en
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Open in Telegram
1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
አዲስ ከተማ ክ/ከተማ "ወንዞች የውሃ መሄጃ እንጂ የቆሻሻ መጣያ አይደሉም" በሚል መሪ ሃሳብ የፅዳት ዘመቻ ንቅናቄ ተካሄደ፡፡ በፅዳት ዘመቻው የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ፣ የአዲስ አባባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጄንሲ ዋና ደሬክተር አቶ ገዘኸኝ ዴሲሳ፣ የፌዴራልና የአዲስ አባባ የፖሊስ አባላት፣ የጽዳት አምባሳደሮች እንዲሁም የክፍለ ከተማው አመራሮችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት የፅዳት ንቅናቄ ተካሂዷል፡፡ በእለቱ መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ ወንዞችንና የወንዝ ዳርቻዎችን በማልማት ውብና ማራኪ እያደረገ መሆኑን ገልፀው ወንዞች የውሃ መውረጃ እንጂ የቆሻሻ መጣያ አለመሆናቸውን በተግባር ማሳየት ይኖርብናል ብለዋል:: የአዲስ አባባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጄንሲ ዋና ደሬክተር አቶ ገዘኸኝ ዴሲሳ በበኩላቸው በሁሉም አካባቢ የሚገኙ ወንዞችን በማፅዳት ፅዱ፣ ውብና ማራኪ አከባቢ መፍጠር ጠቅሰው ፅዳት የዘመናዊነት መገለጫ እንደመሆኑ መጠን ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የአካባቢውን ፅዳት በመጠበቅ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ ታህሳስ 25/ 2018 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ብሎክን መሰረት ያደረገ የአንድ ማዕከል ሳምንታዊ የፅዳት ንቅናቄ መርሃ-ግብር ተካሄደ። የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ፅዳት አስተዳደር ጽ/ቤት በወረዳ 8 አስተዳደር ብሎክን መሰረት ያደረገ የአንድ ማዕከል ሳምንታዊ የፅዳት ንቅናቄ መርሃ-ግብር አካሄዷል። የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሃንስ ለገሠ ቆሻሻ በአግባቡ ማስተዳደር ካልተቻለ ለጤና ጠንቅ ምክንያት በመሆኑ ተግባሩ የአንድ ቀን ብቻ ሳይሆን የሁል ጊዜ መሆኑን ጠቁመው፣ አካባቢንን ውብ ፅዱና ለኑሮ ምቹ ከማድረግ ባሻገር አዲስ አበባ ከተማን የቱሪስት መዳረሻና የፅዳት ተምሳሌት ማድረግ እንደሚገባ፣ ፅዳት የስልጣኔ መገለጫ በመሆኑ ሁሉንም ሰው ብሎኮች በርብርብ ሞዴል ለማድረግ የድርሻውን እንዲወጣ መልዕክት አስተላፈዋል። የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ማናዬ ጫኔ በበኩላቸው የንቅናቄው ዓላማ አካባቢያችን ቆሻሻ የማይጣልበት፣ የቆሻሻ አወጋገድ፣ አስተዳደር አግባቡ በማስገንዘብ አካባችንን ውብ ፅዱ ለመኖሪያ ምቹ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀው፣ ቆሻሻ እንደ ባህሪው ካስተዳደርነው የሀብት ምንጭና ስራ ዕድል እንዲሁም በገቢ ምንጭ ከፍተኛ ሚና እንዳለው በመገንዘብ የህብረተሰቡ በፅዳት በንቃት በመሳተፍ ሞዴል ብሎክ በባለቤት ሚናውን እንዲወጣ ተናግረዋል። በመጨረሻም የወረዳ 8 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አዋዝ አስፋው በተጠናከረ የነዋሪዎች ተሳትፎ ሞዴል ብሎክን መፍጠር ዓላማ አድርጎ እየተሰራ እንዳለ ጠቁመው፣ ፅዳት የሁልጊዜ ተግባር በመሆኑ ሁሉም ሰው የአካባቢውንና የክ/ከተማውን አልፎም ከተማውን መጠበቅ እንደሚገባው መልዕክት አስተላልፈዋል። Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የአረንጓዴ አሻራ አካል የሆነው የሻይ ልማት ኢኒሺዬቲቭ ተከላው በጥሩ ሁኔታ እየተከወነ ነው። በመትከል የታየው መልካም ጅማሮ በአግሮ–ፕሮሴሲንግ ከተደገመ ሙሉ ስለሚሆን የግሉ ዘርፍ እሴት በማከል ቢሳተፍ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ በተጨማሪ በኤክስፖርት ሀገራችንን ተጠቃሚ ያደርጋታል። The tea development initiative, which is part of the Green Legacy program, is being implemented successfully. The promising start observed in planting, if followed through with full agro-processing and supported by private sector participation to add value, will benefit our country through exports in addition to meeting domestic consumption needs.

ፍትሀዊ እና አካታች ስራ Hojii haqa qabeessaa fi hunda hammataa!

አዲስ የቱሪስት መዳረሻ ! በወንዞች ዳርቻ ልማት ጊዮን አካባቢ ከሰራነዉ መሰረተ ልማት አንዱ የሆነዉ የከተማችን ትልቁ ፋዉንቴን ( የዉሃ ትርኢት) በሙከራ ላይ Gahuumsa Turistii Haaraa ! Misooma qarqara laggeeniitiin naannoo Giyoonitti bu'uura misoomaa hojjenne keessaa tokko kan ta'e Faawunteeniin (agarsiisni bishaanii) guddaan yaalii irra jira.

አዲስ አበባን በአፍሪካ ለሕፃናት ማሳደግ ምቹና ተመራጭ ከተማ ለማድረግ የጀመርነው ሥራ ፍሬ እያፈራ ይገኛል። በከተማችን እየተተገበረ ባለው የቀዳማይ ልጅነት ልማት መርሃ ግብር አማካኝነት፣ በየሰፈሩ የለየናቸው ውስብስብ እና ከፍተኛ የአካል ጉዳት ያለባቸው 177 ሕፃናት እንደየጉዳታቸው ሁኔታ የተዘጋጁ ምቹ ዊልቸሮች ድጋፍ ተደርጎላቸዋል። ዊልቸሮቹ እንደየሕፃናቱ የአካል ጉዳት ሁኔታ ተስማሚ ሆነው መሠራታቸው ለሕፃናቱ ምቹና ውጤታማ ድጋፍ እንዲሰጡ ያደርጋቸዋል። ይህም የአካታችና ሁሉን አቀፍ ልማታችን አካል ሲሆን፣ ከተማችን ማህበራዊ ፍትህ የነገሰባት ትሆን ዘንድ በቀጣይ ተደራሽ ያልሆኑ ሕፃናትን ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንሰራለን። ይህንን በጎ ተግባር ያስተባበራችሁና አብራችሁን በቅርበት እየሠራችሁ ያላችሁ አጋሮቻችንን፣ በተለይም የክሊንተን ሄልዝ አክሰስ ኢኒሼቲቭን በተጠቃሚ ሕፃናትና ወላጆቻቸው ስም ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! Finfinnee akka Afrikaatti daa'imman guddisuuf magaalaa mijattuufi filatamtuu taasisuuf hojiin eegalle bu'aa argamsiisaa jira. Magaalaa keenyatti hojirra oolaa kan jiru sagantaa misooma daa'immanii jalqabaatiin daa'imman hanqina qaamaa wal xaxaa fi cimaa qaban bakkeewwan garaagraa irraa adda baafnee 177 akkaataa hanqina isaaniitiin kan qophaa'an wiihilcheerootni mijatoon deeggarsa taasifamaniiru. Wiihilcheerotni kunneen akkaataa hanqina qaamaa daa’immaniif mijatoo ta'anii hojjetamuunsaanii daa’immaniif deeggarsa mijataa fi bu’a qabeessa akka kennan kan taasisuudha. Kunis qaama misooma hunda hirmaachisaa fi hunda-haammataa keenyaa yemmuu ta'u, magaalaan teenya haqummaan hawaasummaa kan itti moo'e akka taatu taasisuuf kuttannoon ni hojjenna. Tola ooltummaa kana haala kan mijeessitan fi nuwaliin walitti dhiheenyaan hojjechaa kan jirtan tumsitoonni keenya, keessattuu Inisheetiivii Heelzi Aksasii Kiliintan maqaa daa'iimman fayyadamtoota fi maatii isaaniitiin onneerraa isin galateeffadha. Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!

“ምሁር ማነው?" የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የምሁራን ሚና ለሀገራዊ ብልጽግና” በሚል ርዕስ የጥናታዊ ጽሁፍ እያቀረቡ ይገኛሉ። የአካዳሚያዊ አመራሮችና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ገለጻው እየተሰጠ ይገኛል። የዛሬው መርሃ ግብር 75ኛ ዓመት በዓሉን ለማክበር ላለፉት ሳምንታት ሲደረጉ የነበሩ ተከታታይ ገለጻዎች እና ፕሮግራሞች ማጠቃለያ ነው። #PMOEthiopia

የሱፐርቪዥን ስርዓት የተቋማዊ እምርታ ልኬት ነው፣ #AAFDRMC_ታህሳስ 23/2018ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ቢሮ በእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮምሽን የሱፐርቪዥን ምልከታ አካሄደ። የሱፐርቪዥን ቡድንም በኮምሽኑ በዘርፎች ያለውን ምልከታ ከትናት ከታህሳስ 22/2018ዓ.ም ጀምሮ ምልከታ ያደረገ ሲሆን። የአደጋ ስጋት ቅነሳ ዘርፍ የአደጋ ምላሽ ዘርፍ፣ የድህረ አደጋ ምላሽ ዘርፍ፣ የቴክኖሎጂና ምህድስና ዘርፍ፣ የኮምሽኑ ጽ/ቤት እና የስልጠና ማእከሉ ያስመዘገቡትን የስድስት ወር ድሎች ከሪፖርት እስከ ተግባር ያሉትን ውጤቶች በተጨባጭ መረጃ ምልከታ አድርገዋል። የሱፐርቪዥን ምልከታው ክፍተቶችን ማረምና ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል አቅም የሚፈጥርና ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ አቅም የሚፈጥር ነው። የአንድ ተቋም የሚለካው ብዙ አይነት የEvaluation and Assesment ስርዓቶች ያአሉሲሆን ከዛ ውስጥ አንዱ ደግሞ ሱፐርቪዥን ነው። የሱፐርቪዥን ስርዓት የተቋማዊ እምርታ ልኬት ማሳያ ስለሆነ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት መልእክት ያስተላለፋት የኮምሽኑ ዋና ኮምሽነር አህመድ መሐመድ ተናግረዋል ። በተያዘው በጀት ዓመት በመጀመሪያዎቹ 6ወራት የተከናወኑ የተግባር ስራዎችን አፈጻጸም እና የህዝብ ተጠቃሚነት፣ አገልግሎት አሰጣጥና መልካም አስተዳደር ስራዎች፣ የቅሬታና አቤቱታ ስርዓት፣ ከአቅም ግንበታ ስራዎች፣ ከሕዝብ ተደራሽነት በዕቅድና ከዕቅድ አልቆ የተፈፀመበት መንገድ ፣ ከአሰራርና ከአደረጃጀት፣ ከምቹ ሁኔታዎች፣ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም በጥልቀት ምልከታ የሚያደርግ መሆኑን የሱፐርቪዥኑን ቡድን የሚመሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ስራ አስኪያጅ በም/ክ ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊና እና የሱፐርቪዥኑ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ ገልፀዋል:: #AAFDRMC

ንፅህናዋ የተጠበቀ ከተማ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪስቶች ሳቢ፣ ለኢንቨስትመንት ደግሞ ተመራጭ ስትሆን "ንፅህና የሥልጣኔ መገለጫና የዜጎች ክብር መገንቢያም ነው -በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ … See more