Grace Gospel
ትውልድ የእግዚአብሔርን ፍቅር በመማር በእግዚአብሔር ፍቅር ህይወቱ እንዲቀየር ለማድረግ የጸጋውን ወንጌል እናስተምራለን። Comment @EsseyShalom @Metu_boy
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
ትውልድ የእግዚአብሔርን ፍቅር በመማር በእግዚአብሔር ፍቅር ህይወቱ እንዲቀየር ለማድረግ የጸጋውን ወንጌል እናስተምራለን። Comment @EsseyShalom @Metu_boy
#የእግዚአብሄር_ቃል ! #ክፍል_አንድ #ለምን_ስለ_እግዚአብሄር_ቃል_መማር_አስፈለገ ? 📌ለእግዚአብሄር ቃል ያለን እይታ ፣ስለ እግዚአብሄር ቃል ያለን ግንዛቤ እንዲሁም ለእግዚአብሄር ቃል የሰጠነው ዋጋ የእግዚአብሄር ቃል በህይወታችን ላይ ያለውን ተፅዕኖ ይወስናል ። የእግዚአብሄር ቃል በአማኝ ህይወት ውስጥ የሚሰራው አማኙ ስለ እግዚአብሄር ቃል መረዳት ልክ እንጂ ቃሉ ባለው ስልጣንና አቅም ልክ ወይም እግዚአብሄር እንዲሰራ በወደድነው ልክ አይደለም ፤ ይልቁንም ቃሉ የሚሰራው ስለቃሉ ባለን የተስተካከለ እውቀትና መረዳት ልክ ስለሆነ ስለ እግዚአብሄር ቃል መማር አስፈላጊ ነው። 📌ለእግዚአብሄር ቃል የምንሰጠው ትኩረት ለቃሉ ያለን አቀባበል እንዲቀየር ስለእግዚአብሄር ቃል እንማራለን፤ ምክንያቱም ቃሉ የእግዚአብሄርን ያክል ስልጣን ያለው መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ለምሳሌ የቀበሌ አስተዳደር ቃል Operational የሆነበት ክልል የሚያስተዳድርበት ቀበሌ ላይ ብቻ ነው። በአንጻሩ የሃገሪቱ መሪ በሀገሪቱ ላይ የሚናገረው ሁሉ ተግባራዊ ይሆናል፣ ይገዛል የእርሱ ቃል የእርሱን ስልጣን ያህል ያዝዛል። ስለዚህ የእግዚአብሄር ቃል የስልጣኑ ልክ የእግዚአብሄርን ስልጣን ያህል ያክላል ።እግዚአብሄር ማዘዝ የሚችለውን መስራት የሚችለውን ያክል ማድረግ ይችላል። ቃል የሚሻረው በቃል ነው!! በቅድሙ ምሳሌ መሰረት የአንድ ቦታ አስተዳዳሪ ከእርሱ በተሻለ ስልጣን ባለው ሰው ቃሉ ወይንም ውሳኔው ሊሻር ይችላል። በህይወታችን ላይ ሰይጣን፣ ሰዎች ሁኔታወች ወዘተ ...የሚናገሩብንን ክፉ ቃላት ለመሻር የሚያስችለንና የሚያስፈልገን ከሁሉ ቃላት በላይ ከፍ ያለ ስልጣን ያለውን የእግዚአብሄርን ቃል በተነገረብን ላይ ከፍ በማድረግ ቃልን በቃል መሻር ነው። ብዙ ሰዎች ሟርትን በተለይም የአማኝን ሟርት ይፈራሉ ማለት አንዳች…
ትውልድ የእግዚአብሔርን ፍቅር በመማር በእግዚአብሔር ፍቅር ህይወቱ እንዲቀየር ለማድረግ የጸጋውን ወንጌል እናስተምራለን። Comment @EsseyShalom @Metu_boy
ትውልድ የእግዚአብሔርን ፍቅር በመማር በእግዚአብሔር ፍቅር ህይወቱ እንዲቀየር ለማድረግ የጸጋውን ወንጌል እናስተምራለን። Comment @EsseyShalom @Metu_boy
የእግዚአብሄር ቃል ክፍል አስር ዛሬም ሁኔታ፣ሰዎች፣ሰይጣው፣አለም የራሳችን ህሊና ስለ እኛ ብዙ እውቀት(መረጃ) ሊሰጡን ይችላሉ። እነዚህ ሁሉ ግን ከእግዚአብሄር ቃል ውጪ ከሆኑ ልንቀበላቸው አይገባም። ስለእኛ የእውቀት ምንጭ ልናደርጋቸው ፈጽሞ አይገባም። ስለዚህ የእግዚአብሄር ቃል ስለእኛ የሚናገረውን ልንሰማ ልንቀበል ልናምንና በድፍረት ልንናገር ያስፈልጋል። ዮሐንስ 1 19፤ አይሁድም፡— አንተ ማን ነህ? ብለው ይጠይቁት ዘንድ ከኢየሩሳሌም ካህናትንና ሌዋውያንን በላኩበት ጊዜ፥ የዮሐንስ ምስክርነት ይህ ነው። 23፤ እርሱም፡— #ነቢዩ_ኢሳይያስ_እንዳለ፡— የጌታን መንገድ አቅኑ ብሎ #በምድረ_በዳ_የሚጮኽ_ሰው_ድምፅ_እኔ_ነኝ፡ አለ። ተጨማሪ ጥቅሶች:- ኢሳ 40:3-5 ማር 1:2-3 ሉቃ3:3-6 ማቴ3:3 መጽሃፍ ቅዱስ ስለእኛ የሚናገረው በእርግጥ ለአእምሮ አይመችም ፤ እስቲ ለመጥምቁ ዮሐንስ የተባለውን አስብ:- ድምፅ ነህ ማለት አሁን እንዴት ይሆናል?? ለአእምሮ ምን ትርጉም ይሰጣል?? እኛም ራሳችንን ስናውቅ መጽሃፍት ሁሉ በሚያወሩለት በክርስቶስ በኩል ፤የመጽሃፍ ትምህርት በሆነው የመዳን እውቀት በሆነው የፅድቅ መረዳት ሊሆን ያስፈልጋል። 2 ቆሮንቶስ 5 16፤ #ስለዚህ_እኛ_ከአሁን_ጀምሮ_ማንንም_በሥጋ_እንደሚሆን_አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም። ኦ ስለዚህ እንዴት እንወቅ? 1ኛ ቆሮንቶስ 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁰ #በክርስቶስ_ኢየሱስ ለመሆን የበቃችሁት ከእርሱ የተነሣ ነው፤ #እርሱ #ከእግዚአብሔር_ዘንድ_ጥበባችን፣ #ጽድቃችንና_ቅድስናችን፣ #ቤዛችንም_ሆኖአል። ተጨማሪ ጥቅሶች ሮሜ 6:11 2ቆሮ 5:17 1ቆሮ1:2 2ቆሮ 2:14 ሮሜ6:23,8:1 ማቴ 5:13-14 ሮሜ 8 16፤ #የእግዚአብሔ…
የእግዚአብሄር ቃል ክፍል ዘጠኝ ስለዚህ እለት እለት ወደ ቃሉ ስንቀብ ከቃሉ ለመማር፣ለመታረም፣ለመመከር ለመገሰፅ የለመድነው የኖርንበትም እንኳን ቢሆን ለመጣል ተዘጋጅተን ፈጽሞ በተከፈተ ልብ ሊሆን ይገባል። 3. ስለእኛ በትክክል ይናገራል መጽሃፍ ቅዱስ ትክክለኛ የእግዚአብሄር ሃሳብ በመሆኑ የእውቀታችንን ምንጭ ሊሆን የሚገባው እርሱ ብቻ ነው። እናም ስለእኛ ከራሳችን በላይ በትክክል የሚያውቀውና የሚናገረው እርሱ በመሆኑ ቃሉን ስናጠና ራሳችንን በትክክል በቃሉ መስተዋት ከቃሉ ላይ ማየት አለብን። ያዕ 1:23 ልክ መስተዋት የእኛን ትክክለኛ መልክ እንደሚያሳየው ሁሉ ቃሉ የመንፈሳዊ ማንነታችን ፣አቋማችን እንዲሁም መልካችን ትክክለኛ ማሳያ ነው ። ሰው የእግዚአብሄር አምሳል በመሆኑ የሳይንስ ግኝት ሳይሆን የእግዚአብሄር ቃል ነው ስለማንነቱ ትክክለኛው ትምህት፤ልክ እንደዚሁ በክርስቶስ አምነን ስለዳንን ሰዎች ደግሞ በይበልጥ ይናገራል። መጥምቁ ዮሐንስ ስለራሱ አይሁድ በጠየቁት ጊዜ ብዙ መናገር ይችል ነበር፦ የካህናት ዘር ፣ የካህኑ ዘካርያስ ልጅ ፣ የአገልግሎቱን አይነትና ቆይታ ወዘተ ... ነገር ግን እግዚአብሄር እርሱን በሚያይበት ቃሉ ስለእርሱ በተናገረው በዚያ እውቀት ራሱን አወቀ። ይቀጥላል ክፍል ስንምትን ለማግኘት ይህን ይጫኑ
https://t.me/shalomgracegospelYour current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.