1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
3ኛውየአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡
ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ ዙር አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ ጉባኤ በማጽደቅ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ያስተላልፋል::
ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ተመራጭ አባላት ከመራጩ ህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ምላሽ ይሰጣል፡፡
በተመሳሳይ ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ይጠናቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤ
https://linktr.ee/AddisMediaNetwork
AMN - ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም
ስኬቶቻችን የሰንደቃችን ከፍታ የሚጨምሩ ናቸው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
እንኳን ለሰንደቅ ዓላማ ቀን አደረሳችሁ!
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት እመርታዊ ስኬቶችን እያስመዘገበች የሚመጥናትን ከፍታ እየያዘች ትገኛለች። ለዘመናት የቁጭት እና እንጉርጉሮ ትርክት ምንጭ የነበረዉን ዓባይን ገርታ የኃይል እና ብርሃን ምንጭ አድርጋለች፡፡
በንጋት ኃይቅ በምግብ ሉዓላዊነቷ ላይ ጉልህ ሚና የሚጫወት የዓሣ ምርት ማግኘት ችላለች፤ ዐዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ደሴቶችንና ከተሞችን ፈጥራለች፡፡ የዓባይን የቁጭት ትርክት ወደ ድል እና አሸናፊነት ብስራት ቀይራለች፡፡
ተጨማሪ የኃይል ምንጮችን ከውኃ እስከ እንፋሎት፣ ከፀሐይ ብርሃን እስከ ኑውክሊየር ኃይል እና ነፋስ በመገንባት ላይ ናት፡፡ እነዚህ ሁሉ የሰንደቋን ከፍታ እና ተምሳሌትነት የሚያጎሉ ናቸው፡፡
ኢትዮጵያ ከገጸ ምድር ባሸገር በከርሰ ምድር ያሉ ሀብቶቿን ወደመጠቀም ተሸጋግራለች፡፡ በተፈጥሮ ጋዝ ማውጣት የታየዉን ስኬት ለማላቅ፣ በነዳጅ ዘይትም ለመድገም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ጀምራለች፡፡ የግብርና ዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ የዐፈር ማዳበሪያ በራሷ ለማምረት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሳለች፡፡ ይህም የምግብ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ የተጀመረውን ሥራ ይበልጥ የሚጠናክር ሆኗል።
የሕዝቧን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር ከቢሮ እስከ ግቢ በሚል ጀምራ፣ ከከተማ እስከ ገጠር ወደሚል ተሸጋግራለች፡፡ በአዲስ አበባ የተጀመረዉ የከተሞችን ገጽታ የመቀየር ንቅናቄ ዘመናዊነትን፣ የስማርት ሲቲ ጽንሰ ሐሳብን እና ሰውን ከተፈጥሮ የማስማማት ልምምድን ያስተዋወቀ ነው፡፡ ይህም የዲፕሎማሲ ማእከል የሆነችውን መዲናችንን በዓለማቀፍ ደረጃ ያላትን ገጽታ የሚያጎላ፣ የሰንደቃችንን ከፍታ የሚጨምር ነው፡፡
ከተማችንን የማዘመኑን ጅማሮ ወንዞቻችን በማከም የተፋሰሶችን ደኅንነት የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡ ከእንጦጦ ጀምሮ እየተሠራ ያለዉ የወንዞች ዳርቻ ልማት የአዋሽ ተፋሰስን ሥነ ምኅዳር ጭምር የሚያክም ለአካባቢ ጥበቃ አብነት ነው፡፡ የገጠር አኗኗር ዘይቤያችንን በማዘመን ኢትዮጵያን በበጎ የምትመሰል ሀገር የማድረግ ጥረታችንም ፍሬው እየታየ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ የሰንደቃችንን በኩራት መውለብለብ የሚያጎሉ የትጋታችን ውጤቶች ናቸው፡፡
ዛሬ የምናከብረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በነፃነት ቀን የተገኘ አይደለም፤ ነፃ ሆኖ ለሌሎች ነፃነት ከፍ ብሎ ሲውለበለብ የታየ የነፃነት ምልክት እንጅ፡፡ ነፃነቱን ለማስከበር ግን ቀደምቶቻችን ደም፣ ሥጋ እና ዐጥንት ገብረዋል፡፡ ኢትዮጵያን የዓለም የነፃነት ቀንዲል አድርገዉ አስረክበውናል፡፡
ዛሬም እንደትናንቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በደም እና በዐጥንት ለማስበር የቆረጡ ጀግኖች አሉን፡፡ በምድር፣ በአየር፣ በባሕር እና በሳይበር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በማስከበር ሰንደቋ የነፃነት ተምሳትነቱ እንዲቀጥል የሚተጉ ጀግኖቻችን አሉ፡፡
የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የምናከብረዉ በሁሉም ግንባር፣ በሁሉም ዓውድ ስለኢትዮጵያ ዋጋ የሚከፍሉ ጀግኖቻችን በማመስገን፣ ሰንደቃችንም በክብር ከፍ አድርገን በማውለብለብ፣ ለላቀ ከፍታዉ እንደምንተጋ ቃል በመግባት ነው፡፡ የተጀመሩ ትልልቅ የሰንደቅ ዓላማ ፕሮጀክቶች ለማሳካት ደግሞ ያለስስት በጋራ መጣር፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ ማናቸዉንም ዋጋ መክፈል ከዜጎች ይጠበቃል፡፡
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ጥቅምት 3/2018 ዓ/ም
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በመዲናችን አዲስ አበባ ነዋሪዎች ስፓርታዊ እንቅስቃሴን ባህል ፣ የአኗኗር ዘይቤ ፣ ጤናን መጠበቂያ ፣ ማህበራዊ ግንኙነትን ማጎልበቻ መንገድ እያደረጉት ይገኛል ።
በየእለቱ በተለይም በእረፍት ቀናት ህፃናት ፣ ወጣቶች ፣ አረጋዉያን በተናጠል እና በጋራ የተለያዩ ስፓርታዊ እንቅስቃሴዎችን በመኖሪያ አካባቢ እና ከትራፊክ እንቅስቃሴ ዝግ በሆኑ መንገዶች ሲያከናዉኑ መመልከት የተለመደ ሆኗል ።
ማዕከላቱ ጤናን ለመጠበቅ ፣ ተተኪ ስፓርተኞችን ለማፍራት የሚያግዙ በመሆናቸዉ ህብረተሰባችንም ወደ ማዕከላቱ በመሄድ ስፓርታዊ እንቅስቃሴዎች የማድረግ ልምምዱን ይበልጡን ማሳደግ ይገባዋል ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
Madiinaa teenya Finfinneetti jiraattonni sochiilee qaamaa daandii aadaa, mala jireenyaa,eegumsa fayyaa fi walitti dhufeenya hawaasummaa cimsu taasisaa jiru.
Guyyaa hundaa keessattuu guyyaalee boqonnaa daa'imman,dargaggoonni fi maanguddoonni qophaa qophaatti fi waloon sochilee qaamaa adda addaa naannawa jireenyaa fi daandiilee sochii tiraafikaa irraa cufaa ta'an irratti yeroo gaggeessan arguun kan baratame ta'eera.
Giddugaloonni fayyaa eegsisuuf, walitti dhufeenya hawaasummaa jabeessuuf akkaaumas kanneen ispoortiin dhaloota bakka bu'an oomishuuf kanneen gargaaran waan ta'aniif hawaasni keenyas gara giddugalootaa deemuun shaakala sochiilee qaamaa gochuu daran guddisuutu irra jiraata.
Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!
ዘንድሮ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረው የብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን " ሰንደቅ አላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉአላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ" በሚል መሪ ቃል በነገው እለት ጥቅምት 3/ 2018 በመላ አገራችን ይከበራል።
በሠንደቅ ዓላማ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 863/2006 (እንደተሻሻለው) አንቀጽ 2 መሰረት በየዓመቱ ጥቅምት ወር በገባ መጀመሪያ ሳምንት ሰኞ የብሔራዊ ሰንደቅ አላማ ቀን እንደሚከበር ተደንግጓል።
በዚህ ዓመትም ሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታን በዋጀ መልኩ ለ18ኛ ጊዜ ከሰንደቅ ዓላማ መርሆዎች ጋር ተገናዝቦና የኢትዮጵያን ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራትና ማንሰራራት በሚያረጋግጡ ውይይቶች ታጅቦ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት መሪነት በመላው ሀገሪቱ በነገው እለት ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ንደሚከበር አስታውቋል።
በፌደራል የመንግስት ተቋማት፣ በክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በትምህርት ቤቶች ፣ በመከላከያ ሰራዊት ካምፖች እንዲሁም በኤምባሲዎችና የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች በተመሳሳይ ሰዓት ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ላይ ሠንደቅ ዓላማ በመስቀልና በሠንደቅ ዓላማ ፊት ቃለ መሐላ በመፈፀም እንዲሁም በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር መግለጫው አመልክቷል።
Image - #AMN
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ለረጅም ግዜ ህብረተሰቡን ሲያንገላቱና አገልግሎትን በገንዘብ ሲሸጡ የነበሩ የቦሌ ወረዳ 12 ቡድን መሪና ባለሙያዎች ከመንግስት ስራ ማሰናበቱን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡
ኤጀንሲው እንዳስታወቀው በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 የነዋሪዎች ቡድን መሪ የሆኑትን ጨምሮ አገልግሎቶችን በገንዘብ ሲሸጡ እና ህብረተሰቡን ሲያንገላቱ የነበሩ ባለሙያዎች ከመንግስት ስራ እንዲሰናበቱ ዉሳኔ ተላልፏል።
ኤጀንሲው በደረሰው የተገልጋይ ጥቆማ የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የነዋሪዎች አገልግሎት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ክብረት ቦጋለ እንዲሁም የነዋሪዎች አገልግሎት ባለሙያ የሆኑት አቶ ሞላ ልንገረዉን በተለያዩ ግዜያት ተገልጋዮችን ማንገላታትና አገልግሎትን ያለአግባብ በገንዘብ ሲሸጡ የነበረ መሆኑን በማስረጃ በማረጋገጥ በአዋጅ 87/2017 ዓ.ም ላይ በተቀመጠዉ አሰራር መሰረት ከስራ እንዲሰናበቱ ዉሳኔ ተሰጥቷል ብሏል፡፡
ይህ የተቋሙ ዉሳኔ ለሌሎች ተቋማትም ሆነ ሌሎች የተቋሙ ሰራተኞች ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ኤጀንሲው የገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ የሚገጥመዉን ችግር ለመቅረፍ ኤጀንሲዉ ቁርጠኛ እርምጃ ለመዉሰድ ዝግጁ መሆኑንም ገልጿል፡፡
የኤጀንሲው መልእክት ለከተማችን ነዋሪዎች እንደሚከተለው ቀርቧል።
ውድ ነዋሪዎቻችን
ተቋማችን እራሱን ከህገ-ወጥነት ለመከላከል የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና የስራ ክፍል እንዲሁም የህግ ክፍል በማደራጀት የመረጃ አቅምን እያጠናከረ ያለና የዲጂታል አገልግሎቱም ኦዲት የሚደረግበት ስርዓት የዘረጋ በመሆኑ ይህንን ተቋማዊ ቆራጥ አቋም በመረዳት ከህገ-ወጥ ደላሎች እና አገልግሎትን በገንዘብ ከሚሸጡ እራሳችሁን እንድትጠብቁ እንዲሁም እራሳችሁም ተባባሪ ከመሆን እንድትቆጠቡ እያሳሰበ መሰል ሁኔታዎች በአገልግሎታችን ላይ ሲገጥማችሁ በ7533 የነፃ የስልክ መስመር ወይም ከታች ባለው የፌስቡክ ገፅ በቀጥታ ጥቆማ እንድትሰጡን ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን!!
ሌብነትን በፅኑ እንታገላለን!
ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በተገልጋይ ነፃ የስልክ መስመር 7533 ይደውሉ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ስራችን ግልፅነት የተላበሰ፣ የተጠያቂነት ስርአት የተጠናከረበትና መልካም አስተዳደር የሰፈነበት እንዲሆን እንደ ከተማ አስተዳደር በምናደርገው ጥረት የከተማችን ነዋሪ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይኖርበታል።
