ማኅሌት ሚዲያ
Open in Telegram
ወደ ማኅሌት ሚዲያ እንኳን በሰላም መጡ፡፡ በዚህ ቻናል የተለያዩ መንፈሳዊ ስብከቶች እና ተከታታይ ትምህርቶች እንዲሁም የመንፈሳዊ መጻሕፍት ዳሰሳዎች ፣ አጫጭር የቤተ-ክርስቲያን አስተምሮዎች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል፡፡የቻናሉን ይዘቶች ለሌሎች በማጋራትበማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ፡፡
Show more2 075
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-2030 days
Posts Archive
2 075
Repost from የሥዕላት ዓይነት ማሳያና ማሳያ
፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨
ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት ኢየሉጣ
የዚህን ዓለም ጣዕም በመናቅ ....
‹‹ሞት ቢሆን፣ ሕይወትም ቢሆን፣ መላእክትም ቢሆኑ፣ ግዛትም ቢሆን፣ ያለውም ቢሆን፣ የሚመጣውም ቢሆን፣ ኃይላትም ቢሆኑ፣ ከፍታም ቢሆን፣ ዝቅታም ቢሆን፣ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ››
በማለት ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረውን ቃል በተግባር በማሳየት ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ ራሳቸውን ለመከራና ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡
ቅዱሳኑ ተጋድሏቸውን እስኪፈጽሙ ድረስም ቅዱስ ገብርኤል አልተለያቸውም፡፡ በቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት ቅድስት ኢየሉጣና ቅዱስ ቂርቆስ ብቻ ሳይሆኑ ብዙ ምእመናንም ተጠቅመዋል፡፡
ስሙ በሚጠራባቸው ገዳማትና አድባራት መልአኩ የሚያደርጋቸው ድንቅ ድንቅ ተአምራት ለዚህ ማስረጃዎች ናቸው፡፡
ይህም ቅዱሳን መላእክት በእግዚአብሔር ስም መከራ የሚቀበሉ ምእመናንን እንደሚጠብቁና ከልዩ ልዩ ደዌ እንደሚፈውሱ የሚያስረዳ ታሪክ ነው፡፡ (ሮሜ. ፰፥፴፰-፴፱)
ቅዱስ ቂርቆስንና ቅድስት ኢየሉጣን የተራዳው የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል በአማላጅነቱ እንዲጠብቀን
‹‹በተአምኖ ንሴፎ ትንባሌ ዚአከ መዓልተ ወሌሊተ፤ በእግዚአብሔር ታምነን በቀንም በሌሊትም የአንተን ልመና ተስፋ እናደርጋለን››
እያልን ዘወትር ልንማጸነው ያስፈልጋል፡፡ እርሱ ከፈጣሪው ከእግዚአብሔር በተሰጠው ቃል ኪዳን መሠረት ከሚደርስብን ልዩ ልዩ መከራና ሥቃይ ያድነናልና፡፡
‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙርያ ይሠፍራል፤ ያድናቸውማል›› ተብሎ እንደ ተጻፈ (መዝ. ፴፬፥፯)፡፡
የቅዱስ ገብርኤል፣ የቅድስት ኢየሉጣ እና ቅዱስ ቂርቆስ ጸሎታቸው፣ ምልጃቸው ይጠብቀን፡፡
2 075
የ2ዙር የመጨረሻ ምዝገባ ዛሬና ነገ (25/26) ሲሆን ከ27 ጀምሮ የመማርያ ቻናሉ ማንንም የማይቀበል ይሆናል ።
ስለዚህ ላልሰሙ እህት ወንድሞቻችሁ ሊንኩን በማጋራት እንዲመዘገቡ አሳውቋቸው ።
👉 t.me/bahire_hasab2 👈
2 075
➕➕➕ ጳጉሜን በባሕረ ሐሳብ ➕➕➕
✍ የሰው ልጅ ሕይወት ከጊዜ ጋር በእጅጉ የተቈራኘ ፍጥረት ነው፡፡ እያንዳንዱ ማኅበረሰብም የራሱ የሆነና ይህን ከሕይወቱ ጋር የተቈራኘውን ጊዜ የሚቀምርበት የዘመን አቈጣጠር አለው፡፡ ኢትዮጵያም የራሷ የሆነ ሐሳበ ዘመን ማለትም የዘመን አቈጣጠር አላት፡፡ ይህ የዘመን አቈጣጠር (ሐሳበ ዘመን) የዘመናት፣ የዓመታት፣ የወራት፣ የሳምንታት፣ የዕለታት፣ የሰዓታት፣ የደቂቃዎች፣ የቅጽበትና (የካልዒትና) የመሳሰሉት ጊዜያት በሐሳብ የሚመዘኑበት፣ የሚሰፈሩበት፣ የሚቈጠሩበት ምድብና ቀመር ተሰጥቶአቸው የሚገኙበትን ውሳኔና ድንጋጌ እያሰማ የሚጠራበት ትምህርታዊ ውሳኔ ነው፡፡
✍ ነገር ግን ከግእዝ ቋንቋ በመቀጠል በጣም አስጊ ሁኔታ ላይ ከደረሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ትምህርቶች መካከል አንዱ ይህ ጥንታዊው የባሕረ ሐሳብ ትምህርት ነው ። ለዚህም አንዱ ምክንያት በደፈናው " ትምህርቱ ይከብዳል " የሚል ትውልዱን የሚያሰንፍ ብሂል ነው ። ትምህርቱ ጥልቀት ያለው ቢሆንም ትንሽ ጊዜ ሰጥቶ ለተማረውና ለተረዳው ግን እጅግ በጣም ደስ የሚልና ቀላል ትምህርት ነው ።
✍ ስለዚህ በጥቂቱም ቢሆን በዓላትን ፣ አጿማትን ፣ ዕለታትን በቀላሉ ማውጣት እንችል ዘንድ ዘመኑን በዋጀ ፣ ቀለል ባለና ማራኪ አቀራረብ ትምህርቱን በቴሌግራም ለመስጠት ዝግጅታችን ጨርሰናል ።
ነሐሴ 27 ምሽት 3:30 ይጀመራል።
ቻናሉን በመቀላቀላ ብቻ መዝገቡ !
👉 t.me/bahire_hasab2 👈
2 075
🌷እንኳን አደረሳችሁ!!!
===================
✨ሚካኤል አባቴ
✨ሚካኤል ወዳጄ
✨ሚካኤል ሞገሴ
✨ትልሀለች ነፍሴ!!
የቅዱስ ሚካኤል ረድኤት፣ በረከት፣ ጥበቃና ምልጃው አይለየን ሕዝባችንን ከመከራ ሀገራችንን ከጥፋት ይታደግልን💚💛❤️
2 075
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ፍልሰታ ማለት ምን ማለት ነው?
ፍልሰታ የሚለው ቃል የተገኘው ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ መለየት፣ማረግ፣ወደላይ መውጣት የሚለውን ትርጉም ይይዛል። በእዚህ መሠረትም ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን ድንግል ማርያምን የሥጋዋ ከመቃብር መለየት እና ማረግን ያመለክታል። ይህ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከተወሰኑት ሰባቱ አጸዋማት ውስጥ ለዓመቱ የመጨረሻው ጾም ነው።
ፍልሰታ ጾም ለምን እንፆማለን?
የፍልሰታ ጾም ከነሐሴ 1 እስከ 15 የሚጾም ሲሆን በቤተ ክርስቲያናችን አስተምሮ መሠረት እመቤታችን ያረፈችው በጥር 21 ቀን ነው። ሐዋርያትም አስከሬኗን ሊቀብሩ ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሔዱ አይሁድ በምቀኝነት ልጇ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷል። አሁንም እርሷ ገቢረ ተአምር ልታደርግ አይደል? ብለው አስከሬኗን ተሸክመው የሚሔዱትን ሐዋርያትን በታተኗቸው። በዚህን ጊዜ መላእክት የእመቤታችንን አስከሬን ከአይሁድ ነጥቀው በገነት አኖሩት። በስምንተኛው ወር በነሐሴ ሐዋርያት ከነሐሴ 1 እስከ 14 ሁለት ሱባዔ ገብተው ከጌታችን ተቀብለው በጸሎትና በምህላ ቀበሯት። በዚህ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ቶማስ የተባለው ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወጥቶ ነበር እና መገኘት አልቻለም ነበር።
እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን ከላይ እንደተጠቀሰው በነቢያት ትንቢት እንደተነገረላት እንደ ልጇ ተነሥታ ስታርግ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ አገኛት። በዚህን ጊዜ ትንሣኤዋን ሌሎች ሐዋርያት አይተው ለእርሱ የቀረበት መስሎት በረከት ቀረብኝ ሲል ተበሳጨ።ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ ብሎ እራሱን ከደመና ላይ ሊወረውር ቃጣው። በዚህን ጊዜ እመቤታችን ቶማስን አፅናናችው ከእርሱ በቀር ትንሣኤዋን ያየ አለመኖሩን ነገረችው።ለምስክርነት እንዲሆንም በቀብሯ ጊዜ የነበረውን ሰበኗን ሰጥታው አረገች።
ሞት በጥር፣በነሐሴ መቃብር
ቶማስም ሰበኗን ደብቆ ይዞ ሐዋርያት ካሉበት ደረሰ። ሐዋርያትንም የእመቤታችን ነገር ምን ደረሰ? አላቸው። ሐዋርያትም እመቤታችን ሱባዔ ገብተን ጌታችን አስከሬኗን ከዕፀ ሕይወት አምጥቶ ሰጥቶን በክብር ቀበርናት አሉት። ቶማስም መልሶ ሞት በጥር፣በነሐሴመቃብር?አላቸው።ሐዋርያትም መለሱለት ቶማስ አትጠራጠር። ቀድሞ ጌታችን በተገለጠ ጊዜ ትንሣኤውን ጣቶቼን በተቸነከሩ እጆችህ ካላስገባሁ ብለህ የደረሰብህን ታውቃለህ አሁንም የእመቤታችንን መቀበር አላመንክምን? አሉት። ቶማስ ግን ሐዋርያትን ይዞ ወደ መቃብሯ ሔደ። መቃብሯን ከፍተው ሲመለከቱ ሐዋርያት ደነገጡ። በዚህን ጊዜ ቶማስ አታምኑኝም ብየ ነው እንጂ እመቤታችን አርጋለች። ስታርግም በደመና ከሀገረ ስብከቴ ስመጣ ተገናኘን ለምልክቱም ይኸው የቀበራችሁበት ሰበን አላቸው።ሐዋርያትም ለበረከት ሰበኗን ተከፋፍለው ወደየሀገረ ስብከታቸው ሔዱ።
በዓመቱ ግን ሐዋርያት ተሰበሰቡ እና ትንሣኤሽን ቶማስ አይቶ እኛም በረከት አይቅርብን ብለው ከነሐሴ አንድ ጀምረው ሱባዔ ገቡ።በነሐሴ 14 አስከሬኗን ትኩስ በድን አድርጎ አምጥቶ ሰጥቷቸው ከቀበሯት በኋላ በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16 እመቤታችን ተነሥታ ጌታችን ከመላእክት እና ቅዱሳን ጋር ሆኖ ሐዋርያትን አቁርቧቸዋል።(ውዳሴ ማርያም ትርጉም)።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮ እና ሐዋርያት መሠረት ላይ የታነፀችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያትን ግብር ምሳሌ በማድረግ ልክ እንደ ሐዋርያት ለሐዋርያት የተገለጠ በረከት እና የእመቤታችን ረድኤት እንዲያድርብን እንጾመዋለን።በቤተ ክርስቲያናችን ከአምስቱ የአዋጅ አጽዋማት መካከልም በመሆኑም ሁሉም ምእመናን እንዲጾም ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች።
ነቢዩ ዳንኤል በትንቢተ ዳንኤል ምዕ 10፣21 ላይ እንደተጠቀሰው ”በዚያም ወራት እኔ ዳንኤል ሦስት ሳምንት ሙሉ ሳዝን ነበርሁ።ማለፊያ እንጀራም አልበላሁም፥ ሥጋና ጠጅም በአፌ አልገባም፥ ሦስቱም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ዘይት አልተቀባሁም።” እንዳለ ጾሙን ከፅሉላት ምግቦች ከሥጋ እና ወተት ውጤቶች በመጾም እና ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሔድ፣በስግደት፣በምፅዋት እና በጾሎት ይጾሙታል።
2 075
እኔ በእግዚአብሔር ዘንድ የምቆመው ገብርኤል ነኝ ሉቃ1÷19
ለተዋህዶ ልጆች በሙሉ እንኳን በሰላምና በጤና ጠብቆ ተወዳጅ ለሆነው ለሩህሩሁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ ።
መዝሙር 91÷11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋል እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።
አሳዳጊዬ ነው ሆኖ እናት አባቴ ገብርኤል ባለበት ይሸሻል ጠላቴ ።
የተወዳጁ የቅዱስ ገብርኤል ስሞች በመፃሕፍት ይህን ይመስላል ።
1,ሊቀ መላዕክት
2,መጋቤ ሐዲስ
3,አብሳሬ ትብስእት
4,ዜናዌ ሐዲስ
5, ፍሱሐ ገፅ
6, መልአከ ብርሀን
7, የራማው ልዑል
8, መልአከ ሰላም
እየተባለ በሊቃውንት እና በመፃህፍት ይወሳል።
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።”
— መዝሙር 34፥7
የተወዳጁ የቅዱስ ገብርኤል ረድኤት እና በረከት ጠብቆቱ እና አማላጅነቱ በሁላችን ላይ ይደርብን ።
ዲ/ን ዳዊት ፈለቀ
ይቆየን
