en
Feedback
Ethiopia Studio 🇪🇹

Ethiopia Studio 🇪🇹

Open in Telegram

አስመሳይ ሆኖ ስኬታማ ከመሆን ራሱን ሆኑ መወደቅ መልካም ነው ⁉️

Show more
902
Subscribers
-124 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
የአማራ ክልላዊ መንግስት 2 የፀጥታ ሀላፊዎችን አሰናበተ። ____ የአማራ ክልል መንግስት የክልሉን የፀጥታ ሁኔታ ከገመገመ በኋለ ሀላፊነታቸውን በአግባቡ አልተወጡም በማለት ሁለቱን ሀላፊወች አግዷል።
+2
የአማራ ክልላዊ መንግስት 2 የፀጥታ ሀላፊዎችን አሰናበተ። ____ የአማራ ክልል መንግስት የክልሉን የፀጥታ ሁኔታ ከገመገመ በኋለ ሀላፊነታቸውን በአግባቡ አልተወጡም በማለት ሁለቱን ሀላፊወች አግዷል። 1. የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ኮማንደር መንገሻ አውራሪስና 2. የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የፀጥታ አማካሪ ከፋለ እሱባለው ከሃላፊነት ማንሳቱን የተገኘው መረጃ ያሳያል። ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork

የአማራ ክልላዊ መንግስት 2 የፀጥታ ሀላፊዎችን አሰናበተ። ____________________ የአማራ ክልል መንግስት የክልሉን የፀጥታ ሁኔታ ከገመገመ በኋላ ሀላፊነታቸውን ትተው ከፅንፈኞች ጋር በመሆን
+2
የአማራ ክልላዊ መንግስት 2 የፀጥታ ሀላፊዎችን አሰናበተ። ____________________ የአማራ ክልል መንግስት የክልሉን የፀጥታ ሁኔታ ከገመገመ በኋላ ሀላፊነታቸውን ትተው ከፅንፈኞች ጋር በመሆን ቃለ ማሃላቸውን ክደው ሀገር ሲያፈርሱ ህዝብን ከህዝብ ሲያተራምሱ በመገኘታቸው ሁለቱን ሀላፊወች አግዷል። 1. የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ኮማንደር መንገሻ አውራሪስና 2. የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የፀጥታ አማካሪ ከፋለ እሱባለው ከሃላፊነት ማንሳቱን የተገኘው መረጃ ያሳያል። ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork

በያገሩ ለምንከናበው ውድርደትና ስቃይ አንዱ የዲፕሎማሲ መላሽቅ ነው። ያንን ዘመን ወደኋላ ሄደን እንደገና ብናየው እውነትም አምርረን የታገልነው ኢህአዴግ ጭቆናውና ብዝበዛው የገነነ ይሁን እንጅ ዜጋ ግን እንዲህ ተከምሮ ሳይሞት የቀብርን ሂዎት አይኖርም ነበር። ስደት የኛ ማንነት እስኪመስል ድንበራችንን ዘለው ሁለት መንግስትን አቋርጠው ሲወጡ አንድም የተቀየረ አሰራር አልተዘረጋም። በየ ስድት ወሩ ከዕስር አውጡን የሚል ዘመቻን እንደ አጀንዳ የተቀበልነው በራሳችን ድክመት ነው። በሰው ልጅ ሂዎት የሚሸቅጠው የአገሬው ደላላ ሰውን የመሰለ ፍጡር መልምሎ ሲያስኮበለል መቀጣጫ የሚሆን ህግ አልተወጣለትም። በየከተማው በሰው ልጅ ሂዎት ነግዶ የሚገነባው ህንፃ አልተወረሰበትም። ጥሩ ጀብድ እንደሰራ አድርጎ ቀብረር ብሎ እየደለለ ሲኖር ጠያቂ የለውም። ወዲህ ዲፕሎማሲያችን እጅግ የላሸቀ ነው። ያው እንዲህ ያለ እንደሎሚ የሚሆመጥጥ ሀቅ ስንናገር የተለመደውን ማስፈራሪያና አይን ያወጣ ብሄር ቆጥረው ስድብንና ዛቻቸውን እንደሚደፉብን የታወቀ ነው። አገሪቱ በስደተኞች ከምዕራቡ አለም ስዳኞተች ይልቅ ከሳኡዲና አረብ ኤምሬትስ ( አጠቃላይ ከገልፉ አገሮች የምታስገባው ገንዘብ ከፍተኛውን ደረጃ የያዘ ነው። ታዲያ በዚህ ቀጠና የሚኖረን የተቋም አደረጃጀት ምን መምሰል እንዳለበት ግልፅ ነው። ነገሩ ግን የተለያየ ሆኖ አንድም የተሻለ ማወቅር በለለበት ሰዎችን በማመላስ የተጠመደ ዲፕሎማሲ ብቻን እየተከተልን ነው። ለጉዳዮ ስር ነቀል መፍትሄን ከመፈለግ ይልቅ በሩቅ እያዮ ዝምታን መምረጥ ሆኗል። በህጋዊ መንገድ ወደ አረብ አገር ሰዎችን እንልካለን አሉ እንጅ አንድ ፓስፖርት ለመስጠት አንድ አመትን ጠብቁ እየተባሉ ነው። እንኳን 500ሺ ሰው 5ሺም ሰው በህጋዊ መንገድ እንደማይሄድ ግልፅ ነው። አሰራሩ እጅግ ተቃራኒ ነው። መላ ቅጡ ጥፍት ያለበት ከማወቅራዊ አሰራር ይልቅ መላምትን የለመደው የሀገሪቱ የውጭ ፖሊሲ እየደጋገመ ዜጋንም አገርንም እያዋረደ። ስንናገራቸው ከሪያድ እስከ አዲስ አበባ መልክት ይላላካሉ። አቅጣጫን ስንጠቁማቸው ከኛ በላይ ሊቅ የለም ይላሉ። በብሄር ተባድነው የሚላኩ ዲፕሎማቶች በአይን ግልምጫጨቸው ሊበሉን ይደርሳሉ። እንደ አገር ስናስብ ደስ አይላቸውም ምክኒያቱም መጀመሪያም የብሄር ኩታን መሰረት ያደረገ እንጅ በጥሩ አመራርነ ሰጭነት የተመለመለ ማዋቅር አለመዱም። በባዶ የሚሰጡት ጩጨ ተስፋ ህዝብን ከማታለል ውጭ ምንም ቁም ነገር የለውም። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ወደውጭ የሚልካቸውን ሰዎች ከብሄር ኩታ ውጭ ካላዋቀራቸው ስራ አይሰሩም ስንል ለአዲስ አገዛዝ ጥላቻ ይዘን የቆምን ይመስላቸዋል። ዳሩ ግን እንኳን ብዙ ችግር ካለው የገልፉ የዲፕሎማሲ ውጤት የተቋሞችን አሰራር ከተመላሹ ዜጋ ቢጠየቅ ብዙ ነውር አለው። እነሱ እንደ ብሄር ቢሰለፉም መከራው ግን እንደ አገር ነው እየለበለበን ያለው። በጣም ትልቁ ችግር ግን አሁንም መንግስት የማይከታተለው የዲፕሎማሲ ኪሳራ የፈጠረው ብልሹ አደረጃጀታችን ነው። ሱሌማን አብደላ ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork

photo content
+1

የትህነግና የፌደራል መንግስት የድብቅ ውል በጌታቸው ረዳ በኩል ተዘርግፏል። መከላከያ ሰራዊት በፋኖ ላይ የሚዘምተው ይህን ውል ለማስፈፀም ነው። ጌታቸው ለትግራይ ዳያስፖራ ከፌደራል መንግስት ጋር በአማራ ላይ በድብቅ የተዋዋሉትን ተናግሯል። ☝ ከደቂቃዎች በኋላ የሚለቀቀውን መረጃ ለማገኘት ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⬇⬇ https://youtube.com/@AhaduMedia2023

የት*ግ*ሬ ልሂቅ ልኩ ይሄ ነው። የበታችን ስሜት ናላውን አዙሮታል። የፈለገበት ድረስ ሲወርድ ማየት ነው። ትናንት በአሜሪካ ጌታቸው ረዳን ተቀብለዋል። ጌታቸው ለማስመሰል የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ እን
+1
የት*ግ*ሬ ልሂቅ ልኩ ይሄ ነው። የበታችን ስሜት ናላውን አዙሮታል። የፈለገበት ድረስ ሲወርድ ማየት ነው። ትናንት በአሜሪካ ጌታቸው ረዳን ተቀብለዋል። ጌታቸው ለማስመሰል የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ እንዲኖር ፈልጓል።  "እየመረረንም ቢሆን ራሳችን እስክንችል" ወዘተ ብሏቸው ነው። የትግራይ ባንዲራ በትልቁ ተሰቅሏል። የኢትዮጵያ አልነበረም። ጌታቸው ሲደርስ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ስክሪን ላይ ቡግ አድርገው አጠፉት። ስልጣን ላይ እያሉ ይዘውት ሲዞሩት የነበር ነው። አሁን ጠሉት። ኢትዮጵያ ለእነሱ "ባጣ ቆየኝ" ነች። ራሳቸው የእኛ ሲሉት የነበረውን ሁሉ ጠልተውታል። ትርክታቸው ተንዷል። ጭንብላቸው ተገልጧል። የት*ግ*ሬ ልሂቅ እውነተኛ ልኩ ይህ ነው። ስልጣን ይዞ እንኳን አገራዊ ስነልቦና ያልተላበሰ፣ አራት ኪሎ ገብቶ ጀኔሬተር ከመሃል አገር ሰርቆ ወደ ቀበሌው የሚወስድ ኃይል ነው። ይህ ኃይል ገና ወደታች ይወርዳል። ይምዘግዘግ! ከዚህ ኃይል ጋር መነጋገር የሚቻለው ቦታው ላይ ተደላድሎ ሲቀመጥ ነው። ጥጋቡ የሚተነፍስለት በቅዠት የሚመኘው ሁሉ ባዶ እንደሆነ ካየ ብቻ ነው። ይህ ኃይል እፈልገዋለሁ የሚለውን ጉም ዘግኖ አይቶት ካልሆነ በስተቀር ለድርድር አይመችም። የሚፈልገው ጉድጓድ ድረስ ይውረድ። የጥጋቡን ውጤት ግጦ ይመለስ። ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork

ቃል በቃል ባይሆንም ከስር ያለው ሀሳብ አንድ በወሎ አካባቢ የተሰማራ ኮረኔል በቅርቡ በተካሄደ አንድ የስብሰባ መድረክ ላይ ለአወያዮቹ የተያገረው ነው ፦👇 << ...ከላይ ያለው አመራር እንድንገጥመው የላከንን ሀይል አቅልሎ የመዘነበት ሚዛን ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈለን ነው። ፈፅሙ አታውቁትም። ጭራሽ ተራ ሽፍታና የመንደር ስብስብ አይነት አድርጋችሁ ስታቀርቡት የነበረበት ሁኔታ ያሳዝናል። እንደውም ካላችሁ ይህ ኃይል ኢትዮጵያ ውስጥ መሰልጠኑን ሁሉ እጠራጠራለሁ። ቁሞ የማይዋጋ ሚሊየን ሰራዊት ቢንጋጋ ትንሽ እንኳ ፈቅ የምናደርገው አይደለም። እኔ በግሌ ይህን ትኩረት የተነፈገው ከባድ ጦርነት ከምታውቁት ወቅታዊ የሰራዊቱ አቋም አንፃር አነፃፅረን ዳግም ብንፈትሸው ይሻላል እላለሁ! >> አይዞሽ ገለቴ!🏃‍♂😄 ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork

በአማራ ክልል ስር የሚገኘው አዲ አርቃይ ወረዳ መጠሪያውን ሊቀይር ነው በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ውስጥ የሚገኘው አዲ አርቃይ ወረዳ ስያሜውን ለመለወጥ ሁለት አማራጮችን ለህዝብ ውይይት አቀረበ
በአማራ ክልል ስር የሚገኘው አዲ አርቃይ ወረዳ መጠሪያውን ሊቀይር ነው በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ውስጥ የሚገኘው አዲ አርቃይ ወረዳ ስያሜውን ለመለወጥ ሁለት አማራጮችን ለህዝብ ውይይት አቀረበ። የወረዳው ምክር ቤት ስያሜውን “ሰገነት” አሊያም “ሰላም በር” ወደሚል መጠሪያ ለመቀየር የወሰነው፤ ነባሩ መጠሪያ “የክልሉንም ሆነ የወረዳውን ህዝብ የሚገልጽ ባለመሆኑ ነው” ብሏል። ከትግራይ ክልል ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አጎራባች የሆነው የአዲ አርቃይ ወረዳ ምክር ቤት የስያሜ መቀየር ውሳኔውን ያስተላለፈው፤ ከሁለት ሳምንት በፊት ሐምሌ 1፤ 2015 ባደረገው ስብሰባ እንደሆነ የምክር ቤቱ ምክትል አፈጉባኤ አቶ ደረጀ ጌትነት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የወረዳው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ይህን ጉዳይ በተመለከተ ጥናት የሚያደርግ ኮሚቴ ከስብሰባው አስቀድሞ አቋቁሞ እንደነበር አቶ ደረጀ ገልጸዋል። ጥናቱን ሲያከናውን የቆየው ኮሚቴ በሐምሌ ወር መጀመሪያ በተካሄደው የወረዳው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ፤ ሶስት የስያሜ አማራጮችን አቅርቦ እንደነበር ምክትል አፈ ጉባኤው አመልክተዋል። ከቀረቡት አማራጮች “ሀገረ ሰላም” የሚለው ውድቅ ሲደረግ “ሰገነት” እና “ሰላም በር” የሚሉት መጠሪያዎች ግን ለህዝብ ውይይት እንዲቀርቡ መወሰኑን አክለዋል። https://t.me/gimbmedianetwork

ስጋታችኝ ፋኖ ነው ፣ጌታቸዉ ረዳ፣ አሜሪካ ወደ አማራ ክልል፣ሌሎች ዜናዎችንም ከደቂቃዎች በኋላ ሰብስክራይብ በማድረግ ይጠብቁን⬇⬇ https://youtube.com/@AhaduMedia2023

#የኬጂ ተማሪዎች ሁሉ ሳይቀር ዛሬ ላይ"ወደፊት ምን መሆን ነው የምትፈልጉት?" ሲባሉ "ፋኖ" እያሉ ነው። ፋኖነት መንፈስ ሆኗል። ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ
+2
#የኬጂ ተማሪዎች ሁሉ ሳይቀር ዛሬ ላይ"ወደፊት ምን መሆን ነው የምትፈልጉት?" ሲባሉ "ፋኖ" እያሉ ነው። ፋኖነት መንፈስ ሆኗል። ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork

''ፋኖ ከበራፉ ድረስ በመጣ ውለታ-ቢስ ኃይል የሚደርስበትን ጥቃት ከመመከት ባሻገር ፣ በሀገረ መንግስቱ ውስጥ የአማራን ህዝብ ቁልፍ የማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች በመደራደር ማስከበር በሚችልበት ቅኝት መቃኘት አለበት!'' የሚለው የብዙዎች ሀሳብ ምንም የሚያወላዳ አይደለም! የአማራ ህዝባዊ ትግል የሚከተሉትን 6ት አበይት የትግል አላማዎች ያነገበ መሆን አለበት። ✅የአማራ ሕዝብ የኅልውና አደጋ የሆነውን ሕገ-መንግስትና ፌዴራላዊ አወቃቀር መከለስ ✅የአማራ ሕዝብ በአማራነቱ የሚደርስበትን የኅልውና አደጋ መቀልበስ ✅ የአማራ ሕዝብ ሥልታዊ ፖለቲካዊና ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ መገለል ማስቀረት ✅ የአማራን ህዝብ ተፈጥሯዊ የሆነውን የሕዝባዊና ግዛታዊ አንድነት መብት ማስከበር ✅የአማራን ህዝብ በሀገሪቱ የማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካ የሚኖረውን ተሳትፎ ማሳደግ ✅አማራው ለአገር ልማት ባበረከተው አስተዋፅዖ እና በመልማት ፀጋው ልክ የልማት ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ ህዝባዊ ትግሉ በነዚህ ሰፊና ጥልቅ ጉዳዮችን በያዙ አንኳር ነጥቦች ዙሪያ በሚያጠነጥን ፖለቲካዊ ቅኝት መቃኘት አለበት! እንቅስቃሴውም አውዱንና ወቅቱን ቀዋጀ መልኩ 'ወደፊት' መሆን ይኖርበታል ! ይኸው ነው! ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork

በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ 11:30 አካባቢ የጀመረው ተኩስ አሁንም የከባድ መሳሪያ ድምፅ አልፎ አልፎ እየተሰማ ይገኛል። እስካሁን በነበረው የተኩስ ልውውጥ በፓትሮል መኪኖች እና በፀጥታ ኃይሎ
+1
በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ 11:30 አካባቢ የጀመረው ተኩስ አሁንም የከባድ መሳሪያ ድምፅ አልፎ አልፎ እየተሰማ ይገኛል። እስካሁን በነበረው የተኩስ ልውውጥ በፓትሮል መኪኖች እና በፀጥታ ኃይሎች ላይ ጉዳት ደርሷል። ዝርዝር መረጃ ከአይን እማኞች አንደበት በነገው እለት በአድሱ የዩቱብ ቻናላችን  ዜና እወጃችን ይሰሙታል። ➨ ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇 https://www.youtube.com/@AhaduMedia2023

በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ 11:30 አካባቢ የጀመረው ተኩስ አሁንም የከባድ መሳሪያ ድምፅ አልፎ አልፎ እየተሰማ ይገኛል። እስካሁን በነበረው የተኩስ ልውውጥ በፓትሮል መኪኖች እና በፀጥታ ኃይሎ
+1
በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ 11:30 አካባቢ የጀመረው ተኩስ አሁንም የከባድ መሳሪያ ድምፅ አልፎ አልፎ እየተሰማ ይገኛል። እስካሁን በነበረው የተኩስ ልውውጥ በፓትሮል መኪኖች እና በፀጥታ ኃይሎች ላይ ጉዳት ደርሷል። ዝርዝር መረጃ ከአይን እማኞች አንደበት በነገው እለት በአድሱ የዩቱብ ቻናላችን ዜና እወጃችን ይሰሙታል። ➨ ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇 https://youtube.com/@Ahadu-Media

በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ 11:30 አካባቢ የጀመረው ተኩስ አሁንም የከባድ መሳሪያ ድምፅ አልፎ አልፎ እየተሰማ ይገኛል። እስካሁን በነበረው የተኩስ ልውውጥ በፓትሮል መኪኖች እና በፀጥታ ኃይሎች ላይ ጉዳት ደርሷል። ዝርዝር መረጃ ከአይን እማኞች አንደበት በነገው እለት በአድሱ የዩቱብ ቻናላችን ዜና እወጃችን ይሰሙታል። ➨ ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇 https://youtube.com/@Ahadu-Media

ትልቅ ሰፕራይዝ🤣 የባል በቀል ናይጄሪያ ውስጥ ነው፣ ባል ሚስቱ የሱን እግር እየጠበቀች እንደምትማግጥበት ይጠረጥራል። አውጥቶ አውርዶ ለስራ ፊልድ በሚወጣበት ጊዜ ከመኝታ ክፍሉ ውስጥ ድብቅ ካሜራ ይ
ትልቅ ሰፕራይዝ🤣 የባል በቀል ናይጄሪያ ውስጥ ነው፣ ባል ሚስቱ የሱን እግር እየጠበቀች እንደምትማግጥበት ይጠረጥራል። አውጥቶ አውርዶ ለስራ ፊልድ በሚወጣበት ጊዜ ከመኝታ ክፍሉ ውስጥ ድብቅ ካሜራ ይገጥማል። ከስራ ሲመለስም በድብቅ የተገጠመው ካሜራ ያስቀረውን ተነቀሳቃሽ ምስል ሲፈትሽ እውነትም ሚስት የገዛ አልጋው ላይ ከጎረምሳ ጋራ አንሶላ ስትጋፈፍ ቀድቶ ኖሮ ከሀ እስከ ፐ ለባል ያሳየዋል። በዚህ የሚስቱ ድርጊት ቆሽቱ ያረረው አቶ ባል የሆዱን በሆዱ ይዞ ሚስቱን ለልደቷ ቤተሰቦቿን ሁሉ እንድትጠራ፣ ሰርፕራይዝ ሊያደርጋት እንደሚፈልግ ይነግራታል። ሚስትም አንደታዘዘችው ቤተሰቦቿን በሞላ ለልደቷ ትጠራለች። ባልም እሱ ቤት ባልነበረበት ወቅት በገዛ መኝታ ክፍሉ ውስጥከጎረምሳ ጋራ ስትዛለል ያስቀረውን ፎቶ በፍሬም ውስጥ አድርጎ በስጦታ ወረቀትም ጠቅልሎ የልደት ስጦታ ያበረክትላታል። ምንነቱን ለማየት የጓጉት ቤተሰቦች እንድትከፍተው በሞራል ይገፋፏትና ወረቀቱን ስትገልጠው የራሷ ጉድ መሆኑን ስታይ በድንጋጤ እራሷን ሳተች። ሰውየው የሰራው ስራ ልክ ነው አይደለም የሚለው ጥያቄ በናይጄሪያ ማህበራዊ ሚዲያ የጭቅጭቅ አርዕስት ሆኖአል። (Via Muktarovich Ousmanova ) @Gimbamedianetwork

እጅግ አሳፋሪው መንግስታዊ ገመና...! //በጋዜጠኛ መሳይ መኮንን// &lt;&lt; የኢትዮጵያን ኢንሳይደር ቢሮ በሩ ሳይሰበር ንብረቶቹ መዘረፋቸውን አሳውቋል። ይህን አስመልክቶ ሀቅ የሚዲያ ኮሚኒኬሽ
እጅግ አሳፋሪው መንግስታዊ ገመና...! //በጋዜጠኛ መሳይ መኮንን// << የኢትዮጵያን ኢንሳይደር ቢሮ በሩ ሳይሰበር ንብረቶቹ መዘረፋቸውን አሳውቋል። ይህን አስመልክቶ ሀቅ የሚዲያ ኮሚኒኬሽን የበተነው መግለጪያ ላይ ''ዘረፋው የተቀነባበረ'' እንደሆነ ገልጿል። ከዚህ ቀደም ኢትዮ 251 ሚዲያም ተመሳሳይ ዘረፋ ተፈጽሞበታል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ እንዲሁ በር ሳይሰበርበት ንብረቶቹ ተወስደዋል። መሰል ድርጊቶች በሌሎች አካላት ላይም ተፈጽሟል። በጣም በተጠና ሁኔታ የሚደረገው እንዲህ ዓይነት እርምጃ የአገዛዙን ማፊያ አሰራር በግልጽ የሚያመለክት ነው።ከዚህ ጀርባ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚሉት አብይ አህመድ አምጦ የወለደው ተቋም እጁ እንዳለበት ይነገራል። >> << ወርቁ ጋቸና የሚባል በአብይ ሳምባ የሚተነፍስ ሰውዬ የሚመራው ይህ ተቋም የሲሲሊያ ማፊያዎችን የሚያስንቁ የወንጀልና የስለላ ስራዎች የሚሰራ እንደሆነ ይታወቃል። አብይ የሚፈራቸውን የራሱ ሰዎችን መኝታ ቤታቸው ካሜራ ገጥሞ የአልጋ ላይ ጨዋታቸውን ሳይቀር የሚቀርጽ እንደሆነ ውስጥ አዋቂዎች ይገልጻሉ። በካሜራ ውስጥ ድብቅ ገበናቸው የተቀረጸባቸው ሚኒስትሮችና ቁልፍ አመራሮች እንዳሉም ይነገራል። አፋቸው ተለጉሞ ፥ ከሰውዬው ፍላጎት ውጪ ወለም ዘለም እንዳይሉ የሆኑ አመራሮች ይህንኑ ፈርተው እንደሆነም ይታወቃል። ይህ መስሪያ ቤት አብይ ድብቅ ወንጀል ሊሰራበት ያቋቋመው መሆኑ በግልጽ መታወቅ አለበት። >> ይህ ሀገሪቱ በሲሲሊ ማፊያ እጅ እንደወደቀች አንዱ ማሳያ ነው! ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork

ተዘግተው የነበሩ የሶሻል ሚዲያዎች (TELEGRAM,YOUTUBE,TIKTOK, FACEBOOK,...) አሁን ያለ VPN መስራት ጀምረዋል
ተዘግተው የነበሩ የሶሻል ሚዲያዎች (TELEGRAM,YOUTUBE,TIKTOK, FACEBOOK,...) አሁን ያለ VPN መስራት ጀምረዋል

እናንተ ህዝብ ላይ ችግር አትትከሉ እንጅ ችግኙንስ ህዝብ ይተክለዋል። የስራ ክፍፍል ጠቃሚ ነው! ውጤትም ያመጣል። ፖለቲከኞቹ ችግር አትትከሉ እንጅ ችግኙን አርሶ አደሩ በግብርና ባለሙያ ታግዞ ይተክለዋል። እየውልህ፦ የደቡብ ሱዳን ታጣቂና ሌላው ንፁሃንን እያጠቃ መከላከያ ችግኝ ሲተክል ውጤታማ ስራ አይደለም! የቀበሌ ሰራተኛ ቢሮ ዘግቶ ግብር ከፋይ እያጉላላ ጭቃ ያጨማለቀበት ችግኝ እርግጠኛ ሁን አይፀድቅም! ክስረት። ሚኒስትሩ በአውሮፕላን፣ በመአት መኪና፣ ድግስ በርካታ ወጭ አውጥቶ፣ ሚዲያ አንጋግቶ የሚተክለው ችግኝ ኪሳራ ነው። አንድ ቀን ለፕሮፖጋንዳ በጭቃ ለውሰኸው የምትመጣውን ችግኝ ቀርቶ ግዙፍ ፕሮጀክት ትረሳዋለህ። እየተዋወቅን። ለሁለት ደቃቃ ፕሮፖጋንዳ ሚሊዮን ብር እየከሰረ አያዋጣም። ለሚሰራ ስጡት። ቀን ሙሉ የሚሰራ ይስራው። የሚሻለው! ይህ ሁሉ ወጭ በአንድ ቋት ሆኖ፣ ችግኝ እተክላለሁ ብሎ ስራ የሚጎዳው ላይ አስርም አምስትም ብር አዋጥተህ ለአርሶ አደሩ አበል ክፈለው። ስራ አጥቶ የተቀመጠው ወጣትም ተወዳድሮ ጭምር መስራት ይችላል።  ፕሮጀክት አድርገህ የስራ እድልም ይፈጥር ነበር።  የግብርና ባለሙያዎችን በደንብ አሰልጥነህ አሰማራ። ለፕሮፖጋንዳ እንደምትለው ባይሆንም በርካታ ይተከላል። አንተ ድንጋይ ስር ሸጉጠኸው ከምትመጣው በተሻለ ይፀድቃል። ችግኝ በዘመቻ አይሆንም።  ደግሞ አንድ ቀበሌ ሚሊዮን ሊተክል? ውሸት ነው። ለኢትዮጵያ ህዝብ ችግር አትትከሉበት እንጅ ችግኙን በትንሽ ወጭ፣ በነፃም ጭምር ይተክለዋል። ሱፍ ለብሰህ ለሁለት ደቂቃ ለምትሰራው ፕሮፖጋንዳ የሚወጣን ወጭ የአንድ ቀበሌ ህዝብ መአት ችግኝ ይተክልበታል። ችግር እየተከላችሁ ችግኞቹ ብቻ ሳይሆኑ የሰው ነፍስ በየቀኑ እየጠወለገ ነው። ጫካ ሄዶ ችግኝ ለመትከል አልተቻለም። ይህ ሁሉ የዘጭዘጭ ወጭ ለአርሶ አደሩ ማዳበሪያ ይሆን ነበር። ማዳበሪያ ብታደርሱት ችግኙን ደግሞ በትንሽ ውሎ አበል መስራት ይችል ነበር። የአካባቢው ህዝብ መካከል ተመርጦ የተከለውን እንዲንከባከብ ቢደረግ አዋጭ ነበር። ይህንም ተውት ከፈለጋችሁ። ችግኝም አትትከሉ። ከፈለጋችሁ በብዙ ኪሳራም ፕሮፖጋንዳ ስሩበት። ግን ችግር በቃን። የተከላችሁት እሾሃማ ችግር መሄጃ መንቀሳቀሻ ነሳን። ተውን። ችግር አትትከሉምን። አንደኛው ክልል ሌላኛውን ክልል ለመበጥበጥ ታጣቂ አያደራጅ፣ አንዱ የሌላውን ውስጣዊ አንድነት አይረብሽ።  ንፁሃንን የሚያጠቃ የግልና የቡድን ታጣቂ አታደራጁ። ስንጠቃ የፀጥታ ኃይሉ አልታዘዝኩም አይበል። ችግኝ የሚተከለውን ተውትና ንፁሃን በአንድ ጉድጓድ የሚቀበሩበትን አሰቃቂ ችግር አስቁሙ።  ህዝብ ላይ የጀመራችሁትኝ ዘመቻ አቁሙ። ተገንጣይ ኃይልን እየደገፋችሁ ህዝብን እረፍት አትንሱ። አንዱ በሌላኛው ህዝብ ላይ ልክ እንደ ጠላት ደባ ሲሰራ አይዋል። በእናንተ ችግር ምክንያት የኢትዮጵያ ህዝብ እረፍት አጣ። የብሔር ጠብ፣ የኃይማኖት ጥቃት፣ የታጣቂ ጥቃት፣ በህዝብ ላይ ሰራዊት ማሰማራት፣ ደባ፣ ሴራ.... በቃ ችግር አትትከሉ! ችግር ባልተከላችሁ እንጅ ያለውም በበቃን። ገጀራና ክላሽ ቀርቶ የአየር ንብረት ለውጥ በገደለን እቴ። ንፋስ፣ ሙቀት ምናምን! ያንቃቃና! ከእናንተው ችግር አይበልጥ። ደግሞ ችግር መትከል ብታቆሙ ችግኙን ህዝብ "ሆ" ብሎ ይተክለው ነበር። ተውን በቃ። ችግርን አመቱን ሙሉ እየተከላችሁ በሁለት ደቂቃ ለፕሮፖጋንዳ የምትተክሉት ችግኝ አያድነንም። ➨ ጋዜጠኛ ጌታቸዉ ሽፈራዉ ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇 https://t.me/gimbamedianetwork