ሰናይ ግጥም
Open in Telegram
ሰው ማለት ሰው ያጣለት ለሰው የቆመ ሰው ማለት ነው 😍 ✍️ Creater @Amele_Senai ተቀላቀሉን @gitimochi
Show more1 220
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 220
ወርቃማ አባባሎች
* ፍቅር የስሜቶች ሁሉ መዝሙር ነው።/አርስቶትል/
* ፍቅር የተፈጥሮ ሁለተኛ ብርሃን ናት።/ማርቲን ሉተር/
* ፍቅር የአንድ ሰው ከሁሉም በላይ የላቀ ስጦታ ነው።
/ጆአንአኒሲን/
* ከፍቅር ሁሉ የጀማሪ ፍቅር ንፁህ ነው።/ ከቃል መፅሀፍ/
* የምግብ ፍላጎት የሚዘጉ ሁለት ነገሮች ብቻ ናቸው፥ትካዜ እና ፍቅር
@giximochi
1 220
✅️ሁላችንም ሁለት ኪሶች ሊኖሩን ይገባል !!
****
እንዴት ታደርጋለህ መሰለህ?🤔
✅️ሁሌም ሁለት ኪሶች ይኑሩህ:: ሁለቱም ኪሶች ውስጥ እጅህን ስትሰድ የተለያዩ ወረቀቶችን ታገኛለህ : ሁለቱም ወረቀቶች የተለያየ ጽሁፍ እንዲኖር አድርግ
ስትጨነቅ: ብቸኝነት ሲሰማህ: ሲከፋህ እና አቅም ሲያንስህ እጅህን ወደ ቀኝ ኪስህ ትሰድና ወረቀቱን አውጥተህ ታነባለህ
እንዲህ ይላል:
👇🏾
✅"አለም የተፈጠረችው ለእኔ ነው : የማያልፍ የለምና ይህም ያልፋል:: ብርቱ እሆናለሁ: በፈተናም እፀናለሁ"
*
✅በሌላ ጊዜ ደግሞ አለም በእጅህ የገባች ሲመስልህ: ኪስህ ሲሞላ እና ሰው ሁሉ ሲያሸበሽብልህ እጅህን ወደ ግራ እጅህ ኪስህን ትሰድና ወረቀቱን አውጥተህ ታነባለህ
እንዲህ ይላል:
👇🏾
⭐“ከአፈር ነው የመጣሁት : ወደ አፈርም እመለሳለሁኝ:: ሸክላ ነኝና በማንኛውም ጊዜ ተሰባሪ ነኝ”
🙌🏼❤️
1 220
የእኔ አባት የእኔ ደግ የኔ የዎህ ነፍስህን በአፀደ ገነት ያኑርልን በጣም ነው የምወደህ ጎበዝ ሰራተኛ ነህ ከኑሮ በአሜሪካ እስከ እስከ እሁድን በኤቤስ 😭😭😭😭😭
1 220
ለፈገግታ
በአንድ ሰፈር የሚኖሩ አንድ ብልጥ እና አንድ ሞኝ ልጅ ነበሩ፤
ከእለታት አንድ ቀን ብልጡ ልጅ ሞኙን በመጣራት ና..... እንጫወት ሲል ጠየቀው።ሞኙ ልጅም "እኔ ጨዎታ አልችልም" ሲል መለሰለት። በመቀጠልም ብልጡ ልጅ፤ "እሺ እንቆቅልሽ እንጫዎት"
በማለት ሲጠይቀው፤አሁንም በድጋሚ አልችልም ይለዋል።" እንቆቅልሽ የምንጫወተው እኮ እኔ አንድ ብር፤አንተ ደግሞ 50 ሳንቲም አስይዘህ የጠፈው/ያላወቀ/ ይባላል" ይላል ብልጡ ልጅ።ሞኙ ልጅ በዚህ ሀሳብ ይስማማል፤ጨዋታውን ሞኙ ልጅ ይጀምራል
እንቆቅልህ
ምን አውቅልህ
አስራ ሁለት እግር ያለው በሰማይ ላይ የሚሄድ ሲል ይጠይቀዋል
ብልጡም ይግባኝ አላውቀውም
መልሱን ንገረኝ ሲል ብልጡ ልጅ ይጠይቀዋል።ሞኙም መልሱን
አላውቀውም ሃምሳ ሳንቲምክን እንካ አለው ይባላል🤣🤣
@gitimochi
@gitimochi
1 220
ሁለት ልደት አሉት
እንዴት ማለት
አንድ በአባቱ አለም ሳይፈጠር
ሁለት በእናቱ በድንቅ ምስጢር
.........
የኢያቄብ የሀናን ልጅ ማርያም
እንዴት ቢወዳት ነው እንዴት ቢያከብራት
የአለሙን ጌታ በእቅፎ ያስታቀፋት
አንቺ ቤተልሄም የእንጀራ ቤታችን
ምንኛ ታደለሽ አንቺን ሲመርጥሽ
ቤተ መንግስቱ ለእሱ ሆኖል ቆሻሻ
በረት ውስጥ ተወልዶል ትህትናን ሲሻ
የተወለድከው ለእኛ ደስታ ለራስህ መከራ
ለእኛ የወርቅ አክሊል ለራስህ የእሾህ አሜኬላ
ለይስሀቅ ወርዶል ነጭ በግ ሊታረድ
አንተ ግን አንተ ነህ ኢየሱስ የመስዋቱ በግ
አለምን የሚፈውስ የሚያድነው
የአንተ ደም ብቻ ነው
እንኳን ተወለድክ የአለሙ ጌታ
የአዳምን እንባ ለውጠህ አደረከው ደስታ
የመወለድህ ረቂቅነት ቢያስደንቅም
ዓለምን ከአዳንክብት ምስጢር ግን አይበልጥም።
እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን። እመቤቴ ማርያም ሆይ የማህፀንሽ ፍሬ የተባረከ ነው እና ደስ ይበለሽ🙏
ደስታ የተባለውን ንጉስ ክርስቶስን ወልደሽልናልና ምስጋና ይገባሻል?።
ሀገራችንን ሰላም አርግልን
መልካም የልደት በዓል
#ገና ታህሳስ 28 እለት ሰንበት
✍ሰናይት ሲሻው
@gitimochi
@gitimochi
1 220
ለፍቅር መስፈርትሽ ምን ይሆን?
አለ አይኖን እያየ
መልሶን ሲጠብቅ ዝም ብላ አይን አይኑን አየችው
ከብዙ ዝምታ በኋላ,,,,,,,,, በእርግጠኝነት ቤት ይሆን መኪና ሲል በግንባሩ ተለማመጣት
አሁን ዝም ማለት አልቻለችም,,,,,,ቤት ያረጃል ይሰለቻል እድል ከለለህ መንግስት ለስራ ብሎ ይወስደዋል ፡መኪናም ጋራጅ ትገባለች ስትል ንግግሮን ዘጋች።
ታፈቅሪኛለሽ?,,,,,,, አለ
ዙሪያ ቀኞን አይታ አላውቅም እያለች ቦርሳዋን ይዛ ሄደች ።
ከዚያ ቀን በኃላ አይቶት አያውቅም ከዓመታት በኋላ እሱ ልጆቹን እና ሚስቱን ይዞ አንድ ሬስቶራንት ተገናኙ በጣም ደስ አላት ከሚስቱ እና ከልጆቹ ጋር አስተዋወቃት እና ጣቶን ሲያይ ምንም ቀለበት የለም ግራ በመጋባት ስትነሳ እየሸኛት ፤የፍቅር መስፈርትሽን አላገኘሽውም እስካሁን አዳም እንዴት እነዚ የሚያምሩ ጣቶችሽ ላይ ቀለበት አላረግም ሲል ጠየቃታ
እንዲውም በአርምሞ የምትታወቀው ሄዋን የምወደው የማፈቅረው ሰው ከፊት ለፊት ቆሟል ግን ለዚ ሰው አባ የሚለው ጩጬ ልሰጠው አልታደልኩም አለች እምባ እያነቃት ስታለቅስ ለመጀመሪያ ጊዜ አያት አሳዘነችው ቀጠለችለት መስፈርቴ ለሚያፋቅሩት ሰው መስዋትነት መክፈል መሆን ነው ደስታህን ካየው በቂዬ ነው አለች እና እንደመሄድ ስትል ቆይ ከዚህ በኃላስ ምን አሰብሽ አላት ያኔ እንደሚወዳት አስተያየት እያያት
አለውቅም እኔጃ አለች እና አይበሉባውን ሳማችው አይኖቾ ደመና እንዳዘሉ ልዝነብ አልዝነብ እንደሚሉ ዝናብ ያዘቻቸው እና በቃ ደህና ሁን አለችው።😢
✍ ሰናይት ሲሻው
@gitimochi
@gitimochi
1 220
ብር ፍቅርን ሰውሮት ጎጆ ቢያጣፍጥም
እኔ ግን ምስኪኑ
ያንችን ልብ ትርታ ለማንም አልሰጥም
ይሔው በደረቴ ሀቅ አንሾካሾከኝ
የልቤን ጥግጋት
በምቱ ሊያጠምደው ቀርቦ እየታከከኝ
ኣኣ...
ፍቅር ዘመተብኝ
እንጃልኝ
አንችን ከነኩብኝ😂
@gitimochi
Senai poem
1 220
ከግጥም አታልፊም
።🌓
🌓1
መጣሽም :አልመጣሽ
ኮራሽም: አልኮራሽ
ደመቅሽም ፡አልደመቅሽ
አወቅሽም ፡አላወቅሽ
ብትሽኮረመሚ፡ ብትኮሳተሪ
ዝም ፡ጭጭ ፡ብትይ ፡ደሞም፡ ብታወሪ
ብትገላመጪ ፡ብትንቀባረሪ
መፅሐፍ ፡ብትደግሚ፡ ቁርአን ፡ብትቀሪ
መሐይም፡ ብቶኚ፡ አልያ ፡ብትማሪ
ያሻሽን፡ ቢያረግሽ፡ ያሻሽን ፡ብቶኚ
,ልብሽ ፡ቢርገበገብ፡ አልቅሰሽ፡ ብታዝኚ
ብትንከራተቺም እኔን አታገኚ!
ምናልባት!
አንጀቴ፡ እንኳን ፡ሳስቶ፡ ልቤ ፡ቢወድሽም
አድናቆት፡ ካለው፡ ቃል፡ ከግጥም፡ አታልፊም
poet :🔆 ዳዊት ጥዑማይ
Join and share
╔═══❖••❖═══╗
@yegtm_hywet
@gitumochi
╚═══❖••❖═══ ╝
❥❥ ⚘ ❥❥
1 220
አንዱ ወንበዴ ሰው በጩቤ ወግቶ ይገልና ይታሰራል፤ ፍርድ ቤት ይቀርባል ከዛ ዳኛው ይሄን ጩቤ ታውቀዋለህ ብሎ ጠየቀው? ተከሳሽም በፍፁም አይቼው አላውቅም አለ። በሌላ ቀጠሮ አሁንም አታምንም ይሄን ጩቤ ከዚህ በፊት አይተኸው አታውቅም ብሎ ዳኛው ተናዶ ጠየቀው፤ ተከሳሽም እዎ ይሄንንማ አይቼው አውቃለው አለ። ዳኛውም ደስ ብሎት በዚ ጩቤ እከሌን ስለመግደልህስ ታምናለህ አለው፤ እዎ ክቡር ፍርዱ ቤት ይሄን ጩቤ የማውቀው እኮ ባለፈው እርሷው አሳይተውኝ ነበር እርሱ እንዴ🤪
@gitimochi
@gitimochi
1 220
በውሸት ታሪክ ላይ ያልተመሰረተ
ገጠርም የሚባል አደል ከተማም ማለት ያዳግታል ብቻ መካከለኛ ከተማ ይባል ብዙ እህት እና ወንድም አለኝ ለቤቱ ሁለተኛ ልጅ ነኝ ስሜ ውዴ ይባላል ታለቅ ወንድም እና ከእኔ በታች ሶስት እህቶች እና መንታ ወንድሞች አሉኝ በጠቃላይ ሰባት ነን ከእናት እና ከአባቴ ጋር ዘጠኝ ሆን ማለት አይደል። ፐ ዘርህን እንደ ምድር አሸዋ አበዘዎለው ያለው ለአብርሃም ሳይሆን ለእኔ አባት ነው የሚመስለው ስለ ኑሮችን ሳወራ ደሃ ነን ነጭ ደሃ ነው የሚሉት ሲያጋንኑት። እናቴ መንታ ወንድሞቼን በቅርቡ ነው የወለደቻቸው መውለድ ፈልጋ አይደለም ማስወረጃ ብር አጥታ ነው የሰፈሩ ሰው የእንቁላል መፈልፈያው ምንድነበረ? እኩልቤተር ናት በዚ ኑሮ ልጆችን ለምን ታሰቃያቸዎለች ይላሉ ለእኛ አዝነው አይመስለኝም በወለደች ቁጥር ይዘው መጠየቅ ስለማረራቸው ይመስለኛል እኔ ስምንተኛ ክፍል ነኝ እህቶቼ ታች ክፍል ናቸው ውጤታቸው ከመጨረሻ አንደኛ ነው ድህነት የገባቸው አይመስሉም ኃላፊነቱን በሙሉ ራሴ ላይ የምጠለው አዳሪ ትምህርት ቤት ብገባ ሚኒስትሪን በደንብ ሰርቼ ይሄ ስቃይ ይቆማል በማለት ማታ ሳነብ ነው የማድረው እንደማረገው ደግሞ በደንብ አውቃለው የራሳችን ዬኒፎርም የለንም ጫማም እንደዛው በፈረቃ ስለምንማር አንደኛዎ እህቴ ልብሱን ጫማውን አውልቃ ለዛችኛው ትሰጣለች እኔም እንደዛው በዚ መሀል ይረፍዳል አንድ ክፍል ጊዜ ያመልጠናል ስለለመድነው ምንም ማለት አይደለም በግዜ የሄድን እንደሆነ የክላስ ጓደኞቻችን በሰላም ነው ብለው ያፌዙብናል ቦታ ሰጥቻቸው አላውቅም። ወንድሜ በሶስት ዓመት ይበልጠኛል ትምህርቱን አቁሞ ጋራጅ ይሰራል ለእኛ ሲል ያገዝኩት እየመሰለኝ በዘይት የተጨማለቀውን ልብሱን አጥብለታለው ባይለቅም እንዳይከፋን ፈገግ ይላል ውዷ እህቴ ሳይል አይውልም ፍቅራችን ልዩ ነው ሀብታም ስሆን መጀመሪያ ላንተ ነው መኪና የምገዛለህ እለዋለው።ስለ አባቴ ሳወራ ልጆቹን በጣም ይወዳል ስራውንም አለው አለው አልሆነለትም ሄደ የት? ሄዶል በቃ። ሚንስትሪ የምፈተንበት ቀን ደረሰ እንዳሰብኩት ቀላል አይደለም ተፈትኜ ጨረስኩ እናቴም ስራ መስራት ጀምራለች ልብስ እናጥባለን እህቶቼ መንታዎቹን ይጠብቃሉ ግን ጠግበን ማደር አልቻልንም። ወንድሜን አናገርኩት ውጪ ላከኝ አልኩት ትምህርትሽስ ብሎ ሲጠይቀኝ የምማረው ለገንዘብ እንደሆነ በዚህ ሁኔታ እንደማንቀጠል ፆማችንን ማደር እንዳንፈገፈን ስቃያችንን አብዝቼ ነገርኩት። በሀሳቤ ተስማማና ፕሮሰስ ጀመርን መታወቂያ ፖስፖርት ሁሉንም ጨራረስኩ መሄጃ ገንዘብ ወንድሜ ተበደረ ከባለ ጋራጁ ባለቤት ሁላችንም ተላቀስን እና ጉዞ ወደ ቤሩት ከደረስኩ በኋላ አሰሪዎቼ ተቀበሉኝ የምፈልገውን ማንኛውም ነገር እንድጠይቃቸው ነገሩኝ። በጣም ሀይማኖተኛ ፈጣሪያችውን ፈሪሃ ነበሩ የሀብት መጠናቸው የሚጋነን አይደለም ግን ጥሩ ኑሮ ሀሪፍ ይከፍሉኛል። የመጀመሪያውን ደሞዝ ለ ወንድሜ ላኩለት እዳውን እንዲከፍል በየወሩ እልካለው እንዲጠቀሙበት እና እንዲያስቀምጡ ስልክ አስርዬ የአመት በዓል ጊዜ ስጦታ ሰጠችኝ ስለ ሀገሬም ሆነ ስለቤተሰቤ ለማወቅ ቀላል ሆነልኝ እንደ fb imo ያሉትን መጠቀም ከአንዲት አረብ ሰራተኛ መፅናኛ ነው እና በfb ከአንዱ ጋር ተዋወቅን ርቄ ስላለው ይሆን አላውቅም ኢትዮጵያ ስመለስ ወንዱ ሁሉ አግብቶ ይጠብቀኝ ይመስል እሱ ጋር ሙጭጭ አልኩኝ ብር ሲለኝ መላክ ነው ማስቀመጥም እሱ ጋር ሆኖል ስራዬ በፍቅር እፍፍፍ አልን እኔ ብቻ ሳልሆን ይሄ የብዙዎቻችን የአረብ ሰራተኞች ችግር ይመስለኛል ወንድ ብርቃችን ነው ምን አስዋሸን። ሁለት ዓመት ሊሞላኝ ሲል ግን ብዙዎችን ያስደነገጠ ቤሩትን እንዳልነበረች ያደረገ ፍንዳታ ተፈጠረ። ፍንዳታው ከተፋጠረበት ቦታ የእኛ ይርቃል ግን መስተዋቱ አይኔ እያየ ተሰነጣጠቀ የኢትዮጵያ አምላክ ነው የደረሰለኝ እንጂ ዛሬ ይሄን ታሪክ ባላወራውት ተረስቼ ነበር። በዚህም እኔ እና ቤሩት ደንግጠናል ሀገሬን አልኩኝ አሰሪዎቼም ኑሮቸው ተናጋ ማለት ይቻላል እንደ ሀገር ነው እና የሚከፍሉኝ እራሱ እየተጭናነቁ ሆነ እኔም የሰበሰብኩትን ሰልባጅ ይጄ ወደ እምዬ ሀገሬ ኢትዮጵያ ቤተሰቦቼ ደነገጡ ምክንያት ገና ብዙ እንደምቆይ ነበር የሚያውቁት ምንም ለውጥ የላቸውም ጥያቼው እንደሄድኩ ነበር በጣም አዘንኩኝ ተቀማጭ ብርም የለም እናቴም ጉስቅል ብላለች ፍቅረኛ የተባለውም ስልኩ አይሰራም የለም አእምሮዬ ተረበሸ ፈጣሪን ለምን አልኩት እጄ ላይ ባለው ብር ዱባይ የመሄድ እና ለመጨረሻ ጊዜ ስቃዩን ማብቃት እንዳለበኝ ወሰንኩ። ዱባይ ከገበው ጊዜ አንስቶ ሁሉም ነገር ቦታ ቦታ ይዞል እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነኝ አሁንም በስደት ላይ ነኝ ምን አልባት በቅርቡ ወደ ሀገሬ እመጣለው።
ጨረስኩ
ባለታሪክ????
✍ሰናይት ሲሻው
@giximochi
@giximochi
1 220
በተቀደሠው ተራራ
ቅዱስ እግዚአብሔር
ተገለጠ ከሙሴ ጋር
የኮሬብ ተራራ
የአምላክን ክንድ ሲፈራ
ተንቀጠቀጠ ቅዱሱ ተራራ
እግዚአብሔር አምላክ ሆኖ
በደመና ለሙሴም ትእዛዝ ተሰጠው አለው ወደኔና
ሙሴም ወጣ ወደ ሲና
እግዚአብሔርም በደመና ሆኖ
ትእዛዛትን ሰጠ
ተራራውም ከአምላኩ ክብር የተነሳ
ቀለጠ እንደ ሻማ
እንደጧፍ ነደደ አረረ በሰለ
ክብሩንም መሸከም ስላልቻለ
ዘ ሲና ያተራራ
ክብር የተገለጠበት ከሙሴ ጋራ
የእስራኤል ሕዝቦች ተሳሳቱ
መሪያቸው ሙሴ ባለመታዬቱ
አሮንን አማልክት ስራልን አሉት
በአሮን ላይ ሸመቁበት
ከሚስቶቻቹህና ከልጆቻቹህ
ወርቅን ስጡኝ አላቸው
እነሱም ሰጡት ታውሮ ልቦናቸው
የኀይላቸው ትእቢት
የዐይናቸው አምሮት
የነፍሳቸውም ምኞት
የልባቸው ክፋት
ከፈርኦን ባርነት ያወጣቸውን
መቼ አሰቡት እግዚአብሔርን
እየዘፈኑ ሲያመጡ ጣጣ
ሙሴም ፈጥኖ ሲመጣ
ለሞተ መሥዋዕት አገኛቸው
እየተበላ እየተጠጣ
ተንበርክከው እየሰገዱ
በጣኦታትም ስህተት ሄዱ
ከግብጽ ባርነት ያወጣቸውን ትተው
አምላክ ይላሉ አምላክ ላልሆነው
መልስም ለማይሰጠው
የሰው እጅ ሥራ ለሆነው
እግዚአብሔር አምላክን ትተው
ዛሬም አሉ ከእነሡ ተምረው
ጠንቋይ ያውቃል ብለው
ከመንገድ የወጡ በሀሠት አብለው
ጠንቋዮች በምትሃት አስተዋቸው
እውነት ፈሪጁን ትተው
ሄዱ ጠንቋይ በሆነው
ጠንቆይም አስጠንቆይም ልብ ብለህ ስማ
በጥንቆላ አይደለም ሀገር የምትለማ
በንስሐ ተመለሱ
መዳንም እንዳለ እንዳትረሱ
ኀጢአትም እንዳለ
መዳንም አለ
በንስሐ መታደስ
ወደ ቀልብ መመለስ
ወደ እግዚአብሔር መቅረብ
በንስሐ ታጥቦ ተመልሶ ማበብ
የእግዚአብሔር ቸርነቱ
ጠፍተን እንዳንቀር ነው ፍላጎቱ
እግዚአብሔር ልጆቼ ሲለን
አቤት እንበለው አባታችን
ዐይናችንን ያብራልን
የፍቅር ጣዕሙን ይስጠን
✍Senait Sishaw
1 220
ትንቢቱ ይፈፀም ዘንድ
ወንበዴ ነበርኩ ቀማኛም አይገልፀኝ
የመንደሩ ሰው በባህሪዬ የጠላኝ
ቀና ብለው ላዩኝ የማራራ
እጄን መስደድ ነው ካገኘውት ጋራ
የአባቴ እንባ ረግጬ የምወጣ
ይልኛል ተመከር ችግር ሳይመጣ
መልሴም አባ በእንቁላሉ ሳልቀጣ
መቀበል ነው ያለውን ጣጣ
በማለት ከቤት ስወጣ
ሳይደግስ አይጣላ ነገር
ደም ተቃባው ከንጉሳያን ዘር
የአባቱን ዙፋን የሚወርሰው
የገደልኩት አንድያ ልጁን ነው
ምን ውስጥ ልግባ ወዬት ልሸሸግ
እረኛው የጠፋ ሆንኩኝ ብቸኛ በግ
አባባ ጋር ሄድኩኝ እየተጣደፍኩ
ይቅር ይለኝ ዘንድ ስሩ ተንበረከኩ
ልብሴ በደም ተጨማልቆል
የንጉሱ ልጅ ህይወት በእጄ ጠፍቶል
አባቴ ልብህ እንዳያዝንብኝ
ይቅር ለእግዜር አልኩት መርቀኝ
በምላሹ ፊቴን በእጆቹ እየደባሰሰ
ያንተ እንደዚ መሆን እኔ ነኝ እያለ አለቀሰ
ነጩን ቲሸርቱን አውልቆ ለእኔ አለበሰ
በደም የተነከረውን እሱ ለበሰ
አሳዳጆቼ በሩን በርግደው ገቡ
አንዴ እኔን ቀጥሎ አባቴን አዩ
ነገሩ እንዲ ነው ልጅ ባጠፋ
አባት አንገቱን ደፋ
በደም የቆሸሸውን ልብስ የለበሰው
ይሄ ነው አሉ ንጉሱን ልጅ ያሳጣው
ይሙት ይሙት ብለው ፈርዱ
በሰይፍ አንገቱን አረዱ
አይእኔ እያየ ሞተ አባቴ
የሞቱ ቀን ጀመረች ህይወቴ
የደረሰብኝ ስቃይ የመጣውት መዘዝ
ከዕለት ወደ ዕለት ሆነብኝ የሚጠዘጥዝ
የአባቴ ሱሪ ውስጥ አገኘው ወረቀት
ሳነበው ገረፈኝ እንደ ስለት
ምናልባት አልሆንኩልህም ጥሩ አባት
እዚ ቦታ እንድደርስ ክፍያለው ብዙ መስዎዕት
ባንተ መቼም ቢሆን አልደራደር
ፍቅሬን አሳይሃለው ወርጄም ቢሆን መቃብር
አንተ ግን አስብ ስለወደፊት
የቀረችህን ዕድሜ ፈጣሪህን አስብባት
በጉብዛናህ ወራት አስበኝ እንዳለው
አምላክህን መቼም እንዳታሳዝነው
ጉልበትም ይሆናል ደካማ
ይልፈሰፈሳል እንደ ቄጤማ
እንዳያልቅ በልብህ ውስጥ ያለው ሻማ
ልጅ ስትወልድ በእንቁላሉ ቅጣ
እንደ አባት ሲያሻህ ተቆጣ
አደራ ልጄ ወዳጄ!
✍ሰናይት ሲሻው
@giximochi
@giximochi
