ማህደር ሚድያ ⛪️
Open in Telegram
ይህ ቻናል የ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማራጪ ሚድያ በመሆኑ አለማቀፍ የመረጃ ስርጪት ላይ በትጋት ይሰራል።®@ማህደረ መገናኛ ብዙኃን
Show more1 695
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 695
በሲነርጂ ሀበሻ ፊልምና ኮሚኒኬሽን በመዘጋጀት ላይ የሚገኘው የሰማዕቱ ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ፊልም ጽሑፍ በሊቃውንት ጉባኤ እንዲመረመር ታዘዘ !
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜
ኅዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ)
@የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ሲነርጂ ፊልምና ኮሚኒኬሽን በኢትዮጵያዊው ሰማዕት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሊቀ ጳጳስ የስማዕትነት ተጋድሎ ዙሪያ የሚያጠነጥን ፊልም ለመስራት የሚያደርገው እንቅስቃሴታሪክን የሚያጎድፍ ሆኖ ስለተገኘ ሊቆም እንደሚገባ በመግለጽ ኅዳር 25 ቀን 2016ዓ.ም በቁጥር 1673/2789/2016 በተጻፈ ደብዳቤ መግለጹ ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ የፊልሙ ጸሐፊ እና ዳይሬክተር ሞገስ ታፈሰ ዶ/ር እየተዘጋጀ የሚገኘውን ፊልም ቤተክርስቲያናችን በሊቃውንቶቿ አማካኝነት መርምራ፣ የሚታረም ካለ አርማና የሚቃናውን አቅንታ በምትሰጠን አስተያየትና ማስተካከያ መሠረት ፊልሙን የምንሠራ መሆኑ ታውቆ አስፈላጊው ትብብር ሁሉ ይደረግልን። በማለት በጽሑፍና በአካል ጠቅላይ ቤተ ክህነት በመገኘት በፊልሙ ዝግጅት ዙሪያ ማብራሪያ በመስጠት ለተፈጠረው የመረጃ ክፍተት ይቅርታ ጠይቀዋል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም ዶ/ር ሞገስ ታፈሰ ያቀረቡትን ይቅርታ በመቀበል በአካልና በጽሑፍ በፊልሙ ጽሑፍ ዝግጅት ዙሪያ መረጃ ከመስጠት ባለፈ በቤተ ክርስቲያናችን በኩል የፊልሙ ጽሑፍ እንዲመረመርላቸውና እርማት በሚያስፈልገው ጉዳይ ዙሪያ እርማት እንዲደረግበት መጠየቃቸው የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህን ተከትሎም የፊልም ጽሑፉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ጉባኤ በሚገባ ተመርምሮና መታረም ያለበት ሁሉ ታርሞ እንዲቀርብ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ መመሪያ የተሰጠ ሲሆን የፊልም ጽሑፉም በሊቃውንት ጉባኤ እየተመረመረ መሆኑ ታውቋል። ሊቃውንት ጉባኤ የፊልሙን ጽሑፍ መመርመሮ ሲያጠናቅቅም ውጤቱን የምንገልጽ ይሆናል።
መረጃው የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ሕዝብ ግኝኙነት ነው።
የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን
አማራጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤ/ክ ድምፅ
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/jimmadiocese
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/jimmadiocese
✍️ ትክክለኛውን የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የማኅበራዊ ድኅረ ገጽ ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ያጋሩ!
1 695
ለሲነርጂ ሀበሻ ፊልምና ኮሚኒኬሽን በመዘጋጀት ላይ የሚገኘው የሰማዕቱን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ አኩሪ ታሪክ የሚያጎድፍ ፊልም ቀረጻ እንዲቆም ተጠየቀ !
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜
ኅዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ)
@የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!!
ሲነርጂ ፊልምና ኮሚኒኬሽን በኢትዮጵያዊው ሰማዕት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሊቀ ጳጳስ የስማዕትነት ተጋድሎ ላይ የሚያጠነጥን ፊልም ለመሥራት ቀረጻ ለመጀመር ዝግጅት ማጠናቀቁን ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች በተገኘው መረጃ እና ከፊልሙ እስክሪፕት ቅጅ ለመረዳት የቻለው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ለተቋሙ በጻፈው ደብዳቤ ስክሪፕቱን "እንኳን እኛ የታሪክ ባለቤቶች ይቅርና ሰማዕቱን በግፍ ረሽኖ የገደላቸው የጠላት የኢጣሊያን ወራሪ ኃይል ሊናገረው ቀርቶ ሊሰማው የማይችልን የሐሰት ታሪክ በመፍጠር የሰማዕቱን ሊቀ ጳጳስ አባት አኩሪ ታሪክ የሚያጎድፍ ብሎም የቤተ ክርስቲያናችንን ክብር የሚነካ ጽሑፍ ሆኖ አግኝተነዋል" ብሏል።
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እንዲህ አይነቱ ታሪክን የሚያጎድፍ እና ከቤተ ክርስቲያናችንም አልፎ የመላ ኢትዮጵያውያንን ሥነ ልቦና የሚጎዳ የፊልም ቀረጻ ሥራችሁን እንድታቆሙ እና በቀጣይም በቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶችና ታሪክ ዙሪያ ማንኛውንም አይነት ፈልምና ቀረጻ ከማከናወናችሁ በፊት ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ ፈቃድ የመጠየቅ ግዴታ ያለባችሁ መሆኑን እየገለጽን ከዚህ ውጭ በራሳችሁ የሐስት ትርክት ፍላጎት ብቻ በመነሳሳት የቤተ ክርስቲያናችንን ታሪክ እናበላሻለን የምትሉ ከሆነ ግን በምትፈጽሙት ሕገ-ወጥ አድራጎት በሕግ ለመጠየቅ የምንገደድ መሆኑን እናሳውቃለን ሲል ተቋሙን አስጠንቅቋል።
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በዚሁ ደብዳቤው መንግስታዊ የፀጥታ አካላትም ደርጅቱ እያከናወነ ያለውን የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶች ታሪክ የማዛባት ሕገ-ውጥ እንቅስቃሴ ተከታትለው በማስቆም ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስቧል።
የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን
አማራጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤ/ክ ድምፅ
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/jimmadiocese
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/jimmadiocese
✍️ ትክክለኛውን የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የማኅበራዊ ድኅረ ገጽ ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ያጋሩ!
1 695
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን
ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በማስመልከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ።
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜
ኅዳር 25 ቀን 2016 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ)
@የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!!
"ወዳጆች ሆይ፥ በእናንተ መካከል እንደ እሳት ሊፈትናችሁ ስለሚሆነው መከራ ድንቅ ነገር እንደ መጣባችሁ አትደነቁ፤ ነገር ግን ክብሩ ሲገለጥ ደግሞ ሐሤት እያደረጋችሁ ደስ እንዲላችሁ፥ በክርስቶስ መከራ በምትካፈሉበት ልክ ደስ ይበላችሁ።" 1ኛ ጴጥርስ 4፥12:13
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ::
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በጥብቅ እናወግዛለን፤ የጸጥታ ተቋማትም ጥቃቱን እንዲከላለሉ እንጠይቃለን።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአርሲ ዞን በሹርካ ወረዳ ሶሌ ሚካኤል፣በዲገሎ ማርያም፣በሮቤ እንደቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም አብያተክርስቲያናት ላይ በተለያዩ ጊዜያት 36 ኦርቶዶክሳዊያን በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ሀገረ ስብከቱ ባደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል።
በዚሁ ጥቃት በሶሌ ዲገሉ እና ጢጆ ለቡ በተባሉ ቀበሌዎች 28 ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው ተለቅመው የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም 7ቱ ሴቶችና 21ዱ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል። በዚህ ጥቃትም እድሜያቸው ከሰባ ዓመት አዛውንት እስከ ሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት ይገኙበታል። በዛሬው ዕለት ደግሞ በዲገሉ ማርያም ቤተክርስቲያን 5 ኦርቶዶክሳዊያን ከመገደላቸው በተጨማሪ የሦስት ኦርቶዶክሳውያን ቤት ደግሞ ተቃጥሏል።
ከዚህ ቀደም በሮቤ አንዲቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ቤተክርስቲያን በዓለ ማርያምን አክብረው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ የነበሩ ሦስት ኦርቶዶክሳዊያን ጨለማን ተገን ባደረጉ ነፍሰ ገዳዮች መገደላቸው ይታወሳል።
የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ በሚፈጸመው የኦርቶዶክሳዊያን ጥቃት ዙሪያ በጋራ እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ዐይነት የጥቃት ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አንዳንድ አካላት ላይ በመንግሥት በኩል የማያዳግም ርምጃ እንደተወሰደባቸው ሀገረ ስብከቱ በላከው ሪፖርት አረጋግጠዋል።
ይህ ዐይነት ሃይማኖት ተኮር ጥቃት በምእመናን ላይ መድረሱ አግባብነት የሌለውና እምነትን በነጻነት የማራመድ መንግስታዊ መብትን የሚጥስ በመሆኑ መሰል ሕገ ወጥ ጥቃትን ለመከላከልና ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት መብቶቻቸውን ተቋማዊ በሆነ መንገድ ማስከበር እንዲችሉ ያቋቋሙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ድርጊቱን በማውገዝ ችግሩ ከመሠረቱ እንዲፈታ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር መፍትሔ መፈለግ ሲገባው በዝምታ በማለፉ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ቅሬታ ተሰምቷታል።
ይህ ዐይነቱ ኦርቶዶክሳዊያን ላይ ያነጣጠረ ግድያ እንዲቆምና የወንጀሉ ፈጻሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ በሀገረ ስብከቱ በኩል እየተደረገ ያለው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትም በድርጊቱ እጅጉን ማዘኑን እየገለጸ ጉዳዩን ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመሆን የሚከታተለው መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።
በሌሎች ስፍራዎች የሚያጋጥሙ ተመሳሳይ ጥቃቶችን በእንጭጩ ለመቅጨትና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ ማበጀት ይቻል ዘንድ አህጉረ ስብከት ችግሮች በሚያጋጥሙ ወቅት ሪፖርት እንዲልኩ ቀደም ሲል በደብዳቤ በተላከላቸው የስልክና ዘመናዊ የመገናኛ ዘዴዎች አማካኝነት በፍጥነት በማሳወቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እያሳሰብንና ለሞቱት ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ሁሉ ልዑል እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንዲያወርስልን በመጸለይ የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥታት የሚደርሱ ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች እንዲቆሙና መሰል ጥቃት እንዳይፈጸም ለኦርቶዶክሳዊያን ወገኖቻችን ከለላ እንዲሰጡልን እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
ኅዳር ፳፬ቀን ፳፻ ፲፮ዓ.ም
1 695
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት አምስት ኦርቶዶክሳውያን በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜
ኅዳር 25 ቀን 2016 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ)
@የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!!
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሽርካ ወረዳ ሄላ ጢጆ ሴሮ ቀበሌ አምስት ኦርቶዶክሳውያን በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
ግድያው የተፈጸመው ኅዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ማለዳ ላይ ሲሆን ከሟቾቹም መካከል የ21 ዓመት ወጣትና የ70 ዓመት የእድሜ ባለጸጋ እናት እንደሚገኙበት ከአካባቢው ምእመናን በስልክ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
ምእመናን ጨምረው እንደገለጹት እስካሁን ማንኛውም የመንግሥት አካል የወሰደው እርምጃ የለም።
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሺርካ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ከኅዳር 13 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት በምእመናኑ ላይ አሰቃቂ ግድያ እየተፈፀመ እንደሚገኝ መዘገቡ ይታወሳል።
መረጃው፦ የ ©ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት ነው
የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን
አማራጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤ/ክ ድምፅ
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/jimmadiocese
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/jimmadiocese
✍️ ትክክለኛውን የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የማኅበራዊ ድኅረ ገጽ ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ያጋሩ!
1 695
በጅማ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ለተከታታይ 4 ቀናት የተዘጋጀው ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ በሠላም መጠናቀቁ ተገለጸ።
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜
ኅዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ)
@የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!!
በጅማ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ለተከታታይ 4 ቀናት የተዘጋጀው ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ በሠላም መጠናቀቁ ተገለጸ።
መንፈሳዊ ጉባኤው የተዘጋጀው በጅማ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አማካኝነት ሲሆን ሰንበት ት/ቤቱ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዩቤልዩ ምሥረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው መሆኑ ተገልጿል።
በጉባኤው ላይ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን መምህራን ሰባኪያንና ዘማርያን ተገኝተው ለሕዝበ ክርስቲያኑ ሰፊ የወንጌል አገልግሎትና ልዩ ልዩ ሥልጠናዎችን በመስጠት ፍሬያማ አገልግሎት መስጠታቸውን ጉባኤውን በመምሪያ ደረጃ ፈቃድ አሰጥተው በቅርበት የመሩት የጅማ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ ክቡር ላዕከ ወንጌል መ/ር ባዬ ገልጸዋል።
የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን
አማራጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤ/ክ ድምፅ
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/jimmadiocese
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/jimmadiocese
✍️ ትክክለኛውን የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የማኅበራዊ ድኅረ ገጽ ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ያጋሩ!
1 695
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና ሌሎች የክርስቲያን ማኅበረሰብ አካላት የኢትዮጵያ አብያተክርስቲያናት ሕብረትን ለመመስረት ወሰኑ !
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜
ኅዳር 21 ቀን 2016 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ)
@የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ እርስቲያንን ጨምሮ ሌሎች የክርስቲያን ማኅበረሰብ አካላት የኢትዮጵያ አብያተክርስቲያናት ሕብረትን ለመመስረት ወሰኑ።
በኢትዮጵያ ስላለው የሰብአዊ ቀውስ እና የግጭት ሁኔታ በተደረገው የውይይት ዓውድ ፣ አብያተ ክርስቲያናት አንድነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ተገንዝበው ዛሬ ብሔራዊ የአብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ለመመስረት ራሳቸውን አደራ ሰጥተዋል" ብለዋል። ሲል የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።
በጉባኤው የተገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ በቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሊቀ ጳጳስ የተመራ ሲሆን ፤ የወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ዲቢሳ እና የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሱራፌል ልዑካን ቡድኖቻቸውን በመምራት ተሳትፈዋል።
የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ ሁነቱን ታሪካዊ የአንድነት ትዕይንት በኢትዮጵያ ሲል ገልጿል።
ዜናው የተዋሕዶ ሚድያ ማእከል ነው።
የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን
አማራጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤ/ክ ድምፅ
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/jimmadiocese
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/jimmadiocese
✍️ ትክክለኛውን የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የማኅበራዊ ድኅረ ገጽ ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ያጋሩ!
1 695
የእናታችን ፅዮን ማርያም ዓመታዊ በዓለ ንግሥ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በተገኙበት በጅማ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ካቴድራል ተከበረ።
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜
ኅዳር 21 ቀን 2016 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ)
@የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!!
የእናታችን ፅዮን ማርያም ዓመታዊ በዓለ ንግሥ ብጹዕ አቡነ እስጢፋኖስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጅማ፣ የየም፣ የሰሜን ጎንደር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ ክቡር መልዐከ ሠላም ተስፋ ሚካኤል አሰፋ የጅማ እና የየም አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሀገረ ስብከቱ የመምሪያ ኃላፊዎች ፣ የጅማ ከተማ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን መምህራን ፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና በርካታ የጅማ ከተማ ምእመናን በተገኙበት በጅማ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።
የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን
አማራጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤ/ክ ድምፅ
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/jimmadiocese
✍️ የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/jimmadiocese
✍️ ትክክለኛውን የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን የማኅበራዊ ድኅረ ገጽ ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ያጋሩ!
1 695
ክቡር ደሙ ነውና፡፡
ይህ የስርየት መክደኛ ለእኛ የሚያስተላለፈው ተጨማሪ መልእክትም አለው፡፡ ይኸውም አማናዊው መሥዋዕት ክርስቶስ መሥዋዕት ኾኖ ዓለምን ማዳኑ እንደማይቀርና መሥዋዕቱ የሚቀርብበት ስፍራም በቅድስተ ቅዱሳኑ (ቤተ መቅደሱ) ውስጥ እግዚአብሔር በምሕረት በሚገለጥበት በቃሉ ማደሪያ በጽላቱ ላይ መኾን እንደሚገባው ያስገነዝበናል /ዕብ.፬፥፲፮/፡፡ ይህም እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ ሚልክያስ ላይ አድሮ ‹‹ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይኾናልና በየስፍራውም ስለ ስሜ ዕጣንን ያጥናሉ፤ ንጹሕም ቍርባን ያቀርባሉ፤›› /ሚል.፩፥፲፩/ በማለት እንደ ተናገረው የስርየት መክደኛው አንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምሥጢረ ቍርባንን ለምትፈጽምበት ጽላት ወይም ታቦት ምሳሌ መኾኑን ያሳየናል፡፡ የስርየት መክደኛውን የሚጋርዱት በጥሩ ወርቅ የተሠሩት የኪሩቤል ምስሎችም አማናዊው መሥዋዕት በሚሠዋበት ጊዜ በዙሪያው ረበው የሚገኙ የመላእክት ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን እንዳስተማሩን ሁለቱ ኪሩቤል የተባሉት ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል ናቸው፡፡ ይህን ለማስገንዘብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በመንበረ ታቦቱ ላይ ምስለ ፍቁር ወልዳ እንዲቀመጥ ታዝዛለች፡፡ ምስለ ፍቁር ወልዳን ላስተዋለ ሰው በትክክል የታቦተ ጽዮንን መንፈሳዊ ትርጕም ይረዳል፡፡
ታቦተ ጽዮን ከሌሎች የብሉይ ኪዳን ንዋያተ ቅድሳት በተለየ መልኩ እጅግ ግሩም የኾነ ምሥጢርን በውስጧ ይዛለች፡፡ ይህን ድንቅ ምሥጢር ለመረዳትም አንድ ምሳሌ እንመልከት፤ ንጉሥ ዳዊት የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳኑ ታቦት ከአቢዳራ ቤት ወደ ጽዮን ከተማ ባስመጣበት ወቅት በታቦቷ ፊት በሙሉ ኃይሉ በደስታ እየዘለለ ለእግዚአብሔር መንፈሳዊ መዝሙርን አቅርቦ ነበር /፪ሳሙ.፮፥፲፪-፲፯/፡፡ ከዚህ ጋር ተመሳሳይ የሚኾን ድርጊት በሐዲስ ኪዳንም ተፈጽሟል፡፡ ይኸውም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለቅድስት ኤልሳቤጥ ሰላታ በሰጠቻት ጊዜ የስድስት ወር ፅንስ የነበረው ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ የእመቤታችንን የሰላምታ ድምፅ በሰማ ጊዜ እንደ አባቱ እንደ ዳዊት በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ኾኖ በደስታ ዘሏል (ሰግዷል) /ሉቃ.፩፥፵፬/፡፡ ቅዱስ ዳዊት በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት እየተደሰተ ለአምላኩ የምስጋና ቅኔን መቀኘቱም ለሰው ልጆች ዅሉ የመዳናችን ምክንያት የኾነችውን ቅድስት ድንግል ማርያምንና ልጇን በቃል ኪዳኗ ታቦት በኩል አስቀድሞ በዓይነ ሕሊና ስለ ተመለከታቸው ነበር፡፡
