en
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Open in Telegram
1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
“የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን።” - ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

“ኢትዮጵያ ሲያምርባት ዓይኑ የሚቀላ፤ ህዳሴ ሲያልቅ ምን ያደርጋል የሚል፤ የባህር በር ጥያቄ ሲነሳ የሚሸማቀቅ፤ ለኢትዮጵያ ብልጽግና ከጎኗ መቆም የሚጠላ ሁሉ ራሱን እንደማንጎ የሚቆጥር ግራዋ ነው። ስራው በፍሬው ስለሚታወቅ!” - ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላማዊ ትግል ማድረግ ለሚፈልግ ሰው በሩ ክፍት ነው የተገደበ ፓርቲ የለም:: ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ሃሳቦች-ክፍል ሁለት ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት የኢትዮጵያን እድገት የማይሹ ሀገራት በጦርነት እንደማያሸንፉን ያውቁታል። ያላቸው ምርጫ ባንዳዎችን መላክ ነው። ኢትዮጵያን በቅጡ ያላወቁ የውስጥ ባንዳዎች ደግሞ ከጠላት ጋር በማበር ዓላማቸውን የሚያሳኩ ይመስላቸዋል። ይህ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቻው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው። መንግስት ችግሮች አሉኝ የሚሉ አካላት ጋር ቁጭ ብሎ በመነጋገር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አሁንም በሩ ክፍት ነው። የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ የተቀመጡ ዋነኞቹ ጉዳዮች ምንድን ናቸው - ህወሃት ያካሄደው ምርጫ ህጋዊ ምርጫ ባለመሆኑ መሰረዝ - በትግራይ ክልል ህጋዊ ባለሆነ ምርጫ የተቋቋመው የክልሉ አስተዳደርና ምክር ቤት እንዲፈርስ - ከሁሉም ወገን የተወጣጣ ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም - በህዝብ የተመረጠውን የፌደራል መንግስት ስርዓት ማክበር - በክልሉ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሃይሎች ትጥቅ መፍታትና በተሃድሶ ወደ መደበኛ ህይወታቸው መመለስ - የተቋረጡ አገልግሎቶችን ወደ ስራ ማስመለስ - ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን መመለስ - የትኛውም የውጭ ግንኙነት የማከናወን ስልጣን ያለው የፌደራል መንግስቱ ብቻ መሆኑን ማክበር የሚሉት ናቸው። በትግራይ ክልል ያለውን የሰላም ሁኔታ በሚመለከት በትግራይ ክልል ተጨማሪ ወጊያ እንዲካሄድ አንፈልግም። ከዚያ ይልቅ ተባበረን ሀገር ማልማት ነው የምንፈልገው። ከዚያ ውጭ መንግስትን በሃይል ለመጣል ፍላጎት ካለ እሱ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም። የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የሚመድበው በጀት ለልማት ሳይሆን ለታጣቂ እየዋለ ነው። ይህ ትክክል አይደለም። ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል። በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብበር ለልማት መስራት ይገባል። 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በተመለከተ ምርጫውን ለማከናወን መንግስት በቂ አቅምና ዝግጁነት አለው። 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስካሁን በኢትዮጵያ ከተካሄዱ ምርጫዎች የተሻለ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ምርጫው ዴሞክራሲያዊና ብዘሃ ድምጾች ያሉት እንዲሆን በሃላፊነት እንሰራለን። እኛ እንደ ፓርቲም፤ እንደ መንግስትም ዝግጁ ነን። ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከወዲሁ መዘጋጀት አለባቸው። ተቋማዊ ሪፎርም በሚመለከት በአገልግሎት አሰጣጥ ያለውን እንግልት ለመቀነስ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ እይሰፋ ነው። አሁን ላይ 18 ማዕከላት አገልግሎት እየሰጡ ነው። ሶስት ማዕከላት ደግሞ በቅርቡ ስራ ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተያዘው በጀት ዓመትም ይህን ቁጥር ወደ 100 ለማድረስ እየተሰራ ነው። ይህም በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል። ዲጂታላይዜሽንን በሚመለከት ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል። ይህ ትልቅ ቁጥር ነው። 93 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ሲሆኑ 55 ሚሊዮን ዜጎች ደግሞ የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል። ይህ ኢትዮጵያን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የጀመረነው ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን አመላካች ነው። የዓባይ ውሃ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በሚመለከት ኢትዮጵያ በብሔራዊ ጥቅሟ ላይ ኢ-ፍትሃዊና ኢ-ርታዊ ውሳኔ የተወሰነባት ሀገር ናት። ዓባይን መጠቀም ተፈጥሯዊና ህጋዊ መብቷ ነው። ሃብቱም በጋራ ለመጠቀም በቂ ነው። ኢትዮጵያ አሁንም ያላት አቋም ግልጽ ነው። ግብጻዊያንም ሱዳናዊያንም ወንድሞቻችን ናቸው። ስለዚህ የሚያዋጣው በመነጋገርና በመተባበር በጋራ ማደግ ነው። እኛ ማንንም በሚጎዳ መልኩ አናቅድም አንሰራም። ቀይ ባህርን በተመለከተ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን። ይህንን በተረጋጋ መንገድ ማየት ያስፈልጋል። ኢትዮጵያን የቀይ ባህር የማጣት ውሳኔ ማን ወሰነ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም። ይህን የሚያህል የህልውና ጉዳይ ማን እንደወሰነ መጠየቅ ተገቢ ነው። ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም። ለጎረቤቶቻችን መናገር የምንፈልገው ኢትዮጵያ ስታደግ ለቀጣናውም ልማት ምንጭ ትሆናለች። የምንፈልገው በትብብር ማደግ ነው። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

ቀይ ባህርን በተመለከተ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን። ይህንን በተረጋጋ መንገድ ማየት ያስፈልጋል። ኢትዮጵያን የቀይ ባህር የማጣት ውሳኔ ማን ወሰነ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም። ይህን የሚያህል የህልውና ጉዳይ ማን እንደወሰነ መጠየቅ ተገቢ ነው። ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም። ለጎረቤቶቻችን መናገር የምንፈልገው ኢትዮጵያ ስታደግ ለቀጣናውም ልማት ምንጭ ትሆናለች። የምንፈልገው በትብብር ማደግ ነው። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የዓባይ ውሃ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በሚመለከት… See more

ተቋማዊ ሪፎርም በሚመለከት… See more

7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በተመለከተ ምርጫውን ለማከናወን መንግስት በቂ አቅምና ዝግጁነት አለው። 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስካሁን በኢትዮጵያ ከተካሄዱ ምርጫዎች የተሻለ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ምርጫው ዴሞክራሲያዊና ብዘሃ ድምጾች ያሉት እንዲሆን በሃላፊነት እንሰራለን። እኛ እንደ ፓርቲም፤ እንደ መንግስትም ዝግጁ ነን። ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከወዲሁ መዘጋጀት አለባቸው። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

በትግራይ ክልል ያለውን የሰላም ሁኔታ በሚመለከት በትግራይ ክልል ተጨማሪ ወጊያ እንዲካሄድ አንፈልግም። ከዚያ ይልቅ ተባበረን ሀገር ማልማት ነው የምንፈልገው። ከዚያ ውጭ መንግስትን በሃይል ለመጣል ፍላጎት ካለ እሱ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም። የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የሚመድበው በጀት ለልማት ሳይሆን ለታጣቂ እየዋለ ነው። ይህ ትክክል አይደለም። ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል። በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብበር ለልማት መስራት ይገባል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ የተቀመጡ ዋነኞቹ ጉዳዮች ምንድን ናቸው:- - ህወሃት ያካሄደው ምርጫ ህጋዊ ምርጫ ባለመሆኑ መሰረዝ - በትግራይ ክልል ህጋዊ ባለሆነ ምርጫ የተቋቋመው የክልሉ አስተዳደርና ምክር ቤት እንዲፈርስ - ከሁሉም ወገን የተወጣጣ ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም - በህዝብ የተመረጠውን የፌደራል መንግስት ስርዓት ማክበር - በክልሉ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሃይሎች ትጥቅ መፍታትና በተሃድሶ ወደ መደበኛ ህይወታቸው መመለስ - የተቋረጡ አገልግሎቶችን ወደ ስራ ማስመለስ - ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን መመለስ - የትኛውም የውጭ ግንኙነት የማከናወን ስልጣን ያለው የፌደራል መንግስቱ ብቻ መሆኑን ማክበር የሚሉት ናቸው። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia