GRACE_TUBE ™✍
Open in Telegram
🗣የማይረዱህ ሰዎች ስላላዩህ ላንተ ምንም የማይፈይዱልህ ስዎች አልፈውክ ስለሄዱ ግራ ልትጋባ አይገባም ከወደክበት ልትነሳ እግዚአብሔር አንተን ለማንሳት በማን አይን መታየት እንዳለብክ የሚያውቅ ጌታ ነው!! ቢመችህም ባይመችህም ቦታው ቦታህ ካልሆነ መነሳትህ አይቀርም!! በመጥፎ ሰዎች ትብታብ በተናጠች ሀገር ውስጥ በጎ ሰዎች እንዳሉ አትዘንጉ share @JESUSlovingly142
Show more6 749
Subscribers
No data24 hours
-287 days
-7930 days
Posts Archive
6 749
#በስድብ_ፈንታ_አመስግኑ
ብዙ ጊዜ ስንሳደብ እና መጥፎ ቋንቋ ስንጠቀም “እኔ ይህን አለማድረግ አልችልም ልማዴ ነው" እንላለን፡፡ እናም ሲጎዱን አንድ ነገር መናገር ካለብንም፣ በስድብ ፈንታ ምስጋና መናገርን እራሳችንን እናስተምር።
ነገር ግን፣ ሰው እያሰቃየኝ ዝም ማለት አልችልም ትላለህ፡፡ ከመናገርም አልከለክልህም፡፡ ሆኖም ከመሳደብ ይልቅ ምስጋናን ተናገር፡፡ ከመበሳጨት ይልቅ ምስጋናህን ግለጽ፡፡
ለጌታህ መናዘዝ ትችላለህ፡፡ በጸሎትህ ውስጥ ጩኽ፤ እንዲሁ መከራህን ያቀልልሃል፣ ፈታኙም ሰይጣን በምስጋናህ ውስጥ ይሸሻል፣ የእግዚአብሔርም እርዳታ ወዳንተ ይቀርባል። ከተሳደብክ፣ የእግዚአብሔርን ስጦታ ትከለክላለህ፤ እናም ፈታኙ በአንተ ላይ እንዲበረታ ታደርጋለህ፤ በዚያም እራስህን የበለጠ በህመም ውስጥ ታስገባለህ፡፡ ብታመስግን ግን የክፉ መንፈስን ጥቃት ትቃወማለህ፡፡
ነገር ግን ምላስ ብዙውን ጊዜ በልማድ ኃይል አንዳንድ መጥፎ ቃላትን ከመናገር ወደኋላ ማለት አይችልም:: ከዚያም በምትወድቅበት ጊዜ ኹሉ ቃሉ ከመናገርህ በፊት ጥርሶችህን ጠብቀው ይዘጉ፡፡ ምላስህ የደም ጠብታ ብታፈስስ ይሻላታል ፤ ከስድብም በኋላ የማያቋርጥ ቅጣት ከምትቀበል በጊዜው ሥቃይን ብትታገሥ ይሻልሃልና፡፡
@JESUSlovingly142
6 749
ጠርቶ አበረታህ!
፨፨፨፨//////፨፨፨
ፈተና ከበዛበት አለም፣ ጭንቀት ከሰፈነበት ምድር፣ ከእረፍት አልባው ኑሮ ያለምንም ቅድመሁኔታ በበረከቱ ሊቃኝህ፣ በመግቦቱ ሊደግፍህ፣ ካንተ በላይ ሆኖ ሊረዳህ፣ በፍላጎትህ ልክ ሊቃኝህ እንደ ሁልጊዜው በጥበቃው የማይለይህ፣ በመግቦቱ የማይርቅህ ዘወትር አብሮህ የሚቆመው ደጋፊና አበርታቹ አምላካዊ ሃይል አብሮህ አለ። ቀዳማዊ አባትህን አዳምን ከአፈር አበጅቶ ካለመኖር ወደመኖር ያመጣው ድንቅ ፈጣሪ ያንተን ህይወት በእስትንፋስ አምሳያ፣ በነፍሱ ርቀት ልክ በተስፋ ሊሞላህ፣ ሊያረጋጋህ፣ ሊያንፅህ፣ ወደ እራሱ ሊጠራህ፣ ዘወትር ሊደግፍህና ሊያግዝህ የተዘጋጀ አምላክ አለህ። ፍጥረቱን የሚዘነጋ፣ የእጆቹን ስራ የሚረሳ፣ አምሳያውን ችላ የሚል ፈጣሪ የለንም። ከበባው በሙሉ እኛን በማሰቡ፣ ጥበቃው በሙሉ እኛን ለመደገፍና ለማበርታት ነው።
አዎ! ጀግናዬ..! ጠርቶ አበረታህ! መርጦ ባረከህ፣ ቀርቦ ገሰፀህ፣ አከበረህ፣ በችግሮችህ ምክንያት ተዓምራትን ሰራብህ። እንባህን ለብሶትህ ማውጫ፣ ለህመምህ ማስታገሻ አደለህ፤ ፈተናን አንደ ብረቱ እሳት ያጠነክርና ለመሞረድ፣ ለማስተካከል ያግዝ ዘንድ ሰጠህ። ለበጎ ነው፣ ለመልካም ነው ብሎ ማሰብን የመሰለ ፈተናንን መሻገሪያ፣ ችግርን ማስታገሻ አፅናኝ ቃል የለም። ማንኛውም ሰው ምንም ቢደርስበት፣ ለምንም ቢጋለጥ፣ ምንም ቢገጥመው ዋናው ጉዳይ የሚሰጠው ትርጉም እንጂ የገጠመኙ ምንነት አይደለም። ምን ሲሆን ምን እንደሚያስከትል፣ እንዴትስ አትራፊና ጠቃሚ እንዲሆን የሚያውቀው የችግሩ ገፈት ቀማሽ ነው። የአምላክን መኖር እስክትጠራጠር፣ በእምነትህ እስክትፈተን፣ ተስፋህ እስኪዋዥቅ የሚያደርሱ እጅግ የገዘፉ ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሊገጥሙህ ይችላሉ። ብዙ ነገር ቢያስረሱህም የአምላክን አብሮነት እንዲያስረሱህ፣ ጠብቆቱን እንዲያስክዱህ፣ አምነትህን እንዲያጎድሉ ግን አትፍቀድ።
አዎ! አምላክን ማመን፣ በእርሱ መታመን የፀና ሃይል ነው። እርሱን መጠበቅ፣ በእርሱ መመካት የትልቅነት ሚስጥር ነወ። ቸር ነኝ ብሎ ቸርነቱን አይፈፅምም፤ ደግ ነኝ ብሎ ደጋግ ተግባር አይከውንም። መናገር ሳይኖርበት የሆነው፣ ሳያሳውቅ መገለጫው ያደረገው አምላካዊ ባህሪ አለው። እርሱን መቀበል፣ በእርሱም መገዛት ምርጫ ቢሆንም አሳራፊው ግን እርሱ ነው። መቀመጥ የሚወዱና መጓዝ የሚያስደስታቸው ሰዎች እያንዳንዳቸው በሚወዱትና በሚያስደስታቸው ተግባር ውስጥ ጉዳት ቢኖርም እይታቸው ግን ጥቅሙና ፍላጎታቸው ነው። አምልክህ አብሮህ እንዳለ፣ መንፈሱ በውስጥህ እንደሚመላለስ፣ በፍቃድህ፣ በፍላጎትህ ልክ ተዓምራትን ሊሰራ እንደሚችል አምኖ እድሉን መስጠት፣ በፅናት መጠበቅ ያንተ ምርጫና ውሳኔ ነው። አምላክን መጠበቅ፣ እርሱን ማመን፣ በእርሱ መታመን እንደ ሰዋዊው እምነትና ጥበቃ ህፀፅ ያለው፣ ጉድለት የማይጠፋው አይደለምና ጥሪውን አክብር፤ በመመረጥህ ደስ ይበልህ፤ በእምነትህ ፅና፤ ድንቅ በስራዎቹም እየታደስክ ኑር።
ውብ ምሽት ይሁንልን!
😊 💪
@JESUSlovingly142
6 749
#ከኖርኩት፦ ብቸኝነትን ተላመድ አለዝያ የከበቡህን ያጣህ ቀን በምድር ሰው የጠፋ እስኪመስልህ ድረስ ውስጥህ ይረበሻል።
#አስተውል፦ብቸኝነት ምርጫህ አድርግ እያልኩ አይደለም በራሱ የሚተማመን አስተዋይ እና ነገሮችን በብልሀት እና በማሰተዋል የሚያደርግ ሰው ሁን ስሜታዊ ሆነህ ብዙ ነገሮችህ እንዲበላሹ አታድርግ።
አቅምህን ለማሳየት ግድ ከሆነብህ ግን አድርገው;;
አንቺም እህት እንደዛው
@JESUSlovingly142
6 749
አንዳንዴ እብዶች ተብዬ የልባችንን እውነት ሲናገሩ ከስንት አንዴ ጤነኛ እንደሆኑ እናስባለን! ግን እለት በእለትስ የሚያወጡት ቃል የብዙሃኖችን እውነት ቢሆንስ? አልያም እኛ ስንረዳ ተሳስተን ቢሆንስ?የእነርሱ ቃል እውነታን ያዘለ ከሆነ ሁሌ ምን አልባት እኛ ስተናል!!!
6 749
There are two medicines for all ills.time and silence
ለሁሉም ህመም ሁለት መድሃኒቶች አሉ.
#ጊዜ እና #ዝምታ
@JESUSlovingly142
