cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Amazing_God

This is a channel that give Tanks to the lord,for he fills our life with good tings. @agape_deep_love

Show more
Ethiopia11 788The language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
199
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
.........ከባለፈው የቀጠለ 2,መሰናከልና የክፋት መልስ መመለስ ፍቅር የሚቀዘቅዝበት ምክኒያት ለፍቅራችን መልስን መጠበቅ ነው፡፡ ለፍቅር ድርጊታችን  ከምንወደው ሰው መልስ የምንጠብቅ ከሆንን አንዳንዴ መልካም መልስ ስለማናገኝ ይፍጠንም ይዘግይም ፍቅር መቀዝቀዙ አይቀሬ ነው፡፡ ፍቅር እንካ በእንካ ጉዳይ አይደለም፡፡ ፍቅር የመስጠት የመባረክ የማንሳትና የመጥቀም ጉዳይ ነው፡፡ ፍቅር እንዲያው ለመስጠት ብሎ የመስጠት ጉዳይ እንጂ መልስን ጠብቆ የመስጠት ጉዳይ አይደለም፡፡ የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? የማቴዎስ ወንጌል 5፡46-47 ፍቅር እግዚአብሄር ለሌላው ሰው እኛ ውስጥ ያስቀመጠውን መልካምነት በታማኝነት የማስጠት ጉዳይ ነው፡፡ ፍቅር ደጋግ መጋቢነት ነው፡፡ ፍቅር ንግድ አይደለም፡፡ ፍቅር ስጦታ መስጠት ነው፡፡ ፍቅር ሌላውን የተመረቀ እድለኛ ማድረግ ነው፡፡ ይቀጥላል..........
Show all...
..........ከባለፈው የቀጠለ 1,ስንፍናና አለመትጋት ፍቅርን ሊያጠፉ የሚመጡ ብዙ ውሆች ስላሉ ፍቅር እንዳይጠፋ ትጋት ይጠይቃል፡፡ ፍቅር ከተተወ ይጠፋል፡፡ ፍቅር እንክብካቤ ካልተደረገለት ይበላሻል፡፡ እንደእሳት ፍቅር ካልቆሰቆሱትና ካላቀጣጠሉት ይከስማል፡፡ ፍቅር እንደችግኝ ማዳበሪያ ካላደረጉለት ውሃ ካላጠጡትና ካልኮተኮቱት ይደርቃል፡፡ ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ። ወደ ዕብራውያን 10፡24-25 ፍቅር ሌላውን በመረዳት ራስን ከሚወዱት ሰው ጋር ማስተባበር ነው፡፡ ፍቅር የምንወደውን ሰው ማጥናትና መረዳት ይጠይቃል፡፡ የምንወደውን ሰው ለመረዳት መነጋገር መወያየት ይጠይቃል፡፡ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ። ወደ ዕብራውያን 10፡25 ፍቅር ራስን በምንወደው ሰው ቦታ አስቀምጦ ነገሮችን ካለአድልዎ ማየት ይጠይቃል፡፡ የምንወደውን ሰው ለመረዳት ጊዜ መስጠት ይጠይቃል፡፡ የምንወደውን ሰው ለመረዳት ጥረት ይጠይቃል:: 2,መሰናከልና የክፋት መልስ መመለስ ይቀጥላል...........
Show all...
የብዙ ሰዎች ፍቅር የሚቀዘቅዝባቸው ሶስቱ ዋና ዋና ምክኒያቶች ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። የማቴዎስ ወንጌል 24፡12-13 ፍቅር ታላቅ ሃብት ነው፡፡ የፍቅር ህይወት ታላቅ ስብእና ነው፡፡ ፍቅር ክብር ነው፡፡ ፍቅር ውበት ነው፡፡ ኢየሱስን እንደ አዳኛችን የተቀበልን ሁሉ ከእግዚአብሄር በመወለዳችን የእግዚአብሄር ፍቅር በእኛ ውስጥ አለ፡፡ የመውደድ እምቅ ጉልብት ቢኖረንም ይህ በውስጣችን የተጠራቀወመውን ጊልበት አውጥቶ ለብዙዎች በረከት ለማድርግ የሚያስፈልጉ ነገሮች አሉ፡፡ በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም። ወደ ሮሜ ሰዎች 5፡5 ፍቅር መታወቂያችንና ክብራችን ነው፡፡ ፍቅር ሃብታችንና መገለጫችን ነው፡፡ ለፍቅር ተወልደናል፡፡ ሰው ፍቅር ከሌለው የተፈጠረበተን አላማ የሳተ ከንቱ ሰው ነው፡፡ ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡1 ፍቅር ምንም ያህል የከበረ ቢሆንም ፈተና አለበት፡፡ የፍቅርን ፈተና ያላለፉ ሰዎች ፍቅራቸው ትቀዘቅዛለች፡፡ ፍቅር ቅፅበታዊ አይደለም፡፡ ፍቅር ከትትልና እንክብካቤ የሚፈልግ ነገር ነው፡፡ ፍቅር ዝም ብሎ ከተተወ ፍቅርን ሊያቀዘቅዙ የሚችሉ ብዙ ነገሮች ስላሉ ፍቅር ይቀዘቅዛል፡፡ ፍቅር ግን እንዳይቀዘቅዝ እንዲያውም እየጋለና እየጨመረ እንዲሄድ ለማድረግ እነዚህን ፍቅርን የሚያቀዘቅዙትንና የወይንም ቦታችንን የሚያጠፉትን ጥቃቅን ቀበሮዎች ከህይወታችን መሰለልና ማጥፋት አለብን፡፡ ወይናችን አብቦአልና የወይናችንን ቦታ የሚያጠፉትን ቀበሮች፥ ጥቃቅኑን ቀበሮች አጥምዳችሁ ያዙልን። መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 2፡15 1,ስንፍናና አለመትጋት ይቀጥላል.........
Show all...
1ኛ ጴጥሮስ 2 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴ በሰው ዘንድ ወደ ተናቀው፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ወደ ተመረጠውና ክቡር ወደ ሆነው ወደዚህ ሕያው ድንጋይ እየቀረባችሁ፣ ⁵ እናንተ ደግሞ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕት ታቀርቡ ዘንድ፣ ቅዱሳን ካህናት ለመሆን እንደ ሕያዋን ድንጋዮች መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ትሠራላችሁ። ⁶ ምክንያቱም በመጽሐፍ እንዲህ ተብሎ ተጽፎአልና፤ “እነሆ፤ የተመረጠና ክቡር የማእዘን ድንጋይ፣ በጽዮን አኖራለሁ፤ በእርሱም የሚያምን፣ ከቶ አያፍርም።” ⁷ እንግዲህ ለእናንተ ለምታምኑት ይህ ድንጋይ ክቡር ነው፤ ለማያምኑት ግን፣ “ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣ እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ።” ⁸ ደግሞም፣ “ሰዎችን የሚያሰናክል፣ የሚጥላቸውም ዐለት ሆነ።” የሚሰናከሉት ቃሉን ባለመታዘዛቸው ነው፤ የተመደቡት ለዚህ ነውና። Good morning Ppl😊
Show all...
ቆላስይስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ፤ ² በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም። ³ ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና፤ Good morning Ppl😊
Show all...
Good morning Ppl😊
Show all...
1ኛ ዮሐንስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵-¹⁶ ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። ¹⁷ ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። Good morning Ppl😊
Show all...
When ever you're crying or feeling sad just remember this Bible verse I WILL RESCUE YOU; I WILL PROTECT YOU; I WILL BE WITH YOU IN TROUBLE ----------PSALM 91:14---------- Good morning Ppl😊
Show all...
ዘዳግም 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም ኃይልህ ውደድ። ⁶ እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ። Good morning Ppl😊
Show all...
This is How God describes a Godly woman - Generous “Being enriched in every thing to all bountifulness, which causeth through us thanksgiving to God.” 2 Corinthians 9:11 - Dependent “But he answered and said, It is written, Man shall not live by bread alone, but by every word that proceedeth out of the mouth of God.” Matthew 4:4 - Humble “But he giveth more grace. Wherefore he saith, God resisteth the proud, but giveth grace unto the humble.” James 4:6 - Speaks truth “But speaking the truth in love, may grow up into him in all things, which is the head, even Christ:” Ephesians 4:15 - wisdom Proverbs 31 - Dressing modest “And, behold, there met him a woman with the attire of an harlot, and subtil of heart.” Proverbs 7:10 - Patience “Rejoicing in hope; patient in tribulation; continuing instant in prayer;” Romans 12:12 - Strength “Therefore, my beloved brethren, be ye stedfast, unmoveable, always abounding in the work of the Lord, forasmuch as ye know that your labour is not in vain in the Lord.” 1 Corinthians 15:58 - Forgiveness & compassion. “Blessed are the merciful: for they shall obtain mercy.” Matthew 5:7 - Bravery “Be strong and of a good courage, fear not, nor be afraid of them: for the LORD thy God, he it is that doth go with thee; he will not fail thee, nor forsake thee.” Deuteronomy 31:6 Good morning 😊
Show all...
" የአባቴ ብልጠት" ታሪኩ እውነተኛ ቢሆንም ሥነጽሑፋዊ በሆነ መንገድ ቀርቧል አንድ ቀን ወደ ትምህርት ቤት እየሄድኩኝ መንገድ ላይ አስገራሚና አስተማሪ ነገር ገጠመኝ ለሊቱን ዘንቦ ስለ ነበረ(የድሬ ዝናብ) መሬቱ አሸዋማ ቢሆንም አልፎ አልፎ ከጭቃ ጋር እየታገልኩ ስሄድ ሁለት ጎልማሳ ሰዎች ከፊት ለፊቴ ይሄዱ ነበር ። አንደኛው ሁለት ትንንሽ ልጆች ይዛል ልጆቹም ከፊት እየሮጡ አስቸገሩ አባታቸው "ተው ትወድቃላችሁ እኔ ልያዛችሁ" ቢላቸውም አሻፈረኝ አሉ ከዚያ አባትየው ትንሽ አሰላስሎ ለጋደኛው "አሁን እንዴት እደምይዛቸው ተመልከት" አለው ከዚያ አባትየው እየተንገዳገደ "ልወድቅ ነው ልጆቼ ያዙኝ" ብሎ ጭኸ ልጆቹም በፍጥነት አንዱ የግራ እጁን ሌላኛው የቀኝ እጁን ያዙት እርሱም ጠበቅ አርጎ ያዛቸውና ልጆቼ እንዳልወድቅ እጄን አትልቀቁኝ አላቸው እነርሱም እሺ አባዬ አሉት ይሄኔ አባትየው ዞር ብሎ ለጓደኛው አየህ እንዴት እንደያዝኩቸው ትወድቃላችሁ ልያዛችሁ ብላቸው አንወድቅም ብለው ይወድቃሉ ያዙኝ ብላቸው ግን እንይዘዋለን ብለው ይያዛሉ አለው ልያዛችሁ ብዬ ከማልይዛቸው ያዙን ብዬ ብይዛቸው ይሻልል አለው። በጣም ገረመኝ የአባትየው ብልጠት የሰማዩ አባቴን አስታወሰኝ የልጆቹ መረዳት አባታቸውን መያዛቸው ነው እውነቱ ግን እነሱ በአባታቸው መያዛቸው ነው። አገልግሉኝ ያለን ለካ ሊያገለግለን ፈልጎ ነው! ዘምሩልኝ ያለን ለካ ሊባርከን ፈለጎ ነው! ስጡኝ ያለን ለካ ሊሰጠን ፈልጎ ነው! እንጂማ የትኛውን ጉድለቱን ልንሟላ የትኛውን ደካሙን ለናግዝ " እርሱም ሕይወትንና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና አንዳች እንደሚጎድለው በሰው እጅ አይገለገልም።" (የሐዋርያት ሥራ 17:25) ለካ የሳምራዊቷን ሴት ውሃ አጠጪን ያላት እንደተጠማች አውቆ የህይወትን ውሀ ሊያጠጣት ነው ለካ "ውሀ አጠጪን ብሎ ውሃ የሚጠጣ የአባት ብልጠት" " ኢየሱስ መልሶ።... ውኃ አጠጪኝ የሚልሽ ማን መሆኑንስ ብታውቂ፥ አንቺ ትለምኚው ነበርሽ የሕይወትም ውኃ ይሰጥሽ ነበር አላት።" (የዮሐንስ ወንጌል 4:10) እሷማ ምንታርግ ምድራዊ ውሃ የሚለምን ሰማያዊ ውሃ ያጠጣኛል ብላ እንዴት ትጠርጥር የአባቷ ብልጠት አልገባትም "ሊያጠጣ ሲፈልጎ አጠጡኝ እንደሚል " እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቡን ከባርነት ቤት ሲያወጣ ያለውን ተመልከቱ " እግዚአብሔርም ሙሴን ተናገረው። ወደ ፈርዖን ግባ እንዲህም በለው። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ያገለግለኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ።"(ኦሪት ዘጸአት 8:1) የእውነት ግን እስራኤል ነው እግዚአብሔርን ያገለገለው ወይስ እግዚአብሔር ነው የእስራኤልን ያገለገለው? ማነው መና ከሰማይ ያወረደው? ማነው ደመና ጋርዶ የእሳት አምድ ዘርግቶ ያገለገለው? ማነው በምድረ በዳ ከነክፉ አመላቸው እንደ ንስር በክንፍ የተሸከማቸው? እግዚአብሔር ነው። እነሱማ አስመረሩት እንኩዋን ሊያገለግሉት። ታገለግሉኛላችሁ ብሎ አውጥጦ እራሱ አገለገላቸው ። የአባቴ ብልጠት አገልግሉኝ እያለ ማገልገሉ፤ አክብሩኝ ያለ ማክበሩ፤ ስጡኝ እያለ መስጠቱ ነው። እኔ በአባቴ ብልጠት ተገርሚያለሁ እናንተስ?
Show all...
“የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና።” — ማቴዎስ 5፥7 “ምሕረትን ለማያደርግ ምሕረት የሌለበት ፍርድ ይሆናልና፤ ምሕረትም በፍርድ ላይ ይመካል።” — ያዕቆብ 2፥13
Show all...
በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና፥ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን። እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን። ወደ ሮሜ ሰዎች 14 : 8
Show all...
መዝሙር 125 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በእግዚአብሔር የታመኑ እንደማይታወክ ለዘላለም እንደሚኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው። ² ተራሮች በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ሆኑ፥ ከዛሬ ጀምሮ ለዘላለም እግዚአብሔር በሕዝቡ ዙሪያ ነው።
Show all...
ሆሴዕ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁶ እርሱም የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር ነው፤ የመታሰቢያው ስም እግዚአብሔር ነው። ⁷ ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤ ምሕረትንና ፍርድን ጠብቅ፥ ዘወትርም በአምላክህ ታመን። Good morning 😊
Show all...
“ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና።” — ዕብራውያን 11፥6 Good morning
Show all...
How God describe a Godly Friendship -Faith “Faithful are the wounds of a friend; but the kisses of an enemy are deceitful.” Proverbs 27:6 -Wise “He that walketh with wise men shall be wise: but a companion of fools shall be destroyed.” Proverbs 13:20 -With out Anger “Make no friendship with an angry man; and with a furious man thou shalt not go:” Proverbs 22:24 -Helping each other “For if they fall, the one will lift up his fellow: but woe to him that is alone when he falleth; for he hath not another to help him up.” Ecclesiastes 4:10 -Kindness “Wherefore by their fruits ye shall know them.” Matthew 7:20 -Forgiveness “Blessed are the merciful: for they shall obtain mercy.” Matthew 5:7 -Loving at all time “A friend loveth at all times, and a brother is born for adversity.” Proverbs 17:17 Good morning 😍
Show all...
How God describe a Godly Friendship -Faith “Faithful are the wounds of a friend; but the kisses of an enemy are deceitful.” Proverbs 27:6 -Wise “He that walketh with wise men shall be wise: but a companion of fools shall be destroyed.” Proverbs 13:20 -With out Anger “Make no friendship with an angry man; and with a furious man thou shalt not go:” Proverbs 22:24 -Helping each other “For if they fall, the one will lift up his fellow: but woe to him that is alone when he falleth; for he hath not another to help him up.” Ecclesiastes 4:10 -Kindness “Wherefore by their fruits ye shall know them.” Matthew 7:20 -Forgiveness “Blessed are the merciful: for they shall obtain mercy.” Matthew 5:7 -Loving at all time “A friend loveth at all times, and a brother is born for adversity.” Proverbs 17:17 Good morning 😍
Show all...
“ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።” — ኢሳይያስ 9፥6 ሉቃስ 2 10 እነሆ÷ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ 11 እነሆ፥ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃን ተወልዶላችኋል ፤ ይኸውም ቡሩክ ጌታ ክርስቶስ ነው ። 12 ለእናንተም ምልክቱ እዲህ ነው ፦ ሕፃን አውራ ጣቱን ታስሮ ፥በጨርቅም ተጠቅልሎ በበረት ውስጥ ተኝቶ ታገኛላችሁ:: ማቴ 2፥11 “ወደ ቤትም ገብተው ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት፥ ወድቀውም ሰገዱለት፥ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን ከርቤም አቀረቡለት።” 🌷🌷እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም በጤና ጠብቆ አደረሳችሁ አደረሰን በዓሉ የሰላም የፍቅር የመተሳሰብ ይሁንልን በዓል ይሁንላችሁ🌷🌷 enkun adersachehu 😍😍
Show all...
“ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58 Good morning 😍
Show all...
“ትካዜህን በእግዚአብሔር ላይ ጣል፥ እርሱም ይደግፍሃል፤ ለጻድቁም ለዘላለም ሁከትን አይሰጠውም።” — መዝሙር 55፥22 እንዴት አመሻችሁ 😍
Show all...
ዘዳግም 11 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ ነገር ግን እግዚአብሔር ያደረጋትን ታላቂቱን ሥራ ሁሉ ዓይኖቻችሁ አይተዋል። ⁸-⁹ እንግዲህ እንድትጠነክሩ፥ ትወርሱአትም ዘንድ ወደምትሻገሩባት ምድር እንድትገቡ እንድትወርሱአትም፥ እግዚአብሔርም ለእነርሱና ለዘራቸው ይሰጣት ዘንድ በማለላቸው ወተትና ማርም በምታፈስሰው ምድር ዕድሜአችሁ እንዲረዝም፥ ዛሬ ለእናንተ የማዝዘውን ትእዛዝ ሁሉ ጠብቁ። Good morning 😍
Show all...
“ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ፥ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉት፥” — ቆላስይስ 3፥23 Good morning 😊
Show all...
ምሳሌ 20 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹ ልቤን አነጻሁ፥ ከኃጢአትም ጠራሁ የሚል ማን ነው? … ¹¹ ሕፃን ቅንና ንጹሕ መሆኑ በሚያደርገው ሥራ ይታወቃል። Good morning 😍
Show all...
“እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንዲሰጣችሁ፥ ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ።” — ዮሐንስ 15፥16 በመጀመሪያ ኢየሱስን ለመከተል የመረጡት ሰዎች አይደሉም። ይልቁንም እርሱን እንዲከተሉ ሰዎችን የመረጠ ኢየሱስ ነው። በመጀመሪያ ኢየሱስ ሰዎችን ጠራ። ከዚህ በኋላ ሰዎች ኢየሱስን ለመከተልና ላለመከተል ነፃ ናቸው። ይሁን እንጂ ኢየሱስ ከጠራው ሰው በስተቀር እርሱን _ መከተል የሚችል ማንም ሰው የለም ። ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንደመረጠ ሁሉ ደግሞም ሾማቸው። ሹመቱ «መሄድ» ማለትም ምስክር መሆን ነው። ሥራቸውም «ፍሬ ማፍራት» ነው። ኢየሱስ ሲናገር፥ «እኔ መረጥሁአችሁ. ሄዳችሁ ብዙ ፍሬ እንድታፈሩ» አለ" የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት እንደ ቅርንፍ ናቸው" የቅርንጫፍ ሥራ ፍሬማፍራት ነው" ይህ ቁጥር ባለበት ዐውደ ንባብ ውስጥ «ፍሬ ማፍራት» ማለት ሌሎችን ወደ ክርስቶስ ማምጣት ማለት ነው። የሐረጉ ቀዳማይ ፍቺ ይህ ነው። እንዳንዱ ክርስቲያን «ሄዶ ፍሬ እንዲያፈራ» ተሾሞአል። ሩቅ ቦታ ለመሄድ አልተጠራን ይሆናል" ነገር ግን ሁላችንም እንድንሄድ ተጠርተናል። ወደ ገዛ ቤተሰቦቻችንና ጎረቤቶቻችን እንድንሄድ ተጠርተናል። አንድም ክርስቲያን እኔ ለመሄድና ፍሬ ለማፍራት አልተጠራሁም አይበል። እያንዳንዱ ክርስቲያን ደቀ መዝሙር እንደሆነ ሁሉ እያንዳንዱም ክርስቲያን የወንጌል መልእክተኛ (ሚሲዮናዊ) ነው። እግዚአብሔር tእያንዳንዱ ክርስቲያን የሰጠው ሥራ ለዘላለም የሚኖር ሥራ ነው። በእርግጥ የእግዚአብሔርን ሥራ የምንሠራ ከሆነ፤ ሥራችን ለዘላለም ይኖራል። የእግዚአብሔርን ፍሬ የምናፈራ ከሆነ ፍሬአችን ለዘላለም ይኖራል። የምንሠራው የእግዚአብሔርን ሥራ እንደሆነና የምናፈራውም የእግዚአብሔርን ፍሬ እንደሆነ ሁላችንም እርግጠኞች እንሁን። ሥራውም ሆነ ፍሬው የእኛ አይደለም። በእርግጥ የእርሱን ሥራ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የምንሠራ ከሆነ፤ በኢየሱስ ስም የለመነውን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይሰጠናል። እግዚኣብሔር የተናገረውን የምናደርግ ከሆነ እርሱም የተናገረውን ያደርጋል። ፍሬ ለማፍራት ጸጋና ኀይል እንዲሰጠን ጠይቀን ጥያቄአችን ሳይመለስ የቀረው ስንት ጊዜ ነው? ለጥያቄአችን መልስ ሳናገኝ ስንቀር «መልስ ያላገኘነው ለምንድን ነው?» ብለን እንጠይቃለን? የዚህ ምክንያቱ በዚህ ቁጥር ላይ ኢየሱስ የሰጠውን ትእዛዝ በሚገባ አለመረዳታችን ነው። ይኸውም ሄደን ፍሬ እንድናፈራ ጸጋና ኀይል እንዲሰጠን በቅድሚያ ጠየቅን። ኢየሱስ ግን እንዲህ አለ፥ «ሄዳችሁ ፍሬ አፍሩ። ከዚያም እግዚአብሔር የጠየቃችሁትን ጸጋና ኀይል ይሰጣችኋል»። እግዚአብሔር ሄደን ፍሬ እንድናፈራ የሚያስፈል?ንን ጸጋና ኀይል የሚስጠን ፈቃዱን ለመታዘዝ ያለንን ፈቃደኝነት ተመልክቶ ነው። እዚህ ላይ አንድ ትልቅ እውነት እንማራለን። ይኸውም እግዚአብሔርን የምናከብርበትና ከዚህም ክብር የምንካፈልበት አንድ መንገድ ብቻ ኣለ፤ ያም መንገድ የመታዘዝ መንገድ ነው። መንፈስ ቅዱስን የምንቀበለው ስንታዘዝ ብቻ ነው (ዮሐ. 14፥15–16)። ኢየሱስ በሕይወታችን የሚገለጠው ስንታዘዝ ብቻ ነው። እግዚአብሔር በእኛ ውስጥ የሚኖረው ስንታዘዝ ብቻ ነው። በhርስቶስ ፍቅር መኖር የምንችለው በመታዘዝ ብቻ ነው። የክርስቶስን ወዳጅነት የምናገኘው በመታዘዝ ብቻ ነው። እንዲሁም ላቀረብነው የጸሎት ጥያቄ መልስ የምናገኘው ስንታዘዝ ብቻ ነው። እነዚህን ሁሉ ታላላቅ በረከቶች ማግኘት የምንችለው ኢየሱስን ስንታዘዝ ብቻ ነው። በዚህ ቁጥር ላይ መባል ያለበት አንድ ሌላ ነገር አለ። ይኸውም በዚህ ቁጥር ላይ «በስሜ» የሚል አንድ ቁልፍ ቃል አለ። በዮሐ 14፥13 ላይ ማብራሪያ ስንሰጥ «በክርስቶስ ስም» ማለት «በክርስቶስ ምትክ» ማለት እንደሆነ ተናግረናል። ስንጸልይ በክርስቶስ ምትክ (እግር) ሆነን መጸለይ አለብን። ከዚህ ቀጥሎ የምናገኘው ምሳሌ ይህንን እውነት በግልጽ ያሳየናል። ኢየሱስ ወደ ሩቅ አገር የሄደን ነጋዴ ይመስላል። ነጋዴው ወዳሰበበት አገር ከመሄዱ በፊት የንግዱን ኀላፊነት ለአገልጋዩ ይሰጣል። ነጋዴው እርሱ በሌለበት ጊዜ ንግዱን በሙሉ ኀላፊነት እንዲያስተዳድር ለአገልጋዩ ሙሉ ሥልጣን ይሰጠዋል። ከዚህም በላይ አገልጋዩ በነጋዴው ስም እንዲጠቀም ነጋዴው ሙሉ ሥልጣን ይሰጠዋል። እንዲህ ያለ ኀላፊነት የተሰጠው አገልጋይ በራሱ ሥልጣን የሚያደርገው ምንም ነገር የለም። የጌታውን ገንዘብ በራሱ ስም ከባንከ ለማውጣት ቢሞክር ጌታው ይቀጣዋል። ነጋዴው አገልጋዩን እንዲህ ሊያምነው የቻለው ለምንድን ነው? ነጋዴው አገልጋዩን ሊያምነው የቻለው አገልጋዩ ታዛዥና ታማኝ ስለሆነ ነው። አገልጋዩ ታዛዥና ታማኝ በመሆኑ በጌታው ስም መጠቀምን ጨምሮ ንግዱን በኀላፊነት እንዲያስተዳድር ሙሉ ሥልጣን ተሰጠው። ልክ እንዲሁ ኢየሱስ በዚህ ምድር የነበረውን በዚህ ምድር አገልግሎት ጨርሶ ወደ ሰማይ ሲሄድ ሥራውን («ንግዱን») ለእኛ ሰጥቶናል። የመንግሥተ ሰማይን ሀብትና በረከት ሁሉ በስሙ እንድንጠቀም ሙሉ ሥልጣን ሰጥቶናል። የክርስቶስ አገልጋዮች ሆይ! በስሙ ለመጠቀም የተሰጣችሁን ሥልጣን በአግባቡ ተጠቀሙበት! በስሙ ለሰጣችሁ ኀላፊነት ራሳችሁን ስጡ። ኢየሱስ እንዲህ ይለናል፥ «ሄዳችሁ ፍሬ እንድታፈሩ ሾምሁአችሁ። እስከ ምድር ዳርቻ ሁሉ ምስክሮቼ እንድትሆኑ ሾምሁአችሁ (የሐዋ. 1፥8)። የሕይወት ውሃ ምንጭ እንድትሆኑ ሾምሁአችሁ (ሐ. 7፥38)። በመከራ ለሚሰቃየው ዓለም የመንግሥተ ሰማይን ሀብትና በረከት ሁሉ እንድታፈሱ ሾምሁአችሁ»። የተሾምንበትን ነገር ከምን አደረስን? አሁንስ ምን እያደረግን ነው? ከአሁን ጀምሮ ለራሳች› ደስታን፥ ሰላምንና መጽናናትን እንድናገኝ የምናቀርበውን ጥያቄ አናቁም። ከዚህ ይልቅ ግን ይህ ሐሳብ ብቻ በእኛ ውስጥ ይኑር «እኔ የራሴ አይደለሁም፤ እኔ የእርሱ ነኝ እኔ የእርሱ ነኝ የእርሱም የእርሱም አገልጋይ ነኝ። ሕይወቴ አንድ ትርጉምና ዓላማ ብቻ ነው ያለው ያም የእርሱን ፈቃድ ማድረግ»" የእርሱን ፈቃድ ማድረግ የሕይወታችን ብቸኛ ምኞት ሲሆን ወደ እኛ ቀርቦ እንዲህ አልላችሁም ይለናል፥ «ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም ... ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ» ቁ. 15። የክርስቶስ አገልጋዮች ሆይ! ሹመታችሁን ተቀብላችሁ «ሄዳችሁ ለክብሩ የሚሆነውን ፍሬ አፍሩ»። መልካም ምሽት 😊
Show all...
“አቤቱ፥ ቀኑን ሁሉ ወደ አንተ እጮኻለሁና ማረኝ።” — መዝሙር 86፥3 “አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ ነውና፥ ወደ እርሱም ብትመለሱ ፊቱን ከእናንተ አያዞርምና ወደ እግዚአብሔር ብትመለሱ ወንድሞቻችሁና ልጆቻችሁ በማረኩአቸው ፊት ምሕረትን ያገኛሉ፥ ደግሞም ወደዚህች ምድር ይመለሳሉ።” — 2 ዜና 30፥9
Show all...
“ደስ ያላት ልብ መልካም መድኃኒት ናት፤ ያዘነች ነፍስ ግን አጥንትን ታደርቃለች።” — ምሳሌ 17፥22 Good morning 😊
Show all...
መዝሙር 40 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹ አቤቱ፥ አንተ ምሕረትህን ከእኔ አታርቅ፤ ቸርነትህና እውነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ። ¹² ቍጥር የሌላት ክፋት አግኝታኛለችና፤ ኃጢአቶቼ ያዙኝ፥ ማየትም ተስኖኛል፤ ከራሴ ጠጕር ይልቅ በዙ፥ ልቤም ተወኝ። ¹³ አቤቱ፥ ታድነኝ ዘንድ ፍቀድ፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን። Melkan welo 😊
Show all...
1ኛ ጴጥሮስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹ ወዳጆች ሆይ፥ ነፍስን ከሚዋጋ ሥጋዊ ምኞት ትርቁ ዘንድ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ እለምናችኋለሁ፤ ¹² ስለሚመለከቱት ስለ መልካም ሥራችሁ፥ ክፉ እንደምታደርጉ በዚያ እናንተን በሚያሙበት ነገር፥ በሚጎበኝበት ቀን እግዚአብሔርን ያከብሩት ዘንድ በአሕዛብ መካከል ኑሮአችሁ መልካም ይሁን።
Show all...