የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት
መዝሙር ጥናት አጫጭር ኮርሶች የቤተክርስቲያን ስርዓት አጠባበቅ ጥያቄ እና መልስ የተለያዩ የሰ/ቤት ጉባኤዎች ያገኙበታል ሰንበት ትምህርትቤት እናት ናት join&share ቻናላችንን ይቀላቀሉ @fra_haymanot16 group t.me/fra_haymanot_16 ጥያቄ፣ሀሳብ እና አሐስተያየት ካሎት @yoniyekidye
Show more1 207
Subscribers
-224 hours
-87 days
-3030 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
ክብሬ_ነው
ክብሬ ነው ክብርህን መናገሬ
ፅድቄ ነው ፍቅርህ መመስከሬ
ጌታዬ አምላኬ እልሃለሁ (2)
ስጠራህ ሳመልክህ እኖራለሁ (2)
አይቼ የእጅህን ታምራት
ሰምቼ የቃልህን ትምርት
ሆኛለሁ ምስክር ላዳኝነትህ
ስጋን ተዋህደህ ለኛ መገለጥህ (2)
ተከተልኩ ሁሉን ነገር ንቄ
መድኃኒት መሆንክን አውቄ
ከመልካሟ ቤትህ ተጠልያለሁ
የእጅህን በረከት ካንተ እጠግባለሁ (2)
እርፍ ይዤ ላላርስ ወደኅውላ
እያየው መረቤን ስትሞላ
እመካብሃለሁ ባንተ መድህኔ
አምላኬ ነህና የምትራራ ለኔ
አባቴ ነህና የምታስብ ለኔ
ቸርነት ምረት ከበዛልኝ
ለስምህ ውዳሴ ቅኔ አለኝ
ክብሬና ሞገሴ አንተ ነህ ጌታ
ተመስገን (2) ጠዋትና ማታ (2)
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
@yoniyekidye
-ክብሬ ነው ክብርህን መናገሬ.MP37.15 MB
🕊 እንኳን አደረሳችሁ ! 🕊
[ ጾመ ሐዋርያት ! ]
† 🕊 † 🕊 †
[ ክፍል አንድ ]
በስመ አብ ፥ ወወልድ ፥ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን።
በየአመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ [ ሰኞ ቀን ብቻ ] የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ፡፡ እነርሱም ዓቢይ ጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው፡፡ እነዚህአጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸው እሁድ ሲሆንየሚገቡት ደግሞ ሰኞ ቀን ነው፡፡ በየትኛውም ዓመት ይህን ዕለት አይለቁም፡፡
ስለዚህ የ፳፻፲፭ [2015] ዓ.ም ጾመ ሐዋርያት ዛሬ ሰኞ ግንቦት ፳፰ [28] ገብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊና ሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትን ኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮው በበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡
የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመው የትመጣውን ፣ ትንቢቱን ፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩን መረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙ እንማር ዘንድ በአጭሩ ቀርቧል !
ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸው ለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸው ካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት ፣ ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾምመሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡
ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢት በመናገር ፣ ምሳሌ በመመሰል ሰፊ ትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው " ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው ? " ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡ እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው ፦ " ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገርግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም ፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና ፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም ፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል ፤ የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡" [ ማቴ.፱፥፲፬ ]
በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ "ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡" የሚል ስለ ጾመ ሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህ አምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮ ይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደ በኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ "ሙሽራው ከተወሰደ" በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያት ነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና መጽሐፍቅዱሳዊ መሆኗን ይመሠክራል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡ ወለወላዲቱ ድንግል ፡ ወለመስቀሉ ክቡር፡፡
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
@yoniyekidye
የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት
ግሩፑ ላይ ማድረግ የማይቻሉ ነገሮች እና ሕጎች 1 ማንኛውም መንፈሳዊ ያልሆነ ነገር መልቀቅ የተከለከለ ነውነው። 2 መንፈሳዊ ያልሆነ ወሬ ማውራት የተከለከለ ነው 3 በድንግል ማርያም አማላጅነት የማያምን ሠውን አድ ማድረግ የተከለከለ ነው .group
https://t.me/fra_haymanot_16channal @fra_haymanot16 ለ ሐሳብ እና አስተያየት @yoniyekidye
Show all...
TikTok · በሆ/ደ/ገ/ የፍሬ ሀይማኖት ሰ/ቤት
Check out በሆ/ደ/ገ/ የፍሬ ሀይማኖት ሰ/ቤት’s post.
Photo unavailableShow in Telegram
አይቀርም አይቀርም አይቀርም እንዴት ይቀራል
ታላይ መንፈሳዊ ጉባዬ በሆለታ ደብረ ገነት የፍሬ ሀይማኖ ሰንበት ት/ቤት 41ኛ ዓመት በማስመልከት የተዘጋጀ ጉባኤ ታላላቅ መምህራን አባቶች፣ሰባኪያን እና ዘማሪዎች ስለሚገኙ እርሶም የበረከቱ ተካፋይ ይሁን እያለች ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ታሳስባለተ
"ኑ በእግዚአብሄር ደስ ይበለን"መዝ 95:1
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
@yoniyekidye
Photo unavailableShow in Telegram
💛 ዳግም ትንሳኤ 💛
እንኳን ለዳግም ትንሳኤ
በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
@yoniyekidye
Photo unavailableShow in Telegram
አይቀርም በሆለታ መንበረ ስብሐት ቅቸድስት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ልደትሽ ልደታችነው እያልን በልደቷ ዋዜማ ማለትም በ30 ታላቅ የአእላፍ ዝማሬ በመዘጋጀቱ የተዋህዶ ልጆች የሆናቹ በሙላ ላልሰማ በማሰማት እና በቦታ ተገኝተን ለእናታችን ምስጋና እናቅርብ
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
@yoniyekidye
Photo unavailableShow in Telegram
ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም
ተነስቷል በዚህ የለም😍
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
@yoniyekidye
Photo unavailableShow in Telegram
ቀዳም ስዑር
ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ
የጌታችንን መከራ በማሰብ
በፆም ታስባ ስለምትውል
የተሻረች ቅዳሜ ተብላ ተሰይማለች።
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
❤ 1
Photo unavailableShow in Telegram
🕊 † ሰሙነ ሕማማት † 🕊
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ አርብ ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
† የስቅለት ዓርብ ይባላል †
ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና [ ማቴ ፳፯፥፴፭ ] የስቅለት ዓርብ ይባላል።
† መልካሙ ዓርብ ይባላል †
ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምህረት ፣ የሕይወት አርማ ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደረገው ፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል።
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
@yoniyekidye
Photo unavailableShow in Telegram
[ ዘሐሙስ ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ † ጸሎተ ሐሙስ ይባላል † ]
ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ [ ማቴ ፳፮፥፴፮ ] ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም [ ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ] ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።
[ † የምስጢር ቀን ይባላል † ]
ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር [ ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ ] በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል።
[ † የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል † ]
መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ [ ሉቃ ፳፪፥፳ ] የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።
[ † የነጻነት ሐሙስ ይባላል † ]
ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም [ ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ ] የነጻነት ሐሙስ ይባላል።
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
share & join
group
https://t.me/fra_haymanot_16
channal
@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት
@yoniyekidye
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.