዊት ደወለች። በተደጋጋሚ ስትደውል እንዳታስብ በማለት ስልኩን አንስታ ቤት እንደማትመጣ ነገረቻት። ፊደላዊት እንደዛ ስትላት ገብቷታል። ቅር እያላትም ቢሆን እሺ አለች። "የኔ ፍቅር እነሱ እንዳያስቡ በእኔ ስልክ ደውልና ውጪ እንደምታድር ንገራቸው።"አለች ሐምራዊ ቀዳማዊ በሔዋን በጣም ስለተናደደ ላለማሳወቅ አመንትቶ ነበር ከእንደገና መናገር እንዳለበት ሲያስብ ስልኳን ተቀበለና ለሙሉሰው ደወለ። "ሔሎ ""ሔሎ ጋሼ ቀዳማዊ ነኝ" "አቤት ልጄ ደህና አመሸህ? ቆየህሳ ምነው?" "ደህና ነኝ ከከተማ ስለወጣሁ እዛው ነው የማድረው።ቤት እንደማልመጣ ላሳውቅህ ብዬ ነው"አለ ቀዳማዊ ፈራ ተባ እያለ "እሺ እንዳታመሽ ራስህን ጠብቅ ለእናትህ እነግራታለሁ "አለ "እሺ ጋሼ አመሰግናለሁ! ከፈለከኝ በዚህ ስልክ ብትደውልልኝ ታገኘኛለህ!"አለና ስልኩን ዘግቶ ለሐምራዊ ሰጣት። ቀዳማዊ የተከደኑ የሐምራዊ አይኖች ላይ እንደተከለ ነው። በስስት ይመለከታታል። እንቅልፍ ወስዷታል። አምላክ ለቀሪ ሕይወቱ በደስታ የሚኖርበትን የልብ ቁልፍ እንደሰጠው አመነ። እርሷ የምድር ሕይወቱን ገነት ለማድረግ ከሰማይ የተላከች መላዕክ እንደህነች አመነ። የምድር ገነት መግቢያ በሩ ሐምራዊ ድካምና ሕመም በአንድ ላይ ሆነው እንቅልፍ እንዲወስዷት አድርገዋል። እንደተኛች ከንፈሯን በስሱ ሳም አደረገና ብርድ ልብሱን በደንብ እስከ እግሯ ጥፍር ድረስ ሸፍኖ ትከሻውን አንተርሷት ተኛ። ሐምራዊ ሰመመን ከሚመስል እንቅልፏ ነቅታ አይኖቿን በቀስታ ስትገልጣቸው ቀዳማዊ ትኩር ብሎ እየተመለከታት ነበር። "እንዴ የኔ ፍቅር አልተኛህም እንዴ?"አለች። "አይ ተኝቻለሁ ቀድሜሽ ስለነቃሁ ነው እንጅ"አለ ቀዳማዊ በግራ እጁ በቀኝ አይኗ በኩል የተነሰነሰውን ፀጉር ወደ ኋላ እየመለሰ። ሐምራዊ አንገቱን ስማ ወደ እሱ ጠጋ አለችና ከእንደገና በእቅፉ ውስጥ ሆና ተኛች። ፀጉሮቿን እየነካካ ለሊት ሲያስባቸው የነበሩትን በርካታ ሀሳቦች አንድ በአንድ መገርመም ጀመረ። ቀዳማዊ ለሊቱን በሙሉ ሲያስብ የነበረው ስለ ሐምራዊ ኃላፊነት ነበር። ደስታዋን እንዴት ማስቀጠል እንዳለበት። በእርግጥ የመጀመሪያ ደስታዋ ከእርሱ ጋር መሆኗ ቢሆንም ነገር ግን ሕይወታየውን በተለዬ መልኩ ለማድረግና እሷን በምንም መልኩ ማሳዘን እና መከፋት እንደሌለበት ነው ያሰበው። በሌላኛው ሀሳቡ ደግሞ የሔዋን ሁኔታ አለ። ሔዋንን ማሳመን እንዳለበት አምኗል። አላምን ካለችው ግን ምርጫውን ለእሷ ለማሳወቅ እንደሚገደድ ወስኗል። " ይሄን ውሳኔ ሲወስን ታዲያ የክሀዲነት ስሜት ተሰማው። ግን ደግሞ በውለታቸው ታስሮ ሐምራዊን ሳይወስን ቢቀር ደስተኛ ሳይሆን እድሜ ልኩን እንደሚያዩት በዚህም እነሱ ሊቆጩ እንደሚችሉ አምኗል። ይሄን ሁሉ ሸክም ይዞ ነበር የሐምራዊን ፀጉሮች በስስት እየነካካ አቅፎ የነበረው። ተነስተው አንድ ላይ ሻወር ከወሰዱ በኋላ ቁርስ በልተው። "አንቺ ስለደከመሽ ማሽከርከር የለብሽም! ቀስ አድርጌ እኔ እየነዳሁት እንሄዳለን"አለና መንገድ ጀመሩ። በመጀመሪያ እሷን ቤቷ አድርሷት ወደ ቤቱ ለመመለስ ነው ያሰበው። የሐምራዊ ቤት ሲደርሱ ፊደላዊት ውጭ ላይ ተቀምጣ ፅሐይ እየሞቀች በዛውም የሆነ ትልቅ መፅሐፍ እያነበበች ነበር። ዘበኛው በሩን ከፍቶ ቀዳማዊ ፊት ለፊት ፊደላዊትን ሲያያት ደነገጠ። "አይዞህ አትጨናነቅ። ማታ አብረን እንደምናድር ስላወቀች ችግር የለውም"አለች ሐምራዊ የቀዳማዊን ድንጋጤ ተመልክታ። መኪናውን በትክክል ካቆመ በኋላ ወርደው ለፊደላዊት ሰላምታ ሰጥተው ሐምራዊን እቅፍ አድርጎ ይዟት ገባ። ፊደላዊት በደስታ ሁለቱን እየተመለከተች በአይኖቿ ሸኘቻቸው። "የኔ ፍቅር በጣም እንደማፈቅርሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ። ያሉትን ችግሮች በተቻለኝ መጠን በፍቅር ለመፍታት እሞክራለሁ። ካልሆነም መፍታት በሚኖርብኝ መንገድ እፈታለሁ።አንቺ እረፍት አድርጊ እደውልልሻለሁ።"አለና ግንባሯን ስሟት ሊወጣ ሲል "ቀዳ "አለች በተስረቅራቂ ድምጿ አይኖቿን እያስለመለመች "ወይዬ " "አፈቅርሀለሁ" "እኔም አፈቅርሻለሁ!" አለና ተመልሶ አቅፎ ስሟት ወጣ። ፊደላዊትን ላለማየት አንገቱን ደፍቶ ሊወጣ ሲል "ቀዳማዊ!" አለች አንገቱን እንደደፋ "አቤት "አለ ካሁን አሁን የሆነ የማያውቀው ቃል የሚያስፈራ የሚያስደነግጥ ነገር እየጠበቀ "አመሰግናለሁ ልጄ! የልጄን ደስታ መልሰህልኛል። ያለፉትን አመታት በምን ሁኔታ ውስጥ እንዳለፈች እኔና እግዚአብሔር ብቻ ነን የምናቀው። ይሄው በመጨረሻም ልጄን መልሰህልኛል"አለችና አቀፈችው። ቀዳማዊ የሆነ የተሸከመው ሸክም ሲወርድለት ታወቀው። "ምንም ምስጋና አያስፈልገኝም የራሴን ደስታ ነው የመለስኩት። እኔም በትዝታዋና በፍቅሯ ስሰቃይ ነበር የኖርኩት። ቢያንስ እሷስ እናቷ ከጎኗ ነበረች። እኔ ግን ብቻየን ያለ አፅናኚ ነበር ፍቅሯን ተሸክሜ የኖርኩት"አለ። "አሁን ሁለታችሁም ደስተኞች የምትሆኑበት ጊዜ ነው። የእናትህን አዎንታ ለማግኘት ሞክር እናትህ ጋስ ማውራት ያለብህን ተነጋገር። ፍቅር ያለ ወላጅ ይሁንታ ምንም ነው። ከሁለቱም ወገን ምርቃት ስታገኙ ነውና ሕይወታችሁ የተባረከ የሚሆነው በራሳችሁ ብቻ የምታቃኑት አይደለም። የወላጆች በረከትም አስፈላጊ ነውና እንደዛ አድርግ"አለች ፊደላዊት። ቀዳማዊ ምንም አይነት መልስ ሳይመልስላት ተሰናብቷት ከጊቢ ወጣ። ** "ልጄ አስከፋውህ እንዴ?"አለች ሔዋን......... @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፱~ ( 209 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 የሔዋንን ንግግር እያብሰለሰለ እያለ አሳንሱሩ ተከፈተ። ከአሳንሱሩ ወጥቶ ወደ ግራ ታጠፈና የመጀመሪያው በር ጋ አንኳኳ "ይግቡ የሚል "የሴት ድምፅ ሲሰማ ገባ። "ጤና ይስጥልኝ ይህ የአርክቴክት ሐምራዊ ሱራፌል ቢሮ ነው ምን እንርዳዎት"አለች ፅሐፊዋ። እስከዛሬ ይህ የአርክቴክት ሐምራዊ ቢሮ ነው ምናምን አትልም ዝም ብላ ተቀብላ ነበር የምታስተናግደው። ቀዳማዊ ለመልካም አቀባበሏ ፈገግታውን በመጠኑ ከሰጣት በኋላ የባለ ጉዳዮች መቀመጫ ወንበር ላይ ተቀምጦ። "አርክቴክቷ ብዙ ቀጠሮ ይኖርባት ይሆን? ማለቴ የድሮ ጓደኛሞች ነበርን። እስኪ ያላትን ፕሮግራም ንገሪኝ"አለ። "ይቅርታ ጌታዬ ያላትን ፕሮግራም መናገር አልችልም ግን አስቸኳይ ከሆነ በስልክ ላናግራትና ላስገባዎት" "አይ ተይው በቃ ይቺን ወረቀት አድርሺልኝ።"ብሎ የሆነች ወረቀት ሰጥቷት ወጣ። "ከማን ነው?" "አላውቀውም ላስገባህ ብለውም አይ ችግር የለውም ዝም ብለሽ ይህን ስጫት የስራ ጊዜዋን መውሰድ አልፈልግም። ነው ያለኝ" "እሺ ገብቶኛል አመሰግናለሁ "ብላ ወረቀቱን ቀስ አድርጋ ገለጠችው። " የተለዬ ፀደይ ወሩ የዝናብ ፅሐይ ቱግ ብላ የወጣችበት ነበር። አዲስ አበቦች ፈንድቀዋል ያያቸው አልነበረም። ንግስቷ ግን በፍቅርና በደስታ ተመለከተቻቸው። የእጣኑ ጭስ ግሩም ነው ቅዳሴውም በጀሮ ልክ የተመጠነ ይመስል እንደ ንጋት ወፎች ድምፅ በጆሮ እየተንቆረቆረ የሐሴትን ባህር ይሞላል።" የሚል ፅሁፍ ነው። ሐምራዊ ከወንበሯ ተነሳችና ለፅሐፊዋ "ማንም ሰው እንዳይገባ ስራ ላይ ነኝ። እሺ የፈለግሽውን ምክንያት ልትሰጫቸው ትችያለሽ "አለችና ተመልሳ ወደ ቢሮዋ ገባችና ወረቀቷን በደንብ ታነብ ጀመር "የተለዬ ፀደይ፣ አበቦች ፈንድቀዋል፣የዝናብ ፅሐይ ቱግ ብላ የወጣችበት ......"እያንዳንዱን ቃሉን እያስገባች እየነጠለች ከእንደገና እያዋኻደች ገጣጥማ እያነበበች እንቆቅልሹን ልትፈታ ጣረች። በርካታ ወረቀቶችን ተጠቀመች። ፍለጋዋን ቀጥላለች "እንደ ንጋት ወፎች ድምፅ በጆሮ እየተንቆረቆረ የሐሴትን ባህር ይሞላል። አዲስ አበቦች ፈንድቀዋል። ያያቸው ግን አልነበረም።" ቃላቱቹን እየለያየች መበርበሯን ቀጥላለች። "ወፎች የሚኖሩበት ከእነሱ እኩል የሚሰማ የንጋት ማህሌት ቅዳሴ እሺ ይሄ ደግሞ ' አዲስ አበቦች ፈንድቀዋል' ' አዲስ አበባ ናቸው። ከዚህ በፊት ወጥተው አያውቁም። እነዚህን አዲስ አበቦች ማንም ልብ ያላቸው አልነበረም ከንግስቷ በቀር። የተለዬ ፀደይ ወሩ የዝናብ ፅሐይ ቱግ ብላ የወጣችበት ነበር። የዝናብ ፅሐይ የሚወጣበት ወር አገኘሁት!!!!! አገኘሁት መስከረም አዲስ አበቦች የወጡበት አደዮች የፈነደቁበት ንግስቷ አዲስ አበባን በአዲስ አበቦቹ የሰየመችበት። እንጦጦ ሆና ቁልቁል ስትመለከት አዲስ አበባ ላይ አዲስ አበቦች ፈንድቀው ነበር። እርሷም አዲስ አበባ አየሁ ማለት የእነዛን አበቦች መገኛ አዲስ አበባ ስትል አወጣችላት። ሐምራዊ በደስታ እየተፍለቀለቀች ከቢሮዋ ወጣችና በፍጥነት መኪናዋን አስነስታ ቀጥታ የፍላሚንጎን መስመር ይዛ በመስቀል አደባባይ ስትደርስ ወደ ቀኝ በመታጠፍ በፒያሳ ቀጥ ብላ በመውጣት ወደ እንጦጦ የሚያደርሳትን የአዲሱ ገበያ መንገድን ያዘች። ቀዳማዊ እንጦጦ ኪዳነምህረት አጠገብ ትንሽ ገባ ብሎ የባህርዛፍ ስር ካለ ድንጋይ ተቀምጦ የአዲስ አበባን መልክና ሁናቴ በአርምሞ ይመለከታል። አልፎ አልፎ ከፍ ብለው የሚታዩት ህንፃዎቿ የተለዬ ውበት አጎናፅፏታል። ጥቅጥቁ ጫካ በቀንም ወፎቹ ይንጫጫሉ። የማለዳው እጣን ጭስ ወደ አፍንጫው በተደጋጋሚ እየመጣ በሀሴት ሲስብ ቆዬ። የሔዋንን ንግግር ከእንደገና አብሰለሰለው። "ቆይ እኔ የማላቀው ነገር አለ? እንዴት ይሄን ያህል ክሪቲሳይዝ ታደርገኛለች? አለች" አለና ራሱን ጠየቀ። በጭራሽ የሚያስባቸው ሀሳቦች በሙሉ ስሜት አልሰጥ አሉት! "ወይስ ከነ ትዮቢስታ ጋር አውርታ ነው?" የሚል ሌላ ጥርጣሬም በልቡ አሰበ። * "ልጄ ግን ከቀዳማዊ ጋር እንዴት ናችሁ?"አለች ትዮቢስታ "ምንም አይደለንም"ደሐብ ቆፍጠን ብላ መለሰች። "ምነው ምን ተፈጠረ ደግሞ? ደህና አልነበራችሁ?" "አሁን ደህና አይደለንም እናቴ"አለች ደሐብ ኮስተር ብላ "እሺ ልጄ እንደ ፍላጎትሽ እኔ ብቻ የምፈልገው የአንቺን ደስታ እና ወግ ማዕረግሽን ነው"አለች "ይገባኛል እናቴ ግን የቀዳማዊ ድርጊት በጣም የሚያበሳጭ ና የሚያናድድ ነው። እንደዚህ ብጥብጥ እንዳደረገኝ ብጥብጥ አደርገዋለሁ ቆይ ብቻ "አለች በእልህ። "ለምን ዕልህሽን በመልካም ነገር አትለውጭውም። እንደዛ አድርገሽ ለምን የጠበቀውን ነገር አታበላሽበትም። ከአንቺ መጥፎ አፀፋ ሲጠብቅ ጥሩ ነገር ስትሰጪው በጣም ነው የሚናደደው!"አለች ትዮቢስታ "ያ ደደብ ይሄ አይገባውም ተይውማ ቆይ ምን እንደማደርግ እኔ ነኝ የማውቀው። ተንበርክክኮ ይለምነኛል ያን ጊዜ የማደርገውን እኔ አውቃለሁ"አለች ደሐብ ** "የኔ ፍቅር ፈልጌ ፈልጌ አገኘውህ"አለችና ሐምራዊ በጀርባው በኩል ሆና አቀፈችውና አንገቱን ሳመችው። ዞር ብሎ ወትሮስ ላታገኝኝ ነበር?"አለና ፈገግ ብሎ ዘወር ሲል ከንፈሩን ደግሞ ሳም አደረገችው።" እንዴት ነው ንግስቷ እዚህ ሁና ነበር አዲስ አበቦቹን ያየቻቸው? እዚህ ሆና ነበር ስም ያወጣችላት ለአዲስአበባችን?"አለች ሐምራዊ አንገቱ ስር እየተወሸቀች "አዎ"አለ ቀዳማዊ በግንባሯ በኩል ሳይያዙ የቀሩ የራስ ፀጉሮቿን እየሳመ። "እና ምንን መሰረቴ በማድረግ ነው እዚህ የጠራኸኝ?" "ታውቂያለሽ እዛ ሰው በሰው ይጋፋል። ተፈጥሮን ደግሞ በውክቢያ መሀል አታይም ብቻሽን ነው። ለምሳሌ የምትወጅውን ልጅ በሰው መሀል የምትጠግቢውን ያህል አታይውም። ምክንያቱም በብዙ ሀሳቦች ትጠመጃለች። ሌሎች እንዳያዩብኝ ብለሽም ትቀኒያለሽ። እንዲህ አይነት ቦታ ግን የምትወጂውን ሰው በነፃነት ለመመልከት ይረዳል። ከአንዳች መጥፎ ስሜትም ትወጭበታለሽ"አለና ከንፈሯን በስሱ ሳም አደረጋት። "ፍቅር ከዚህ እንውጣና የሆነ ቦታ ይዤህ ልሂድ!"አለች "አይ እርግቤ እዚህ ምቾት ተሰምቶኛል። ልክ ምሽት ላይ እንዳለው የአየር ሁኔታ ነው ያለው። በዛ ላይ አንቺ አለሽ"አለና አቀፋት። "ግን ከእትዬ ጋር በምንድን ነው የተጣላችሁት?" "ያን ጊዜ ነዋ ከአንተ ጋር የተጣላን እለት በዛ ላይ የምርቃትህ ሴሪሞኒ ላይም አልመጣሁም። በዛ ነው እንጅ ከዛ በኋላ ላለፉት ዘጠኝ አመታት በምንም ነገር አልተገናኘንም!"አለች። ቀዳማዊ ዝም ብሎ ያስብ ጀመር። "በቃ ብዙ አትጨናነቅ የኔ ፍቅር እግሯ ስር ተንበርክኬ ይቅርታ እጠይቃታለሁ። ምንም ችግር የለም።"አለች ሐምራዊ "አይ እኔ የማስተካክለው ነገር ይኖራል። ቀላል ነው" አለና ሳም አደረጋት። "እሺ የኔ ፍቅር። በነገርህ ላይ ዛሬ ስራ የለኝም አብሬህ ለመዋል ነው የመጣሁት!"አለች ሐምራዊ ቀዳማዊን ሙሉ ለሙሉ ከሀሳብ ነፃ ለማድረግ " በጣም ደስ ይላል "አለ ስለ ብዙ ነገር እያነሱ እየተጫወቱ እየተላፉ ከቆዩ በኋላ ሁለታቸውንም ሲርባቸው ወርደው ወደ አዲሱ ገበያ አካባቢ በሚገኝ ሰልማ ሆቴል ጎራ ብለው ምሳ አዘው እየተጎራረሱ በሉ። "የሆቴሉን አስተናጋጅ ጠርቶ አልጋ እንዳለ እና እንደሌለ ጠይቆ አልጋ እንዲይዝለት ጠየቀው። ክፍያውን ፈፅሞ የሩሙን ቁልፍ አምጥቶ ሰጠው። ወይን ሩማቸው ድረስ እንዲያመጣላቸው አስተናጋጁን አዘው ወደ ክፍላቸው አመሩ። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፰~ ( 208 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 "እየውልህ ልጄ አንተ ገና ምኑንም አታውቅም። የዋህ ነህ። ማን እንደሚፈልግህና ማንን እንደምትፈልግ እንጅ ማን እንደሚያስፈልግህ አታውቅም። ወጣትነት በጣም ከበዱ ጊዜ ነው። የምርጫዎቻችንን ብዛት እንጅ የምርጫዎቹን ምን ምን መሆን አይስተዋልም። ብዙ ልጆች የምታፈቅራቸውን ወይም ውበቷን አይተው ገብተው ለዘላለም እየተሰቃዩ የሚኖሩ አሉ። እና ምን ልልህ ፈልጌ ነው ይሄን የምነግርህ። በውሳኔህ እኔ ደስተኛ አይደለሁም። ከሐምራዊ ይልቅ ለአንተ ደሐብ ነች የምትሆንህ! እርግጥ ሊሆን ይችላል። የተወሰነ ባህሪዋ ጥሩ ላይሆንልህ ይችላል ግን ያን ባህሪዋን እንድትተው አድርገህ አንተ በምትፈልገው ሰውነትና ባህሪ ልክ መስራት ትችላለህ። ግዴለህም ሐምራዊ አትሆንህም"ብላ ደምድማ ስትናገር። ቀዳማዊ መላ ሰውነቱ ተለዋወጠ። ፊቱ በአንድ ጊዜ የጨለማ ብርኖስን መሰለ። አፉ ተንቀጠቀጠ። ምንም ነገር ለማለት አንደበቱ ተቆለፈ። ሔዋን ሁኔታውንና የፊቱን መለዋወጥ ስትመለከት በድንጋጤና በፍርሃት ተርበተበተች። ከልጅነቱ ጀምሮ የምታውቀው ቀዳማዊ አልመስልሽ አላት። ግን ሁኔታው እንዲህ ቢሆንም ስሜቱን በግልፅ መናገር ተሳነው። እንደምንም የቀዳማዊን ሁኔታ ተቋቁማ "የምትለኝ ነገር አለ? እኔ ለአንተ ይሆንሀል ብዬ ያሰብኩትን ነው የነገርኩህ። አንተ ደግሞ የተሰማህን በግልፅ ንገረኝ። ለምን እንደዚህ ልትሆን ቻልክ?" ቀዳማዊ ለማናገር አስቦ ከእንደገና ተወው። "ነገር በሆድ አይያዝም ልጄ አውጣው እኔ ዙሮ የአንተ ፍላጎት ፍላጎት ነው። በፍላጎትህ ሳይሆን በውሳኔህ ነው ጣልቃ የምገባው።" አለች "ያው እኮ ነው። እንደዚህ ከሆነ ታዲያ ለምን እንዳወራሽ ትጠይቂኛለሽ?"አለ ቀዳማዊ። "ቢያንስ የልብህን እውነት ከነገርከኝ ልረዳህ እችል ይሆናል።"እትዬ በርግጥ እኔ ያኔ ያህል የሚያስብልኝን አላውቅ ይሆናል ግን በአንቺ አዬን ብቻ ሲታይ ነው እሱም። እኔ የሚያስብልኝንና የሚያሳስበኝን አውቃለሁ።በ ሐምራዊና በደሐብ ያለው ልዩነት የተራራ ያህል ነው። ሐምራዊ ሲበዛ ደግ ባለፈ ድርጊቷ የምትፀፀት ያን ስህተቷን ላለመድገም የምትምል ሳበዛ ተፀፃች የሆነች ልጅ ናት። ለስህተቷ ደግሞ ያለምንም ማመንታት ዋጋ የምትቀበል ደግ ነች። ደሐብ ደግሞ እርሷ ያላት ነገር ሌሎች ጋር አለ ብላ የማታምን እብሪተኛ፣ ጥፋቷን አምና ደግማ ላለመስራት የምትጥር ሳትሆን ጥፋት እንዳልሰራች አድርጋ መደባበቅ የምትወድ ሰዎችን ከራሷ በታች እንጅ ከእሷ በላይ አድርጋ መቀበል የማትወድ እጅግ ሲበዛ ተንኮለኛ ነች። እና እነዚህን ሁለት ሴቶች ፊት ቁሜ አልመርጥም ምክንያቱም አንድን ሰው መምረጥ አይቻልም። ደሐብ ለእኔ በጭራሽ ምርጫዬ ውስጥ የምትገባ ሴት አይደለችም።"አለ ቀዳማዊ " እንዴት የአንተን ማንነት ባልተቀበለች ሴት እንዲህ እርግጠኛ ትሆናለህ?" "ማንነቴን ስላልተቀበለችው ሳይሆን ያኮረፈችው። ማንነቴን ስላልነገርኳት ነው። ይህ ደግሞ የኔ ነው ብለሽ የምታስቢው ሰው የሆነ ያልነገርሽው ነገር እንዳለ ሲገባው ያኮርፋል። እሷም ጋር እንደዛ ነው የሆነው። በወቅቱ ጓደኛዬ እሷ ነበረች። አዎ ስላልነገርኳት ከፍቷታል ግን ደግሞ ስሜቷን በግልፅ ነው ያሳየችው። አላስመሰለችም!" "ምን እያልክ ነው ቀዳማዊ ደሐብ እያስመሰለች ነበር እያልክ ነው?" "አዎ በደንብ። በዛን ጊዜ ከቴሌቭዥኝ ቃለመጠይቄ በኋላ ከሐምራዊ ጋር ስንጣላ ደሐብ ደግሞ ያን አጋጣሚ እንደመግቢያ ቀዳዳ ተጠቀመችው። ከሐምራዊ ለየት ብላ በእኔ መታየት ፈለገች። ይህንን ደግሞ እኔ እንዳምን የምርቃቴ መጣች። ምክንያቱም ሐምራዊ እንደማትመጣ ስለምታውቅ። አዎ ልክ ነበረች። እኔም ሐምራዊ አለመምጣቷን ሳይ ደሐብን አመሰገንኩ። ግን እውነታው ያ አይደለም። እውነታው አንዷ ለዘጠኝ አመት ወንድ እየቀያየረች ስትጠብቅ ሌላኛዋ ደግሞ የልቧን ማህተብ በፍቅር አስራ በተስፋ የምትጠብቅ ናት። ስለ ደሐብ በጣም በርካታ ነገሮችን ልነግርሽ እችላለሁ አለና በትውስታ የሆነ ነገር አስታወሰ። ትውስታ፦ "እየውልህ እኔ ምንም ነገር አስቤ አይደለም። ግን እውነታውን ማወቅ አለብህ ብዬ ስላሰብኩ ነው።ደሐብን በጣም ነው የምወዳት ነገር ግን ደግሞ ያን ያህል እሞትላታለሁ ምናምን ማለቴ አይደለም። ይሄን ስልህ ደግሞ ጭራሽ ምንም አይነት ስሜት እንደሌለኝ አድርገህ አታስበኝ" "እሺ አሁን መናገር ምትፈልገውን ተናገር ይሄን ሁሉ ዙሪያ ጥምጥም አትሂድ።"አለ ቀዳማዊ "እየውልህ ደሐብ ለአንተ የምትሆን ሴት አይደለችም። በጣም ሲበዛ ከዚህም ከዚያም የምትል አይነት ልጅ ናት። አለ አይደል ቁጥብ አይደለችም። እንደውም ደውዬ ለምን አላስደምጥህም አለና ለደሐብ ደወለላት "አቤት ኤፋ" አለች ደሐብ "የኔ ፍቅር ዛሬ በጣም ናፍቀሽኛል።" "ዛሬ ብቻ ነው የናፈኩህ? ሁሌም አይደል እንዴ የምናፍቅህ" የዛሬው ግን ይለያል" "በል እሺ እኔም ናፍቀኸኛል። ዛሬ እንደውም ፈታ ማለት እፈልጋለሁ የተለመደችው ቦታችን ምሽት ላይ እንገናኝና እየተጫወትን እናድራለን" "እሺ የኔ ፍቅር አመሰግናለሁ" "ሄይ አትሟዘዝ ፍቅርህን የምትፈልግበት ሂድና ፈልግ እኔና አንተ ላይ ፍቅር ብሎ ነገር የለም ዛሬን መደሰት ብቻ!"አለችና ስልኩን ዘጋችው።"እኔና እሷ እንዲህ ነን እንደተናገረችው ነው። በእኔና ብሷ መሀል ዛሬ እንጅ ነገ የለም። እሷም ስትፈልግ እኔም ስፈልግ እንገናኛለን አበቃ"አለና ኤፍሬም ተነስቶ ሄደ። ከትውስታ መልስ "አሁንስ ደሐብ ምን አይነት ሴት እንደሆነች ተረዳሽ እትዬ? እኔ ይቺን ሴት አግባ እሷ ጋር ሁን ከምትይኝ እድሜ ልኬን ቆሜ ብቀር ይሻላል። ምክንያቱም እናንተን ላለማስቀየም የሕይወት ልክ ደስታየን ላጣት እችላለሁ እንጅ በፍፁም ደሐብን አላገባም" አለ ቀዳማዊ ኮስተር ብሎ "እየውልህ አሁን አንተ በደሐብ በኩል የሚመጣን ማንኛውንም ነጌቴቭ ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነህ። በአንፃሩ ደግሞ ለሐምራዊ ልብህን ስለከፈትክ ስለ ሐምራዊ ምንም ነገር ብትባል አታምንም አትቀበልም። ይሄ ማንኛውም ሰው የሚያደርገው የጥላቻውን መግለጫና የፍቅሩን መቀበያ እምነቱ ነው"አለች ሔዋን። ቀዳማዊ አይኖቹን ከደን አድርጎ ራሱን አወዛወዘና "እሺ በቃ ችግር የለውም። አንቺ የኔን ደስታ ነው የምትፈልጊው?" "አዎ ልጄ ደስታህን ስለምፈልግ እኮ ነው እንዲህ የማስገድድህ። ደስተኛ የምታደርግህ ደሐብ ነች ብዬ የምከራከርህ"አለች። "እሺ በጣም አመሰግናለሁ እትዬ!"አለና ሊወጣ ሲል። "ምንድነው መኪናውን አትይዝም እንዴ?"አለች ዝም ብሎ በእግሩ ሲወጣ አይታ "አይ በእግሬ ነው መንቀሳቀስ የፈለኩት አስፈላጊ ከሆነ ኮንትራት ታክሲ እይዛለሁ"አለና ወጣ። ትንሽ በእግሩ እንደሄደ ኮንትራት ታክሲ ጠራና ገባ "ወደየት ልንዳ ጌታዬ "አለ ራሰ በራው የታክሲ ሾፌር "ወደ ቦሌ"አለ ቀዳማዊ። የአራት ኪሎን መስመር ይዞ በብሔራዊ ቤተመንግስት ታጠፈና በካሳንቺስ ወርዶ በአትላስ አድርጎ ወደ ቦሌ ይዞት ሄደ። ከአንድ ትልቅ ህንፃ ስር ትቶት ታክሲው ከአካባቢው ተሰወረ። ቀዳማዊ ወደ ህንፃው ከመግባቱ በፊት ህንፃውን ከቆመበት ቦታ እስከ መጨረሻው ፍሎር ድረስ ከተመለከተ በኋላ ገብቶ ወደ ሁለተኛ ፎቅ የሚያደርሰውን አሳንሱር ገብቶ ተጫነ። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፯~ ( 207 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 በሳቅ እየተፍለቀለቀች ቤት ገባች። ፊደላዊት እያየቻት ግራ ተጋባች።አንድ ቀን ባላት የተስፋ ዓለም ቅዥት እንዲህ ሆና የምትመጣ ስለሚመስላት ትፈራለች። አንድ ቀን ከራሷ ማንነት ውጪ ሆና የምትመጣ እየመሰላት ለልጇ አጥብቃ ታዝናለች። "እማ የኔ እናት የኔ ሁሉ ነገር መካሪዬ ጠባቂያ "አለች ሐምራዊ። "ምን ሆነሽ ነው የኔ ልጅ ጠጥተሽ ባልሆነ?!"አለች ፊደላዋት "እኔ የአንቺ ልጅ እማ? ብጠጣም ምንም አልሆንም!"አለች እየሳቀች። ትኩር ብላ ስትመለከታት የስካር ሳይሆን ፍፁም የሆነ የደስታ ስሜት ነው። ፍራቻዋ እየቀነሰ "እሺ የኔ ውድ ልጅ ደስታሽን ነው የምፈልገው።እስኪ ቁጭ በይና የተፈጠረውን ንገሪኝ" አለች ፊደላዊት።ሐምራዊ ከእናቷ ጎን ተቀምጣ የተፈጠረውን በሙሉ አንድ በአንድ ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ነገረቻት። ፊደላዊት በቃላት ከሚገለፅ በላይ ደስታዋን ከገለፀችላት በኋላ "እውነትሽን ነበር ለካ! ሰው የሚያምነው ልብን እንጅ ሌላ መሆን የለበትም። ልጄ በሕይወቴ ያልተማርኩትን ፅናት አንቺ አስተምረሽኛል።ለአንቺ ደስ ብሎኛል። እንኳን የፍቅርሽን ፍሬ ለመቅመስ አበቃሽ። ረጅም አመት የደስታ ጊዜ እንድታሳልፊ እመኛለሁ"አለች። "እማ ለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ! አንቺ ነሽ ከእኔም በላይ ስትሰቃይ የነበረው። ከእኔ እኩል ተከፍተሻል አዝነሻል።አንቺ እናቴ ብቻ አይደለሽም የልብ ጓደኛየም ነሽ"አለችና ጉንጯን ስማት ደረቷ ላይ ትኝት አለች። ** " እሱ እስከወዲያኛው ሄዷል። የኔ መሆን አይችልም።ግን የቱ ጋ ነው ስህተት የፈፀምኩት?" ብላ አይኖቿን የቤቷ ጣራ ላይ ሰክታ ማሰብ ጀመረች። የትኛውም የትዝታ ጀልባዋ ስህተት የፈፀመችበት ትውስታ ላይ ሊመልሳት አልቻለም። ዝም ብላ ኮርኒሱን እየተመለከተች እያለ ሳታስበው እንባዋ በጉንጮቿ እየፈሰሱ በአገጯ ወርደው አንገቷ ስር እንደ ምንጭ ውሃ አቁረው ሲቀዘቅዛት ነበር ከሀሳብ አለሟ የነቃችው።እንባዋን ጠራርጋ ከእንደገና ምርር ብላ አለቀሰች። "ቆይ ለምን እኔን? የፈለገ መጥፎ ብሆን ለአንተ መጥፎ ነኝ። እኔ እኮ እወድሀለሁ" ቢያልፍም ለራሷ የነገረችው እውነት ነበር። ፍቅር በምክንያት የሚፀነስ ነፍስ እንደሆነ ብታምንም ነገር ግን እሷ ይሄን እውነት ለመጋፈጥ የፈለገች አትመስልም። ምንም እንኳ ብትወደውም እብሪተኝነት የልቧን መሻት ከልሎት ምንም አለማድረጓና አሳልፋ መስጠቷ እንደ እግር እሳት ሆነባት። ቀዳማዊ የተዘጋ ልቧን ሁሌም በተለዬ ስሜት የሚያንኳኳ ከህልሟ የሚያናጥባት ከማስመሰል ሕይወቷ የሚያስወጣት ቅዠቷ መሆኑን አምናለች። ነገር ግን ደግሞ እንዳረፈደች ገብቷታል። ደሐብ የምታደርገው ሁሉ ተደበላልቆባት ምንም ነገር ላይ ሳታርፍ እንቅልፍ ወሰዳት። *** ቀዳማዊ የሐምራዊን የፍቅር አይኖች እያስታወሰ፣ አስተያየቷ በስስት ስትመለከተው የአይኖቿ ሽፋሽፍት በፍርሀትና በፍቅር ከአይኖቿ ሊነቀሉ ሲታገሉ የተመለከተውን ትዕይንት ከእንደገና እየደገመ። የልቡን ምት እያዳመጠ የዘላለም ደስታውን እያሰበ ስለተኛ ነበር እንቅልፍ የወሰደው። አምሽቶ ቢተኛም ነገር ግን በጠዋት ተነስቷል። በሕይወታችን ቀድመን ካልነቃን መወሰን እንቸገራለን። ለመወሰን እውናዊ የሆነ ማንነት ያስፈልገናል። ካልነቃን የማለዳ ወፍቾ ዝማሬን አንሰማም። ካልነቃን የሕይወት ዥዋዥዌ ውስጥ ሆነን በመኖርና ባለመኖር መካከል ያለ ማንነታችንን ከቅዠት ጋር እናመሳስለዋለን። ካልነቃን ከተስፋ ጉልላታችን ልንቆም አንችልም።ካልነቃን የነገ ተስፋችንን ልናልም ልናስብ አንችልም። ቀዳማዊ እየተንጠራራ በእርጋታ አልጋው ላይ እንዳለ ከወገብ በላይ ራቁቱን ሆኖ እጆቹን በቀስታ እያፍታታ ከቆየ በኋላ ከአልጋው ተነሳና ቁምሳጥኑን ከፍቶ የሚለብሰውን ልብስ ይመርጥ ጀመር። በዚህ ጊዜ ሔመን ወደ ክፍሉ ስትገባ ቀዳማዊ ድንግጥ አለ። ሔመንም በፓንት ስታየው እንደማፈር ብላ ፊቷን አዞረችና ለቁርስ አትመጣም እንዴ?"አለች ካለወትሮው በዚህ ስዐት የቀን ልብሱን ለመልበስ ሲመርጥ ደንግጣ። ምክንያቱም ቀዳማዊ ጠዋት ተነስቶ ቱታውን ለብሶ ቁርስ አብሮ ከበላ በኋላ ነው የቀን ልብሱን ለብሶ ስለሆነ የሚወጣው ። "እበላለሁ እንጅ ምን አይነት ጥያቄ ነው ደግሞ ይሄ ሔሚ?"አለ "ምን ላድርግ ያለ ወትሮህ ልብስ ስትለብስ ጊዜ ነዋ!"አለች ሔመን አሁንም ፊቷን እንዳዞረች። "ኧረ ተሳስተሻል ሔሚዬ መጣሁ"አለ። ሔዋን ከወትሮው በተለዬ መልኩ ፊቷን ለስለስ አድርጋ ማዕዱ ጋር ተሰይማለች። ሙሉሰው ምንም አልጣመውም።ሁኔታዋን ዝም ብሎ ይከታተላል። ቀዳማዊ አንድ ጉርሻ ጎርሶ ቀና ሲል ከሔዋን ጋር ተያዩ።በዚህ ጊዜ አይኖቹን ከእርሷ ሳይነቅል ቀስ አድርጎ እያኘከ ከተመለከታት በኋላ የምግቡን ሳህን ጠረንጴዛው ላይ አስቀመጠው። የሔዋን ሁኔታ ቀዳማዊን ምቾት ስለነሳው አፉ ላይ ያስገባውን ምግብ መዋጥ ተሳነው። ዝም ብሎ እያኘከ ሁላቸውንም ግራ ቀኝ ይመለከት ያዘ። ማዕዱ ተነስቶ ሁሉም ወደየ ውሎው ሊሄድ ሽር ጉድ ሲል ቀዳማዊ ቀድሞ ተዘጋጅቶ ስለነበር በረንዳ ላይ ከተደረደሩት ጫማዎቹ አንደኛውን አንስቶ ቁጭ ብሎ እየለበሰ ሳለ "ወደ የት ልትሄድ ነው?" አለች ሔዋን። እስካሁን ሲፈራ ሲቸር የነበረው ይሄን ጥያቄ እንዳትጠይቀው ነበር። "ብዙ የምጨርሳቸው ጉዳዮች አሉ።የማገኘው ሰውም አለ"አለ ከመጀመሪያው ውሸት ቀጥሎ እውነቱን እየተናገረ። "ቆይ ትንሽ መነጋገር አለብን። ሁለታችን ማውራት ያለብን ጉዳይ አለ"አለች። ቀዳማዊ ይበልጥ ይፈራት ጀመር **** "ቁርስሽ እንዲህ ይጣፍጣል? ለነገሩ የኔ ልጅ እኮ ጣፋጭ ነሽ። በሁሉም ግንባር ስትሰለፊ በቃ በድል ነው ምትወጪው"አለ ሱራፌል ፈገግታዋን እየለገሳት "አመሰግናለሁ አባዬ። እንዲህ ከወደድከውማ ሁሌም ነው የምሰራልህ" " እንዴ በደስታ ነዋ።በእነዚህ እጆችሽ የተሰራ ምንም ነገር ይጣፍጣል። በዚህ እርግጠኛ ነኝ እኔም ደስ ብሎኝ እያጣጣምኩ እንዳያልቅብኝ ነው ቀስ ብዬ የምበላው"አለና ግንባሯን ሳማት። "እውይ የኔ አባት ማድነቅ ስትችልበት እኮ"አለች። ፊደላዊት ይሄን ሁሉ ትዕይንት በእፎይታ ሆና ትመለከታለች። "እስኪ ግን ስለ ሰውዬሽ የሆነ ነገር በይን"አለ ሱራፌል በመጨረሻ። "አባዬ ደግሞ"ብላ አፈረች። "እሺ እንዳልሽ በቃ። እኔ ብቻ ወድጄዋለሁ። ይሄው በመጀመሪያው እንዲህ አይነት ቁርስ እንድበላ አድርጎኛል። ስለዚህ ውለታው አለብኝ። ከዚህ በኋላ አንቺ እንኳ ችላ ብትይው እኔ እንከባከበዋለሁ"አለና ሳቀ። "ልጄን አታሳፍርብኝ"አለች ፊደላዊት። "ምን እሷ ናት እንጅ እያሳፈረችኝ ያለችው እኔማ በምን አቅሜ"እያለ አንድ አንድ እየተባባሉ እየተጨዋወቱ።ቁርሳቸውን ከበሉ በኋላ። ሱራፌል "እጅሽ ይባረክ የኔ ልዕልት"አለና ግንባሯን ስሞ የሚስቱን ጉንጭ ስሞ ወጣ። ሐምራ እጇን ታጥባ ልብሷን ቀየረችና ወደ ስራ ወጣች። "በይ የኔ እንቁ የተቀደሰ ቀን ይሁንልሽ። በሳቅና በጨዋታ የጀመርሽው ቀን ደስ የሚልና ብሩህ ይሁንልሽ"አለችና ፊደላዊት በስስትና በፍቅር እየተመለከተች ሸኘቻት። @amba88 @ken_leboch

" ኤሴቅ " ክፍል ~፪፻፮~ ( 206 ) በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888 "በሰላም ይሆን ጥፍት ብሎ የዋለው?"አለች ሔዋን በቀዳማዊ ጠፍቶ መዋል ሀሳብ እየገባት። "ምን ይሆናል ብለሽ ነው እማዬ ያው የትምህርት ቤት ጓደኞቹን አግኝቶ እየተጫወተ ይሆናል"አለች ሔመን። "እስኪ ስልኬን አቀብይኝ ሔመኔ "ብላ ስልኳን ተቀበለችና ደወለች። ስልኩ አይነሳም ከእንደገና ደግማ ስትደውል "አቤት እትዬ ሔዋን!"አለች ደሐብ። "ልጄ ደህና ዋልሽ?" "ደህና እግዚአብሔር ሰላም ነሽ አንቺ?" "ደህና ነኝ ልጄ ቀዳማዊ እኮ ሙሉቀን ሳይመጣ ሲውል ጊዜ ከአንቺ ጋር ከሆነ እንድታገናኝኝ ብዬ ነበር"አለች ሔዋን። "እኔ ጋ አይደለም እትዬ ሔዋን!" "ጭራሽ አንቺ ጋር አልተገናኛችሁም?" "አዎ እኔ ጋር እኮ አንገናኝም"አለች ደሐብ በንዴት ከንፈሯን እየነከሰች። "እሺ ይቅርታ ልጄ በቃ መልሼ እደውልልሻለሁ ከአንቺ ጋር መስሎኝ ስለነበር ነው"ብላ ስልኩን ዘግታ ለሙሉሰው ደወለችለት። "አቤት የኔ ሔዋን"አለ ሙሉሰው "ቀዳማዊ ከአንተ ጋር ነው?"አለች " ኧረ አይደለም ምነው?" ድንግጥ ብሎ ጠየቃት "እስከ አሁን አልመጣም። ጠዋት እንደወጣ እኮ ነው"አለች ሔዋን "ቆይ እስኪ መልሼ እደውልልሻለሁ "አለና ሙሉሰው ለዮፍታሔ ደወለለት። ዮፍታሔ የሙሉሰውን መደወል ሲመለከት በፍጥነት አነሳውና "መቼም ስለ ልጅህ ልትጠይቀኝ ነው አደዋወልህ"አለ። "አዎ ሔዋን ደንግጣ ስትደውልልኝ ጊዜ ነው ለአኔተ የደወልኩት" "አይ ደህና ነው አይዟችሁ አንዲት ስራ እየሰራልኝ ስለሆነ ነው ይመጣል"አለ። "እሺ በል በቶሎ ላከው እናቱ ትቆጣለች።እናቱ ዛሬም እንደ ልጅ ነው የምታየው"አለ ሙሉሰው " እሺ እሺ ይቅርታ በልልኝ"አለ ዮፍታሔ *** አስተናጋጁ ሐምራዊ ሳታየው ቀዳማዊን በጥቅሻ ጠራው "ሐምራዬ መጣሁ ሽንት ቤት ደርሼ"አላትና አስተናጋጁን ተከትሎ ሄደ። አስተናጋጁም ስልኩን ሰጠው "ጋሽ ዮፍታሔ"አለ ቀዳማዊ "እንዴት ዋላችሁ ልጆች "አለ ዮፍታሔ "ደህና ነን ጋሽ ዮፍታሔ" "ጥሩ አባትህ ደውሎልኝ ነበር። ሲመስለኝ እናትህ ጠፍተህ በመዋልህ ሳትጨነቅ አልቀረችም እና አንድ መላ እንድትዘይድ ብዬ ነው"አለ ዮፍታሔ "እሺ ጋሼ በጣም አመሰግናለሁ!"አለና ስልኩን ለአስተናጋጁ ሰጥቶ ተመለሰ። ትንሽ ሲጫወቱ ከቆዩ በኋላ "ሐምራ "አለ ቀዳማዊ "ወይዬ ፍቅሬ!"አለች ሐምራዊ ፂሙን እየነካካች። "መሽቷል እኮ የኔ ቆንጆ። አንቺም እኔም በድንገት ነው ወጥተን በዚሁ የቀረነው። ወላጆቻችን የሚያስቡ አይመስልሽም?"አለ። ሐምራዊ ክፍት ብሏት "ለዛሬ እንተዋቸውና ራሳችንን እንስማ!"አለች "እኔም በጣም ደስ ይለኝ ነበር። ግን እናትሽ ይሄን ካወቀች ደስ አይላትም። መጀመሪያ ከእኔ ጋር ሆነን ስለ ፍቅራችን እንነግራትና ከዛ በኋላ በነፃነት እንደፈለግን እንሆናለን"አለ ቀዳማዊ። ሐምራዊ ደስ አላት። ከእሷ አልፎ ለእናቷ ስሜት መጨነቁ ይበልጥ አስደሰታትና "አመሰግናለሁ የኔ ፍቅር አለችና ከንፈሩን ሳም አደረገችው። "አሁን ይሄ ከንፈር የሚያስም ንግግር ሆኖ ነው። እንደው ለመሳም ምክንያት ፍለጋ ካልሆነ በቀር "አለና ስቆ እሱም በተራው ከንፈሯን ስሞ ተቃቅፈው ወጡ። ** "ልጄ ምነው አስጨነከኝ እኮ"አለች ሔዋን ቀዳማዊ ቤት ሲገባ። ቀዳማዊ በፈገግታ "አይዞሽ አትጨነቂ እናቴ ምን ይሆናል ብለሽ ነው?!"አለ ቀዳማዊ እየሳቀ። "ምንድነው ነገሩ እ? ራቅ ሳቅ ብለሀልሳ?" "ደስ ብሎኝ ነዋ"አለ። "በል ደስታህን አካፍለንና እኛም አብረንህ እንደሰት" "ዛሬ አይደለም የምነግራችሁ" "ባክህ ሁላችንም እናውቃለን ከነገርከን ንገረን"አለች ሔመን። ሔዋን ገላመጠቻት። ቀዳማዊ ድንግጥ ብሎ "ምኑን ነው የምታውቁት?"አለ ድንግጥ ብሎ "ፍቅር እንደያዘህ ናዋ። እኔም አውቃለሁ እማዬም ታውቃለች።የማያውቀው አባዬና ኤሊያና ነበሩ ይሄው እነሱም አሁን አወቁ"አለች ሔመን። "እንደው ምን ይሻልሻል ልጄ? ለአንቺ መናገር እኮ በገዛ እጅ ንገሩልኝ እንደማለት ነው"አለች ሔዋን። ቀዳማዊ ይበልጥ ግራ እየተጋባ "ቆይ ቆይ እንዴት አውቀሽ ነው የነገርሻት?" "ስታንጎራጉር ነዋ በጊታር ስትዘፍን ሰምቼህ"አለች ሔዋን። ቀዳማዊ ያን ምሽት አስታወሰው። የሐምራዊን የስዕል ቤት አይቶ የመጣ ጊዜ ነበር የተጫወተው። ምንም አላለም ዝም አለ። "ግን ከማን ፍቅር እንደያዘህ አንተ ንገረን። እኛ የገመትናት አለች"አለች ሔመን ቀጥላ። ቀዳማዊ ይበልጥ ፈራ ሊገምቷት የሚችሉትን ሴት ስለገመተ እውነቱን ለመናገር አመነታ። "እንዴ ምንድነው እንደዚህ ሰው ማስጨነቅ። ተውት በቃ እሱ ሲፈልግ ይነግረናል"አለ ሙሉሰው።ቀዳማዊ ጨንቆት ነበር በሙሉሰው ንግግር ትንሽ ቀለል አለው። "ክፍሌ ገብቼ ልምጣ "አለና ሄደ። " ወጣት ነው። ይሳቀቃል በዛ ላይ እድሜው ነው ስለዚህ ብዙ አትጫኑት"አለና ሙሉሰው እነ ሔዋንና ሔመን ላይ ኮስተር አለባቸው። "አሁን እንዴት ነው የምነግራት?" "በርግጠኝነት አትቀበላትም"ቀዳማዊ ከራሱ ጋር ይወያይ ጀመር "ምነው ቀረህ በዛው ቀዳማ"አለች ሔዋን ድምጿን ከፍ አድርጋ "መጣሁ እትዬ ልብስ ልቀይር ብዬ ነው"አለ "በቃ የፈለገ ይሁን እንግዲህ ለብቻዋ እነግራታለሁ"ብሎ ወሰነ። " የዮፍታሔን ስራ እንዴት አደረክለት ልጄ?"አለ ሙሉሰው ቀዳማዊንም ከሀሳብ ነፃ ለማድረግ የነ ሔዋንንም ርዕስ ለማስቀየር። "ያው ያቅሜን ያየሁትን ስህተት ከነ መፍትሔው ነግሪያቸዋለሁ። እሱም ደስ ብሎታል። ዋና መሀንዲሱም ዲዛይኑን አልተረዳውም ነበር መሰለኝ ክፍተት ነበረው። ይሄን ክፍተት ለማስረዳትም አርክቴክቷ መጥታ ነበር።" "ማን ናት አርክቴክቷ ቀዳ?"ብላ ሔመን ሰፍ ብላ ጠየቀችው። "ታውቂያታለች!" "እሺ ማናት? ንገረኝ" "ሐምራዊ ነች" ሔዋን ዘወር ብላ አየችው። ቀዳማዊ አንገቱን ሰበር አደረገ። "አዎ ጎበዝ ልጅ ናት ሲሉ ሰምቻለሁ። የአሮንን ረልስቴት ዲዛይን የሰራችው እሷ ናት ሲባል ሰምቻለሁ!"አለ ሙሉሰው። "አዎ ጋሽ ዮፍታሔም ጎበዝ አርክቴክት እንደሆነች ነግሮኛል።" አለ ቀዳማዊ "ታድላ ቀዳዬ አስተዋውቀኝ!"አለች ሔመን "እስኪ አሁን አስተዋውቀኝ የምትይው ምን ልታደርግልሽ ነው? ስራዋን ትታ ይምትጠቅመኝ መስሎሽ ነው?"አለች ሔዋን። "እንዴ በደንብ ነዋ የምትጠቅመኝ የምትረዳኝ በዛ ላይ ልምድ አላቴ የተሰሩ ዲዛይኖችን ትሰጠኛለች እለማመዳለሁ ብቻ አንተ አስተዋውቀኝ "አለች ሔመን። "እሺ ችግር የለውም አስተዋውቅሻለሁ አታስቢ"አለ ቀዳማዊ። ሔዋን አሁንም አሁንም ቀዳማዊን እየዞረች ታየዋለች። ቀዳማዊ በጣም ተጨነቀ። ሔዋን ሐምራዊን እንደማትወዳትና እንደጠላቻቴ ያውቃል።ይሄን ጥላቻዋን እንዴት መቀየር እንዳለበት ፊቷግ ይበልጥ ሲያየው ይበልጥ ተጨነቀ። ሔዋንን ላለማየት አንገቱን ሰበር እያደረገ ከሔመን ጋር ያወራል። የሔዋን እይታና የቀዳማዊን ሽሽት ሙሉሰው እየተመለከተ ይበልጥ ግራ እየተጋባ አንድ ጊዜ ሔዋንን ሌላ ጊዜ ቀዳማዊን እያቀያየረ ምን እንደሆኑ ለማወቅ ይሞክራል... @amba88 @ken_leboch