1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት የሚያሳልጥ የቴክኖሎጂ አሰራር አቅም ተገንብቷል
አዲስ አበባ፤ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት የሚያሳልጥ የቴክኖሎጂ አሰራር አቅም መገንባቱን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ።
በአዲስ አበባ ከተማ 23 ወረዳዎች በኃይል መቆራጥ የሚፈጠርን የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተት ምላሽ የሚሰጥ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።
በዚሁ ጊዜ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፤ የመዲናዋን ነዋሪዎች የተቋማት የአገልግሎት ፍላጎት እርካታ የሚያረጋግጥ ዘመናዊ አሰራር እየተዘረጋ ነው ብለዋል።
በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተፈጠረው ዘመናዊ የቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓት አቅም ለተገልጋዮች የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማሳለጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በወረዳዎች የተገነባው የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክትም በኃይል መቆራረጥ ምክንያት የሚፈጠርን የአገልግሎት ክፍተት ምላሽ በመስጠት የደንበኛ እርካታን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
በተለይም በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ወቅት የኤሌክትሪክ ኃይል ሲቋረጥ የሚፈጠሩ የአገልግሎት ክፍተቶች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ለደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚረዳ አስረድተዋል።
በቀጣይም የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች በአስተማማኝ የኃይል አቅርቦትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ አሰራር የማስቀጠል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል።
የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ፤ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቱ የወሳኝ ኩነት አገልግሎቶችን ለማሳለጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብለዋል።
በቀጣይም አገልግሎት በሚበዛባቸው ወረዳዎች የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቶችን በማስፋት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲያገኙ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እሸቱ ለማ (ዶ/ር)፤ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቱ በኃይል መቆራረጥ ምክንያት የሚፈጥርን የአገልግሎት ክፍተት አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንደሚረዳ ተናግረዋል።
#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የፀሃይ ብርሃንን በመጠቀም አገልግሎት አሰጣጡን ማቀላጠፍ እንደሚገባ ተገለፀ
የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ እያደረገ ባለው የተቋም ግንባታ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ቴክኖሎጂ ማሸጋገሩ ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በከተማዉ በሚገኙ በተመረጡ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በሚያጋጥማቸው 22 ወረዳዎችን በመለየት አማራጭ በፀሃይ ብርሃን የሚሰራ የሶላር ሲስተም በይፋ በዛሬው እለት አስመርቋል፡፡
በመርሀ-ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወንድሙ ሴታ (ኢ/ር) ኤጀንሲው ባለፉት አመታት የተለያዩ የሪፎርም አጀንዳዎችን ቀርጾ ሲሰራ መቆየቱን በማንሳት በከተማችን የምንሰጠው አገልግሎቶች አስተማማኝ እንዲሆን ለማድረግ የአገልግሎት መቆራረጥ እንዳይኖር ከማድረግ አንጻር የተጀመረውን ሪፎርም የምናዘልቅበትና ቀድሞ የነበረውን ሲስተም በአዲስ በመተካት የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት ማዕከልን ጨምሮ በ119 ወረዳዎች ላይ በተሟላ መልኩ አገልግሎት የምንሰጥበትን ሁኔታ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡
በተያያዘም አስተማማኝ የሀይል አቅርቦት ለሁሉም ወረዳዎች በማቅረብ በዘላቂነት ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በመርሀ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ኤጀንሲዉ ለአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆ ሊሆኑ የሚችሉ የግብዓት ችግሮችን በመቅረፍ አገልግሎትን ሊያቀላጥፉ የሚችሉ አሰራሮችን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ አክለዉም በ22ቱም ወረዳዎች የተጀመረዉ በቀጣይ ሌሎች የሃይል መቆራረጥ ሊያጋጥማቸው የሚችሉ ወረዳዎችን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር እሸቱ ለማ መንግስት በርካታ የልማት ስራዎች እየሰራ መሆኑን በመግለጽ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመሰረታዊነት በመፍታት አገልግሎትን በሚያሳልጥ መልኩ ቀልጣፋ፣ተደራሽ፣በጥራትና በብቃት በአጭር ጊዜ ውስጥ አገልግሎትን ለህብረተሰባችን ከመስጠት አኳያ ኤጀንሲው ራሱን ሪፎርም እያደረገና ተቋምን እየገነባ የመጣበት ለሌሎች ተቋማት ምሳሌ እና ሞዴል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ዛሬ ጠዋት ጂቡቲ ስደርስ ክቡር ፕሬዝደንት ኢስማኤል ኦማር ጉሌህ አቀባበል አድርገውልኛል። ውይይታችን በጆኦፖለቲካል ጉዳዮች፣ በቀጠናዊ ሰላም እና ፀጥታ ብሎም የሁለትዮሽ ትብብራችንን በተለይም በንግድ፣ ሎጂስቲክስ እና የልማት ሥራዎች በምናጠናክርበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነበር። ይኽም ለሰላም እና መረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ትስስር እና የጋራ ብልጽግና ያለንን የወል ጽኑ አቋም የሚያመለክት ነው።
Har'a ganama wayitan Jibuutii gahu Kabajamoo Pirezdaanti Ismaa'el Omaar Guuleh simannaa naaf taasisaniiru. Mariin keenyas dhimmoota siyaasaa lafa naannawaa kennyaa, nageenyafi tasgabbii naannichaa akkasumas walta'insa keenya garlamee, keessaayyuu daldala, loojestiksiifi hojiilee misoomaa cimsuu irratti kan xiyyeeffate ture. Dabalataanis hejjennoo waloo cimaa tasgabbii, hidhata dinagdeefi badhaadhina irratti qabnus kan agarsiisedha.
This morning, I arrived in Djibouti and was warmly received by President Ismaïl Omar Guelleh. Our discussions focused on geopolitical dynamics, regional peace and security, and strengthening bilateral cooperation, particularly in trade, logistics, and development, reaffirming our shared commitment to stability, economic integration, and mutual prosperity.
የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለምአቀፍ ትስስር ዘላቂ ለማድረግ ወደ 25 ሚሊዮን የሚጠጉ መንገደኞችን በአመት የማስተናገድ አቅሙ ላይ ከደረሰው ከአዲስ አበባ ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋ ጣቢያ እየለማ ይገኛል። ይኽ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግምባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ አላማን ያነገበ ነው።
የቢሾፍቱ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ይሆናል። ይኽም ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ የኢንደስትሪ ማስፋፊያ አጀንዳ እና የረጅም ዘመን የአቪየሽን ስትራቴጂ ጋር የተናበበ ነው። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያጠናክራል። በAfCFTA ማህቀፍ የአፍሪካን የማገናኘት አቅም ይጨምራል። የንግድ እና ቱሪዝም ኮሪደሮችን ያሰፋል። ኢትዮጵያንም ቀዳሚ የበይነአኅጉር ማዕከል ያደርጋታል።
ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ 40 ኪሎሜትር አካባቢ የምትገኘውና 1910 ሜትር ከፍታ ያላት ቢሾፍቱ ለአውሮፕላኖች ሥራ የተመቸ ከባቢ ያላት ሲሆን መዳረሻቸውን ኢትዮጵያ ላደረጉም ሆነ ለትራንዚት መንገደኞች ብቁ ሁኔታ ያላት ናት። ለመዲናችን ያላት ቅርበት ከነባሩ የአየር ትራንስፖርት ምኅዳር ጋር በቀላሉ የተዋሃደ አሠራር እንዲኖር ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። የመጀመሪያው ምዕራፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ሥራ በአመት 60 ሚሊዮን ተጓዦችን የሚያስተናግድ ሲሆን ሲጠናቀቅም አፍሪካን ከአለም ቀዳሚ የአየር ትራንስፖርት መነኻሪያዎች አንዷ የሚያደርጋትን በአመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ላይ ይደርሳል።
Guddina saffisaa geejjiba qilleensaa Itoophiyaa fi hidhata idil-addunyaa Daandii Qilleensaa Itoophiyaa bal’achaa dhufe waaraa taasisuuf, Buufata Xiyyaaraa Finfinnee, Boolee humnasaa waggaatti imaltoota miiliyoona 25 keessummeessuurra gahetti dabalataan buufanni guddichi haaraan misoomaa jira. Tarsiimoon buufataalee xiyyaaraa adda addaa ijaaruu kun, fuulduratti Itoophiyaa balbala geejjiba qilleensaa Afriikaa adda duree taasisuudhaaf kan kaayyeffatedha.
Buufanni Xiyyaaraa Idil-addunyaa Bishooftuu seenaa Afriikaa keessatti piroojeektii bu’uura misoomaa geejjiba qilleensaa isa guddichadha. Kunis rifoormii diinagdee biyyaalessaa Itoophiyaa, ajandaa babal’ina Indastirii fi tarsiimoo aviyeeshinii yeroo dheeraa waliin kan walsimedha. Piroojeektichi dorgomtummaa idil-addunyaa Daandii Qilleensaa Itoophiyaa kan cimsudha. Waliigaltee Gabaa Bilisaa Ardii Afriikaa (AfCFTA) keessatti Afriikaa daran kan wal quunnamsiisudha. Kooriidariiwwan daldalaafi Tuurizimii ni babal’isa. Itoophiyaas wiirtuu walgeettii Ardii Afriikaa ishee taasisa.
Finfinneerraa gara kiibba bahatti naannoo KM 40 irratti kan argamtuufi ol-ka’insa meetira 1910 kan qabdu Bishooftuun hojii xiyyaarotaatiif kan mijatte yoo taatu, imaltoota Itoophiyaa dhufaniifi kanneen karaa Itoophiyaa darbanii imalan keessummeessuuf haala gahaa ta’e qabdi. Dhiyeenyi magaalaa guddoo keenyaaf qabduus geejjiba qilleensaa duraan ture waliin hojmaanni salphaatti walsimu akka jiraatu haala kan mijeessudha. Hojiin boqonnaa jalqabaa buufata xiyaarichaa waggaatti imaltoota miiliyoona 60 kan keessummeessuu yoo ta’u, yeroo guutummaan xumuramutti waggaatti gahumsa imaltoota miiliyoona 110 keessummeessuu horachuun, Itoophiyaan aduunyaarratti geejjiba qilleensaatii warra adda duree keessaa tokko akka taatu kan taasisudha.
To sustain Ethiopia’s rapid aviation growth and Ethiopian Airlines’ expanding global network, a new mega hub is being developed alongside Addis Ababa Bole International Airport, which is nearing its expanded capacity of 25 million passengers annually. This multi-airport strategy aims to future-proof Ethiopia’s role as Africa’s leading air transport gateway.
Bishoftu International Airport (BIA) will be the largest aviation infrastructure project in Africa’s history. It aligns with Ethiopia’s national economic reforms, industrialization agenda, and long-term aviation strategy. The project will strengthen Ethiopian Airlines’ global competitiveness, enhance Africa’s connectivity under the AfCFTA framework, expand trade and tourism corridors, and position Ethiopia as a premier intercontinental hub.
Located about 40 km southeast of Addis Ababa at an altitude of 1,910 meters, Bishoftu offers optimal conditions for aircraft performance and efficient handling of both origin-destination and transit passengers. Proximity to the capital ensures seamless integration with the existing aviation ecosystem. The first phase of the airport will handle 60 million passengers per year, with an ultimate master plan capacity of 110 million passengers annually, placing Ethiopia among the world’s top aviation hubs.
ዛሬ ማለዳ በከተማችን እየተገነቡ ከሚገኙ ስምንት የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል የቀበና እና የጊንፍሌ ወንዞችን የሥራ ሂደት ገምግመናል።
በእርግጥ የወንዝ ዳርቻ ልማት ለአገራችን አዲስ ተሞክሮ ቢሆንም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ አስደናቂና ለውጥ አምጭ ሥራዎች ተከናውነዋል። በተለይም 19 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውና ከእንጦጦ እስከ ካራማራ ድልድይ ድረስ የሚዘልቀው የቀበና ፕሮጀክት፣ ልክ እንደ እንጦጦና ፒኮክ ፓርኮች ሁሉ በአሁኑ ወቅት ግንባታው ወደ መጠናቀቂያው ተቃርቧል።
ብክለት ተወግዶ፣ የአፈርና የሥነ-ምህዳር ጥበቃ ተደርጎላቸው፣ ተፈጥሯዊ ይዘታቸውን አጥተው የነበሩ ወንዞቻችን ታክመው ሲያንሰራሩ ማየት ትልቅ ስኬት ነው። የደረቁ የውሃ ምንጮች እንደገና ሲፈልቁ፣ መጥፎ ሽታ ተወግዶ አካባቢው በአገር በቀል ዛፎች ተከቦ ለነዋሪዎች ምቹ፣ ጤናማና ንጹሕ አየር የሚተነፈስበት ማራኪ ገጽታ ሲላበስ ማየት የልፋታችን ትልቁ ውጤት ነው።
በዚህም የከተማችንን ዘላቂ ልማት የሚያረጋግጡ የውሃ ግድቦች፣ በርካታ ድልድዮች፣ ቼክ ዳሞች፣ ዘመናዊ የእግረኛና የሳይክል መንገዶች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ የልጆች መጫወቻዎች፣ ካፌና ሬስቶራንቶች እንዲሁም ሰፋፊ የመኪና ማቆሚያዎች ተገንብተዋል። የከተማችንን ገጽታ የሚቀይሩ የአረንጓዴና የውበት ሥራዎችም በመጠናቀቅ ላይ ይገኛሉ።
ይህ ልማት በአሁኑ ወቅት ለሪል እስቴትና ለሆቴል አልሚዎች እጅግ አዋጭ የኢንቨስትመንት አካባቢ ፈጥሯል። በመሆኑም፣ ዕውቀትና ገንዘብ ያላችሁ ባለሀብቶች በዚህ ልዩ የልማት ዕድል ላይ እንደወትሮው በንቃት እንድትሳተፉ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
በመጨረሻም፤ ይህንን የትውልድ ኩራት የሆነ ፕሮጀክት ከውጥን እስከ ፍጻሜው እውን ለማድረግ ሌት ተቀን አብራችሁን የደከማችሁ አመራሮችን፣ ኮንትራክተሮችን፣ ባለሞያዎችን፣ ኢንተርፕራይዞችንና የልማቱ ባለቤት የሆናችሁ የአካባቢውን ነዋሪዎች ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
Har'a ganama magaalaa keenyatti ijaaramaa kan jiran piroojektoota misooma qarqara lagaa saddeet keessaa adeemsa hojii laggeen Qabbannaa fi Ginfillee gamaaggamnee jirra.
Dhugumatti, misoomni qarqara lagaa biyya keenyaaf muuxannoo haaraa ta'ullee, yeroo gabaabaa keessatti hojiiwwan baay'ee dinqisiisoo fi jijjiirama fidan hojjetamaniiru.
Keessattuu, kiloomeetira 19 kan uwwisuu piroojektiin qabbannaa, Inxooxxoo irraa hanga riqicha Kaarramarraa kan ittifufu, akkuma paarkii Inxooxxoo fi Piikook yeroo ammaa kana ijaarsi isaa gara xumuramuutti dhihaateera.
Balfi dhabamsiifamee, eegumsi biyyee fi naannoo taasifameefii, laggeen qabiyyeesaanii uumamaa dhabanii turan yaalamanii yeroo bayyanatan arguun milkaa'ina guddaa dha. Maddoonni bishaanii gogan irra deebiin yeroo maddan, hafuurri badaan dhabamsiifamee nannichi mukkeen biyya keessaatiin naanneffamee jiraattotaaf mijataa, fayya-qabeessa fi qilleensa qululluun kan itti harganamu fuula dinqisiisaa yeroo uffatu arguun bu'aa dadhabinaa keenyaa isa guddaadha.
Kanaanis misooma ittifufaa magaalaa keenyaa kan mirkaneessan hidhoota bishaanii, riqichaalee hedduu, cheek daamiilee, daandiilee lafoo fi biskileetii ammayyaa, dirreelee ispoortiin itti hojjetamu, bakkeewwan daa'imman itti taphatan, kaaffee fi reestooraantiilee akkasumas bakkeewwan dhaabbii konkolaataa babal'aan ijaarameera. Fuula magaalaa keenyaa kan jijjiiran bakkeewwan magariisaa fi miidhaginaa illee xumuramuu irratti argamu.
Misoomnin kuni yeroo ammaa kana misoomsitoota riilisteetii fi hoteelaaf naannoo invastimantiif baay'ee bu'a qabeessa ta'e uumeera. Kana waan ta'eef abbootiin qabeenyaa beekumsaa fi maallaqaa qabdan carraa misoomaa adda ta'e kana irratti akkuma kana duraa si'aa'inaan akka hirmaattan yaamicha koon dhiheessa.
Xumurarrattis; piroojektii boonicha dhalootaa ta'e kana jalqabaa hanga xumuraa dhugoomsuuf halkanii fi guyyaa kannneen dadhabdan hooggantoota, kontiraaktaroota, ogeessota, Intarpiraayizootaa fi abbaa misoomichaa kan taatan jiraattota naannichaa onnerraa galateeffadha.
Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!
ኢትዮጵያ እና ቻይና ለአስርት አመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት አላቸው። ይኽ ግንኙነት በቅርቡ ወደ በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የስትራቴጂክ ትብብር አድጓል። ዛሬ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ተቀብዬ በጽናት በሚጓዘው የኢትዮጵያ እና ቻይና የመንግሥት እና ሕዝብ ግንኙነት ላይ ተነጋግረናል። በተለያዩ የልማት ትብብር ርዕሰ ጉዳዮችን ለማከናወን ያለንን ጽኑ አቋም በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገናል። በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተናል።
Itoophiyaafi Chaayinaan hariiroo cimaa waggoota kurnan lakkoofsise qabu. Hariiroon kun dhiheenya gara tumsa tarsiimawaa haalotaan hin jijjiramnetti guddateera. Har’a Ministira Dhimma Alaa Chaayinaa Waang Yii simachuun hariiroo sirnaawaa mootummaa fi uummataa, Itiyoophiyaafi Chaayinaa irratti mari’anneerra. Keessattuu dhimmoota walta'insa misoomaa irratti kutannoo cimaa qabnu itti fufsiisuu irratti marii taasifneerra. Diinagdee, daldala, bu’uuraalee misoomaa, dhiyeessii anniisaafi geejjibaa, akkasumas dameewwan haaraa uumamaa jiran kanneen akka daldala elektirooniksii, diinagdee dijiitaalaa, Artifishiyaal Intelijensiifi misooma anniisaa magariisaa irratti tumsa keenya cimsuuf marii'anneerra.
Ethiopia and China have enjoyed a strong relationship for decades, further strengthened recently by its elevation to an all-weather strategic cooperation partnership. I welcomed the Minister of Foreign Affairs of China, Mr. Wang Yi, and reflected on the enduring partnership between the peoples and governments of Ethiopia and China. We discussed a range of development cooperation issues and reiterated our shared commitment to advancing development. We also discussed deepening cooperation in the economy, trade, infrastructure, energy, and transportation, as well as tapping the potential for collaboration in emerging areas such as e-commerce, the digital economy, artificial intelligence, and green energy.
አቅም የሌላቸው ወገኖች፤ በዓሉን በር ዘግተው ቤታቸው መዋል የለባቸውም በሚል በጋራ ለማሳለፍ ያካሄደው የማዕድ ማጋራት ከወገኖች ጋር ደስ ብሎን በዓሉን እንድናሳልፍ አድርጓል' -ክቡር ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ
በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኘዉ የተስፋ ብርሃን ምገባ ማዕከል በተካሄደው የማዕድ ማጋራት ላይ የተገኙት የተከበሩ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ፤ ባለስልጣኑ አቅም የሌላቸው ወገኖቹ በዓሉን በር ዘግተው ቤታቸው መዋል የለባቸውም በሚል በጋራ ለማሳለፍ ያካሄደው የማዕድ ማጋራት ከወገኖች ጋር ደስ ብሎን በዓሉን እንድናሳልፍ ማድረጉንና ይህ አርዓያነት ያለው በጎ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
በተጨማሪም የከተማ አስተዳደራችን በተለያዩ ጊዜያት የሚያከናውናቸው ሰው ተኮር የልማት ስራዎች የጎደለበትን፣ ያልሞላለትንና አቅም ያጣውን ወገናችንን በር የሚያንኳኳና ህይወት የሚቀይር ነው ያሉ ሲሆን የከተማ አስተዳደራችን ስኬቱን የሚለካው በገነባነው መሠረተ ልማት፤ በሰጠነው አገልግሎት ሳይሆን በለወጥነው የህዝባችን ህይወት ነው ብለዋል። በተለይም የጎደለባቸውን፤ የተራቡትንና የተገፉትን ህይወት መቀየር መሆኑን ተናግረው፤ ይህ እንዲሳካ በከተማ አስተዳደሩ ብቻ የሚሰራ ሳይሆን በሁሉም አስተዋጽኦ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ባለስልጣኑ ከአጋር ጋር የካሄደው የማዕድ ማጋራት፤ የዚህ አስተዋጽኦ አንዱ ማሳያ መሆኑና በበዓላት ወቅት መረዳዳትና አብሮነትን የሚያጠናክር መልካም ተግባር እንደሆነ ገልፀዋል።
ክቡር ኢንጂነር ወንድሙ አያይዘው የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ብዙ ነገር ያስተምረናል ያሉ ሲሆን ይህም የተራቡትን የማብላት፤ ከተገፉት ጎን የመቆምና የተከፉትን ማጽናናት መሆኑን ገልጸው ይህን ማድረግ የክርስቶስን ፈለግ መከተል ነው ብለዋል።
በዓሉን በምገባ ማዕከሉ እንዲካሄድ ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰብስብ ሁሴን፤ በምገባ ማዕከሉ በዓሉን ከአቅመ ደካሞችና አረጋውያን ጋር ማሳለፍ መቻሉ ክብርና ታላቅ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ የከተማ አስተዳደሩ ወገኖችን ተስፋ የሰጠ የምገባ ማዕከል በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች አቋቁሞ በቋሚነት መመገብ የሚያስችል በጎ ስራ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸው፤ የከተማ አስተዳደሩ ከሚያደርገው ጥረት ጎን ለጎን ባለስልጣኑ አቅም ከሌላቸው እና ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ወገኖች ጋር በዓሉን ሳይጨነቁ አብሮ በማሳለፉና አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሰው ተኮር ተግባር ማከናወናቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል።
የቦሌ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር እሸቱ ለማ የማዕድ ማጋራትና የሰው ተኮር ተግባራት ከተጀመረ ጀምሮ በዝቅተኛ ኑሮ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ህይወት የቀየረ በርካታ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የሰው ተኮር ተግባራት ኢትዮጵያዊ አብሮነትን፤ መደጋገፍን የጎለበተበት እንደሆነ ገልጸዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
