1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
የአለም አይን ማረፊያ ከተማ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/addisababacommunication
ለሕዝባችን የገባነውን ቃል በስኬት እንድንተገብር ላገዘን ፈጣሪ ምስጋና ይሁን!
ዛሬ በዘጠኝ ወራት ጊዜ ውስጥ በፍጥነትና በጥራት በ24 ህንፃዎች የተገነቡትን 1,287 ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶች በይፋ መርቀናል።
የሁላችን መዲና የሆችው ከተማችንን የማርጀት እና የመቆሸሽ ታሪክ በየዕለቱ እየቀየርን፤ የማህበረሰባችንን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ በርካታ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወን ነው።
በተለይም የሕዝባችንን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከ 380,000 (ሶስት መቶ ሰማንያ ሺህ) በላይ ቤቶችን በመገንባት ለተጠቃሚዎች አስተላልፈናል። ይህም ከለውጡ በፊት ባሉት 17 ዓመታት ከተገነቡት 179,000 (መቶ ሰባ ዘጠኝ ሺህ) ቤቶች እጅጉን የላቀ ነው።
የመፍጠርና የመፍጠን መርህን በተጨባጭ ካረጋገጥንባቸው ፕሮጀክቶች ይህ ትልቅ ስኬት 24/7 የሥራ ባህልን በተግባር ላይ በማዋል የተገኘ ዉጤት መካከል አንዱ ነው።
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ በጀርመን አደባባይ፣ በአየር ጤና እና በግራር አካባቢ የሚገኙ ናቸው።
ዛሬ የመረቅናቸው ከ11 እስከ 18 ወለል ያላቸው 24 ሕንፃዎች የያዙት የመኖሪያ ቤቶችን ብቻ ሳይሆን ምቹ የመኖሪያ አካባቢን ጭምር ነው።
ይህም የልጆች መጫወቻ ስፍራዎችን፣ የስፖርት ሜዳን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን ፣ የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችን እና ሌሎች የጋራ መገልገያዎችን አሟልተዋል ።
ይህ ፕሮጀክት ከግንባታ ባለፈ በርካታ የሥራ ዕድሎችን እና የእውቀት ሽግግርን ለወጣቶቻችን አስገኝቷል፤ የግንባታ አቅም ፈጥሯል፤ በተጨማሪም ጥራትንና ፍጥነትን በተመሳሳይ ጊዜ ማረጋገጥ እንደምንችል አሳይቷል። ቤቶቹን በተመጣጣኝ ዋጋ ለንግድ ባንክ ሰራተኞች ያስረከብን በመሆኑ በአንድ በኩል የቤት እጥረትን ለመፍታት አማራጭ እርምጃ ያስቀመጠ ሲሆን፣ በሌላ በኩል የቤት ልማት ፈንድን የፈጠረ ጭምር ነው።
ለዚህ ሥራ ስኬት የበኩላችሁን የተወጣችሁ አመራሮችን፣ ባለሙያዎችን እና ተቋማትን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በጆሃንስበርግ የቡድን 20 የመሪዎች ጉባዔ ላይ ተገኝተዋል።
#aa_prosperity
'ህዳር ሲፀዳ አካባቢያችን ጤና'
የፅዳት ኤጀንሲ አዳዲስ ስልቶችን ይፋ አደረገ
የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ፣ ከበርካታ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው መድረክ፣ ከተማዋን ንጽህናዋ የጠበቀና ጤናማ አካባቢ ለማድረግ የሚያስችሉ አዳዲስ የጽዳት ስልቶችን ይፋ አደረገ። ውይይቱ የተካሄደው "ህዳር ሲፀዳ አካባቢያችን ጤና" በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን፣ የከተማዋን ነዋሪዎች ጤና ከንጽህና ጋር በተያያዘ ያለውን ቀጥተኛ ግንኙነት አጉልቶ አሳይቷል።
በመድረኩ ላይ በዝርዝር የቀረቡት አዳዲስ ስልቶች፣ የአዲስ አበባን የጽዳት አፈጻጸም ለማሻሻል ያለመ ሲሆን፣ የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
ኤጀንሲው ባስተላለፈው ወሳኝ መልዕክት፣ "አካባቢያችን ሲፀዳ፣ ጤናችን ይጠበቃል!" የሚለው መርህ ከቃል ወደ ተግባር እንዲሸጋገር ሁሉም የከተማዋ ነዋሪዎች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። እነዚህ አዳዲስ የጽዳት አሰራሮችና ስልቶች የአዲስ አበባን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የዜጎችን የጤና ሁኔታ በእጅጉ ያሻሽላሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በውይይቱ የተላለፉ ሀሳቦችን አዳምጠው ያለዎትን ሀሳብ ያካፍሉን።
#አካባቢያችን_ሲፀዳ_ጤናችን_ይጠበቃል #ንጹህ_አዲስ_አበባ #ህዳር_ሲፀዳ_አካባቢያችን_ጤና
#የፅዳት_ስልቶች #AddisAbaba
ህዳር ሲታጠን Vs ህዳር ሲጸዳ
#ህዳር_ሲፀዳ_አካባቢያችን_ጤና
#addisababa
#የአካባቢንጽኅና
#ንጹህ_አዲስ_አበባ
ከመንገድ እስከ ደጃፍ ያሉ መብራቶችን ጠግኖ የማስረከብ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሳይሰጡ የቆዩ መብራቶችን በመጠገን ለአካባቢ ነዋሪዎች የማስረከብ ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
ባለስልጣኑ ከዋና እስከ ውስጥ ለውስጥ ያሉ መንገዶችን ጠግኖ ለህብረተሰቡ አገልግሎት ለማዋል በከተማዋ ሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ ለመሆን ያለውን ውስን አቅም በማቀናጀትና ቀን ከሌሊት በስራ ላይ በማዋል ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡
ጥገና ተደርጎ ከጨለማ ወደ ብርሀን ከተለወጡ አካባቢዎች ውስጥ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 እና 7 ቤተል፣ በወረዳ 4 አለም ባንክ እና ወረዳ 8 ቀራንዮ አካባቢ የሚገኙ የውስጥ ለወስጥ መንገዶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡
በውስጥ ለውስጥ መንገዶቹ ላይ ያጋጠመውን ብልሽትና የተጓደሉ መሰረተ-ልማቶች በማሟላት ለህብረተሰቡ የምሽት እንቅስቃሴ ምቹና ደማቅ የተደረገ ሲሆን ህብረተሰቡ በባለቤትነት ከሚፈፀም ስርቆትና ህገ- ወጥ ተግባር እንዲከላከል ባለስልጣኑ የማስረክብ ስራ አከናውኗል፡፡
ህዳር 12/2018
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ጥራት ያለው መንገድ የሰለጠነ ከተማ መገለጫ ነው!
መዲናችን አዲስ አበባ፣ እያደገ በመጣዉ የተሽከርካሪ ቁጥር እና በነበረው የመንገድ እጥረትና ጥራት ችግር ምክንያት ለትራፊክ መጨናነቅ ተጋላጭ ሆና ቆይታለች::
ችግሩን የተገነዘበዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከለዉጡ ማግስት ጀምሮ፣ የረጅምና የአጭር ጊዜ ዕቅድ በመተለም፣ የትራንስፖርት ዘርፉን ታሪክ የቀየረ፣
ምቹ እና የተሳለጠ የመንገድ ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ የታገዙ ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያዎች እና ተርሚናሎችን በስፋት ገንብቶ ችግሩን ከምንጩ ለመፍታት የላቀ ስራ ሰርተል።
በከተማዋ ከመሬት በታች ጭምር ተገንብተዉ የተጠናቀቁና በመጠናቀቅ ላይ ያሉ ደረጃቸዉን የጠበቁ ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ እና ተርሚናሎች በአንድ ጊዜ ከ1ሺ በላይ መኪና በማስተናገድ፣ የትራፊክ መጨናነቅን በመቀነስ፣ የትራንስፖርት ፍሰትን በማሳለጥ፣ የመንገድ ደህንነትን በማስጠበቅ፣ የትራፊክ አደጋን በመቀነስ፣ የጊዜና የነዳጅ ብክነትን በማስቀረት፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን በማቀላጠፍ እና ለዜጎች የስራ-ዕድል በመፍጠርና ምርታማነትን በማሳደግ ከተማዋን ዘመናዊ ገፅታ ያላበሱ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች ናቸዉና ልንጠብቃቸዉና ልንጠቀምባቸዉ ይገባል፡፡
ዛሬ ማለዳ ለህዝባችን ጥያቄ ተጨባጭ ምላሽ እየሰጠንባቸው ካሉት ስራዎች አንዱ የሆነውን የሦስት አዳዲስ ሆስፒታሎች አጠቃላይ የግንባታ ሂደት ገምግመናል።
ሆስፒታሎቹ ከነባሮቹ የላቀ አገልግሎት የሚሰጡ ሆነው እየተገነቡ ያሉ ሲሆን ግንባታቸውም በመጠናቀቅ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሆስፒታሎቹን እየገነባን ያለነው በአቃቂ ቃሊቲ፣ በንፋስ ስልክ ላፍቶ እና በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተሞች ነው።
ሆስፒታሎቹ ከዚህ ቀደም ሆስፒታል ባልነበረባቸው አካባቢዎች መገንባታቸው የህክምና ፍትሀዊ ተደራሽነትን ከማስፋታቸው በተጨማሪ ከመላው ኢትዮጵያ ለሚመጡ ታካሚዎች አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል።
አጠቃላይ 1,500 አልጋ የሚኖራቸው ሲሆን፣ አሁን ላይ ግንባታቸው እየተጠናቀቀ ነው። ቀጣዩ ትኩረታችን ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችን ማስገባት ነው።
አዳዲሶቹ ሆስፒታሎች ለህዝባችን ጥያቄ ተጨባጭ ምላሽ ከመስጠት ባሻገር በሚሰጡት ዘመናዊ የህክምና አገልግሎት የልህቀት ማዕከል ሆነው የሚያገለግሉ ሲሆን፣ ከተማችንን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥሩ ይሆናል።
አስተዳደራችን ከአዲስ ሆስፒታሎች ግንባታ በተጨማሪ በሚኒሊክ፣ በራስ ደስታ እና በዘውዲቱ ሆስፒታሎች አዲስ ሆስፒታል የመገንባት ያህል የማስፋፊያ ስራ አከናውነናል። ከእነዚህም ውስጥ የዘውዲቱ ሆስፒታል ማስፋፊያ ተጠናቅቆ ስራ መጀመሩ ይታወቃል።
ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ
Har'a ganama gaaffii uummata keenyaaf deebii qabatamaa hojiiwwan ittiin kennaa jirru keessaa tokko kan ta'e adeemsa waliigala ijaarsa hospitaalota haaraa sadii gamaaggamnee jirra.
Hospitaalonni kun, hospitaalota qabnu keessaa kan tajaajila olaanaa keennan ta'anii ijaaramaa kan jiran yemmuu ta'u, ijaarsi isaanis sadarkaa xumuraa irratti argama. Hospitaalota ijaaraa kan jirruu, kutaalee magaalaa Aqaaqii Qaallittii, Nifaas Silkii Laaftoo fi Kolfee Qaraaniyoottidha.
Hospitaalonni kana dura naannolee hospitaalli hin jirreetti ijaaramuun qaqqabiinsa yaalaa haqa-qabeessa diriirsuu dabalatee yaalamtoota Itoophiyaa guutuurraa dhufaniif tajaajila kan keennan ta'u.
Waliigalatti, siree 1500 kan qabaatan yemmuu ta'u, ammarratti ijaarsi isaanii xumuramaa jira. Xiyyeeffannoon keenya kan itti aanu meeshaalee yaala fayyaa ammayyaa'oo galchuudha.
Hospitaalonni haaraaleen gaafilee uummata keenyaaf deebii qabatamaa keennuun cinaatti, tajaajiloota ammayyaa kennaniin giddugala gahuumsaa ta'anii kan tajaajilan yemmuu ta'u, galma magaalaa keenyaa giddu gala tuurizimii taasisuuf qabannee milkeessuuf humna dabalataa kan uuman ta'a. Bulchiinsi keenya ijaarsa hospitaalota haaraa dabalatee hospitaalota Minilik, Raas Dastaa fi Zowdituutti hojii haamma hospitaala haaraa ijaaruu ga'u ijaarree jirra. Kanneen keessaas, babal'iinsi hospitaala Zowdituu xumuramee hojii eegaluun ni yaadatama.
Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu
