en
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Open in Telegram
1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
ዛሬ ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ጋር በመሆን፣ የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብርን ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገረውን የቱሉ አራራ የተቀናጀ ሞዴል መንደርን በይፋ መርቀናል። ይህ ሞዴል መንደር በ7 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን፣ እያንዳንዱ ቤት ሁለት መኝታ ክፍሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ አምስት ክፍሎች እንዲኖሩት ተደርጎ ደረጃውን ጠብቆ የተገነባ ነው። መንደሩ በቤተሰብ ደረጃ ለ150 ዜጎች ምቹና ጽዱ መኖሪያ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የመሠረተ ልማት አቅርቦቱም የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ የኤሌክትሪክና የሶላር ኃይል፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ስፍራ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ያካተተ ነው። የነዋሪዎቹን የኑሮ ደረጃ በዘላቂነት ለማሻሻል መንደሩ የምርትና የገበያ ሰንሰለትን ያካተተ የተቀናጀ አሰራርን ዘርግቷል። ይህ የልማት ስራ የወተት ላሞች እና የዶሮ እርባታን እንዲሁም የጓሮ አትክልት ልማትን አጣምሮ የያዘ ሲሆን፣ እስከ መገበያያ ስፍራ የሚደርስ የተቀናጀ የንግድ ሰንሰለት ተፈጥሮለታል። Har'a Giiftii Duree Zinnaasha Taayyaachewfi hooggantoota mootummaa olaanaa waliin ta'uudhaan Mandara Moodeela Qindaawaa Tulluu Araaraa sagantaa tola ooltummaa gannaa gara sadarkaa olaanaatti ceesise ifatti eebbifneerra. Mandarri Moodeelaa kun lafa hektaara kuma 7 irra kan buufate yoo ta'u, tokkoon tokkoo manichaa kutaalee ciisichaa lama dabalatee waliigalatti kutaalee shan akka qabaatu ta'ee sadarkaasaa eeggatee kan ijaaramedha. Mandarichi sadarkaa maatiitti lammiilee 150f mana jireenyaa qulqulluufi mijaawaa akka ta'u yaadamee kan ijaarame yoo ta'u, gama misooma bu'uraatiin daandii keessaa, humna elektiriikiifi soolaarii, bakkewwan sochii jabina qaamaafi misooma magariisaa kan of keessatti haammatedha. Sadarkaa jireenya jiraaattotaa haala waaraa ta'een fooyyessuuf mandarichi hojimaata hidhatiinsa hoomishaafi gabaa qindaawaa diriirseera. Hojiin misoomaa kun loon aannaniifi horsiisa lukkuu akkasumas misooma kuduraa qee walfaanaa kan qabate yoo ta'u, hidhati daldalaa qindaawaa hamma lafa gabaatti diriire uumameeraafi. Together with First Lady Zinash Tayachew and senior government officials, we officially inaugurated the integrated Tulu Arara model village, which has elevated the rainy season volunteer and charity program to a higher level. This model village is spread over an area of 7,000 square meters. Each house has been constructed to standard and contains a total of five rooms, including two bedrooms. The village was designed to provide comfortable and dignified housing for 150 citizens at the household level. Its infrastructure provision includes internal roads, electricity and solar power, a physical fitness and recreation area, and green development initiatives. To sustainably improve the residents’ standard of living, the village has implemented an integrated system that incorporates production and market value chains. This development initiative combines dairy cattle and poultry farming along with backyard gardening, and an integrated commercial chain has been established that extends all the way to market outlets.

ዛሬ ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ጋር በመሆን፣ የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብርን ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገረውን የቱሉ አራራ የተቀናጀ ሞዴል መንደርን በይፋ መርቀናል። ይህ ሞዴል መንደር በ7 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን፣ እያንዳንዱ ቤት ሁለት መኝታ ክፍሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ አምስት ክፍሎች እንዲኖሩት ተደርጎ ደረጃውን ጠብቆ የተገነባ ነው። መንደሩ በቤተሰብ ደረጃ ለ150 ዜጎች ምቹና ጽዱ መኖሪያ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የመሠረተ ልማት አቅርቦቱም የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ የኤሌክትሪክና የሶላር ኃይል፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ስፍራ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ያካተተ ነው። የነዋሪዎቹን የኑሮ ደረጃ በዘላቂነት ለማሻሻል መንደሩ የምርትና የገበያ ሰንሰለትን ያካተተ የተቀናጀ አሰራርን ዘርግቷል። ይህ የልማት ስራ የወተት ላሞች እና የዶሮ እርባታን እንዲሁም የጓሮ አትክልት ልማትን አጣምሮ የያዘ ሲሆን፣ እስከ መገበያያ ስፍራ የሚደርስ የተቀናጀ የንግድ ሰንሰለት ተፈጥሮለታል። Har'a Giiftii Duree Zinnaasha Taayyaachewfi hooggantoota mootummaa olaanaa waliin ta'uudhaan Mandara Moodeela Qindaawaa Tulluu Araaraa sagantaa tola ooltummaa gannaa gara sadarkaa olaanaatti ceesise ifatti eebbifneerra. Mandarri Moodeelaa kun lafa hektaara kuma 7 irra kan buufate yoo ta'u, tokkoon tokkoo manichaa kutaalee ciisichaa lama dabalatee waliigalatti kutaalee shan akka qabaatu ta'ee sadarkaasaa eeggatee kan ijaaramedha. Mandarichi sadarkaa maatiitti lammiilee 150f mana jireenyaa qulqulluufi mijaawaa akka ta'u yaadamee kan ijaarame yoo ta'u, gama misooma bu'uraatiin daandii keessaa, humna elektiriikiifi soolaarii, bakkewwan sochii jabina qaamaafi misooma magariisaa kan of keessatti haammatedha. Sadarkaa jireenya jiraaattotaa haala waaraa ta'een fooyyessuuf mandarichi hojimaata hidhatiinsa hoomishaafi gabaa qindaawaa diriirseera. Hojiin misoomaa kun loon aannaniifi horsiisa lukkuu akkasumas misooma kuduraa qee walfaanaa kan qabate yoo ta'u, hidhati daldalaa qindaawaa hamma lafa gabaatti diriire uumameeraafi. Together with First Lady Zinash Tayachew and senior government officials, we officially inaugurated the integrated Tulu Arara model village, which has elevated the rainy season volunteer and charity program to a higher level. This model village is spread over an area of 7,000 square meters. Each house has been constructed to standard and contains a total of five rooms, including two bedrooms. The village was designed to provide comfortable and dignified housing for 150 citizens at the household level. Its infrastructure provision includes internal roads, electricity and solar power, a physical fitness and recreation area, and green development initiatives. To sustainably improve the residents’ standard of living, the village has implemented an integrated system that incorporates production and market value chains. This development initiative combines dairy cattle and poultry farming along with backyard gardening, and an integrated commercial chain has been established that extends all the way to market outlets.

On the birthday (Christmas) holiday, together with the first lady Zinash Tayachew, we have attended Sheikh Fatima Bin Mebruk School for the Blind and shared a meal. Spending this special morning together has shown us the true spirit of Christmas. On this birth day (Qile) we have shared a source with Queen Zinash Tayachew in Qaro Dhabeyi Sheika Fatima Bint Mubarak. By spending this special morning together we have remembered the true purpose of the holiday. On the blessed occasion of Ethiopian Christmas (Genna), First Lady Zinash Tayachew and I were honored to share a holiday meal with the students of the Sheikha Fatima Bint Mubarak School for the Blind. Spending this special morning together was a powerful reminder of the true meaning of the spirit of Genna. · See original · Rate this translation

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ! ዘንድሮ የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት የምናከብረው የተነገረው የተስፋ ቃል መድረሱን፣ የለውጥ ብርሃን መፈንጠቅ መጀመሩን፣ የመሻገር ዘመን መቅረቡን እያመንን ነው። ጉዟችን በውጣ ውረድ የተሞላ ነበር፤ ተስፋ አስቆራጭ መከራዎችን አስተናግደናል። ከእንግዲህ ፈተናው ጨርሶ አይጎበኘንም ባንልም፣ ተስፋችን የሚወለድበት የዋዜማው ዕለት ላይ ደርሰናል። የፍዳው ዘመን ላይመለስ ተሸኝቶ፣ የማንሠራራት ዘመን እንደመጣ በልበ ሙሉነት መናገር እንችላለን። የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ትናንትን የዋጀ፣ ነገን የታደገ ነው። ከአዳም እስከ ክርስቶስ ልደት የተከናወነው ሁሉ ዋጋ ያገኘው በክርስቶስ መወለድ ምክንያት ነው። ከክርስቶስ ልደት በኋላ ያለው የሰው ልጅ ሕይወት ቀና የሆነው በክርስቶስ ምክንያት ነው። ክርስቶስ በትናንትና በነገ መካከል “ዛሬ” ሆኖ ሁለቱን አስታርቋቸዋል። ለዚህ ነው የክርስቶስን መወለድ በታላቅ ክብር የምናከብረው። ክርስቶስ ባይወለድ ኖሮ ትንቢት የተናገሩ ነብያት፣ መሥዋዕት ያቀረቡ ካህናት፣ ቃል ኪዳን የተቀበሉ አበው፣ ተስፋ ያደረጉ የሰው ልጆች ሁሉ ሥራቸው ታሪክ ብቻ ሆኖ ይቀር ነበር። ዋጋ ከፍሎ ህያው ያደረጋቸው ክርስቶስ ነው። ክርስቶስ ባይወለድ ኖሮ የሰው ልጅ ወደፊት የሚያከናውናቸው የሥልጣኔ፣ የጽድቅ እና የበጎነት ሥራዎች ሁሉ የድኅነት ቅኝት አይኖራቸውም ነበር። ትናንትን የቀደሰው፤ ነገንም የዋጀው፣ ዛሬ የተወለደው ክርስቶስ ነው። ይሄንን ታላቅ ትምህርት እናስተውል ዘንድ ይገባናል። ትናንት የቱንም ያህል ታላቅ ታሪክ፣ ታላቅ ቅርስ እና ታላቅ ዕሴት ቢኖረንም ዛሬያችን ከተበላሸ ዋጋ የለውም። ባቢሎን እና ፋርስ፣ አቴና እና ሮም፣ ሱሜር እና ሜሶፖታምያ - ዛሬ በጥንቱ ክብራቸውና ታላቅነታቸው የሉም። እነርሱ ትናንት ነበራቸው። ያጡት ዛሬን ነው። ዛሬን በማጣታቸው ደግሞ ትናንታቸው ትዝታ፣ ነጋቸው ሕልም ሆኗል። ትውስታ እንጂ እመርታ የላቸውም። ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር ነበረች። የታላላቅ ሥልጣኔዎች ሀገር ነበረች። የታላላቅ መንግሥታትና የታላላቅ ሕዝቦች ሀገር ነበረች፤ የታላላቅ ባህሎች እና የአስደናቂ ቅርሶች ሀገር ነበረች። ጥያቄው “ዛሬስ” የሚለው ነው። ዛሬ በድህነት፣ በኋላ ቀርነትና በረሃብ የምንሰቃይ ከሆነ፣ ታሪካችንን አልዋጀነውም ማለት ነው። ትናንትን የሚዋጀው ዛሬ ነውና። ትናንት የሚቃኘውና የሚተረጎመው በዛሬ መንፈስ ነው። የዛሬ ከፍታ ትናንትን ጨምሮ ከፍ ያደርገዋል። የዛሬ ተዋርዶ ደግሞ ትናንትን ጨምሮ ያወርደዋል። የሀገራችንን ታላቅነት የሚገነዘብ ትውልድ አሁን ተፈጥሯል፡፡ ትውልዱ የድህነትን በትር ደጋግሞ ቀምሷል፤ የኋላቀርነትን አስቀያሚ መልክ እስኪበቃው አይቷል፡፡ የትናንት ስሕተት ያስከተለውን ፍዳ ትከሻው እስኪጎብጥ ለመሸከም ተገድዷል፡፡ የመልክአ ምድር እሥረኝነት ዓይን አፍጥጦ፣ ጥርስ አግጥጦ ሲመጣ የታዘበ ትውልድ ነው፡፡ የችግሩን ልክ መዝኖ መረዳት ብቻ ሳይሆን የመሻገሪያ መርከቡን መገንባት የሚያውቅ ትውልድ ነው፡፡ የትናንት ኩስመናን በዛሬ ትጋት እንደሚያሸንፉ የሚያምኑ ዜጎች ቁጥራቸው በጨመረ ቁጥር የነገ ቁመናችን እንደሚሻሻል ጥርጥር የለውም፡፡ የነቢያት ጽድቅና ትንቢት የቀጠለው የነቢያት አምላክ ክርስቶስ ትንቢታቸውን ፈጽሞ ስለተወለደ ነው። የትንቢት መጻሕፍት ዋጋ ያገኙት በወንጌል መጻሕፍት የተነሣ ነው። ብሉይ ኪዳን ጥቅም ያገኘው በሐዲስ ኪዳን ምክንያት ነው። ሁሉንም ትናንቶች የዋጃቸው ዛሬ ነው። ትናንታችን ዋጋ እና ክብር እንዲኖረው ከፈለግን ዛሬ ተግተን እንሥራ። ብዙ ጊዜያችንን በትናንት ትዝታ እና ትውስታ ውስጥ ከምናሳልፍ፣ በዛሬ ትግልና ውጣ ውረድ ላይ እናጥፋ። ዛሬያችን የተስተካከለና የተቃና ከሆነ፣ ያለ ጥርጥር ትናንትናችን ተገቢውን ክብር ያገኛል። ክርስቶስ ባይወለድ ኖሮ ከክርስቶስ ልደት በኋላ ያለው ዘመን አዲስ ዘመን አይሆንም ነበር። “ነገን ለመተንበይ የተሻለው መንገድ፣ ነገን ራሱን መፍጠር ነው” ይባላል። የሰው ልጆችን ነገ ክርስቶስ ጀመረው፤ ክርስቲያኖች ደግሞ ተራመዱበት። ዛሬ የተሻለ ሥራ የሚሠሩ ሰዎች ነገን የተሻለ አድርገው ይፈጥሩታል። ዛሬን በዋዛና በፈዛዛ፣ በክፋትና በሤራ የሚኖሩ ሰዎች ደግሞ ነገን የባሰ አድርገው ያበላሹታል። የኢትዮጵያ ነገ በዛሬ ሥራና ተጋድሎ እንጂ በዛሬ ምኞትና መሻት ብቻ አይመጣም። አንዳንዶች የኢትዮጵያን ነገ ለማበላሸት ዛሬ በክፋት ሥራዎች ተነክረዋል። እኛ ግን የኢትዮጵያን ነገ ለማቅናት ስንል ነገን በሚዋጁ ሥራዎች ተጠምደናል። ነገን የሚዋጀው ዛሬ መሆኑን ስለምናውቅ፣ ነገን ተቀምጠን አንጠብቀውም። ሠርተን እንደርስበታለን እንጂ። ከቤተልሔም በረት እስከ ቀራንዮ ዐደባባይ የሰው ልጆች ትናንት ሲቀደስ፣ የሰው ልጆች ነገ ሲሠራ መልከ ብዙ ምላሽ ነበረው። የተኙ ነበሩ። የናቁ ነበሩ። ገዳዮች ነበሩ። አሳዳጆች ነበሩ። ሤረኞች ነበሩ። ወሬኞች ነበሩ። አደናቃፊዎች ነበሩ። ነቃፊዎች ነበሩ። በሌላ በኩል ደግሞ ገብቷቸው የተከተሉ፤ ነገን ለመሥራት የተባበሩ፤ እውነት ለመንገር የደፈሩ፤ ለእውነት ለመሠዋት የቆረጡ፤ ጥቂቶች ቢሆኑም ብዙዎችን ለማፍራት የሚተጉ - ነበሩ። የኢትዮጵያ ነገ ሲሠራም ምላሹ ልዩ ልዩ ነው። የሚያሸንፉት ግን ተግተው የሚሠሩት ናቸው። ቪክቶር ሁጎ “ጊዜው የደረሰን ሐሳብ ለማስቆም የሚችል ኃይል በዓለም ላይ የለም” ብሎ ነበር። የኢትዮጵያ ብልጽግና ጊዜው የደረሰ ሐሳብ ነው። ማንም ሊያስቆመው አይቻለውም። የኢትዮጵያ ታላቅነት ጊዜው የደረሰ ሐሳብ ነው። ሊገታው የሚችል ምንም ኃይል የለም። እኛ ዛሬ የቆምነው በትናንት እና በነገ መካከል ነው። ትናንትን በዛሬ ሥራችን ዋጋ እንዲያገኝ እናደርገዋለን። ነገን ደግሞ በዛሬው ሥራችን አሣምረን እንገነባዋለን። የክርስቶስን የልደት በዓል ይሄንን ታሪካዊ ኃላፊነታችንን እያሰብን እናከብረዋለን። በድጋሚ መልካም የልደት በዓል ይሁንልን!! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ! ታኅሣሥ 28፣ 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

የገና አፍታ ከመደመር ትውልድ ጋር #PMOEthiopiaየገና አፍታ ከመደመር ትውልድ ጋር #PMOEthiopia

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! “ዘንድሮ የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት የምናከብረው የተነገረው የተስፋ ቃል መድረሱን፣ የለውጥ ብርሃን መፈንጠቅ መጀመሩን፣ የመሻገር ዘመን መቅረቡን እያመንን ነው። ጉዟችን በውጣ ውረድ የተሞላ ነበር፤ ተስፋ አስቆራጭ መከራዎችን አስተናግደናል። ከእንግዲህ ፈተናው ጨርሶ አይጎበኘንም ባንልም፣ ተስፋችን የሚወለድበት የዋዜማው ዕለት ላይ ደርሰናል። የፍዳው ዘመን ላይመለስ ተሸኝቶ፣ የማንሠራራት ዘመን እንደመጣ በልበ ሙሉነት መናገር እንችላለን።” ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ደ/ር ዐቢይ አህመድ በዓሉን ስናከብር የፍቅር መገለጫ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ በማድረግ የተቸገሩትን በማሰብ እና በመርዳት ፍቅርን በመግለጥ ይሁን። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የአብሮነት ይሁንላችሁ። በድጋሚ መልካም የልደት በዓል ይሁንልን!! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! “ዘንድሮ የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት የምናከብረው የተነገረው የተስፋ ቃል መድረሱን፣ የለውጥ ብርሃን መፈንጠቅ መጀመሩን፣ የመሻገር ዘመን መቅረቡን እያመንን ነው። ጉዟችን በውጣ ውረድ የተሞላ ነበር፤ ተስፋ አስቆራጭ መከራዎችን አስተናግደናል። ከእንግዲህ ፈተናው ጨርሶ አይጎበኘንም ባንልም፣ ተስፋችን የሚወለድበት የዋዜማው ዕለት ላይ ደርሰናል። የፍዳው ዘመን ላይመለስ ተሸኝቶ፣ የማንሠራራት ዘመን እንደመጣ በልበ ሙሉነት መናገር እንችላለን።” ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ደ/ር ዐቢይ አህመድ በዓሉን ስናከብር የፍቅር መገለጫ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ በማድረግ የተቸገሩትን በማሰብ እና በመርዳት ፍቅርን በመግለጥ ይሁን። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የአብሮነት ይሁንላችሁ። በድጋሚ መልካም የልደት በዓል ይሁንልን!! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ፣ ዛሬ በዋዜማው 381 ቤቶችን ከሙሉ የቤት ዕቃና ከበዓል ማሳለፊያ ጋር በስጦታ አስረክበናል። ክብርት አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ከእነዚህ ቤቶች መካከል፦ 273ቱ ቀደም ሲል የወዳደቁ የቀበሌ ቤቶች የነበሩ ሲሆኑ፣ ሙሉ በሙሉ ፈርሰው እንደገና በመገንባት ለቀድሞ ለነዋሪዎች የተላለፉ ናቸው። 108ቱን ደግሞ ለአቅመ ደካሞችና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች፤ ለሀገር የአካል ዋጋ ለከፈሉ የጀግናው የመከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ አባላት፤ ለኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም ለሀገር ባለውለታዎች አስተላልፈናል። ቤቶቹ የሕፃናት መጫወቻን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች የተሟሉላቸው፣ አዲስ የተገነቡ ዘመናዊ መንደሮች ናቸው። ከተማችንን ውብ አበባ ስናደርግ፣ የነዋሪዎቻችንን የኑሮ ዘይቤ በማዘመን እና የኑሮ ጫናዎችን እያቃለልን ጭምር ነው ። በከተማችን ከለውጡ ወዲህ በሰው ተኮር እሳቤ እየተመራን የበጎ ፍቃድ ተሳትፎ ባህል እየሆነ በመምጣቱ 45 ሺህ ቤቶችን በበጎ ፍቃድ ተሳትፎ በመገንባት ለማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ ወገኖችና ለሀገር ባለውለታዎች በማድረስ እምባቸውን ማበስ ተችሏል። “ሃምሳ ሎሚ ለሃምሳ ሰው ጌጡ ነው” እንደሚባለው፤ ሁላችንም እየተባበርን ጊዜያዊ ችግሮችን በጋራ በመሻገር ለዘላቂ ልማት እንተጋለን። ለበጎ ፍቃደኞችና ለአስተባባሪዎች በሙሉ በተለይም የኤን .ኤ ቢዝነስ ቬንቸርስ እና ምርጦቹ 7000 ቤተክርስቲያንን በተጠቃሚዎቹ፣ በከተማው አስተዳደሩ እና በራሴ ስም ከልብ አመሰግለሁ። መልካም በዓል! ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይበርክ!

ከኢትዮጽያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር የስምምነት ሰነድ የፊርማ ስነስርአት መድረክ ተካሄደ። የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ተቋማት ወደ ቀጣይ የተግባር ምዕራፍ ለማሻገርና ተጠሪ ተቋማቱ የአለም አቀፍ ደረጃ (ISO) ሰርቲፋይ ለመሆን እንዲችሉ ከኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢኒስቲትዩት ወደ ቀጣይ የትግበራ ምዕራፍ ለመግባት የሚያስችል የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች በተገኙበት በዛሬዉ እለት የስምምነት ሰነድ የፊርማ ተካሂዷል። በዚሁ መድረክ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እንደገለፁት ተቋማቶቻችን የከተማዋ የእድገት የሚመጥን አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ ለመስጠትና የተገልጋዩ ፍላጎትን ያሟሉ ለማድረግ እንዲሁም የሚሰጡትን አገልግሎቶች የዘመነና የላቁ ለማድረግ ተቋማቶቻችንን ወደ ተግባር ምዕራፍ ለማስገባት ያስችለናል ሲሉ ገልጸዋል። አክለውም የሚሰጡት ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች በከተማዋ የእድገት ግስጋሴ ላይ ያላቸዊ አዎንታዊ ተፅዕኖ የጎላ መሆኑን ጠቅሰዉ ተቋሞቹን በተለይም ወደዚህ የደረጃ ስርዓት በማስገባት አገልግሎት አሰጣጡ ላይ አመርቂ የሆነ ለዉጥ ለማምጣትና የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለተገልጋዩ ህብረተሰብ በዘላቂነት ተደራሽነት እንዲኖራቸው አቅምን የሚያጠነክር ነዉ ሲሉ አስገንዝበዋል። አያይዘዉም የተጀመረዉ የስራ ሂደት ሁሉም ተቋማት ጥራቱን የጠበቀና የአገልግሎት አሰጣጡን በይበልጥ ለመዘርጋትና የተገልጋይ እርካታን ለማሳደግ በትኩረትና በቅንጅት በመስራት ቀጣይነት ያለዉ የዘመነ አገልግሎት ለነዋሪዎቻችን ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራም ገልፀዋል። ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸው በይበልጥ ተደራሽ ለማድረግና በተጨማሪ የሚሰጡ አገልግሎቶች ለተገልጋዮች ቀላል ቀልጣፋ እንዲሁም ምቹ ከማድረግ አንፃር በቀጣይ ከሁሉም ተቋሞች ጋር በቅርበት በመስራት የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ በይበልጥ አመርቂ ለዉጥ ለማምጣት በትኩረት መሰራት እንደሚገባዉ የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሠረት በቀለ አሳስበዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ፣ በከተማችን በሚገኙ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ለሚኖሩ ከ300 ሺህ በላይ ምንም የገቢ ምንጭ ለሌላቸው፣ ለማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ፣ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸውና አቅመ ደካማ ወገኖቻችን የማዕድ ማጋራት መርሐ-ግብር አካሂደናል። የገና በዓል የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልና የፍቅር መገለጫ በመሆኑ፣ በማዕድ ማጋራት ለተቸገሩ ወገኖቻችን ያለንን ፍቅር በተግባር የምንገልጽበት ነው። ይህ የበጎነት ተግባር የከተማችንን ጥልቅ የመረዳዳትና የአብሮነት እሴት ይበልጥ የሚያጸና ሲሆን፤ ዛሬም ጊዜያዊ ችግርን ለማለፍ እጅ ለአጅ ተያይዘን የምንቆም እና ለዘላቂ ልማት የምንተጋ ታላቅ ሕዝቦች መሆናችንን በተግባር ያረጋገጥንበት ነው። በሁሉም በዓላት ካላቸው ላይ ለወገኖቻቸው በማካፈል፣ ለዚህ በጎ ተግባር መሳካት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ አብረውን ለቆሙ ልበ-ቀና ባለሀብቶች፣ በትጋት ላስተባበሩ ወጣቶችና አመራሮች በራሴ፣ በከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም በተጠቃሚ ወገኖቻችን ስም ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። በዓሉ የፍቅር፣ የሰላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ ከወዲሁ ከልብ እመኛለሁ! ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ! መልካም በዓል! ከንቲባ አዳነች አቤቤ