cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Amazing_God

This is a channel that give Tanks to the lord,for he fills our life with good tings. @agape_deep_love

Show more
Ethiopia11 788The language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
199Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

.........ከባለፈው የቀጠለ 2,መሰናከልና የክፋት መልስ መመለስ ፍቅር የሚቀዘቅዝበት ምክኒያት ለፍቅራችን መልስን መጠበቅ ነው፡፡ ለፍቅር ድርጊታችን  ከምንወደው ሰው መልስ የምንጠብቅ ከሆንን አንዳንዴ መልካም መልስ ስለማናገኝ ይፍጠንም ይዘግይም ፍቅር መቀዝቀዙ አይቀሬ ነው፡፡ ፍቅር እንካ በእንካ ጉዳይ አይደለም፡፡ ፍቅር የመስጠት የመባረክ የማንሳትና የመጥቀም ጉዳይ ነው፡፡ ፍቅር እንዲያው ለመስጠት ብሎ የመስጠት ጉዳይ እንጂ መልስን ጠብቆ የመስጠት ጉዳይ አይደለም፡፡ የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? የማቴዎስ ወንጌል 5፡46-47 ፍቅር እግዚአብሄር ለሌላው ሰው እኛ ውስጥ ያስቀመጠውን መልካምነት በታማኝነት የማስጠት ጉዳይ ነው፡፡ ፍቅር ደጋግ መጋቢነት ነው፡፡ ፍቅር ንግድ አይደለም፡፡ ፍቅር ስጦታ መስጠት ነው፡፡ ፍቅር ሌላውን የተመረቀ እድለኛ ማድረግ ነው፡፡ ይቀጥላል..........
Show all...
..........ከባለፈው የቀጠለ 1,ስንፍናና አለመትጋት ፍቅርን ሊያጠፉ የሚመጡ ብዙ ውሆች ስላሉ ፍቅር እንዳይጠፋ ትጋት ይጠይቃል፡፡ ፍቅር ከተተወ ይጠፋል፡፡ ፍቅር እንክብካቤ ካልተደረገለት ይበላሻል፡፡ እንደእሳት ፍቅር ካልቆሰቆሱትና ካላቀጣጠሉት ይከስማል፡፡ ፍቅር እንደችግኝ ማዳበሪያ ካላደረጉለት ውሃ ካላጠጡትና ካልኮተኮቱት ይደርቃል፡፡ ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ። ወደ ዕብራውያን 10፡24-25 ፍቅር ሌላውን በመረዳት ራስን ከሚወዱት ሰው ጋር ማስተባበር ነው፡፡ ፍቅር የምንወደውን ሰው ማጥናትና መረዳት ይጠይቃል፡፡ የምንወደውን ሰው ለመረዳት መነጋገር መወያየት ይጠይቃል፡፡ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ። ወደ ዕብራውያን 10፡25 ፍቅር ራስን በምንወደው ሰው ቦታ አስቀምጦ ነገሮችን ካለአድልዎ ማየት ይጠይቃል፡፡ የምንወደውን ሰው ለመረዳት ጊዜ መስጠት ይጠይቃል፡፡ የምንወደውን ሰው ለመረዳት ጥረት ይጠይቃል:: 2,መሰናከልና የክፋት መልስ መመለስ ይቀጥላል...........
Show all...
የብዙ ሰዎች ፍቅር የሚቀዘቅዝባቸው ሶስቱ ዋና ዋና ምክኒያቶች ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። የማቴዎስ ወንጌል 24፡12-13 ፍቅር ታላቅ ሃብት ነው፡፡ የፍቅር ህይወት ታላቅ ስብእና ነው፡፡ ፍቅር ክብር ነው፡፡ ፍቅር ውበት ነው፡፡ ኢየሱስን እንደ አዳኛችን የተቀበልን ሁሉ ከእግዚአብሄር በመወለዳችን የእግዚአብሄር ፍቅር በእኛ ውስጥ አለ፡፡ የመውደድ እምቅ ጉልብት ቢኖረንም ይህ በውስጣችን የተጠራቀወመውን ጊልበት አውጥቶ ለብዙዎች በረከት ለማድርግ የሚያስፈልጉ ነገሮች አሉ፡፡ በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም። ወደ ሮሜ ሰዎች 5፡5 ፍቅር መታወቂያችንና ክብራችን ነው፡፡ ፍቅር ሃብታችንና መገለጫችን ነው፡፡ ለፍቅር ተወልደናል፡፡ ሰው ፍቅር ከሌለው የተፈጠረበተን አላማ የሳተ ከንቱ ሰው ነው፡፡ ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡1 ፍቅር ምንም ያህል የከበረ ቢሆንም ፈተና አለበት፡፡ የፍቅርን ፈተና ያላለፉ ሰዎች ፍቅራቸው ትቀዘቅዛለች፡፡ ፍቅር ቅፅበታዊ አይደለም፡፡ ፍቅር ከትትልና እንክብካቤ የሚፈልግ ነገር ነው፡፡ ፍቅር ዝም ብሎ ከተተወ ፍቅርን ሊያቀዘቅዙ የሚችሉ ብዙ ነገሮች ስላሉ ፍቅር ይቀዘቅዛል፡፡ ፍቅር ግን እንዳይቀዘቅዝ እንዲያውም እየጋለና እየጨመረ እንዲሄድ ለማድረግ እነዚህን ፍቅርን የሚያቀዘቅዙትንና የወይንም ቦታችንን የሚያጠፉትን ጥቃቅን ቀበሮዎች ከህይወታችን መሰለልና ማጥፋት አለብን፡፡ ወይናችን አብቦአልና የወይናችንን ቦታ የሚያጠፉትን ቀበሮች፥ ጥቃቅኑን ቀበሮች አጥምዳችሁ ያዙልን። መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 2፡15 1,ስንፍናና አለመትጋት ይቀጥላል.........
Show all...
1ኛ ጴጥሮስ 2 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴ በሰው ዘንድ ወደ ተናቀው፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ወደ ተመረጠውና ክቡር ወደ ሆነው ወደዚህ ሕያው ድንጋይ እየቀረባችሁ፣ ⁵ እናንተ ደግሞ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕት ታቀርቡ ዘንድ፣ ቅዱሳን ካህናት ለመሆን እንደ ሕያዋን ድንጋዮች መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ትሠራላችሁ። ⁶ ምክንያቱም በመጽሐፍ እንዲህ ተብሎ ተጽፎአልና፤ “እነሆ፤ የተመረጠና ክቡር የማእዘን ድንጋይ፣ በጽዮን አኖራለሁ፤ በእርሱም የሚያምን፣ ከቶ አያፍርም።” ⁷ እንግዲህ ለእናንተ ለምታምኑት ይህ ድንጋይ ክቡር ነው፤ ለማያምኑት ግን፣ “ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣ እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ።” ⁸ ደግሞም፣ “ሰዎችን የሚያሰናክል፣ የሚጥላቸውም ዐለት ሆነ።” የሚሰናከሉት ቃሉን ባለመታዘዛቸው ነው፤ የተመደቡት ለዚህ ነውና። Good morning Ppl😊
Show all...
ቆላስይስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ፤ ² በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም። ³ ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና፤ Good morning Ppl😊
Show all...
Good morning Ppl😊
Show all...
1ኛ ዮሐንስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵-¹⁶ ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። ¹⁷ ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። Good morning Ppl😊
Show all...
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!