977
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-730 days
Posts Archive
ተቋማትን መገንባት ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ምን ፋይዳ አለው የተባለ እንደሆነ፥ ዘርፈ ብዙ አስተዋጽኦ ያለው ለመሆኑ ብዙ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል። የዓለም ባንክና የተባበሩት መንግሥታት ጥናት እንደሚያሳየው፥ የተቋማት አደረጃጀቶች ለድህነት ቅነሳ ከፍተኛ እገዛ ያደርጋሉ። የተቋማት ተጠናክሮ መውጣትም መሪዎች ሀገርን በሥርዓት እንዲመሩ፣ ሥልጣናቸውም ለግልጽነትና ለተጠያቂነት መርህ የገዛ እንዲሆን፣ እንዲሁም ከአንድ አሠራር ወደ ሌላ ሲሸጋገሩ በሕግ ብቻ እንዲመሩ ይረዳል፡፡
ስለሆነም፣ በተቋማት ላይ የሚደረጉ ማሻሻያዎች የሚከተሏቸው ሞዴሎች በጥንቃቄ ሊመረጡ ይገባል፡፡ ማሻሻያዎች ብሎም የተቋማት ግንባታ በነባራዊ ሁኔታዎች ብሎም በሀገራዊ እሳቤ የተቃኙ ሲሆኑም የተሻለ ውጤትን ያመጣሉ። እንደ ቀደመው ጊዜ ተቋማትን ለማሻሻልና ለማጠናከር የምዕራባውያንን መንገድ መጠቀም የግድ አይደለም።
የሀገረ መንግሥት ግንባታ ውጤታማ የሚሆነው በእያንዳንዱ ዜጋ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት ሲቻል ነው። ይህንም ለማድግ አሰባሳቢ ገዢ ትርክት መፍጠር ያስፈልጋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ያለፉትን ጥሩም ሆነ መጥፎ ታሪኮቻቸውን እንዳለ ተቀብለው፤ የተጣመመውን አቃንተው፤ የተሳሳተውን አስተካክለው፤ የወደፊቷን ኢትዮጵያ በጋራ ራዕያቸው አምሳል ለመገንባት፤ በእኩልነት እና በመከባበር ላይ የተመሠረተ አካታች ስርዓት ለመፍጠር መቁረጥ አለባቸው።
‹‹ትርክት ሆን ተብሎም ይሁን በተለምዶ በዓላማ የሚዘጋጅ ንግርት ነው›› ይላል፥ የዳንኤል ክብረት ‹‹የትርክት ዕዳና በረከት›› በተሰኘ መጽሐፉ። ነእናም ይቀጥላል፥
‹‹ለአንድ ወገን ዓላማ የተቀረጸ፣ ልዩነትንና ብዝኅነትን ያልተቀበለ፣ ማቀራረብና ማግባባት ዓላማው ያልሆነ፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን የማይፈጥር ትርክት፣ ባለፉት ዘመናት ኢትዮጵያን ብዙ ፈትኗታል። ብዙ ዋጋም አስከፍሏታል። ...የትርክቶቻችን መወላገድ ሀገራችን የሚያግባባ ትእምርት እንዳይኖራት አድርጓታል።
ሀገር የትርክት ውጤት ናት። ትርክታቸው ከመጻኢ ዕጣ ፋንታቸው ጋር የገጠመላቸው ሀገራት የሀገረ መንግሥት እና የብሔረ መንግሥት ግንባታቸውን አጠናቀው ኢኮኖሚያዊ ፉክክር እና ዕሳቤያቸው በሉላዊ የዓለም ማኅበረ ፖለቲካ ገዢ እንዲሆን እየተፋለሙ ይገኛሉ። ሀገራችን ለዚህ የሥነ መንግሥት ዑደት ገና ናት። ለምን ቢባል የተቃርኖ ትርክት በኅብር ከማደግ ይልቅ በጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት ማበጀታችን ዋጋ አስከፍሎናል"
(ገጽ 13)፡፡
ነጣጣይ ትርክቶችን በመሻገር፣ አሰባሳቢ ገዢ ትርክት የመፍጠር ጥረታችንን፤ ከተቋማት ማሻሻያ ሥራዎች ጎን ለጎን መከወን፤ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የላቀ አስተዋጽኦው አለው። የሚጋጩ ሕልሞችን ማስታረቅና፣ በአንዲት ሀገር ጥላ ስር የሚንኖር የእኛ ዜጎቹ እጣ ፋንታ የተያያዘና የማይነጠል መሆኑን በመረዳት፤ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የዜግነት ድርሻን ማበርከት ይኖርብናል። እናም አንዘናጋ!
መልካም አዲስ አመት ለሁላችንም።🙏🙏
(ለሚኖረው የፊደልና ስርአተ ነጥብ ግድፈቱ ይቅርታ እጠይቃለሁ።)🙏🙏
#አንዘናጋ❗️ #ነገ_ዛሬ_ነው_የሚሰራው❗️
ሀገረ መንግሥት፣ የጋራ ህልም ባለው ሕዝብና በጠንካራ ተቋማት ተገንብቶ በትውልድ ጥበብና ብርታት፤ በምሁራን ትጋት የሚጸና ነው። ሆኖም የሀገረ መንግሥት ግንባታ በአንድ ጀንበር ሥራ፣ በአንድ ትውልድ ኃላፊነት ወይም በአንድ ተቋም የተናጠል ጥረት የሚፈጠር ነገር አይደለም።
የሀገረ መንግሥት ግንባታ በዜጎች እና በዜጎች፤ በመንግሥት እና በዜጎች፤ እንዲሁም በአመራሮች እና በተቋማት መካከል ያለውን ትስስር ያጠናክራል። በአጠቃላይ ዜጎች ለሀገርና ለተቋማት ያላቸውን አመኔታ ያጠናክራል።
ኢትዮጵያ በተከታታይ ትውልዶች ሉዓላዊነቷን አስከብራ መዝለቅ ብትችልም፤ ለረጅም ዘመናት ተለጣጣቂነት የሌለው የፖለቲካ ሥርዓት የተፈራረቀባት ያልታደለች ሀገር ናት። በውጭ ጫና፣ በተሳሳቱ ‹‹የዘመናዊነት›› ግንዛቤዎችና በተዛቡ ትርክቶች የተነሳ፣ ጠንካራ ሀገራዊ ማንነትን መፍጠር የተሳናት ሀገር ሆና በመቆየቷ፤ አሁን እንደ አዲስ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የመገንባት እንቅስቃሴ ጀምራለች።
በሥልጣኔ ቀደምት ተብለው የሚጠሩ የአውሮፓ እና የእስያ ሀገራት ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ያለፉ ናቸው። ለዚህም እንደ ሁኔታቸው፣ ታሪካቸውና ግባቸው የተለያዩ መንገዶችን ተጠቅመዋል። ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የተለያዩ መንገዶች ወይም አካሄዶች አሉት። እነዚህም ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና የባህል ስልቶችን ያካተቱ ናቸው።
ለምሣሌ፣ ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታቸውን በኢኮኖሚ ልማት ላይ ከመሠረቱ ሀገራት መካከል ቻይና እንደ ጥሩ አብነት ትጠቀሳለች፡፡ ቻይና ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያዎችን ስትተገብር፣ በዋናነት በትራንስፖርት መስመሮችና በባቡር ሀዲዶች ዝርጋታ፤ እንዲሁም ከኃይል አቅርቦት ጋር በተገናኙ መሠረተ ልማቶች ላይ አተኩራለች። ይህም ለዜጎቿ የሥራ ዕድልን ከመፍጠሩም ባሻገር፣ የንግድ እና የገበያ ልማቷን ለማጠናከር አስችሏታል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትም ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታን በኢኮኖሚ ልማት ላይ ከመሠረቱ ሀገራት ተርታ የምትገኝ ናት። አረብ ኤምሬት፣ በነዳጅ ላይ የነበራትን ጥገኝነት በማስወገድ እና የኢኮኖሚ አማራጯን በማብዛት በቱሪዝም፣ በፋይናንስ እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ትኩረት አድርጋለች። በዚህም ስኬታማ ሆናለች። በተመሳሳይ፣ ደቡብ ኮርያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ጥናቶችን በማከናወንና ልማትን በማጠናከር ትኩረት አድርጋ ሰርታለች፡፡ በዚህም በኤሌክትሮኒክስ እና ቴሌኮምዩኒኬሽን ዘርፎች ትኩረት ያደረገ የማሻሻያ ሥራዎችን በመስራት በዘርፉ ግንባር ቀደም መሆን ችላለች።
ከምጣኔ ሀብት ሌላ ትምህርት እና የሰው ሀብት ልማትን መሠረት አድርገው ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ጥረት አድርገው የተሳካ ሥራ የሰሩ ሀገራት አሉ። በዜጎች ትምህርት ወይም ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባትን መርህ አድርገው ከሰሩ ሀገራት መካካል ፊንላድ እና ጀርመንን መጥቀስ ይቻላል።
ፊንላንድ የትምህርት ሥርዓቷን በማሻሻል እኩል የትምህርት ዕድል ለሁሉም በመስጠት ከፍተኛ ቁጥር ያለው የተማረ ዜጋ ብሎም ብቃት ያለው ሠራተኛ ማፍራት ችላለች። ጀርመንም የትምህርት ሥርዓቷን ጥምር በማድረግ (የክፍል ውስጥ ትምህርትን ከቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ጋር በማዋሃድ) የገበያውን ፍላጎት የተከተለ የሰው ኃይል በማቅረብ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሥራዋን ማከናወን ችላለች።
በሌላ በኩል፣ ማኅበራዊ ትስስርን እና አካታች ሥርዓት መፍጠርን የግንባታ መንገድ ያደረጉ አሉ፡፡ ለምሣሌ፣ እንደ ካናዳ ያሉ ሀገራት፣ ብዝኅ ባህልን እና አካታች ብሔራዊ ማንነትን በመፍጠር የሀገረ መንግስት ግንባታ ሥራቸውን ማሳካት የቻሉ ናቸው፡፡ እንደ ሕንድ እና ሲንጋፖር ያሉ ሀገራት ደግሞ፣ የዴሞክራሲ ተቋማትን በማጠናከር፣ የጸረ ሙስና እርምጃዎችን በመውሰድ እና አመራር ላይ በማተኮር የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሥራቸውን ሰርተዋል፡፡
በአጠቃላይ. ሀገራት ፍላጎታቸውን እና ያሉበትን ተጨባጭ ሁኔታ መሠረት አድርገው የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መንገዳቸውን መርጠዋል፣ ያንንም ተግብረዋል።
የኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የመገንባት ጥረት ትኩረት ያደረገው፤ በዘርፎች እና በተቋማት ሀገር በቀል የማሻሻያ እርምጃዎችን መውሰድ ላይ ነው። በርግጥ ይህን ጥረት ስታደርግ ዛሬ የመጀመሪያዋ አይደለም። በተለይም ‹‹የለውጥ ፋና ወጊዎች›› በታዩበት በሃያቸው መቶ ዓመት መባቻ፣ ጉልህ የማዘመን ጥረት ተስተውሏል።
ጥረቶቹ ግን ተቋማትን ከማዘመን ይልቅ ምዕራባዊ መልክ የማስያዝ ዝንባሌ ነበራቸው። ወደ አውሮፓ ሀገራት በመሄድ ተምረው የመጡ ምሁራን፣ ዘመናዊነትን የተረዱበት መንገድም ብዙ ችግር ነበረበት።
ይህን ነጥብ በተመለከተ፤ ባሕሩ ዘውዴ ‹‹ፋና ወጊ የለውጥ አቀንቃኞች በኢትዮጵያ›› በሚለው መጽሐፋቸው የሚከተለውን ያነሳሉ፥
[የአድዋ ድል] ኢትዮጵያን ከምዕራቡ ዓለም፣ በተለይም ከአውሮፓ ጋር የሚኖራትን የግንኙነት ስልት የወሰነ ነበር። በጥቂት የእስያና አፍሪቃ ሀገሮች ብቻ እንደታየው የፖለቲካ ነፃነት ተቀዳጅታ፣ ነገር ግን በተዘዋዋሪ መንገድ አህጉራቱ ላይ በተንሰራፋው የአውሮፓ ጫና ስር ወደቀች። ግብፅ፣ ኢራን፣ ታይላንድ፣ ቱርክና ጃፓን ከዚህ ተርታ የሚመደቡ ናቸው። እነዚህ ሀገራት ነፃነታቸውን አስከብረው ለመቀጠል ከፈለጉ አዲሱን ነባራዊ እውነታ የሚመጥን ማስተካከያ ማድረግ ነበረባቸው። በሌላ አነጋገር ራሳቸውን ማዘመን ነበረባቸው።
የማዘመን ልኬት ከምዕራቡ ዓለም በውሰት የመጣ በመሆኑም ዘመናዊነት አብዛኛውን ጊዜ ከምዕራባዊነት የማይለይ ሆነ። በዚህ ረገድ ጃፓን ራሷን ከማዘመን አልፋ አንዳንዴ የመስፈርቱ ባለቤት የሆነውን የምዕራቡን ዓለምም ለመብለጥ በመቻሏ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ’ነዚህ ከላይ ለተጠቀሱት ሀገሮች የስኬት ተምሳሌትና የማዘመን ሞዴል ሆና ታየች። ዒላማው የምዕራቡ ዓለም ቢሆንም፣ ተመራጩ ስልት የጃፓኑ ሆነ። ይሁን እንጂ እንደ ተአምር ይቆጠር የነበረውን የጃፓንን ስኬት ለመድገም የቻሉት ጥቂቶች ናቸው፣ ያውም ከተገኙ። (ገጽ 298)
በኋላም በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት ከፍተኛና ተስፋ ሰጭ ጥረቶች ተደርገው ነበር። እነዚህም የማኅበራዊና ፖለቲካዊ ለውጥ እንቅስቃሴዎች በ1928ቱ የፋሽስት ወረራ በአጭር ተቀጭተዋል። ከዚያም በኋላ በ1966 የርዕዮተ ዓለም ለውጥ በማድረግ የተሞከረው ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የመገንባት ጥረት ከሽፏል፡፡ የክሽፈቱ መንስኤ የለውጡ መሠረት ሀገር በቀል አለመሆኑ ነበር፡፡ እንዲህ ሆነን ከዛሬ ደርሰናል።
ቀደም ሲል እንደ ተጠቀሰው ‹‹ዘመናዊነት›› በ‹‹ምዕራባዊነት›› እየተጠለፈ፤ ‹‹ሀገር-በቀል›› ጉዳዮች ከ‹‹ኋላ ቀርነት›› ጋር አዛምዶ ማየት ችግር ጎልቶ ታይቷል፡፡ አሁን በትምህርት፣ በፍትሕ፣ በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በሲቪል ሰርቪስ ዘርፍ የተለያዩ ሪፎርሞችን በማድረግ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፥ ሀገር በቀል ሀብቷን መሠረት ማድረግን መርጣለች። አሠራሮች ለዜጎች በሚያመችና በሚስማማ መልኩ ሲዘረጉ፣ ተቋማትም በዛው እየተቃኙ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት መገንባት ይቻላል።
#ከፍ_ላለ_የዝቅታው_አይከብደውም❗️
(ምስጋና ለተቃዋሚም ለደጋፊም)
➖
እንኳን አየር መንገዳችን ተነካ!
ቀፏቸው የተነካባቸው ንቦች መሆናችንን በህብረት እና በቁጣ ጮኸን አሳየን! ይህ ነው ንቃት። ቢያንስ እንዲህ በጋራ “አይይ!!” የምንልበት የጋራ መልክ ማግኘት።
እሰይ!
አንድ የምንሆንበት አንድ ዐቢይ የጋራ ጉዳይ እንዳለን አፅንተን አሳየን። ያውም በከፍታ ላይ ባለው በአየርመንገዳችን አንድ ሆንን። በጣም ደስ ይላል። በከፍታው ላይ ከተስማማን፣ ዝቅ ያሉት ችግሮቻችን አያቅቱንም።
ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተጓዝኩ ጊዜ አውሮፕላኑ ለመነሳት ሲያኮበኩብ በመስኮቱ ቁልቁል መመልከት ጀመርኩ። ምድር ላይ ሳለሁ ከኔ የሚገዝፉ ነገሮች ሁሉ ቀስ በቀስ ትንንሽ እየሆኑ፣ እየደበዘዙ በዐይን የማይታዩ ደቃቆች ሆኑ። ቤቶች የአሸዋ ቅንጣት፣ መንደሮች ጠጠር አከሉ። ሀይቆች የብይ ጉድጓድ፣ ወንዞችና መንገዶች የደም ስር፣ ደኖችም የድንጋይ ሽበት ይመስላሉ። በክልሎች መካከል የሚታይ ወሰን በሀገራት መካከል የተሰመረ ድንበር የለም። ምድር ላይ ትልቅ የነበረው ሁሉ ከፍ ብለው ሲያዩት ያንሳል። ፅንፍና ፅንፍ የቆሙት ይቀራረባሉ። የተራራቁ የመሰሉት ይጠጋጋሉ። ከፍ ሲሉ ሺህ ቦታ ተበታትኖ የቆመ የመሰለው ሁሉ አንድ ይሆናል።
አየር መንገዳችን አንድ የንግድ ተቋም ብቻ አይደለም። ከፍ ብሎ በርሮ ከፍ የሚያደርገን ማንነታችን ነው። ከልዩነታችን በላይ መተሳሰራችንን የሚያበስር የምስራቻችን ነው። በጋራ የምንቆምለት ዓርማችን ነው። ባንዲራ ተሸካሚ አምባሳደራችን ነው። የጥራት እና የብቃት ምስክራችን ነው። ወደምዕተ ዐመት የሚጠጋ የስኬታማ ተቋማዊ ቅብብሎሻችን ማሳያ ነው።
ይህ ማለት መንገዱ ሁሉ ፍፁም፤ ታሪኩ ሁሉ እንከን አልባ ነው ማለት አይደለም። የአገልግሎት ዝንፈት እንደጉም ሊጋርደው ይችላል፣ የአሰራር ውሽንፍር ሊከሰትበት ይችላል፣ የአቋም መዋዠቅም ሊገጥመው ይችላል። ግን እንደንስር አርፎ ራሱን አድሶ ይነሳል እንጂ በፍፁም ወድቆ አይቀርም። ህይወት ለማትረፍ ሊዘገይ ቢችልም ዳግም መብረሩ አይቀርም። ቢዘገይ ይደርሳል። ቢቆምም ይነሳል።
(ለምሳሌ አውሮፕላን መጀመሪያ ኢትዮጵያ የገባ ጊዜ፣ በመጀመሪያው ከጅቡቲ አዲስ አበባ በረራ፣ ጉም አጋጥሞት ቢሾፍቱ አካባቢ ለማረፍ ተገዶ ነበር። ይህንን ታሪክ መርስኤ ሀዘን ወልደቂርቆስ የጻፉት የሀያኛው ክ/ዘመን መባቻ ላይ ማንበብ ይቻላል።)
በመጀመሪያ በረራው ግን አርፎና ፈርቶ አልቆመም። ስላልቆመም የዛሬው ከፍታ ላይ ገስግሶ ደረሰ።
ሰንደቅ ዓላማዋን ይዟልና፣ አየር መንገዳችን፣ ልክ እንደኢትዮጵያ በምክንያት ቢዘገይም፣ ከፍታው ላይ ከመድረስ የሚያስቆመው ምድራዊ ኃይል ግን የለም!
ሌላኛው የከፍታችን ማሳያ የሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድብም፣ እንደምንመለከተው፣ በጩኸቱና በጫጫታው ውስጥ ሁሉ ሳይቆም፣ ከከፍታው ላይ ደርሷል። ሌላኛው በጋራ የመቆሚያና መብረሪያ ከፍታችን ይመስለኛል። በዚህኛው ከፍታችንም አንዳችም ምድራዊ ሀይል እንደማያቆመን እያየን ነው። ታዲያ እንዲህ ከፍታውን ከቻልንበት፣ ዝቅታው እንዴት ሊከብደን? የምርም የከፍታ ዘመናችንን ያቅርብልን።
ክብር ለከፍታችን ለሰራችሁ ሁሉ!🙏🙏
#አፈሩን_በመንካት_እንታደገው
ምድሩንም እንጠብቀው❗️🌿🍀☘️
ሳድጉሩ የተባሉት ህንዳዊ መምህር፣ "አፈርን እናድን!" የሚል ዘመቻ ከጀመሩ ቆይተዋል፡፡ እኒህ ብልህ አዛውንት፣ ሳይንሳዊ መረጃዎችን እየጠቀሱ "አፈር ከሌለ ሰው የለም" ይላሉ።
ታዲያ መፍትሔውስ ምንድነው?
ዛፍ መትከል! ስለዚህ የምድር ህልውና የሆነውን አፈር ለመጠበቅ፣ አፈር እንንካና ምድራችንን እንታደግ።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ትርጉሙም ይኸው ነው!
አፈር መንካት!
ዛፍ መትከል!
አገራችንም አረንጓዴ ዘመቻ ከጀመረች፣ አምስት አመታት አልፏታል። እስከዛሬ ቢሊየን ችግኞችን ተክላ፣ በአጠቃላይ ተጨማሪ ቢሊየኖችን ለመትከል እየሰራች ነው። ለዚህ የተቀደሰ አርበኝነት እንረባረብ። ኢትዮጵያም በምትኩ አረንጓዴ ጀግኖቿን ሁሌ ታመሰግናለች። ተመን አልባ አሻራቸውንም ትመዘግባለች።
#አረንጓዴአሻራ #Greenlegacyethiopia
#ስልጣኔ____101🌿
አንዱ ሲተክል፣ ሌላው የሚነቅልበት፣
አንዱ ሲያጸድቅ፣ ሌላው በመኪና የሚጨፈልቅበት፣
አንዱ ሲያጸዳ፣ ሌላው የሚያቆሽሽበት፣
አንዱ ሲገነባ፣ ሌላው የሚያፈርስበት
አንዱ ቆሻሻ ሲያነሳ፣ ሌላው ቆሻሻ የሚጥልበት
አንዱ ሲያሳምር፣ ሌላው የሚሸናበት
አንዱ ጉድጓድ ሲሞላ፣ ሌላው ጉድጓድ የሚቆፍርበት ሀገር
ሀገር አይሆንም!
አይበለጽግም!
አይሰለጥንም!
ሀገር ሀገር የሚሆነው እንዲህ ባለው የመልካም ዘመቻ ተቃውሞ ነው። ኑ እየተከላቹ ተቃወሙ! ይህ ስልጣኔ 101 ነው።🙏
አረንጓዴ_መልዕክት__ለወዳጅም_ለጠላትም❗️
➖
ሥርዓት እና ነገስታት ይለዋወጣሉ። አይደለም ዙፋናቸው መናገሻ ከተማቸውም ሊቀየር ይችላል። ኅውልታቸው የድንጋይ ክምር፣ ቤተመንግስታቸው ግምጃ ቤት የሆኑባቸው ነጋሢያን ጥቂት አይደሉም። ሥርዓት ሲለወጥ የቋንቋ ዘዬ፣ የተለመዱ ቃላትና ሐረጋት እንደ ደረቀ ቅጠል ይረግፋሉ።
ጃንሆይን ከዙፋናቸው ያወረደው ወታደራዊ ስርዓት የሞዐ አንበሳ አርማቸውን እያደነ ከከተማና ከገጠሩ አጽድቶ በራሱ ሶሻሊስታዊ አርማ ተካ። ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲወጣ የደርግ መመኪያ የነበረው የሌኒን ግዙፍ ሐውልት ከስፍራው ተፈነቀለ።
ድጋፋችንን በመገንባት እያሳየን ተቃውሟችንን በማፍረስ ስንገልጽ እንደመኖራችን... እንደወንድምነቴ ስርዓት በሄደ ቁጥር የማይፈርስ... በመጣ ቁጥር የማይቀለስ... ዝንታለም የማይነቃነቅ ተፈጥሯዊ ሐውልት እስኪ ልጠቁማችሁ። ዶክተር ዐብይን የምትደግፉና የምትቃወሙ ሰዎችን እና ልጆቻቸውን... የልጅ ልጆቻቸውንም ጭምር እኩል የሚጠቅምና የትውልድ ተስፋ የሚሆን የመቃወሚያና የመደገፊያ ዘዴ ጀባ ልበላችሁ!
1. መሪውን ለምትደግፉት
የዶክተር ዐብይ አርማ ተፈጥሯዊ ነው።
እናም ዶክተር ዐብይ ዓርማው አረንጓዴ አካባቢና ንጹህና የተጠበቀ ተፈጥሮ ነው። ለቀድሞ ነገስታት አንበሳ፣ ለ"ያ ትውልድ" ቀዩ ኮከብ በበጎም ሆነ በክፉ መታወሻቸው እንደሆነ ሁሉ ዶክተር ዐብይ በታሪክ ከሚታወስባቸው እልፍ አዕላፍ አርማዎች ውስጥ ደማቁ ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ ያለው ራዕይ ነው።
እናም የምትደግፉት ሕልሙን እውን አድርጉለት። ችግኝ ትከሉ!
የሚተክለው ችግኝ ብቻ እንዳይመስላችሁ! ትውልድ ነው። ህልም ነው። ሀገር ነው። አህጉር ነው። ምግባር ነው። አየር ነው። ምግብ ነው።
2. የምትቃወሙት
ኢትዮጵያውያን በታሪካችን የምንለያይበትንና የምንደጋገፍበትን ጠንቅቀን የምናውቅ ሕዝብ ነን። በሚያለያየው እንደምንለያይ ሁሉ በሚያስተባብረው ለመተባበር አናመነታም። በእርስ በርስ ጦርነትና በስልጣን ፍትጊያ ተወጥረን ባለንበት ሰዓት እንኳ ሀገራችንን ሊቀማን ለመጣ ወራሪ ተባብረን በአንድ ክንድ መክተን በተደጋጋሚ ድል አድርገናል።
እስከዛሬ ሕዝባችንን ከጫፍ ጫፍ ያስተባበሩ ሑነቶች ባብዛኛው ጦርነት፣ ርሃብና በሽታ ነበሩ። ግን እስከመቼ ለችግር ብቻ እንተባበራለን? ለተስፋ ብንተባበርስ! ለሕልምና ለራዕይ ለሀገርና ለትውልድ ብንተባበርስ?
የፖለቲካ መሻኮቻ ብዙ ሜዳ አለ። በእምነት በብሄርና በጾታ ያለንን ልዩነት የምንገልጽበትም መስክ አለን። ተፈጥሮን ግን ለድርድር አናቅርባት፥ ለመቃወምም ለመተቸትም ለመሄስም መጀመሪያ ሕዝብና ሀገር ተከታይ ትውልድም ያስፈልጋል!
እና ዶክተር ዐብይን የምንቃወም በተፈጥሮ አንቃወመው! ተቃውሟችንን በወንዞች ጽዳት፥ በችግኝ ተከላና በሌሎች የተፈጥሮ መጠበቂያ ራዕዮች ማሰማት የታሪክ ጉድፍነት ነው! መሰልጠን ሜዳና መስኩን መለየት ነው። የተቃውሞና የድጋፍ የትችትና የሙገሳ መንገዶችን ከሕልውና መነጠል ነው። የችግኝ ተከላ ጉዳይ በፖለቲካ የሚታጠር አይደለም። የመኖርና ያለመኖር፣ የመጥፋትና የመቀጠል ጉዳይ ነው።
ዐብይን የምትጠሉት፣ የምትጠራጠሩት፣ የምትቃወሙት ሁላችሁ ችግኝ ትከሉ። ተፈጥሮን ከፖለቲካ ለዩ። በዚያውም ታሪክ ተጋሩ። ይህ ወቅት ኢትዮጵያ በችግር በምትጠራበት የዓለም አቀፍ ሚዲያ ላይ በችግኝ ተከላ ዘመቻና ሪከርድ የምትጠራበት የድል ወቅት ነው። እና የምትቃወሙት ጭምር ይህንን የሀገር ታሪክና ድል ተጋሩት!
(በድጋሚ የተለጠፈ)🙏🙏
#ወግ_እና_ወክ #Walk_and_talk❗️
ይኸው ደግሞ በሌላ አዲስ ቅርፅ፣ አዲስ
ሙከራ የሸራተኑ መንገድ ላይ፣ አዲስ ነገር ይዘን ብቅ ብለናል።
#ZCEOወግእናወክ👇🏾👇🏾
የሸራተኑ መንገድ ሚስጥር | ወግ እና ወክ | ክፍል 1
ፈርዶብን እኛ ሁሉንም ነገራችንን “የመጀመሪያው” እያልን መጎረር እንወዳለን' ይሉናል።
እኔ ግን እላለሁ! ለማለት ሳይሆን እውነት ስለሆነ ነው። ይህ ሙከራዬ አዲስም የመጀመሪያም ነው። የማንንም የማይመስል አዲስ ሙከራ። ሙከራው ግን አይረባ ይሆናል። አልተሟላ ይሆናል። ግን አዲስም የመጀመሪያም ሙከራ ነው።
በተለይ ጎበዝ ዳይሬክተርና የተሻለ የጊዜ ነፃነት ኖሮን ቢሆን፣ ያለምነውን ከዚህ በተሻለ ምልአት ማቅረብ በቻልን ነበር።
ጉራችንም ከዚህ ደመቅ ባለ ነበር😁😂
አሁን የሚታየው ሙከራ፣ ከአራት አመት በፊት ተጀምሮ፣ ከዘጠኝ ወራት በፊት ደግሞ በሌላ ሙከራ ታጅቦ፣ ከሰሞኑ ደግሞ ተበያይዶ፣ ዛሬ እንዲወጣ የተፈረደበት፡ የቀደመ አሮጌ ሙከራ ነው። ታዲያ ይህ ተሰርተው ካለቁ ደርዘን የሚሆኑ የአንድ ሲዝን ሙከራዎች ውስጥ፣ አንዱ ስራ ነው። ይህንን ተከትለው በተከታታይ ወደናንተ ይደርሳሉ።
ደግሞም ፍለጋ ነው። የጠፉትን ብቻ ሳይሆን፣ የሚሆኑንን፣ የምንወዳቸውን አሰራሮች እና አቀራረቦችም ፍለጋ ነው። በተከታታይ የምታዩአቸው ስራዎች፣ እኛንም ጭምር ስንፈልግ የምትመለከቱባቸው ናቸው።
ደግሞም እውነት ናቸው። Reality N truth ልንለውም እንችላለን።
እንደ ወጉ ቢሆን፣ እንዲህ ያለው ስራ፡ በሆቴልና አዳራሽ አጀብ በታጀበ ነበር። ግን ደግሞ እኔ ከሱ በጣም ሩቅም፡ ባዳም ስለሆንኩ፣ ሙከራዬን የመወርወር ግዴታ ብቻ እንዳለብኝ ነው የማምነው። እናም ዛሬም አዲሱን ሙከራ ከምሽቱ ሶስት ሰአት ላይ፣ በሀሳብ ሜዳ የዩቲዩብ ቻናል ላይ በቀጥታ ይጠብቁት። ለምታዩም ለማታዩም፣ አይታችሁ ሀሳብና ትችታችሁን ለምትልኩልን ሁሉ፡ ከወዲሁ እናመሰግናለን።🙏🙏
#ZCEOReality
Z CEO ... Reality ... ቀለል ያሉት ደማቆች
#ዛሬሊለቀቅነው❗️
ዛሬ ማታ ለዓመታት የያዝኩትን የአሻራዬን ዘር ልበትን ነው! ምክንያቱም የገጣሚው የደበበ ሰይፉ ቃል አለብኝ።
«የተልእኮህን አባዜ
የህይወትህን ቃል ኑዛዜ
ወርውር
የእጅህን ዘገር
በትን !
ያሻራህን ዘር
ይዘኸው እንዳትቀበር።»
እንዳለው፣ ዛሬ አሮጌም፣ አዲስም፣ የመጀመሪያም የሆነውን ሙከራዬን ይዤው፣ ላለመቀበር ወደእናንተ ልበትነው ነው።
+3
#አልሀምዱሊላህ❗️❗️
እንዲህ ብለን እንጀምራለን። በህይወታችን ምእራፍ ላይ: በቁጥር አንድ ደምቆ የተፃፈ ስኬት።
ሊረፍድብን ይችል ነበር። ሊያመልጠንም ይችል ነበር። አላህ ግን በመጨረሻም ትልቁን እድል ለኛ ለልጆቹ ሰጠን። ሳይረፍድብን ታደገን። ብሌናችን የሆነው እናትና አባታችንን ሀጅ ለማስደረግ አላህ ወፈቀን። ካንተ በላይ እኛ ልጆችህ ነን ተጠቃሚዎቹም ተደሳቾቹም። አላህ ባንተ በኩል ላደረገልንም: ለሚያደርግልንም ሀምድ እናስገባለን። አልሀምዱሊላህ! ሼህ ሀሰን አወል ከእንግዲህ ሀጂ ተብለው ይጠራሉ።
ደግሞ ደግሞ ሳልናገር! የአባት ገንዘብ ለካ ሁሌም ይጣፍጣል። ከላይ እስከታች የለበስኩትንንና የተጫማሁትን እሱ ነው ገዝቶ ያመጣልኝ። ልክ እንደልጅነቴ እየቦረቅኩ ነው ደጋግሜ የምለብሰው😁😁 ያው አባት ሁሌም አባት አይደል።
ስለሆንክልን ሁሉ ዘላለም ስናመሰግንህ እንኖራለን ውዳችን። 🙏
#ጅል⁉️
እውቁ ናይጄሪያዊ ደራሲ ቺኑዋ አቼቤ፣ የሚከተለውን ተረት አጫወተን።
ከእለታት በአንዱ ቀን፣ አንድ አይጥ አልማዝ ዋጠ።
የአልማዙ ባለቤትም በድንጋጤ ሊሞት ነበር።
በሩጫ ሄዶ፣ አንድ ሰው ጠራና፣ "ያን አይጥ ግደልልኝ" አለው።
ሰውየው በግስጋሴ መጥቶ ቢያይ፣ አንድ ሺህ አይጦች ይርመሰመሳሉ።
አንዱ አይጥ፣ ከሌሎቹ ነጠል ብሎ ብቻውን ተቀምጧል።
ሄዶ ይህን አይጥ ገደለው!
ተከፍቶ ቢታይ፣ እውነትም አልማዙን የዋጠው ይህ አይጥ ነው። የአልማዙ ባለቤት ተደንቆ፣
“እንዴት ልትለየው ቻልክ?” አለው።
ሰውየውም መለሰ፡
“ጅሎች ሀብት ሲያገኙ፣ ከሌሎች ጋር አይቀላቀሉም!”🙏
+3
#የጎርጎራ_አርበኞች❗️
ከሁሉም በላይ ... ትናንታችን የተቀበረበት ቦታ ላይ፣ ነገአችንን ለማነፅ የሚተጉ ብርቱዎችን አይቼ፣ ዳስሼ፣ እጄን ለክብር ከፍ አድርጌው፤ በዛውም አፌ ላይ በግርምት ጫንኩት።
ከዚያ የተረጋጋ ሀይቅ የወጣ ወንዝ ያመጣቸው ግንዶች ባህር ማዶ ተሻግረው፣ ከጠላቶቻችን ጋር ተናብበው፣ ከየጢሻው ተጠራርተው ፌስቡክ ላይ ተንጋግተው የሚጮኹት፣ የዚያን ታላቅ ህዝብ ጩኸት እንዳልሆነም በአይኔ በብረቱ አይቼ አረጋግጬ ነው የተመለስኩት። እናመሰግናለን አርበኞቻችን።🙏🙏
+6
#በጎርጎራ_መመረቅ … ስለ ታሪኩ እና እውቅናው⁉️
ጎርጎራን አይቼ ቀረሁ። ተመለስኩ ብል ውሸት ይሆንብኛል። ታሪካችን ከተቀበረበት ቦታ ላይ ታሪክ ሲሰራ አይቼ ጉድ አልኩ። የተሰራውን እፁብ ድንቅ ፕሮጀክት የማደንቅበት ቃል አጣሁ። ስንቱን ፈተና ተቋቁመው፣ ሌት ከቀን ላባቸውን እያንጠፈጠፉ የነገዋን ታላቅ ሀገር የሚገነቡ ጀግኖች አይቼ ለመተረክ ጓጓሁ። እኛ ሚዲያዎች ከዚህ ሁሉ ተዓምራዊ አሻራ፣ ከዚህ ታሪክ ሰሪ ትውልድ እኩል እየተጓዘ መዘገብ ባለመቻሉ በእኔና በሁሉም የሀገራችን ሚዲያዎች አዘንኩ።
እየተዘዋወርኩ ከባልደረቦቼ ጋር ካሜራዎቼን፣ ማስታወሻዎቼን፣ መቅረፀ ድምፆቼን እስከ አፍጢማቸው ሞልቼ፣ ከጎርጎራ
ስመለስ ጉድ ጠበቀኝ! ሚዲያዎች እውቅና ተሰጥቷችኋል ተባልኩኝ። ጉድ ተሰራሁ።
በቅድሚያ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እጅ ዋንጫ የሚያሸልም፣ የብቃት ደረጃ ላይ ባንደርስም፣ ለተስፋችን እውቅና ስለተሰጠን፣ በታላቅ ትህትና እና የሀላፊነት ስሜት በጣም እናመሰግናለን።
ቢሆንም ለሀገራችን ሚዲያዎች እውቅና የተሰጠን፣ ለብቃታችን ሳይሆን፣ ለጥረታችን እንደሆነ እረዳለሁ። የሚዲያው ኢንዱስትሪም በህዝባችን ጥቅም፣ በሀገራችን ታሪክና ሀብት፣ ብሎም ልንገነባው በሚገባን ሀገራዊ ትርክት ልክ፣ እየተንቀሳቀሰ ነው ብዬም አላምንም። ስለዚህ ለሚዲያዎች የተሰጠን እውቅና፣ ሰርተን ስናተርፍ የምንከፍለው እዳችን ነው።
በሞያዊና በሀገራዊ ሀላፊነት ምክንያት፣ ከከተማ ርቄ ስለተመለስኩኝ፣ የእውቅናውን ስነስርዓት መታደም ባልችልም፣ ከዶ/ር ዐቢይ እጅ ዋንጫውን ለመቀበል ባልታደልም፣ ለተሰጠን ድጋፍ ሁሉ፣ በመላው የአዲስ ዋልታ ቤተሰብ እና በራሴ ስም ከልብ አመሰግናለሁ!! ይህ በራሱ ክብር ነው።
ጋዜጠኛ መሀመድ ሀሰን🙏
... ከወደቡ ስንቃረብ ውሃውን እየሰነጠቀ የሚጓዘው መርከብ ሞተሩን አጥፍቶ በለሆሳስ ይተም ጀመር፡፡
ጎርጎራ በህብረ ቀለም ተሸልሞ በአፍታ ብልጭታ ጠፈሩን በብርሃን ጎርፍ የሚያስጌጥ ‹‹ኖቫ›› ሆና ታየችኝ፡፡ ነገሩ ሁሉ ስዕል እንጂ እውን አይመስልም፡፡
በያሬድ ዝማሬ፣ በጥላሁን ዜማ፣ በአፈወርቅ ብሩሽ፣ በጸጋዬ ቅኔ፣ በገብረ ክርስቶስ ክርታስ፣ በድማሙ ብዕረኛ በመንግስቱ ለማ እና በደበበ ሰይፉ ስንኞች ያልተደፈረ ድንግል ውበት አየሁ፡፡ እንደ ጸጋዬ ‹‹አብረን ዝም እንበል›› ከማለት ወጪ ሌላ ዕድል አልነበረም፡፡ ጎርጎራ የጸጋዬ ‹‹አብርን ዝም እንበል›› ቅኔ ናት፡፡
መርከቡ ደምጹን አጥፍቶ ወደ ወደቡ ሲቀርብ፤ የሚሰማኝ በመርከቡ የሚገፋው የጣና ድምጽ ብቻ ነበር፡፡ ከመርከቡ ሆኜ ያየኋትን ጎርጎራ፤ እንደ ጥላሁን ዜማ:
"ማን ብዬ ስምሽን ልጥራው፤
የእኔን ልብ ግራ ገባው፤
ንገሪኝ ልወቀው፣ እቱ ስምሽ ማነው?" አልኳት፡፡
"አብረን ዝም እንበል" አለችኝ፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ...🙏
