en
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Open in Telegram
1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
የሱፐርቪዥን ስርዓት የተቋማዊ እምርታ ልኬት ነው፣ #AAFDRMC_ታህሳስ 23/2018ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ቢሮ በእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮምሽን የሱፐርቪዥን ምልከታ አካሄደ። የሱፐርቪዥን ቡድንም በኮምሽኑ በዘርፎች ያለውን ምልከታ ከትናት ከታህሳስ 22/2018ዓ.ም ጀምሮ ምልከታ ያደረገ ሲሆን። የአደጋ ስጋት ቅነሳ ዘርፍ የአደጋ ምላሽ ዘርፍ፣ የድህረ አደጋ ምላሽ ዘርፍ፣ የቴክኖሎጂና ምህድስና ዘርፍ፣ የኮምሽኑ ጽ/ቤት እና የስልጠና ማእከሉ ያስመዘገቡትን የስድስት ወር ድሎች ከሪፖርት እስከ ተግባር ያሉትን ውጤቶች በተጨባጭ መረጃ ምልከታ አድርገዋል። የሱፐርቪዥን ምልከታው ክፍተቶችን ማረምና ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል አቅም የሚፈጥርና ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ አቅም የሚፈጥር ነው። የአንድ ተቋም የሚለካው ብዙ አይነት የEvaluation and Assesment ስርዓቶች ያአሉሲሆን ከዛ ውስጥ አንዱ ደግሞ ሱፐርቪዥን ነው። የሱፐርቪዥን ስርዓት የተቋማዊ እምርታ ልኬት ማሳያ ስለሆነ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት መልእክት ያስተላለፋት የኮምሽኑ ዋና ኮምሽነር አህመድ መሐመድ ተናግረዋል ። በተያዘው በጀት ዓመት በመጀመሪያዎቹ 6ወራት የተከናወኑ የተግባር ስራዎችን አፈጻጸም እና የህዝብ ተጠቃሚነት፣ አገልግሎት አሰጣጥና መልካም አስተዳደር ስራዎች፣ የቅሬታና አቤቱታ ስርዓት፣ ከአቅም ግንበታ ስራዎች፣ ከሕዝብ ተደራሽነት በዕቅድና ከዕቅድ አልቆ የተፈፀመበት መንገድ ፣ ከአሰራርና ከአደረጃጀት፣ ከምቹ ሁኔታዎች፣ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም በጥልቀት ምልከታ የሚያደርግ መሆኑን የሱፐርቪዥኑን ቡድን የሚመሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ስራ አስኪያጅ በም/ክ ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊና እና የሱፐርቪዥኑ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ ገልፀዋል:: #AAFDRMC Mesfin Ayalew Medhine ኮሚሽኑን በእንዲዚህ አይነቱ ድጋፍና ክትትል ማድረግ ለህዝብ የሚሰጠ

ንፅህናዋ የተጠበቀ ከተማ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪስቶች ሳቢ፣ ለኢንቨስትመንት ደግሞ ተመራጭ ስትሆን "ንፅህና የሥልጣኔ መገለጫና የዜጎች ክብር መገንቢያም ነው -በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ … See more

አዲስ አበባን እንደ ስሟ ጽዱና ውብ በማድረግ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተሠራ ነው AMN | ታኅሣሥ 23/2018 ዓ.ም. አዲስ አበባን እንደ ስሟ ጽዱና ውብ ማድረግ ያስቻሉ ተግባራትን በቅንጅት በማጠናከር የከተማዋን የቱሪስት ተደራሽነት እናሳድጋለን ሲል የከተማዋ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ አስታወቀ። ኤጀንሲው የከተማዋን ጽዳትና ውበት ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል። በሥልጠና መድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወንድሙ ሴታ (ኢ/ር)፥ አዲስ አበባ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ባከናወነቻቸው የጽዳትና ውበት ተግባራት የዓለምን ትኩረት መሳብ መቻሏን ገልጸዋል። ይህ የከተማዋን የቀድሞ ገጽታ የቀየረና በዓለም አቀፍ መድረኮች ጭምር እውቅናን ያስገኘ የጽዳትና ውበት ሥራ ይበልጥ በማጠናከር የከተማዋን የቱሪስት ፍሰት ማሳደግ ይጠበቅብናል ብለዋል ዋና ሥራ አስኪያጁ። ከተማዋን በጽዳትና ውበት ሞዴል እንዳደረግናት ሁሉ፣ አጠቃላይ የቆሻሻ አሰባሰብና አወጋገድ ሥርዓቱን በማዘመን ከዘርፉ በመልሶ መጠቀም የሚገኘውን ሀብት ማሳደግ ይገባልም ብለዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ደሲሳ በበኩላቸው፣ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል የአመራሩንና የባለሙያውን ግንዛቤ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸው፣ ይህም ተቋሙ እየሰጠ የሚገኘውን አገልግሎት ፈጣን፣ ዘመናዊና ውጤታማ ለማድረግ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። "ተደምረን አዲስ አበባን እንደ ስሟ ጽዱና ውብ በማድረግ የቱሪስት መዳረሻ እናደርጋታለን" በሚል መሪ ቃል መሰጠት በጀመረው ሥልጠና ላይ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ የዘርፉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በታምሩ ደምሴ

በከተማችን ትልቁን የውሃ ትርኢት በወንዞች ዳርቻ ልማታችን ገንብተን በማጠናቀቅ ላይ ነን። አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ አበባ ማድረጋችንን አጠናክረን ቀጥለናል ! Magaalaa keenyatti agarsiisa bishaanii guddaa misooma qarqara lagaa keenyaan ijaarree xumuruu irratti argamna. Finfinnee akkuma maqaa ishee abaaboo miidhagduu taasisuu keenya cimsinee itti fufneerra!

ንፅህናዋ የተጠበቀ ከተማ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪስቶች ሳቢ፣ ለኢንቨስትመንት ደግሞ ተመራጭ ስትሆን "ንፅህና የሥልጣኔ መገለጫና የዜጎች ክብር መገንቢያም ነው -በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager See less

ንፅህና ክብርን ከመስጠት ባለፈ በዓለም አቀፍ መድረክ ተወዳዳሪ የሚያደርግ መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለፁ የአዳስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ "ተደምረን አዲስ አበባን እንደ ስሟ ፅዱና ውብ በማድረግ የቱሪስት መዳረሻ እናደርጋታለን!" በሚል መሪ ቃል አገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል ያለመ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከማዕከል እስከ ወረዳ ድረስ ላሉ የመዋቅሩ አመራሮች፣ ለፅዳት አምባሳደሮች፣ ለመማክርት ጉባኤ ዋና ስራ አስፈፃሚዎች እና ለተጋባዥ እንግዶች ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጡ ሙህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል። በስልጠናው ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ እንዳሉት "ንፅህና ክብርን ከመስጠት ባለፈ በዓለም አቀፍ መድረክ ተወዳዳሪ የሚያደርግ መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ባስተላለፉት መልዕክት ንፅህናዋ የተጠበቀ ከተማ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪስቶች ሳቢ፣ ለኢንቨስትመንት ደግሞ ተመራጭ እንደሚያደርጋት ጠቁመው፤ "ንፅህና የሥልጣኔ መገለጫና የዜጎች ክብር መገንቢያ ነው" ብለዋል። አሁን እየታዩ ያሉ የልማትና የውበት ስራዎችን በላቀ ደረጃ ለማሳካት "መደመር" ወሳኝ መሆኑን የገለፁት ኢንጂነር ወንድሙ "ለውጥ የሚመጣው በተበጣጠሰ ጥረት ሳይሆን በጋራ በምናደርገው የተቀናጀ ርብርብ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና የከተማዋ ነዋሪዎች ለጋራ ግብ እንዲሰለፉ ጥሪ አቅርበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ በበኩላቸው አገልግሎት አሰጣጡን በማሳለጥና ውጤታማ በማድረግ የመንግስትን ቅቡልነት ለማረጋገጥ ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመው "ግባችን ከተማዋን ማጽዳት ብቻ ሳይሆን፣ ቆሻሻን ለኢኮኖሚ እድገት መነሻ በማድረግ የስራ እድል መፍጠርና ዜጎች ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ስለመሆኑ ተናግረዋል። "ቆሻሻን ወደ ሀብት" የመቀየር ስትራቴጂን ወደ ተግባር በመቀየር በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ብቻ በዘርፉ የተሰማሩ ማህበራት ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማገኝት መቻላቸውን ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ፖለቲካ ዘርፍ ም/ኃላፊ አቶ ዳዊት ምንዳዬ በበኩላቸው የፅዳት አገልግሎት ዘርፍ የማህበረሰብን ጤና እና የአካባቢን ውበት ለመጠበቅ የሚከናወን ትልቅ የክብር ስራ መሆኑን ገልፀው በዘርፉ የተሰማሩ ሰራተኞች ለሚያበረክቱት ላቅ ያለ አስተዋፅኦ ክብር እንደሚገባቸው ተናግረዋል። በመጨረሻም፣ የተጀመሩ የለውጥ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ የህዝቡ ንቁ ተሳትፎና የባለቤትነት ስሜት አስፈላጊ መሆኑን የገለጹት አቶ ገዛኸኝ "ውብና ፅዱ ከተማን ለትውልድ ማሳደር የሁላችንም ኃላፊነት ነው" በማለት ንግግራቸውን አጠቃለዋል። ከሰልጣኞች በርካታ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በተነሱ ሀሳብ አስተያየቶች ከመድረክ ምላሽ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል። ታህሳስ 23/2018 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

"ዜና አዲስ" አሁን "ዜና አዲስ" AMN - ታኅሣሥ 23/2018 ዓ.ም የቀን 6፡00 ዜናዎቻችንን በቀጥታ ይከታተሉ፤ 👇👇👇👇👇👇👇 ትክክለኛውን የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑን!

On behalf of the City Administration and myself, I extend my warmest wishes for a peaceful and happy 2026 to all ambassadors, international organizations, and friends in Addis Ababa. We look forward to another year of strengthened friendship and cooperation. Happy New Year! H.E Mayor Adanech Abiebie

መዲናችን አዲስ አበባ በፅዳቷ ከአፍሪካ ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ እዉቅና እያገኘች የመጣችዉ በከተማችን በፅዳቱ ዘርፍ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያለዉ መዋቅራችን ተቀናጅቶና ተናቦ የተጠናከረ ስራ በመስራቱ ነዉ ሲሉ በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ አስገነዘቡ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ይህንን ያስገነዘቡት የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ለፅዳት አስተዳደር 22 ለሚሆኑ የወረዳ ፅ/ቤቶች የተለያዩ የመገልገያ ግብዓት ድጋፍ በዛሬዉ እለት ባበረከቱበት ወቅት ነዉ። በመድረኩም ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እንዳስታወቁት በከተማ የጽዳት ስራችን ከሁሉም በላቀ ደረጃ ቆሻሻን ከምንጩ የመለየት ስራን ከማጠናከር በተጨማሪ ቆሻሻን ወደ ሀብትነት በመቀየርና የገቢ ምንጭ በማድረግ ረገድ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በልዩ ትኩረት ተጠናክረው ሊፈጸሙ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። አክለዉም በጽዳት መስክ መጣዉን ለዉጥ በይበልጥ በማስቀጠል በተለይም ህብረተሰቡ ፅዳትን ባህል እስኪያደርግ ድረስ የተለያዩ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን ከቴክኖሎጂ ጋር አስተሳስሮ ተደራሽ በማድረግና ያሉንን ግብዓቶች በአግባቡ በመጠቀም ሁላችንም መዲናችንን የጽዳት ተምሳሌትነቷን የማጠናከር ሀላፊነታችንን በትጋት ልንወጣ ይገባል ሲሉ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አመልክተዋል። በቢሮ ሃላፊ ማዕረግ ም/ዋ/ስራ አስኪያጅ ተፈራ ሞላ (ዶ/ር) በተጠሪ ተቋማት በትኩረት እየተሰራባቸዉ ካሉ ተግባራት አንዱ ሪፎርም እንደሆነ ገልፀው የተጀመረው ሪፎርም የተሟላ እንዲሆንና የሚጠበቀዉን ያህል የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የመጣው ለዉጥ እንዲጎለብት ሁሉም ተቋማት በትኩረት እና በቅንጅት መስራት እንደሚገባቸው ተናግረዋል። የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ደሲሳ በበኩላቸው የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የኤጀንሲውን ተልእኮ ለማሳካት በተለያዩ አግባቦች ለሚያደርገው ድጋፍና ክትትል ያላቸውን ምስጋና ገልጸው መላው መዋቅሩም በጽዳት መስክ የመጡ ለውጦች በዘላቂነት እንዲቀጥሉ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች

እንደ ስሟ ውብ እና አዲስ የሆነችው አዲስ አበባ Finfinnee akkuma maqaashee miidhagduu fi haaraa taate