cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

TIKVAH-ETHIO

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
456
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#Wallpaper #Sunset
Show all...
🌅🌅More Wallpaper 🌇🌇
👉JOIN👈
የቀድሞ ሰራዊት አባላት ጥሪ ተደረገላቸው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ፥ ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት ሰራዊቱን እንዲቀላቀሉ በዛሬው ዕለት ጥሪ አቀረበ። የመከላከያ ሰራዊት ባወጣው ጥሪ ፥ " በሀገራችን እየተደረገ ያለውን ሃገርን የማፍረስ ሴራን በማክሸፍ አገርን የማዳን ዘመቻ ላይ ባላቸው እውቀት ልምድ እና አቅም ከአገር መከላከያ ሠራዊት ጎን በመሰለፍ ይህ አፍራሽ ሃይል እስኪደመሰስ ድረስ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት ባላቸው ተነሳሽነት ከሀገር መከላከያ ጎን በመቆም አቅማቸውና እውቀታቸው የፈቀደውን አስዋፅኦ ለማበርከት ጥያቄ አቅርበዋል " ብሏል። በዚሁ መሠረት ይህን ተልዕኮ መወጣት የሚያስችል አካላዊ ሁኔታ ፣ የጤና ፣ የስነ - አእምሮ ዝግጁነት ፣ እውቀትና ልምድ ያላቸውን አባላት የወጣውን መስፈርት የሚያሟሉ የቀድሞ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ሰራዊቱን እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቀርቦላቸዋል። የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት የሀገር መከላከያን እንዲቀላቀሉ ለቀረበው ጥሪ ሊያሟሉ ይገባቸዋል የተባሉት አጠቃላይ መስፈርቶች ዝርዝር ከላይ በምስሉ ተያይዟል። @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...
የ12ኛ ክፍል ፈተና ከጥቅምት 29 ጀምሮ ይሰጣል። የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጄንሲ የ2013 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል የአጠቃላይ ትምህርት ማጠናቀቅያ ፈተና (የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና) ከጥቅምት 29 - ህዳር 2/2014 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ገልጿል። የብሄራዊ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናው በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ የሚሰጥ መሆኑን በማወቅ በተረጋጋ ስነ-ልቦና ቅድመ-ዝግጅታቸውን እንዲያደርጉ ኤጀንሲው አሳስቧል። በሌላ በኩል ፥ አጠቃላይ የፈተናውን ቅድመ ዝግጅት እና አጠቃላይ ሁኔታ በተመለከተ ነገ ቅዳሜ ከሰዓት 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በኤጀንሲው ተወካይ ዋና ዳይሬክተር በኩል መግለጫ ይሰጣል። @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...
#SNNPRS በደቡብ ክልል መሳሪያ የታጠቀ ግለሰብ በ5 ቀናት ውስጥ እንዲያስመዘግብ ጥሪ ቀረበ። ይህ ጥሪ የተላለፈው በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ትናንት ያካሔዱትን ውይይት መድረክ ተከትሎ ነው። በዚህም መሰረት ማንኛውም የጦር መሳሪያ የታጠቀ አካል ከዛሬ ከጥቅምት 26 ቀን ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ቀናት በአካባቢው በሚገኙ የፖሊስ ጣቢያዎች ቀርቦ ማስመዝገብ ይኖርበታል ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪ ማንኛውም #መታወቂያ የሚሰጥ አካል አዲስ መታወቂያ መስጠት አልያም የመታወቂያ እድሳት ማካሔድ ክልክል መሆኑ ተገልጿል። አስቸጋሪ ሁኔታ ቢፈጠር እና መታወቂያ ማግኘት ግዴታ ሆኖ ከተገኘ ግን የክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ መምሪያ እዝ አውቆት ውሳኔ ሊሰጥበት ይችላል ተብሏል። መረጃው ከደቡብ ክልል ኮሚኒኬሽን ያገኘነው ነው። @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...
#AddisAbaba በእጃቹ ያለውን መሳሪያ እስከ ጥቅምት 27 / 2014 ደረስ ማስመዝገብ ትችላላችሁ። የአዲስ አበባ ፖሊስ በተለያዩ ምክንያቶች የጦር መሳሪያ ምዝገባው እስከ ጥቅምት 27 ቀን 2014 ዓ/ም በድጋሚ መራዘሙን አሳውቋል። የጦር መሳሪያ በእጁ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብ በአስራ አንዱ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያዎችና በሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች በግንባር በመገኘት እንዲያስመዘግብ መልዕክት መተላለፉን ተከትሎ በርካታ ግለሰቦች በእጃቸው ላይ የሚገኝን የጦር መሳሪያ ለተከታታይ 3 ቀናት ማስመዝገባቸው ተገልጿል። መሳሪያ በእጃቸው ላይ ያለ ሰዎች የማስመዝገብ ፍላጎቱ እያላቸው የምዝገባ ቀኑ በማጠሩ ፣ ያላቸውን የጦር መሳሪያ ሌላ ቦታ በማስቀመጣቸው እና ማስመዝገብ እንደሚቻል በቂ መረጃ ያልሰሙ ግለሰቦች በመኖራቸው ምክንያት ምዝገባው እስከ ጥቅምት 27 ቀን 2014 ዓ/ም መራዘሙ ተገልጿል። በእጁ ላይ የሚገኝ የጦር መሳሪያ ያላስመዘገበ ማንኛውም ግለሰብ የተጨመረውን ቀን ተጠቅሞ እንዲያስመዘግብ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል። @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...
#ETHIOPIA ማንኛውም የፀጥታ ችግር እንቅስቃሴ ሲመለከቱ ወይም ደግሞ ጥቆማ ለመስጠት ከፈለጉ ከላይ በተቀመጡት የስልክ መስመሮች ፈጥነው እንዲደውሉ የፌዴራል ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል። #ሼር #Share @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...
#AddisAbaba የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ተጨማሪ አዳዲስ የደንብ ልብሶችን ስራ ላይ ማዋሉን ዛሬ አሳውቋል። ነባሩን የደንብ ልብስ መጠቀም ማቆሙን ተቋሙ ገልጿል፡፡ ከዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ አዳዲሶቹ የደንብ አልባሳትን ብቻ መጠቀም እንደሚገባ እና ነባሩ የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ መቀየሩ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ፖሊስ አሮጌውን የደንብ ልብስ ለብሶ የተገኘ አመራር እና አባል ላይ ጠንከር ያለ የዲስፕሊን እርምጃ ይወሰድበታል ተብሏል። ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት አሮጌው የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ በአዳዲሶቹ መቀየሩን ተገንዝበው አሮጌውን የደንብ ልብስ የለበሰ የፖሊስ አባል ሲያጋጥማቸው መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል። በተጨማሪም የአዲስ አበባ ፖሊስ ስራ ላይ ካዋላቸው አዳዲስ የደንብ አልባሳት ጋር ወይም ከሌሎች የፀጥታ አካላት የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ዩኒፎርም መጠቀም ክልክል መሆኑ በህግ የተደገገ ስለሆነ ከአ/አ ፖሊስ የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ዩኒፎርም የሚጠቀሙ አካላት ማስተካከያ እንዲያደርጉ ተቋሙ መልዕክቱን አስተላልፏል። #AddisAbabaPolice #Share #ሼር @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...
ዕለታዊ የኮቪድ-19 ሪፖርት #Ethiopia ፦ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 15 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 7,341 የላብራቶሪ ምርመራ 327 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል። የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 420 ሰዎች በፅኑ ታመዋል። #ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...
#የመንግስት_ማስጠንቀቂያ የኢትዮጵያ መንግስት ሀገርን ለማፍረስ የተጠመዱ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠነቀቀ። ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ያወጣው የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሀገርን ለማፍረስ የተጠመዱ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ሲል አስጠንቅቋል። መንግስት በመግለጫው "የሽብር ቡድኑ ማሽኖችና በሽርክና የሚሰሩ ሚዲያዎች የሽብር ወሬ እያሰራጩ ናቸው" ብሏል። ቁልፍ ኢላማቸው ደግሞ በአመራሩና ፣ በህዝቡና በወገን ጦር መካከል ጥርጣሬ እንዲፈጠር ፍርሃትም እንዲነግስ ማሸበር ነው ሲል ገልጿል። በተለያየ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ያሉ ተላላኪዎቻቸው የፀጥታ ችግር እንዳለ በማስመሰል የግል ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ የማግባባት ስራ እየሰሩ ይገኛሉም ብሏል። በህዝቡና በወገኑ ጦር ውስጥ ጥርጣሪዎችን ለመፍጠር የመንግስት ባለስልጣናት ቪዛ እየጠየቁ ነው በሚል የውሸት ፕሮፓጋንዳ እየነዙ ናቸውም ሲል ገልጿል። የመንግስት ኮሚኒኬሽን በመግለጫው ከዲፕሎማሲ መርህ ውጪ የአንዳንድ ሃገር ኤምባሲዎች አዲስ አበባ እንደ ተከበበች በማስመሰልና ያሰቡት ውጥን እንዲሳካ በኤምባሲያቸው የሚሰሩ ዜጎቻቸው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እያሳሰቡ ይገኛሉ ብሏል። በእንዲህ አይነት መንገድ ሀገርን ለማፍረስ የተጠመዱ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ያሳሰበው መንግስት በሀገር ጉዳይ ቀልድ የለምና ከድርጊቱ ባልተቆጠቡት ላይ የማያዳግም ርምጃ ይወሰዳል ሲል አስጠንቅቋል። * ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...
" የጦር መሳሪያ የጫነ ተሽከርካሪ ወደ ሆሳዕና ከተማ ገብቷል ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው " - የሀዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሀዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ ጥቅምት 24/2014 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት አካባቢ መነሻውን ከአዲስ አበባ ያደረገ ኮድ 3 ሰሌዳ ቁጥር 19331 ደ.ህ የሆነ ተሽከርካሪ የጦር መሳሪያ ጭኖ በወልቂጤ ከተማ በኩል ወደ በሆሳዕና ገብቷል ተብሎ የሚሰራጨው ወሬ ሀሰት መሆኑን ገልጿል። ይሁንና ተሽከርካሪው በፍጥነት እያሽከረከረ ስለነበረ ሆሳዕና ከተማ ናረሞ አከባቢ በስራ ላይ የነበሩ ትራፊክ ፖሊሶች ለማስቆም ሲሞክሩ ጥሶ በማለፍ በ2 ሞተረኞች ላይ የአካል ጉዳት አድርሷል። አሽከርካሪው ጉዳት አድርሶ ለማምለጥ ጥረት ቢያደርግም በአከባቢው ህበረተሰብና በፀጥታ አካላት ትብብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገልጿል። በተጎጂዎቹም ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት በመድረሱ በንግስት እሌኒ መህመድ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው። ጉዳቱን ባደረሰው አሽከርካሪ ምርመራ በማድረግ የማጣራት ስራ እያከናወነ ይገኛል። ጉዳዩ ይህ ቢሆንም የጦር መሳሪያ የጫነ ተሽከርካሪ ወደ ሆሳዕና ገብቷል ተብሎ የሀሰት መረጃ የተሰራጨ ሲሆን ፖሊስ መረጃው ሀሰተኛ ነው ብሏል። ህብረተሰቡ ትክክለኛነቱ ባልተረጋገጠ ወሬ ሳይረበሽ አካባቢውን ከፀጥታ አካለት ጋር በመተባበር በመጠበቅ ወንጀልን በጋራ እንዲከላከል ጥሪ ቀርቧል። ነዋሪዎች ማንኛውም ጥርጣሬ ውስጥ የሚያስገባ ነገር ካጋጠማቸው 046550330 በመደወል ለፖሊስ መረጃ እንዲሰጡ ተጠይቋል። (የሀዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ) @ETHIO_TIKVHA @ETHIO_TIKVHA
Show all...