en
Feedback
አድስ ዜና

አድስ ዜና

Open in Telegram

ወቅታዊ፣ ጠቃሚ እና እንገብጋቢ መረጃወችን ከስር ከስር ለመከታተል የዚህ ቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ ሆኑ! ይጫኑ @adszena Welcome to addis zena latest Ethiopian news channel you will get trust, usfull and latest news in and around the globe! STAY TUNED WITH ADDIS ZENA👍 @adszena

Show more
1 876
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '23
December '23
+16
in 0 channels
November '23
+21
in 0 channels
Get PRO
October '23
+30
in 0 channels
Get PRO
September '23
+16
in 0 channels
Get PRO
August '23
+28
in 0 channels
Get PRO
July '23
+48
in 0 channels
Get PRO
June '23
+30
in 0 channels
Get PRO
May '23
+28
in 0 channels
Get PRO
April '23
+25
in 0 channels
Get PRO
March '23
+23
in 0 channels
Get PRO
February '23
+34
in 0 channels
Get PRO
January '23
+154
in 0 channels
Get PRO
December '22
+52
in 0 channels
Get PRO
November '22
+75
in 0 channels
Get PRO
October '22
+122
in 0 channels
Get PRO
September '22
+182
in 0 channels
Get PRO
August '22
+283
in 0 channels
Get PRO
July '22
+98
in 0 channels
Get PRO
June '22
+92
in 0 channels
Get PRO
May '22
+112
in 0 channels
Get PRO
April '22
+89
in 0 channels
Get PRO
March '22
+45
in 0 channels
Get PRO
February '22
+28
in 0 channels
Get PRO
January '22
+42
in 0 channels
Get PRO
December '21
+34
in 0 channels
Get PRO
November '21
+87
in 0 channels
Get PRO
October '21
+161
in 0 channels
Get PRO
September '21
+119
in 0 channels
Get PRO
August '21
+228
in 0 channels
Get PRO
July '21
+230
in 0 channels
Get PRO
June '21
+103
in 0 channels
Get PRO
May '21
+89
in 0 channels
Get PRO
April '21
+111
in 0 channels
Get PRO
March '21
+101
in 0 channels
Get PRO
February '21
+67
in 0 channels
Get PRO
January '21
+120
in 0 channels
Get PRO
December '20
+3 075
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
23 December0
22 December0
21 December+2
20 December+1
19 December0
18 December+2
17 December0
16 December0
15 December+1
14 December+1
13 December0
12 December+1
11 December0
10 December0
09 December+1
08 December+1
07 December0
06 December+2
05 December+1
04 December+1
03 December+1
02 December0
01 December+1
Channel Posts
የሴቶች የማራቶን ሪከርድ በጣም ሰፊ በሆነ ከ2 ደቂቃ በላይ በሆነ ግዜ በኢትዮጵያዊቷ ጀግኒት ትግስት አሰፋ በበርሊን ማራቶን ዛሬ ተሰብሯል። "This is the most incredible marathon performance we have ever seen" በማለት የበርሊን ማራቶን አዘጋጆች በገለፁት በዚህ ውድድር ትግስት 2:11:53 በመግባት ታሪክ ሰርታለች። እጅግ አስደናቂ ብቃት። Video credit: Berlin Marathon Facebook page

2
No text...
420
3
1፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በዝግ ባካሄደው ስብሰባ ፌደራል መንግሥቱ በአማራ ክልል ለስድስት ወራት ያወጀውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል። ምክር ቤቱ አዋጁን ያጸደቀው፣ በ16 ተቃውሞ እና በ12 ድምጸ ተዓቅቦ ነው። የምክር ቤቱ አባላት ላነሷቸው የተለያዩ ጥያቄዎች፣ ፍትህ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ሰጥተዋል። 2፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ላጸደቀው በአማራ ክልል ለታወጀው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሰባት አባላት ያሉት መርማሪ ቦርድ ሰይሟል። ምክር ቤቱ የመርማሪ ቦርዱን አባላት በአብላጫ ድምጽ የሾመ ሲኾን፣ አዝመራው አንዴሞ የመርማሪ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲኹም ነጃት ግርማ ምክትል ሰብሳቢ ኾነው ተሹመዋል። የመርማሪ ቦርዱ አባላት ኾነው የተሰየሙት፣ ሣዲቅ አደም፣ መስፍን እርካቤ፣ አብርሃም በርታ፣ ፍሬህይወት ተሾመ እና ወንድሙ ግዛው ናቸው። የመርማሪ ቦርዱ ሰብሳቢዎች እና አባላቱ በምክር ቤቱ ፊት ቃለ መሃላ እንደፈጸሙ ምክር ቤቱ ገልጧል። 4፤ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ ፍኖተሰላም ትናንት በተፈጸመ "የአየር ጥቃት" እንደኾነ በተገመተ ጥቃት የተገደሉት ሰዎች 26 እንደሚደርሱ ስማቸው እንዲጠቀስ ካልፈለጉ የከተማዋ ሆስፒታል ሐኪሞችና ከነዋሪዎች መስማቱን ጠቅሶ ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። በጥቃቱ ከ55 በላይ ሰዎች ቆስለው በሆስፒታሉ እንደሚገኙ የከተማዋ ሆስፒታል ሐኪሞች መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። በከተማዋ እምብርት ላይ በአይሱዙ ተሽከርካሪና ባካባቢው በመንቀሳቀስ ላይ በነበሩ ሰዎች ላይ በተፈጸመው ጥቃት፣ 22ቱ ሰዎች ወዲያውኑ እንደሞቱ ሐኪሞቹ መናገራቸው ተመልክቷል። ሐኪሞቹ ሆስፒታሉ ያልገቡትን ጨምሮ የሟቾች ቁጥር ከ26 ይበልጣል ብለው እንደሚገምቱ፣ አንዳንድ ነዋሪዎች ደሞ ቁጥሩን እስከ 40 እንደሚያደርሱት መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። 5፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ በትግራይ ክልል ለተከሰተው "እጅግ አስከፊ" የአንበጣ መንጋ የክልሉ አስተዳደር ድጋፍ እንደሚፈልግ ዛሬ በ"ኤክስ" (ትዊተር) ገጻቸው አስታውቀዋል። የአንበጣ መንጋው "በቅርብ ዘመናት ውስጥ እጅግ የከፋ" መኾኑን የጠቀሱት ጌታቸው፣ የትግራይ ሕዝብ፣ ፌደራል መንግሥቱ እና ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የአንበጣ መንጋው የሚያስከትለውን ውድመት ለመከላከል የተቻላቸውን ኹሉ ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪ አድርገዋል። 6፤ አዲስ በሚዋቀረው "ማዕከላዊ ኢትዮጵያ" ክልል በነባሩ ከምባታ ጠምባሮ ዞን በተለያዩ ከተሞች ዛሬ "ቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማ" እንደተደረገ ዶይቸቨለ ዘግቧል። በዱራሜ ከተማ ባንኮች፣ ሆቴሎችና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተዘግተው መዋላቸውን ነዋሪዎች እንደተናገሩት ዘገባው ጠቅሷል። የዞኑ ከተሞች ነዋሪዎች አድማ የመቱት፣ የዞኑ አስተዳደር መቀመጫ ዱራሜ በአዲሱ ክልላዊ የመንግሥት አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችና ሌሎች ተቋማት የመቀመጫነት ድልድል ፍትሃዊ ድርሻ አላገኝችም በሚል ቅሬታ ነው። የዞኑ ምክር ቤት የቢሮዎችን ድልድል ውድቅ ያደረገው ሲኾን፣ የዞኑ አስተዳደር ግን ዱራሜ ላይ መቀመጫቸውን የሚያደርጉ ቢሮዎች ቁጥር እንዲጨምር ከቢሮ ድልድል አደረጃጀት አስተባባሪ ኮሚቴው ጋር ስምምነት ላይ ተደርሷል ብሎ ነበር።
394
4
#NewsAlert የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል ግጭት ውስጥ የገቡ ወገኖች "ያለምንም ቅድመ ኹኔታ ግጭት እንዲያቆሙ" እና ችግሩን በውይይት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ዛሬ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ኢሰመኮ፣ መንግሥት የጅምላ እስር ማካሄዱን እንዲያቆም፣ ኮሚሽኑና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ተቆጣጣሪ ድርጅቶች ሲቪሎች በታጎሩባቸው ማዕከላት ክትትል እንዲያደርጉ እንዲፈቅድ፣ በዘፈቀደ ያሠራቸውን ሰዎች ባስቸኳይ እንዲፈታም ጠይቋል። አፍሪካ ኅብረት፣ ኢጋድና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በክልሉ ግጭት ውስጥ የገቡ ወገኖችን እንዲያደራድሩም ኢሰመኮ ጥሪ እድርጓል። በክልሉ በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተሰላም እና ቡሬ እንዲኹም በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረብርሃን ከተሞች በተፈጸሙ የአየር ጥቃቶችና የከባድ መሳሪያ ድብደባዎች ሲቪሎች እንደተገደሉ ሪፖርቶች እንደደረሱት የጠቀሰው ኢሰመኮ፣ መንገዶችን የዘጉ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ሳይቀር እንደተገደሉ፣ ወህኒ ቤቶች ተሰብረው ታሳሪዎች እንዳመለጡ፣ የጦር መሳሪያዎች እንደተዘረፉ፣ የክልሉ ባለሥልጣናት እንደተገደሉና በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ የአማራ ብሄር ተወላጆች በጅምላ እንደታሠሩ መረዳቱንም ገልጧል። በክልሉ በመንግሥት ሃይሎችና በታጣቂዎች መካከል ውጊያው በትላልቅ ከተሞች ቢቆምም፣ በሌሎች የክልሉ በርካታ አካባቢዎች ግን አኹንም ድረስ መቀጠሉን ኢሰመኮ ጨምሮ አመልክቷል።
272
5
- የአውስትራሊያ ፣ - የጃፓን ፣ - የኒውዚላንድ፣ - የእንግሊዝ እና የዩናይትድ ስቴትስ መንግስታት በቅርቡ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የሰላማዊ ዜጎች ሞት እና አለመረጋጋት ያስከተለው ግጭት እንዳሳሰባቸው ዛሬ በጋራ ባወጡት መግለጫ አሳውቀዋል። ሀገራቱ ፤ ሁሉም ወገኖች ሰላማዊ ሰዎችን እንዲጠብቁ፣ ሰብአዊ መብቶችን እንዲያከብሩ እና የሚያጋጩ ውስብስብ ጉዳዮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ተባብረው እንዲሰሩ አበረታተዋል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ለዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲኖር ድጋፉን እንደሚቀጥል አሳውቀዋል። በሌላ በኩል ፦ - የአውሮፓ ህብረት ልዑክ በኢትዮጵያ - የኦስትሪያ ፣ - የቤልጂየም ፣ - የቼክ ሪፖብሊክ ፣ - የዴንማርክ ፣ - የፊንላንድ ፣ - የፈረንሳይ ፣ - የጀርመን ፣ - የሃንጋሪ ፣ - የአየርላንድ ፣ - የኢጣሊያ ፣ - የሉክሰምበርግ ፣ - የማልታ ፣ - የኔዘርላንድስ ፣ - የሮማኒያ ፣ - የፖላንድ ፣ - የፖርቹጋል ፣ - የስሎቬንያ ፣ - የስፔን እና የስዊድን ኤምባሲዎች በጋር ባወጡት መግለጫ ሰሞኑን በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ሁከትና የዜጎች ሞትና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። ሀገራቱ ፤ " ሁሉም ወገኖች ሲቪሎችን እንዲጠብቁ ፣ ጉዳት ለደረሰባቸው ህዝቦች የተሟላ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ቀጣይነት ያለው ሰብአዊ ተደራሽነት እንዲረጋገጥ፣ የውጭ ዜጎች ከግጭቱ ኣካባቢ ለቅቀው እንዲወጡ እና ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ እንዲተላለፉ እንዲፈቀድ፤ የሰላም ስምምነቱ አፈፃፀም በሚቀጥልበት ጊዜ ውስብስብ ጉዳዮችን በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት በጋራ መስራት፣ እና ግጭቱ ወደ ሌሎች የሀገሪቱ ክልሎች ተዛምቶ ብጥብጥ እንዳይፈጠር ተገቢው መከላከል እንዲደረግ እናበረታታለን " ብለዋን። አለም አቀፉ ማህበረሰብ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የረዥም ጊዜ የመረጋጋት ግብ ድጋፉን ይቀጥላል ሲሉ ገልጸዋል። @
365
6
ዐበይት ዜናዎች 1፤ በአማራ ክልል የታወጀው አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ሃላፊ ተመስገን ጥሩነህ በክልሉ ታጣቂ ኃይሎች "አንዳንድ የዞንና የወረዳ ከተሞችን" እንደተቆጣጠሩ አስታውቀዋል። ታጣቂዎች በአንዳንድ ማረሚያ ቤቶች ወንጀለኞችን ከእስር እንዳስለቀቁም ገልጸዋል። ተመስገን፣ የታጣቂ ኃይሎቹ ፍላጎት፣ የክልሉን መንግሥት አፍርሰው ወደ ፌደራል መንግሥቱ ማምራት መኾኑን ትናንት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጠቅላይ መምሪያ ባካሄደው ስብሰባ ላይ አብራርተዋል። የአዋጁ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ፣ ምዕራብ አማራ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ማዕከላዊ ሸዋና ምሥራቅ አማራ ተብሎ በንዑስ ዕዞች እንደተከፋፈለ ተገልጧል። 2፤ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በአማራ ክልል ያለው ግጭት ድርጅታቸውን እንዳሳሰበው በትዊተር ገጻቸው ባሠፈሩት መልዕክት አስታውቀዋል። በክልሉ በመንገዶች መዘጋት ሳቢያ የሰብዓዊ ዕርዳታ ተደራሽነት አስቸጋሪ መኾኑንና በኢንተርኔት መቋረጥ ኮምንኬሽን አዳጋች እንደኾነ ዶ/ር ቴዎድሮስ ገልጸዋል። ግጭት በሰዎች ጤና ላይ "ወዲያውኑ ተጽዕኖ ያሳድራል ያሉት ዶ/ር ቴዎድሮስ፣ ያልተገደበ የዕርዳታ ተደራሽነት እንዲኖር፣ የጤና ተቋማት ከጥቃት እንዲጠበቁና፣ የዓለም ጤና ድርጅትና ሌሎች አጋሮች ሥራቸውን መቀጠል እንዲችሉ ጥሪ አድርገዋል። 3፤ ኢትዮጵያዊያን ላኪዎች እሴት ያልተጨመረባቸውን የከበሩ ማዕድናት ለውጭ ገበያ እንዳያቀርቡ ክልከላ ለመጣል ዝግጅት እየተደረገ መኾኑን የኢትዮጵያ የማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ማስታወቁን ሪፖርተር ዘግቧል። ክልከላው የሚጣለው፣ ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ እሴት ያልተጨመረባቸው የከበሩ ማዕድናትን አገሪቱን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እያሳጧት በመኾኑ እንደኾነ ኢንስቲትዩቱ መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል። አገሪቱ ቀደም ሲል እሴት ሳይጨመርባቸው የከበሩ ማዕድናትን ወደ ውጭ መላክ የሚከለክል መመሪያ የነበራት ሲኾን፣ በኋላ ላይ ግን ይህ ግዴታ ቀርቷል። 3፤ የደቡብ ክልል ምክር ቤት በደቡብ ክልልና በአዲሱ "የደቡብ ኢትዮጵያ" ክልል መካከል በሚኖረው የንብረትና ዕዳ ክፍፍል ላይ መወዛገቡን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። በንብረትና ዕዳ ክፍፍል ዙሪያ ሰሞኑን ለምክር ቤቱ የቀረበው የውሳኔ ሃሳብ፣ የንብረትና ዕዳ ክፍፍሉ በሲዳማና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ላይ ጭምር ተግባራዊ ይሆናል የሚል ሃሳብ ማቅረቡን ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም አንዳንድ የምክር ቤቱ አባላት ግን፣ የራሳቸውን የክልል ምክር ቤቶች ባቋቋሙት ሁለቱ ክልሎች ላይ የንብረት ክፍፍል ውሳኔ ሊተገብር አይችልም የሚል መከራከሪያ እንዳቀረቡ ተገልጧል
410
7
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ እና ጊዳ አያና ወረዳዎች በመከላከያ ሠራዊት እና በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መካከል ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ መኖሩን አዲስ ማለዳ ከነዋሪዎች ሰምታለች። ኹለቱ ኃይሎች በአካባቢው ከዚህ ቀደምም ውጊያ ሲያካሂዱ ነበር የተባለ ሲሆን፤ በተለይ ከባለፈው ከዕሮብ ሐምሌ 26/2015 ጀምሮ ከፍተኛ ውጊያ እያደረጉ እንደሚገኙ ነው የተነገረው፡፡ በተለይም በጊዳ አያና ወረዳ ጢቃ ጃንግር ከተማ ዕሮብ ሐምሌ 26/2015 ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ቀኑ ስድስት ሰዓት ድረስ ከፍተኛ የሆነ የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን፤ ከኹለቱም ኃይሎች በርካታ ሰዎች ሳይሞቱ እና ሳይቆስሉ እንዳልቀረ ነዋሪዎች ጠቁመዋል።
380
8
ዐበይት ዜናዎች 1፤ ዛሬ በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባሕርዳር ለሰዓታት የዘለቀ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ሲሰማ መዋሉን ዋዜማ ተረድታለች። የመንግሥት ኃይሎች፣ በከተማዋ ቀበሌ 13 እና ቀበሌ 14 መንገዶችን ከዘጉ ወጣቶች ጋር እንደተጋጩና ጥይት እንደተኮሱ ዋዜማ ከቀበሌዎቹ ነዋሪዎች ሰምታለች። ከከተማዋ ዳርቻ በአውሮፕላን ማረፊያው በቅርብ ርቀት በሚገኘውና ፈለገ ሕይወት ሆስፒታል በሚገኝበት ቀበሌ 13፣ መከላከያ ሠራዊት ታንኮችን ጭምር አሠማርቶ ነበር ተብሏል። የፋኖ ታጣቂዎች በከተማዋ በቅርቡ ርቀት እንደሚገኙ መረጃዎች አመልክተዋል።e 2፤ በአማራ ክልል ጎንደር ከተማና አካባቢው ዛሬ በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ ሲካሄድ መዋሉን የዋዜማ ሪፖርተር ዘግባለች። በከባድ መሳሪያ የታገዙት ግጭቶች የተካሄዱት፣ ጎሃ ሆቴል በተባለው ታዋቂ ሆቴልና በሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር ጽሕፈት ቤት አካባቢ ነው። ከከተማዋ አቅራቢያ በምትገኘው አዘዞ ከተማም፣ ግጭት ቀጥሎ መዋሉን ከሌሎች ምንጮች መረዳት ተችሏል። 3፤ ፌደራል ፖሊሶች ትናንት ምሽት በቁጥጥር ስር የዋሉትን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ክርስቲያን ታደለን አስከትለው ዛሬ ጧት መኖሪያ ቤታቸውን መፈተሻቸውን ቢቢሲ አማርኛ ቤተሰባቸውን ጠቅሶ ዘግቧል። "የፌደራል ፖሊስ መለዮ የለበሱ" አካላት የምክር ቤት አባሉን ከቤታቸው የወሰዷቸው፣ "በኃይል አፍነው" እንደነበርና "ድብደባ" ጭምር እንደፈጸሙባቸው መስማቱን ዘገባው ጠቅሷል። ክርስቲያን በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው። ምክር ቤት፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ በአባሉ መታሠር ዙሪያ ያለው ነገር የለም። 4፤ የመንግሥት ቃል አቀባይ ለገሠ ቱሉ በአማራ ክልል ከተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስና ግጭት ጋር በተያያዘ ጸጥታ ኃይሎች "ሥምሪት የሚሰጡ" እና "ችግሩን የሚያባብሱ" አካላትን በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመራቸውን ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ለገሠ፣ ግጭት የቀሰቀሱት ኃይሎች፣ የሰሜኑን የግጭት ማቆም ስምምነት ያልተቀበሉ አካላት እንደኾነ ገልጸዋል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጠቅላይ መምሪያ፣ ቀጣይ ርምጃዎቹን እንደሚገልጽ የተናገሩት ለገሠ፣ የሰብዓዊ መብት አያያዝን የሚከታተል አካልም ይቋቋማል ብለዋል። አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ትናንት ከታወጀበት ሰዓት ጀምሮ ስንት ሰዎች በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር እንደዋሉ ግን ቃል አቀባዩ አልገለጡም። 5፤ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ለአዲሱ "የደቡብ ኢትዮጵያ" ክልል ሕገመንግሥታዊ ሥልጣን አስረክቧል። አዲሱ ክልል ከደቡብ ክልል ሕገመንግሥታዊ ሥልጣን መረከቡን ተከትሎ፣ በይፋ የፌደሬሽኑ 12ኛ ክልል ኾኗል። ዛሬ የአዲሱን ክልል ሥልጣን የተረከቡት፣ በሕዝበ ውሳኔ ክልሉን በጋራ ለመመስረት የወሰኑት የወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ጌዲዖ፣ ደቡብ ኦሞና ኮንሶ ዞኖች እንዲኹም የደራሼ፣ ቡርጂ፣ አማሮ፣ አሌና ባስኬቶ ልዩ ወረዳዎች ምክር ቤቶች አፈ ጉባዔዎች ናቸው። 6፤ በአዲስ አበባ ከተማ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የገጠማቸው በርካታ የግል ባንኮች ደንበኞቸቸው በቀን በሚያወጡት የገንዘብ መጠን ላይ ገደብ መጣላቸውን ዘ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። በርካታ ንግድ ባንኮች ደንበኞቻቸው ባንድ ቀን ማውጣት የሚችሉትን ጥሬ ገንዘብ ከ5 ሺህ ብር እንዳይበልጥ ገደብ እንዳስቀመጡ መረዳቱን ዘገባው ጠቅሷል። ብሄራዊ ባንክ በቀን አንድ ደንበኛ ከባንኮች እንዲያወጣ ያስቀመጠው ጣሪያ 50 ሺህ ብር ነው። የባንኮችን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ከፈጠሩት ምክንያቶች መካከል፣ ለላኪዎች ከፍተኛ ብድር መስጠታቸውና የቁጠባ መጠን መቀነሱ ተጠቃሽ እንደኾኑ የባንኮቹ ሃላፊዎች መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። 7፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ በከተማዋ አንዳንድ ሆቴሎችና ሬስቶራንቶች "የአገሪቷን ሕጎች በሚጥስ" እና "ከማኅበረሰቡ ወግ ተቃራኒ በኾነ መልኩ" የግብረ ሰዶም እንቅስቃሴ ስለመኖሩ መረጃዎች እንደደረሱት ገልጧል። የከተማዋ ባሕል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከማኅበረሰቡ "ወግና ባሕል ያፈነገጡ" ድርጊቶች እያጋጠሙ መኾኑን መግለጡን ፖሊስ ጠቅሷል። ግብረ ሰዶማዊነት "በአገሪቱ ሕግ ፍጹም የተከለከ" እና "በሕግ የሚያስጠይቅ" መኾኑን የጠቀሰው ፖሊስ፣ በዚኹ ተግባር ዙሪያ የሚደርሱትን መረጃዎች መሠረት በማድረግ ርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል። ፖሊስ፣ በዚኹ ሕገወጥ ተግባር የሚጠረጠሩ ሆቴሎችና ሬስቶራንቶችም ሕግ አክብረው የመስራት ግዴታ አለባቸው ብሏል፡
367
9
" ግብረሰዶማዊነት በሀገራችን ህግ ፍፅሙ የተከለከና በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር ነው " - ፖሊስ የአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ወግ እና ባህልን ያፈነገጡ ድርጊቶችን አስመልክተው መግለጫ አውጥተዋል። " ሀገራችን በህብረ ብሄራዊነቷ የምትታወቅና የተለያዩ ባህሎችና ወጎች ያሏት ሀገር ነች፡፡ " ያሉ ሲሆን " ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከማህበረሰቡ ወግና ባህል ያፈነገጡ ድርጊቶች እያጋጠሙ ነው " ብለዋል። በከተማው አንዳንድ ሆቴሎችና ሬስቶራንቶች የሀገሪቷን ህግ በሚጥስና ከማህበረሰቡ ወግ ተቃራኒ በሆነ መልኩ የግብረሰዶም እንቅስቃሴ መኖሩን መረጃዎች እያመለከቱ መሆኑን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ መረጃ በመስጠት ተባባሪ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል። ፖሊስ ግብረሰዶማዊነት በሀገራችን ህግ ፍፅሙ የተከለከና በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር በመሆኑ ገልጾ በሚደርሰው መረጃ በመመስረት በህግ አግባብ እርምጃ እንደሚወስድ እያስታውቋል። በዚህ ህገ-ወጥ ተግባር የሚጠረጠሩ ሆቴል ቤቶች እና ሬስቶራንቶች የሀገርቷን ህግ አክብረው የመስራት ግዴታ እንዳለባቸው አሳስቧል። ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘ መረጃ እና ጥቆማ ያለው ማንኛውም ሰው በአቅራቢያው በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በግንባር በመቅረብ በተጨማሪም በነፃ የስልክ መስመር 991 እና 987 እንዲሁም በ011-1- 11-01-11 እና 011-5-52-63-02 በመጠቀም መረጃና ጥቆማ መስጠት እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ @adszena
311
10
ዐበይት ዜናዎች 1፤ የሚንስትሮች ምክር ቤት ዛሬ በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ በሙሉ ድምጽ ወስኗል። ሚንስትሮች ምክር ቤት ውሳኔውን ያሳለፈው፣ የክልሉ መንግሥት በክልሉ የተፈጠረውን የጸጥታ መደፍረስ "በመደበኛ የሕግ ማስከበር ሥርዓት" ለመቆጣጠር አዳጋች መኾኑን በመግለጽ፣ ፌደራል መንግሥቱ በክልሉ አስፈላጊውን የሕግ ማዕቀፍ እንዲደነግግ ትናንት በጠየቀው መሠረት ነው። ምክር ቤቱም፣ የክልሉ ኹኔታ "በመደበኛ የሕግ ማስክበር ሥርዓት ለመቆጣጠር ወደማይቻልበት ደረጃ" መሸጋገሩን ጠቅሷል። በክልሉ የተፈጠረው "ፈር የለቀቀ" እንቅስቃሴና "የታጠቁ ጽንፈኛ ቡድኖች ጥቃት"፣ የሕዝቡን አጠቃላይ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ ማስተጓጎሉንና "ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ መጣሉን" የጠቀሰው ምክር ቤቱ፣ "የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት ለማስጠበቅ" አስቸዃይ ጊዜ አዋጅ አስፈላጊ መኾኑን ገልጧል። 2፤ በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ ትናንት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አቅራቢያ "ከባድ ውጊያ" መካሄዱን ከከተማዋ ነዋሪዎች መስማቱን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል። መከላከያ ሠራዊት ዩኒቨርስቲውን ተቆጣጥሮ እንደነበርና በውጊያው ግን፣ የፋኖ ታጣቂዎች ሠራዊቱ ከዩኒቨርስቲው እንዲሸሽ ማድረጋቸውን ነዋሪዎች እንደነገሩት ዘገባው ጠቅሷል። ዜና ምንጩ፣ አንድ ስማቸው እንዲገለጥ ያልፈለጉ የአካባቢው የመንግሥት ባለሥልጣንም "ምክንያቱን ባይገልጡም" መከላከያ ሠራዊት ዩኒቨርስቲውን ለቆ መውጣቱን አረጋግጠውልኛል ብሏል። ሌላ ስሙ ያልተጠቀሰ የፋኖ ታጣቂ፣ ታጣቂዎቹ ከባሕርዳር ከተማ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መራዊ ከተማን መቆጣጠራቸውንና ባሕርዳርን ከበባ ውስጥ ለማስገባት መሞከራቸውን ገልጧል ተብሏል። 3፤ ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤኤፍ) ለኢትዮጵያ የገንዘብ ብድር ለመስጠት በቅድሚያ ከአገሪቱ የልማት አጋሮች የገንዘብ ድጋፍ ዋስትናና ከአበዳሪዎች በቡድን-20 ማዕቀፍ ስር በብድር ሽግሽግ ዙሪያ "ግልጽ የኾነ ቃል ኪዳን" ያስፈልጋል ማለቱን ብሉምበርግ ዘግቧል። መንግሥት ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት የ2 ቢሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት ጥያቄ አቅርቦ ንግግር ከጀመረ ሰነባብቷል። ድርጅቱ ብድር የሚለቀው፣ በመጀመሪያ በመንግሥትና በድርጅቱ ባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ከተደረሰና ከዚያም ጥያቄውን የድርጅቱ ቦርድ ካጸደቀው በኋላ ነው። ባኹኑ ወቅት የአገሪቱ የውጭ ዕዳ 28 ነጥብ 2 ቢሊዮን ደርሷል። 4፤ ሚንስትሮች ምክር ቤት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ እንዲኾን የሚያስችለውን ደንብ ዛሬ አጽድቋል። ሚንስትሮች ምክር ቤት ደንቡን ያጸደቀው፣ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነታቸው እንዲረጋገጥ ለማስቻል በቅርቡ የወጣውን የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች አዋጅ መሠረት በማድረግ ነው። ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ ኾኖ መዋቀሩ፣ አካዳሚያዊና አስተዳደራዊ ነጻነቱን አስጠብቆ የመማር ማስተማርና የምርምር ተልዕኮውን እንዲያከናውን ያስችለዋል። ደንቡ መጽደቁን ተከትሎ፣ ዩኒቨርሲቲው በአገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ኾኗል። 5፤ ትምህርት ሚንስቴር በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አንድ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ፈታኝና ኹለት ጸጥታ አስከባሪ ፌደራል ፖሊሶች መገደላቸውን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። ግድያውን የፈጸሙት፣ “የታጠቁ ኢመደበኛ ኃይሎች” ባካባቢው በነበረው መከላከያ ሠራዊት ላይ ተኩስ በከፈቱበት ወቅት እንደኾነ መግለጫውን የሰጡት ሚንስትር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል። በዚኹ ክስተት ሳቢያ፣ በሦስት ካምፓሶች 16 ሺህ ተማሪዎች ትናንት ከቀትር በኋላና ዛሬ ጧት የተሰጡ ፈተናዎችን ሳይወስዱ ቀርተዋል ተብሏል። 6፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ዛሬ ጧት በስኬት መጠናቀቁን ትምህርት ሚንስትር ብርሃኑ ነጋ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 28 ቀን በኹለት ዙር የተሰጠው ፈተና፣ "ከፈተና ሥርቆትና ኩረጃ ነጻ በሆነ መልኩ" መከናወኑን ሚንስትሩ አብራርተዋል። ዘንድሮ በአገር ዓቀፍ ደረጃ 840 ሺህ 859 የማኅበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን እንደወሰዱ ተገልጧል። ላለፉት ኹለት ዓመታት በጦርነቱ ሳቢያ መልቀቂያ ፈተና ያልወሰዱ የትግራይ ተፈታኞች፣ የማካካሻ ትምህርት ከተሰጣቸው በኋላ ከመሥከረም 29 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ፣ም ፈተና ይወስዳሉ ተብሏል። 7፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ጎንደር፣ ደሴ እና ላሊበላ ከተሞች ነገ እና ዕሁድ የሚያደርጋቸውን በረራዎች መሰረዙን ዛሬ በድረገጹ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል። አየር መንገዱ፣ ወደተጠቀሱት ከተሞች ለመብረር ትኬት የቆረጡ ደንበኞቹን በረራዎቹ እንደገና ሲጀመሩ ለማስተናገድ ዝግጁ መኾኑን ገልጧል። አየር መንገዱ ወደሦስቱ የአማራ ክልል ከተሞች ለምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ግን አላብራራም።
305
11
በአማራ ክልል አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ በሙሉ ድምጽ መወሰኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባ፣ የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በቀረበው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 አውጇል። በአማራ ክልል የተከሰተው በትጥቅ የተደገፈ ህገወጥ እንቅስቃሴ በመደበኛ የህግ ማስከበር ስርዓት ለመቆጣጠር ወደ ማይቻልበት ደረጃ የሚሸጋገሩ ተጠቁሟል። ሕገመንግስቱ እና ሕገመንግስታዊ ስርዓት ላይ የተቃጣ አደጋን በመደበኛ የሕግ ስርዓት ለመቆጣጠር ባልተቻለ ጊዜ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ ሕገመንግስታዊ መብት እንዳለው ተመልክቷል።
303
12
#ቅዱስ_ሲኖዶስ • የግጭት ተሳታፊዎች ካለፈው የጦርነት ውጤት ተማሩ። • የተፈጠረውን ችግር #በጥበብና #በማስተዋል ፤ በሰለጠነ አካሄድና በሰላማዊ መንገድ ተወያይታችሁ ፍቱ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም ስብሰባ በማድረግ ወቅታዊ ሀገራዊ ሰላምን በተመለከተ አጀንዳ በመቅረጽ በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ መግለጫ ሰጥቷል፡፡    ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም መደፍረስና የእርስ በርስ ግጭቶች ምክንያት የበርካታ ወገኖቻችን ውድ ሕይወት እያለፈ እና በርካታ የሀገርና የሕዝብ ሀብትና ንብረት እየወደመ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ትገልጻለች " ብሏል። " ሰላም ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ፍጡራን መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ " ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ  " ሰላም ከሌለ ቀድሶ ማቁረብ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ ማምረት፣ ተምሮ ማስተማር  ወልዶ ማሳደግ፣ ወጥቶ መግባት፣ አገር መምራትና ማስተዳደር አይቻልም ። በጥቅሉ ሰላም ሲጠፋ አብረው የሚጠፉ መልካም እሴቶቻችን ብዙ ናቸው፡፡ " ሲል አስገንዝቧል። ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ በቅርብ ጊዜ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት የበርካታ ወገኖቻችንን ሕይወት የቀጠፈ ከመሆኑም በላይ ከሞት የተረፉት ወገኖቻችንም ለስደትና ለረሀብ የዳረገ ፣ ለአካልና ለእእምሮ ስብራት ያጋለጠ ከመሆኑም በተጨማሪ በርካታ አድባራትና ገዳማትን እንዲሁም አብያተ ክርስቲያናትን ያፈረሰ እና መተኪያ የሌላቸውን ውድ ቅርሶቻችንን ያወደመ እጅግ በጣም አስከፊ ተግባር መሆኑን አስታውሷል። በመሆኑም ፡- በሀገራችን በኢትዮጵያ የተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነትና ግጭት ተወግዶ ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ልንማጸን ይገባል ብሏል። በሀገራችን በኢትዮጵያ አሁን ያለው የሰላም እጦትና የእርስ በርስ ግጭት ወደፊት ሊያስከትል የሚችለው ችግር ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ለአገራዊ ሰላም የበኩላቸውን ጥረት እንዱያደርጉ መልእክቱን አስተላልፏል። ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ በየትኛውም የሀገራችን ክፍል እየተደረጉ ባሉ ግጭቶች ተሳታፊ የሆኑ ወገኖች ካለፈው የጦርነት ውጤት በመማር የተፈጠረውን ችግር በጥበብና በማስተዋል እንዲሁም በሰለጠነ አካሄድና በሰላማዊ መንገድ ተወያይተው እንዲፈቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪዋን ከአደራ ጋር ታስተላልፋለች ብሏል።
293
13
የዛሬ ዐበይት ዜናዎች 1፤ የአማራ ክልላዊ መንግሥት በክልሉ በመንግሥት ኃይሎችና በታጣቂዎች መካከል የተፈጠረውን ግጭትና ቀውስ ፌደራል መንግሥቱ ጣልቃ ገብቶ እንዲቆጣጠር ጠይቋል። የክልሉ መንግሥት የፌደራል መንግሥቱ በክልሉ "አስፈላጊውን የሕግ ማዕቀፍ" በአፋጣኝ እንዲተገብር ጥያቄ ያቀረበው፣ በክልሉ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስ "በመደበኛ የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ኾኖ በመገኘቱ" እንደኾነ ማሳወቁን ዘገባው ጠቅሷል። በክልሉ የተፈጠረው "የጸጥታ መደፍረስና ጥቃት" በንጹሃን ዜጎችና በክልሉ ላይ ሰብዓዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያደረሰ መኾኑን የጠቀሰው የክልሉ መንግሥት፣ ኹኔታውን ባስቸኳይ ማስቆም እንደሚያስፈልግ ገልጧል ተብሏል። 2፤ በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር መባባስ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ክልሉ የሚያደርጋቸውን በረራዎች ለመሰረዝ መገደዱን ዋዜማ ተረድታለች። አየር መንገዱ ከትናንት ጀምሮ ወደ ጎንደር፣ ላሊበላና ኮምቦልቻ የሚያደርጋቸውን በረራዎች መሰረዙን ለማወቅ ተችሏል። ከጎንደር ከተማ በቅርብ ርቀት በምገኘው አዘዞ ከተማ፣ ዛሬ በመንግሥት ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የከባድና ቀላል መሳሪያ የተኩስ ድምጽ ሲሰማ መዋሉን፣ ዋዜማ ከሥፍራው ያገኘችው መረጃ ያመለክታል። 3፤ የፈረንሳይ ዜና ወኪል የአማራ ፋኖ ሚሊሻዎች የላሊበላ አውሮፕላን ማረፊያን በቁጥጥራቸው ስር እንዳደረጉ ከከተማዋ ነዋሪዎች ሰምቻለኹ በማለት ዘግቧል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም ወደ ጎንደርና ላሊበላ በረራ አቋርጫለኹ ማለቱን ዘገባው ጠቅሷል። በላሊበላ ከተማ ዙሪያ ግጭት መቀጠሉንና ከከተማዋ የሚያስወጡ መንገዶችን ታጣቂዎቹ እንደዘጉ ከከተማዋ ነዋሪዎች መስማቱንም ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል። 4፤ የኢትዮጵያ መንግሥትን የፋይናንስ አስተዳደር ለማሻሻል በአውሮፓ ኅብረት የገንዘብ ድጋፍ የሚተገበር ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ እንደተደረገ ገንዘብ ሚንስቴር አስታውቋል። በኅብረቱ የገንዘብ ድጋፍ ለቀጣዮቹ አራት ዓመታት የሚተገበረው ፕሮጀክት፣ የመንግሥት ተቋማትን የአመራር አቅም ለማጎልበት፣ ዘመናዊ የመንግሥት ፋይናንስ አገልግሎቶችን በታችኛዎቹ መንግሥታዊ መዋቅሮች ለመዘርጋት፣ በመንግሥት ተቋማት የበጀት አስተዳደር ክትትልን ለማሻሻልና የመንግሥትን የግዢ አገልግሎት ተቋማዊ አቅም ለማሳደግ ያለመ እንደኾነ ተገልጧል። አውሮፓ ኅብረት ለፕሮጀክቱ መተግበሪያ 10 ሚሊዮን ዩሮ መድቧል። 5፤ በጋምቤላ መምህራን ትምህርትና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በመውሰድ ላይ ባሉ ተማሪዎች ላይ ትናንት ያጋጠመውን "የጤና እክል" ፖሊስ እየመረመረ መኾኑን የክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ አስታውቋል። ፖሊስ ሦስት የኮሌጁን ምግብ አዘጋጆች በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገ መኾኑን ቢሮው ገልጧል። በተፈታኝ ተማሪዎቹ ላይ ያጋጠመው "የጤና እክል" ምክንያቱ "የምግብ መመረዝ" ወይም "የምግብ መበላሸት" ስለመኾኑ፣ የሕክምና ምርመራ እየተከናወነ መኾኑን ቢሮው ጠቅሷል። ቢሮው በተማሪዎች ሕይወት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለና፣ ተማሪዎቹ ሕክምና ላይ እንደኾኑ ገልጧል። ተፈታኞች የጤና እክል እንደገጠማቸው ግን ቢሮው አልጠቀሰም። 6፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ከነገ ጀምሮ እስከ ቀጣዩ ሳምንት ረቡዕ ድረስ ከማለዳው 12:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት በከተማዋ የሞተር ብስክሌቶች ትራንስፖርት አገልግሎትን ማገዱን አስታውቋል። ኾኖም እገዳው፣ በጸጥታና ትራፊክ ቁጥጥር ላይ የተሠማሩ የመንግሥት አካላትን እንደማይመለከት ቢሮው ገልጧል። የትራንስፖርት ቢሮው፣ የሞተር ብስክሌት አገልግሎትን ላንድ ሳምንት ለምን እንዳገደ ግን ማብራሪያ አልሰጠም።
309
14
ወቅታዊ " በአማራ ክልል ብዙ አካባቢዎች የኢንተርኔት ግንኙነቶች መቋረጣቸውን አረጋግጠናል " - ካርድ " የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል / ካርድ " በአማራ ክልል የተለያዩ አከባቢዎች የበይነመረብ አገልግሎት መቋረጡን ማረጋገጥ መቻሉን አመልክቷል። " የበይነመረብ ግንኙነትን ማቋረጥ ግጭቶችን ለመከላከል እና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን አይበጅም " ያለው ካርድ እገዳው እንዲነሳ ጥሪ አቅርቧል። በአማራ ክልል ብዙ አካባቢዎች የኢንተርኔት ግንኙነቶች መቋረጣቸውን ያመለከተው ካርድ  የኢንተርኔት ግንኙነቶቹ መቋረጥ ሰሞኑን ከተባባሱ ግጭቶች ጋር በተያያዘ እንደሆነ መገመት ይቻላል ብሏል። ድርጅቱ ፤ የበይነመረብ ግንኙነቶችን ማቋረጥ ለግጭቶች መፍትሔ አያመጣም የሚል አቋሙን ከዚህ ቀደም ደጋግሞ መግለፁን አስታውሶ " ይህ እርምጃ ይልቁንም የመረጃ መታፈን ከማስከተል ባሻገር ግጭቶቹን ለመቆጣጠር የሚወሰደው እርምጃ ያልተመጣጠነ እንዲሆን ዕድል ይሰጣል " ሲል አስረድቷል። ስለሆነም፣ መንግሥት የበይነመረብ ግንኙነቶችን ማቋረጡን እንዲያቆም እና ለግጭቶቹ ዘላቂ ፣ ሁሉን አካታች መፍትሔ እንዲያፈላልግ ጥሪ አቅርቧል።
289
15
ሐምሌ 26/2015 አጫጭር መረጃዎች 1፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና የፋኖ ሚሊሻዎች በደቡብ ጎንደር ዞን ዋና ከተማ ደብረ ታቦር አቅራቢያ ትናንትና ዛሬ ውጊያ ማካሄዳቸውን ሮይተርስ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የከተማዋን ሐኪምና ፖሊስ ጠቅሶ ዘግቧል። ሐኪሙ፣ በጥይትና በከባድ መሳሪያ በከባድ ኹኔታ የቆሰሉ ሦስት ሰዎችና ቀላል የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሌሎች 10 ሰዎች በከተማዋ ሆስፒታል የሕክምና ዕርዳታ ማግኘታቸውን እንደነገሩት ዘገባው ጠቅሷል። ዜና ምንጩ፣ ውጊው ዛሬም እንደቀጠለ መኾኑን፣ ወደ ከተማዋ የሚያስገቡ መንገዶች መዘጋታቸውንና ቁስለኞች ከሆስፒታሉ የሚደርሱት በእግር ጉዞ መኾኑን ሐኪሙ ነግረውኛል ብሏል። 2፤ በአማራ ክልል የፋኖ ታጣቂዎች በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ አካባቢ ዛሬም በመንግሥት ኃይሎች ጋር መጋጨታቸውን ዋዜማ ከአካባቢው ምንጮች ሰምታለች። ትናንትም በላሊበላ ከተማ አቅራቢያ በፋኖ ታጣቂዎችና ከመንግሥት ኃይሎች መካከል የተኩስ ልውውጥ እንደነበር የዋዜማ ምንጮች ገልጸዋል። በከተማዋ የሚገኙ ስፔናዊያን ከቤታቸውና ሆቴላቸው እንዳይወጡ ዛሬ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ መልዕክት አስተላልፏል። 3፤ የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ መንግሥታቸው በክልሉ የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር በውይይት ለመፍታት ዝግጁ መኾኑን ለክልሉ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ይልቃል ውይይት የሚፈልጉ አካላት ነፍጣቸውን አስቀምጠው ለውይይት እንዲቀርቡ ጥሪ አድርገዋል። መከላከያ ሠራዊት በክልሉ እያካሄደ ያለው "የሕግ ማስከበር" እንቅስቃሴ መኾኑን ይልቃል በድጋሚ ገልጸዋል። 4፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ በትግራይ ክልል አክሱም ጺዮን ማርያም ቤተክርስቲያን ሰሞኑን የኤጲስ ጳጳሳት ሹመት የሰጡ አራት ጳጳሳት "ከዲቁና ጀምሮ ያለውን ሙሉ ሥልጣነ ክህነታቸውን" መሻሩን አስታውቋል። ሲኖዶሱ ጳጳሳቱ በቤተክርስቲያኗ ላይ "የክህደት" እና "ኑፋቄ" ተግባር ፈጽመዋል በማለት፣ በውግዘት ከቤተክርስቲያኗ እንዲለዩና በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ መወሰኑን ገልጧል። ኾኖም ጳጳሳቱ፣ በድርጊታቸው ተጸጽተው ይቅርታ ከጠየቁ ቤተክርስቲያኗ የምኅረት በሯን እንደምትከፍትላቸው ሲኖዶሱ ገልጧል። ከቀኖና ውጭ የተሾሙ ዘጠኝ ኤጲስ ጳጳሳትም፣ በተመሳሳይ ተወግዘው የክህነት ማዕረጋቸው ተገፏል። 5፤ የደቡብ ክልል ምክር ምክር ቤት ከመጭው ዓርብ ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ጉባኤውን እንደሚያካሂድ አስታውቋል። የምክር ቤቱ ጉባኤ፣ ባለፈው የካቲትና ሰኔ በተካሄዱ ሕዝበ ውሳኔዎች መሠረት ለሚቋቋመውና "የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች" ክልል ተብሎ እንደሚሰየም ለሚጠበቀው አዲሱ ክልል ሥልጣን እንደሚያስረክብ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ፋጤ ሰርመሎ ለክልሉ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። 6፤ በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ለኹለት ዓመታት የመማር ማስተማር ሥራውን አቋርጦ የቆየው መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ተማሪዎቹን መቀበል ጀምሯል። ዩኒቨርስቲው ዛሬ መቀበል የጀመረው፣ የጦርነቱን መቀስቀስ ተከትሎ የመማር ማስተማር ሥራውን ባቋረጠበት ዓመት ዕጩ ተመራቂ የነበሩ ተማሪዎችን ነው። በትግራይ ክልል ከሚገኙት የፌደራል ዩኒቨርስቲዎች መካከል፣ አዲግራትና አክሱም ዩኒቨርስቲዎች ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ቀደም ብለው የምዝገባ ጥሪ አስተላልፈው ነበር። 7፤ ትናንት ምሽት 2:15 ገደማ ከአሥመራ ደቡባዊ ምሥራቅ 55 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ 5 ነጥብ 6 የተለካ ርዕደ መሬት መከሰቱን የአሜሪካው ጅዖሎጂካል ጥናት ተቋም አስታውቋል። የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል፣ ርዕደ መሬተ መከሰቱን በትዊተር ገጻቸው አረጋግጠዋል። ርዕደ መሬቱ የተከሰተው፣ ከከርሰ ምድር በታች 10 ኪሎ ሜትር ላይ እንደኾነ የተቋሙ መረጃ አመልክቷል። ይህንኑ ተከትሎ፣ በትግራይ ክልል በመቀሌ፣ አክሱም፣ አድዋና አዱግራት ከተሞች የመሬት ንዝረት ተከስቷል። በርዕደ መሬቱና በንዝረቱ የደረሰ ጉዳት የለም ተብሏል። 8፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ7879 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ8837 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 66 ብር ከ7582 ሳንቲምና መሸጫው 68 ብር ከ0934 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ60 ከ0475 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ61 ብር ከ3485 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል።
305
16
1፤ በግጭት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ የማልማት ፕሮጀክት አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ ለ2016 ዓ፣ም በግጭት ለተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋሚያና ግንባታ የሚውል 60 ሚሊዮን ዶላር ማጽደቁን ገንዘብ ሚንስቴር ዛሬ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል። በግጭት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ የማልማትና የማቋቋም ፕሮጀክቱ፣ በትግራይ፣ አማራ፣ አፋር፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝና ኦሮሚያ ክልሎች ሲተገበር የቆየ መርሃ ግብር ነው። ለተይዘው በጀት ዓመት ለመርሃ ግብሩ የተመደበው በጀት፣ በኢትዮጵያ መንግሥትና በዓለም ባንክ መካከል በተደረገ ስምምነት ለአምስት ዓመታት ተግባራዊ እንዲኾን የተመደበው የ300 ሚሊዮን ዶላር በጀት አካል ነው፡፡ 2፤ የመንግሥት ኃይሎችና የአማራ ፋኖ ታጣቂዎች ትናንት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን መከት ወረዳ አስተዳደር ዋና መቀመጫ በኾነችው ፍላቂት ገረገራ ከተማ የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ዋዜማ ከዓለማቀፍ ረድኤት ድርጅቶች ምንጮች ተረድታለች። በኹለቱ ወገኖች የተኩስ ልውውጥ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች እንደሞቱና ቁስለኛ እንደኾኑ ምንጮቹ ገልጸዋል። ባለፈው ሳምንትም፣ በሰሜን ወሎ ዞን በመከላከያ ሠራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ መደረጉንና የሰው ሕይወት መጥፋቱን የረድኤት ድርጅቶች ምንጮች ጠቅሰው ነበር። 3፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት ምክትል አስተዳዳሪና የጸጥታ ቢሮ ሃላፊ ጀኔራል ታደሠ ወረደ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት መሠረት 50 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎች ትጥቅ እንደፈቱ ዛሬ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ትጥቅ የፈቱት የቀድሞ ተዋጊዎች በየወረዳቸው ከኅብረተሰቡ ጋር እየተቀላቀሉ መኾኑን ጀኔራል ታደሠ እንደገለጡ ዘገባው ጠቅሷል። ወደፊት ትጥቅ የሚፈቱ ተጨማሪ የቀድሞ ተዋጊዎች ይኖሩ እንደኾነ ጀኔራል ታደሠ ስለመጥቀሳቸው ዘገባው አላመለከተም። 4፤ የአዲስ አበባ አስተዳደር ለመኖሪያ ቤት ግንባታ በአጋርነት ለመስራት የመረጣቸው የግል ሪል ስቴት አልሚዎች ከግማሽ ትሪሊዮን ብር በላይ በኾነ ወጪ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሊጀምሩ መኾኑን ሪፖርተር ዘግቧል። አስተዳደሩ በቀረጸው 70/30 የመንግሥትና የግል አጋርነት የቤት ግንባታ መርሃ ግብር እንዲሳተፉ የመረጣቸው 68 ሪል ስቴት አልሚዎች ናቸው። መኖሪያ ቤቶቹን ለመገንባት ከተመረጡት መካከል፣ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ ፍሊንትስቶን ሆምስና ጊፍት ሪል ስቴት እንደሚገኙበት ዘገባው ጠቅሷል። የከተማ አስተዳደሩ ድርሻ ከሊዝ ነጻ የኾነ የመኖሪያ ቤት መገንቢያ መሬት ማቅረብ ሲኾን፣ አልሚዎቹ ደሞ ቤቶቹን ገንብተው ማጠናቀቅና 30 በመቶውን ለከተማ አስተዳደሩ ማስረከብ መኾኑን ዘገባው አመልክቷል። 5፤ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚንስቴር ሐምሌ 16 ቀን ብቻ ከ20 ሺህ 411 ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ከጅቡቲ ወደብ ወደ አገር ውስጥ ማጓጓዙን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ሚንስቴሩ፣ ከሐምሌ 14 እስከ 16 ባሉት ሦስት ቀናት ያጓጓዘው 60 ሺህ 542 ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ መኾኑን ገልጧል። በተከታታይ ቀናት ተጨማሪ የጭነት ካሚዮኖችን ወደ ወደብ በማስገባት ወደብ ላይ የተከማቸውንና ወደፊት ወደ ወደብ የሚገባውን ማዳበሪያ በፍጥነት እንደሚያጓጉዝም ሚንስቴሩ ጨምሮ ገልጧል። 6፤ የአፍሪካና ሩሲያ የመሪዎች ጉባኤ በሩሲያዋ ፒተርስበርግ ከተማ ነገ እና ከነገ ወዲያ በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ሰብዓዊ ዕርዳታ ትብብር ዙሪያ ይመክራል። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በጉባኤው ላይ እንደሚገኙና፣ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር በተናጥል እንደሚወያዩ የሩሲያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። በጉባዔው ላይ ከሚሳተፉት መሪዎች መካከል፣ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ፣ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ፣ የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቪኒ እና የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ይገኙበታል። የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በጉባኤው ላይ አፍሪካ ኅብረት ይወክለኝ ማለታቸውን የኬንያ ጋዜጦች ዘግበዋል። 7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ7370 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ8317 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 67 ብር ከ0778 ሳንቲምና መሸጫው 68 ብር ከ4194 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ60 ከ4461 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ61 ብር ከ6550 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል።
439
17
አጫጭር ዜናዎች 1፤ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ ኤም-ፔሳ የተሰኘውን የሞባይል ገንዘብ መላላኪያና መገበያያ አገልግሎት እስከ ቀጣዩ ዓመት መስከረም ወር ድረስ ለመጀመር ማቀዱን ቢዝነስ ደይሊ ዘግቧል። የኤም-ፔሳ መጀመር የኩባንያውን ገቢ በማሳደግ፣ ኩባንያው በሦስት ዓመታት ውስጥ ወደ ትርፋማነት እንዲሸጋገር እንደሚያስችለው የኩባንያው ባለ ድርሻ የኾነው የእንግሊዙ ቮዳኮም ኩባንያ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ ባኹኑ ወቅት 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሞባይል ስልክ ደንበኞች እንዳሉት ገልጧል። 2፤ የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ባኹኑ ወቅት በተለያዩ ስደተኛ ጣቢያዎችና የድንበር መቀበያ ቦታዎች 10 ሺህ ሱዳናዊያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች እንደሚገኙ ዛሬ ባወጣው መረጃ አስታውቋል። ከሱዳኑ ግጭት የሸሹ 7 ሺህ ሰዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ በኩርሙክ የድንበር መግቢያ ቦታዎችና 9 ሺህ 800 ሰዎች ደሞ በመተማ "ማንደፍሮ ተራራ" እና "ኩመር" በተባሉ መግቢያ ቦታዎች ላይ እንደሚገኙ ቢሮው ገልጧል። ኾኖም ባለፈው ሳምንት ከሱዳን በመተማና ኩርሙክ በኩል የሚገቡ ሰዎች ቁጥር ካለፉት ሳምንታት መቀነሱን ቢሮው አመልክቷል። በተያያዘ፣ የመተማ አጎራባች በኾነችው ቋራ ወረዳ ሰሞኑን ስምንት የኮሌራ በሽተኞች መገኘታቸውን ተከትሎ፣ የበሽታውን ሥርጭት ለመቆጣጠር ከቋራ የመተማ ከተማ አቅራቢያ ወደኾነችው ገንዳውሃ ከተማ የሚወስደው መንገድ ላልተወሰነ ጊዜ ተዘግቷል ተብሏል። 3፤ ሂውማን ራይትስ ዎች ላለፉት ሦስት ዓመታት ክስ ሳይመሠረትባቸው በእስር ላይ የሚገኙ ሰባት የተቃዋሚው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር አመራሮች ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቋል። የፓርቲው አመራሮች ከእስር እንዲለቀቁ ተደጋጋሚ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ቢተላለፍም፣ መንግሥት ግን ሊፈታቸው እንዳልቻለ ድርጅቱ ገልጧል። ታሳሪዎቹ ለጠበቆቻቸውና ቤተሰቦቻቸው ሳይነገራቸው፣ ወደተለያዩ ማቆያ ቦታዎች እንደተዛወሩ ድርጅቱ ጠቅሷል። 4፤ ጠይባ ሐሰን የስደተኞችና የስደት ተመላሾች አገልግሎት ዳይሬክተር ጀኔራል ኾነው በጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ እንደተሾሙ ተቋሙ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ጠይባ እስከሹመታቸው ዕለት ድረስ የተቋሙ ምክትል ዳይሬክተር ጀኔራል ኾነው በማገልገል ላይ ነበሩ። ጠይባ የተቋሙ ዳይሬክተር ጀኔራል ኾነው የተሾሙት፣ ተቋሙን ለኹለት ዓመታት ከስድስት ወር በዳይሬክተር ጀኔራልነት የመሩት ተስፋሁን ጎበዛይ ባለፈው ሳምንት ከሃላፊነት መነሳታቸውን ተከትሎ ነው። ጠይባ ቀደም ባሉት ዓመታት፣ በኦሮሚያ ክልል የሻሸመኔ ከተማ ከንቲባ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የጠቅላይ ሚንስትሩ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ኾነው አገልግለዋል። 5፤ እናት ፓርቲ መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን "እንደ ተቋም ጸንታ እንዳትቆም በእጅ አዙር ጉልህ የማፍረስ ሥራ እየሠራ" ነው ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ከሷል። መንግሥት የጎሳ ፖለቲካን ቤተክርስቲያኗ ውስጥ "በማስረጽ"፣ "በመጫን"፣ "ከፋፋዮችን ደግፎ በማሠማራት" እና "ለእኩይ አዓማቸው አስፈላጊውን ኹሉ" ያደርጋል በማለት ፓርቲው ወቅሷል። በኦሮሚያና ትግራይ ክልሎች ቤተክርስቲያኗን ለማፍረስ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉት አካላት ባልተናነሰ ፌደራል መንግሥቱና የኦሮሚያና ትግራይ ክልላዊ መንግሥታት "እኩል ተጠያቂነት አለባቸው" ያለው ፓርቲው፣ የፌደራሉና የትግራይ ክልላዊ አስተዳደር በትግራይ በቅርቡ የተጀመረው "ሕገ ቤተክርስትያን የጣሰ" እንቅስቃሴ ወደ ትክክለኛው የእርምት ሂደት እንዲመለስ እንዲያደርጉ ጠይቋል። 6፤ ኢትዮ ቴሌኮምና የኢትዮጵያ ኮምንኬሽን ባለሥልጣን ትርፋማ ባልኾኑ ገጠራማ አካባቢዎች የቴሌኮም መሠረተ ልማቶችን የማስፋፋያ ወጪ ማን መቻል እንዳለበት ውዝግብ ላይ መኾናቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። ኢትዮ ቴሌኮም ውድድር ውስጥ እንደገባ አትራፊ ኩባንያ ትርፍ በማያስገኙ የአገሪቱ አካባቢዎች የቴሌኮም መሠረተ ልማቶችን የመዘርጋት ግዴታ እንደሌለበት ሲገልጽ ቆይቷል። የኩባንያው ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፣ ባለሥልጣኑ ከቴሌኮም ኩባንያዎች ገቢ በየዓመቱ ከሚሰበስበው 1 ነጥብ 5 በመቶ መዋጮ ኹለንተናዊ የቴሌኮም ተደራሽነትን ማረጋገጥ ሃላፊነቱ መኾኑን ባለፈው ሳምንት ተናግረው ነበር። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ባልቻ ሬባ ግን፣ የፍሬሕይወትን አስተያየት "አሳሳች" በማለት ውድቅ እንዳደረጉትና ኩባንያው ኹለንተናዊ ተደራሽነትን ማስፋፋት ግዴታው ኾኖ ይቀጥላል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
516
18
የእለቱ ዜናዎች 1፤ የኢትዮጵያ የስደተኞችና ስደት ተመላሾች አገልግሎት ዳይሬክተር ጀኔራል ተስፋሁን ጎበዛይ ከዛሬው ዕለት ጀምሮ ከሃላፊነት መልቀቃቸውን በትዊተት ገጻቸው ባሠራጩት የስንብት ደብዳቤ አስታውቀዋል። ተስፋሁን፣ ተቋሙን ላለፉት ኹለት ዓመታት ከመንፈቅ የመሩ ሲኾን፣ አኹን "ወደ አዲስ ሃላፊነት" መዛወራቸውን ገልጸዋል። ጠይባ ሐሰን፣ ሙሉዓለም ደስታ፣ ያዕቆብ ያላ እና "ተቋሙን የተቀላቀለው አዲስ አመራር" ሃላፊነቱን ተረክቦ ሥራዎችን ያስቀጥላል የሚል እምነት እንዳላቸው ተስፋሁን ገልጸዋል። 2፤ ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ኮይ (ሲፒጄ) በ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" የበይነ መረብ ብዙኀን መገናኛ ቢሮ ላይ የተፈጸመውን ዘረፋ ላይ ፖሊስ የዘረፋውን ምክንያት ለማወቅና አጥፊዎችን ተጠያቂ ለማድረግ "አፋጣኝ" እና "ተዓማኒ" ምርመራ እንዲደረግ አዲስ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። በድርጊቱ ዙሪያ ግልጽ ምርመራ ማድረግ "ሌሎች መገናኛ ብዙኀን ሥራቸውን ያለ ስጋት እንዲሠሩ" እንደሚያስችል ድርጅቱ ገልጧል። የ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" መስራችና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ተስፋለም ወልደየስ፣ ድርጊቱ "የዘፈቀደ ዘረፋ" እንዳልሆነና "በተቋሙ ቪዲዮ የመስራት አቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ጠቃሚ መሳሪያዎች ብቻ ተለይተው እንደተወሰዱ" መናገሩን መግለጫው ጠቅሷል። 3፤ የቻይና ኮሚንስት ፓርቲ የውጭ ግንኙነትና ዓለማቀፍ ጉዳዮች ሃላፊ ዋንግ ዩ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ከዋንግ ዩ ጋር በጽሕፈት ቤታቸው መወያየታቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስታውቀዋል። ዋንግ ዩ በአዲስ አበባ ቆይታቸው፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በቻይናና ኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ትብብሮች ዙሪያ ይመክራሉ ተብሏል። ዋንግ ዩ እስከ ቅርብ ወራት ድረስ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ነበሩ። 4፤ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ዘለንስኪ ትናንት ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት ላይ ዐቢይ ዩክሬንን እንዲጎበኙ እንደጋበዟቸው በኦፊሴላዊ ድረገጻቸው አስታውቀዋል። ዐቢይ ለጉብኝት ግብዣው ምን ምላሽ እንደሰጡ ዘለንስኪ አልጠቀሱም። ዘለንስኪ፣ ሩሲያ የዩክሬን የእህል ምርቶችን ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ከተደረሰው ስምምነት "በተናጥል" መውጣቷን ለዐቢይ እንደገለጡላቸውም ጠቅሰዋል። ዩክሬን 90 ሺህ ቶን እህል በሰብዓዊ ዕርዳታ መልክ ለኢትዮጵያ መለገሷንና 300 ሺህ ቶን እህል በዓለማቀፍ የረድዔት ድርጅቶች አማካኝነት ለኢትዮጵያ እንደተላከ ለዐቢይ አንስቸላቸዋለኹ ብለዋል። 5፤ ኹለተኛው የአፍሪካና ሩሲያ የጋራ የመሪዎች ጉባዔ በቀጣዩ ሳምንት በሩሲያ በፒተርስበርግ ከተማ ይካሄዳል። የመሪዎቹ ጉባዔ፣ አፍሪካና ሩሲያ በሰላም፣ ጸጥታና ልማት ዙሪያ ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር በሚቻሉበት ኹኔታ ዙሪያ ይመክራል። የአፍሪካና ሩሲያ የመሪዎች ጉባዔ፣ ባለፈው ጥቅምት ወር ገደማ በአዲስ አበባ እንዲካሄድ ታስቦ የነበረ ቢኾንም፣ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ሳቢያ ጊዜው ተራዝሞ የጉባዔው አስተናጋጅም ሩሲያ እንድትኾን እንደተወሰነ ይታወሳል። 6፤ ከ40 በላይ አገራት የ"ብሪክስ" ቡድን አባል ለመኾን ጥያቄ ማቅረባቸውን የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት መናገራቸውን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል። "ብሪክስ" ከመስራቾቹ ቻይና፣ ሩሲያ፣ ሕንድ፣ ብራዚልና ደቡብ አፍሪካ ውጭ አዲስ አባል ተቀብሎ አያውቅም። ደቡብ አፍሪካ በነሃሴ የምታዘጋጀው የ"ብሪክስ" መሪዎች ጉባኤ፣ ቡድኑ አዳዲስ አባላትን በሚቀበልበት ኹኔታ ዙሪያ ይመክራል። እስካኹን ኢትዮጵያን ጨምሮ 22 አገራት የቡድኑ አባል ለመኾን በይፋ ጥያቄ እንዳቀረቡ ባለሥልጣናቱ እንደተናገሩ ዘገባው ጠቅሷል። ጋቦን፣ ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ፣ ሳዑዲ ዓረቢያና የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶችን ጨምሮ ተመሳሳይ ቁጥር ያላቸው አገሮች ደሞ ለአባልነት ፍላጎታቸውን ገልጸዋል ተብሏል።
627
19
#Update ዛሬ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሰላም ልኡካኑ መቐለ ትግራይ ሲደርሱ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካብኔ ጉዳዮች ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋ እና ሌሎች የክልሉ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ልዑኩ በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርስ በትግራይ ጊዚያዊ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ በተለያዩ ማህበራትን የማህበረሰብ ወኪሎች እና ወጣት ዘማርያን ደማቅ አቀባበል ይደረግለታል ተብሎ በመርኃግብሩ ቢገለጽም በስፍራው የትግራይ ክልል የሃይማኖት አባቶች ፣ ዘማርያን #እንዳልተገኙ ለማወቅ ተችሏል። በመቀጠል ልዑኩ በክልሉ በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች እገዛ የሚውል 20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በፕላኔት ሆቴል በተደረገ መርኃግብር ላይ ያስረከበ ሲሆን በትግራይ ያሉ የሃይማኖት አባቶች ግን በሥፍራው አልታደሙም። ደጋፉን የተቀበሉት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከቅድስት ቤተከርስትያንዋ የተበረከተውን ድጋፍ የዘገየ ቢሆንም የሚበረታታ ነው ብለዋል። በቅዱስ ሲኖዶሱና በትግራይ አብያተ ክርስትያናት አባቶች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ከተካሄደው ጦርነት ተያይዞ አንዳንድ ጳጳሳት ባደረጉዋቸው ከሃይማኖት ያፈነገጡ ንግግሮች ግንኙነቱ እንዲሻከር ምክንያት መሆኑና፤ ይህን ቅሬታ የፈጠረው አለመግባባት በመመካከር በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት የረፈደ ቢሆንም የሚደገፍ ነው ብለዋል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም ፥ ቅዱስ ሲኖዶሱ ቤተከርስትያንዋ በጀመረችው ጥረት የወደሙ ቤተእምነቶችን ከመገንባትና የተጎዱ የሃይማኖት አባቶች ከመደገፍ በዘለለ የተፈጠረው መቃቃር እንዲሻር በልዩ ጥንቃቄና ፅናት በመስራት ግንኙቱ ተሻሽሎ ትክክለኛ መንፈሳዊ ሂወት እንዲቀጥል ለማድረግ በሚሰራው ስራ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባሰሙት ቃል በትግራይ የተካሄደው ጦርነት ለማቆም ቅዱስ ሲኖዶሱ በግዜው ድምፁ ባለማሰማቱ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል ፣ ይቅርታው የበለጠ እንዲጠናከር ውይይት እጅግ አሰፈላጊ መሆኑ በመገንዘብ የትግራይ የሃይማኖት አባቶች ተባባሪ እንዲሆኑ አባታዊ ምክር አስተላልፈዋል። ያለፈው ዘግናኝና አሳፋሪ ጦርነት ለማቆም የትግራይና የፌደራል መንግስት ሃላፊዎች በፕሪቶሪያ የፈረሙት ስምምነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የሃይማኖት አባቶች ይህንን ፈለግ ተከትለው  በመወያየት መግባባት እና አንድነት መፍጠር ይገባቸዋል ብለዋል። በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ በተመራው የሰላም ልዑክ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ አትሌት ደራርቱ ቱሉና ሌሎች ተገኝተዋል።
524
20
አጫጭር ዜናዎች 1፤ የመንግሥት ባለሥልጣናት በስማቸው ወይም በቅርብ ቤተሰባቸው የተመዘገቡ የንግድ ኩባንያዎችን ወይም የአክሲዮን ድርሻዎችን እንዲያቋርጡ ወይም ለሌላ አካል እንዲያስተላልፉ የሚያስገድድ ረቂቅ ደንብ መውጣቱን ሪፖርተር ዘግቧል። የባለሥልጣናትን የጥቅም ግጭት ማስቀረትን ዓላማው ያደረገውን ረቂቅ ደንብ ያዘጋጀው፣ የጸረ-ሙስና ኮሚሽን እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል። የመንግሥት ባለሥልጣናት ኢንቨስትመንታቸውንና የግል ኩባንያቸውን በወኪሎቻቸው አማካኝነት እንዲመሩ፣ የኩባንያቸውን ካፒታልና ትርፍ በግል ማዘዝ በማይችሉበት የባንክ ሒሳብ እንዲያስቀምጡ ወይም በኩባንያዎች የያዟቸውን ከፍተኛ ሃላፊነቶች እንዲለቁ ያስገድዳል ተብሏል። 2፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የተመራ የቤተክርስቲያኗ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በቅርብ ቀናት ውስጥ ወደ መቀሌ እንደሚጓዝ የቤተክርስቲያኗ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል። የልዑካን ቡድኑ ጉዞ ዓላማ፣ የቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ ለክልሉ ለመስጠት የወሰነውን ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማድረስና በትግራይ ከሚገኙ የቤተክርስቲያኗ ጳጳሳት ጋር "በሰላም ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር" እንደኾነ መምሪያው ገልጧል። በልዑካን ቡድኑ ውስጥ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ያቋቋመው የሰላምና አቀራራቢ ኮሚቴ አባላት እንደተካተቱ መምሪያው ጨምሮ አመልክቷል። 3፤ ፌደሬሽን ምክር ቤት ነገ እና ከነገ ወዲያ በደቡብ ክልል ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ያካሄዱትን የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ ውጤት ለማጽደቅ እንደሚሰበሰብ መስማቱን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። ምክር ቤቱ ውጤቱን የሚያጸድቀው፣ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የሚያቀርብለትን የሕዝበ ውሳኔ ሪፖርት መሠረት በማድረግ እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል። ወላይታ ዞንን ጨምሮ ስድስቱ ዞኖችና አምስቱ ልዩ ወረዳዎች በሕዝበ ውሳኔው በከፍተኛ ድምጽ ከደቡብ ክልል ተነጥለው በጋራ አንድ ክልል ለማቋቋም መወሰናቸው ይታወሳል። አዲሱ ክልል "ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል" ተብሎ እንደሚሰየም ይጠበቃል። 4፤ ሰሞኑን ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ጨምሮ ስድስት የአይኤስ የሽብር ቡድን አባላት ፑንትላንድ ራስ ገዝ ውስጥ ለመንግሥት ጦር እጃቸውን እንደሰጡ የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። እጃቸውን ለመንግሥት ከሰጡት የቡድኑ ተዋጊዎች መካከል፣ አራቱ ኢትዮጵያዊያን እንዲኹም ሁለቱ ሱዳናዊያን እንደኮኑ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ተዋጊዎቹ በቡድኑ ተመልምለው ላንድ ዓመት ያህል ወታደራዊ ሥልጠና ሲወስዱ እንደቆዩ መናገራቸው ተገልጧል። ቡድኑ በተለይ ወደ ቦሳሶ ወደብ ለሥራ ወይም ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለመሻገር የሚሄዱ የውጭ ዜጎችን ለምልመላ ዒላማ በማድረግ ይታወቃል።
439