en
Feedback
Ethio maths

Ethio maths

Open in Telegram

👉አስጠኚ ከፈለጉ ኑ ወደኛ ጎራ🫲🫲

Show more
1 979
Subscribers
-124 hours
-157 days
-6230 days
Posts Archive
#AAU #UAT በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም በመደበኛ መርሐግብር የቅድመ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (UAT) ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.
#AAU #UAT በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም በመደበኛ መርሐግብር የቅድመ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (UAT) ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም ይሰጣል። ፈተናው በተጠቀሱት ቀናት በሦስት ፈረቃ ማለትም ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:30-5:00 ፈረቃ 2: ረፋድ ከ5:30-8:00 ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ8:30-11:00 የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል። መርሐግብሩን እዚህ በጥንቃቄ ይመልከቱ። የመፈተኛ ማዕከልዎን የመፈተኛ ሰዓትዎን በደንብ ይመልከቱ። 🔔 ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ አመልካቾች ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የተዘዋወራችሁ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከል የመረጡ ማየት የተሳናቸው አመልካቾችች በሙሉ ዋናው ግቢ በሚገኘው የአካል ጉዳተኞች ማዕከል ላብ 1 ማክሰኞ ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም በፈረቃ 3 ፈተናቸውን የሚወስዱ መሆኑ ተገልጿል፡፡

#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Ex
#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም 200 (ሁለት መቶ) ልዩ የፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ ዕድል አዘጋጅቷል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም 200 (ሁለት መቶ) ልዩ የፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ ዕድል አዘጋጅቷል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ፣ የተቀመጡ መመዘኛዎችን የሚያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና በብቃት የሚያልፉ ተማሪዎች የስኮላርሺፕ ዕድሉ ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ተብሏል፡፡ የ Presidential Scholarship Program ዕድሉ ተጠቃሚዎች፣ ዩኒቨርሲቲው ባሉት ሰባት ኮሌጆች እና የሕግ ትምህርት ቤት ስር ባሉ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ይመደባሉ። ነጻ የትምህርት ዕድሉ ሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል፣ መጠነኛ የኪስ ገንዘብ እና ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ ድጋፍና የስልጠና ዕድሎችን ያስገኛል፡፡ በዚህ የትምህርት ዕድል በወጥነት ተጠቃሚ ለመሆን፣ የዕድሉ ተጠቃሚዎች በየሴሚስተሩ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.50 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም የዕድሉ ተጠቃሚዎች በተመደቡበት የትምህርት ዘርፍ መቀጠል ይኖርባቸዋል። የዚህ ስኮላርሺፕ ተጠቃሚዎች በቀጣይነት ዩኒቨርሲቲው የድኅረ-ምረቃ (Masters እና PhD) የትምህርት ዕድል ያገኛሉ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የ2019 ዓ.ም ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ 👇 https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements

የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን አስቀድሞ ከተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ማዛወር፣ ተቀብሎ ማስተማር በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን 06/11/2
+1
የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን አስቀድሞ ከተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ማዛወር፣ ተቀብሎ ማስተማር በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተላከ ሰርኩላር፤ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች በሚኒስቴር መ/ቤቱ በመደበኛ እና በሪሚዲያል ፕሮግራም ለዩኒቨርሲቲዎች የሚመደብ መሆኑን አስታውሷል፡፡ ይሁን እንጂ በሚኒስቴር መ/ቤቱ የተመደቡ ተማሪዎች በየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ እየተማሩ ያሉ መሆናቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ጥናት፣ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ ዕውቅና ውጪ ዩኒቨርሲቲዎች ባልተሰጣቸው ስልጣንና አግባብነት በሌለው ሁኔታ ተማሪዎችን ከተመደቡበት ውጭ የመቀያየር ሥራ እነደሚሠሩ አረጋግጧል፡፡ ይህም ህብረ-ብሄራዊነትን የሚጉዳና የእኩልነት መብትንና ፍትሃዊ አሠራርን የሚፃረር ሆኖ እንደተገኘ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በመሆኑም በትምህርት ሚኒስቴር ምደባ የተሰጣቸውን የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዕውቅና ውጪ በምንም አይነት ሁኔታ አስቀድሞ ከተመደቡበት ማዛወርም ሆነ በማንኛውም ሁኔታ ተቀብሎ ማስተማር በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አሳስቧል፡፡ ይህን ውሳኔ ጥሶ የተገኘ የዩኒቨርሲቲ አመራር ተጠያቂ እንደሚሆኑም ሚኒሰቴሩ አስገንዝቧል፡፡

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ፈተና ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ አስመዝግበዋል።
+1
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ፈተና ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ አስመዝግበዋል። ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ረድኤት ሳሙኤል 574.4 እንዲሁም ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪ ናትናኤል ሙላት 570.16 በማምጣት የየትምህርት ቤታቸውን ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ካስፈተናቸው 84 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች፣ 80 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት ሲያስመዘግቡ፤ ሦስት ተማሪዎች ከ450 እስከ 499
+1
የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ካስፈተናቸው 84 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች፣ 80 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት ሲያስመዘግቡ፤ ሦስት ተማሪዎች ከ450 እስከ 499 ውጤት አስመዝግበዋል። በትምህርት ቤቱ በወንዶች 587.17 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ መመዝገቡን የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ሳሊም አህመድ ለአሚኮ ተናግረዋል።

በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ተማሪዎች በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ተማሪ ሰምሃል መሃሪ
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ተማሪዎች በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ተማሪ ሰምሃል መሃሪ የትምህርት ቤቱን ከፍተኛ ውጤት 550.76 ማስመዝገቧ ተገልጿል፡፡

በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የነጋሶ ጊዳዳ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የነጋሶ ጊዳዳ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ትምህርት ቤቱ ለሦስተኛ ተከታታይ ዓመት ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፊያ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል፡፡

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። በአገር አቀፍ ደረጃ ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። በአገር አቀፍ ደረጃ ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) ካሳለፉ 88 ትምህርት ቤቶች መካከል፣ አራት ትምህርት ቤቶች በትግራይ ክልል የሚገኙ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።

የጋሞ ባይራ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) አሳልፏል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተፈተኑ 17
የጋሞ ባይራ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) አሳልፏል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተፈተኑ 172 ተማሪዎቹ በሙሉ (100%) ማለፋቸውን የትምህርት ቤቱ አስተዳደር አሳውቋል።

የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። 566.92 በትምህርት ቤቱ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት ሲሆን
የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። 566.92 በትምህርት ቤቱ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት ሲሆን ዝቅተጋው ውጤት ደግሞ 448 መሆኑ ተገልጿል፡፡ ትምህርት ቤቱ በተከታታይ ለሦስተኛ ዓመት ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማሳለፍ ችሏል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የሚደገፈው ነገሌ ቦረና ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተመሳሳይ በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸውን ተማሪዎች በሙሉ (100%) አሳልፏል። ሌላው በዩኒቨርሲቲው የሚደገፈው በቆጂ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተመሳሳይ በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸውን ተማሪዎች በሙሉ (100%) አሳልፏል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸው 34 ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። 18 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን፣ 568.3 በትም
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸው 34 ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። 18 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን፣ 568.3 በትምህርት ቤቱ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት ሆኗል።

የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል። 566.5 በትምህርት ቤቱ ተማ
የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል። 566.5 በትምህርት ቤቱ ተማሪ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት ሲሆን፣ ዝቅተኛው ደግሞ 417 መሆኑ ተገልጿል። ትምህርት ቤቱ ባለፉት ሦስት ዓመታት ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎቹ በሙሉ ማለፋቸውን ገልጿል። ትምህርት ቤቱ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ያስፈተናቸው 69 ተ
የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎቹ በሙሉ ማለፋቸውን ገልጿል። ትምህርት ቤቱ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ያስፈተናቸው 69 ተማሪዎች በሙሉ ያለፉ ሲሆን፣ በሲዳማ ክልል ይህን ማሳካት ከቻሉ ሁለት ትምህርት ቤቶች አንዱ ሆኗል።

የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል። ትምህርት ቤቱ
የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል። ትምህርት ቤቱ ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ ከ444 በላይ ውጤት ማምጣታቸውን የገለፀው ዩኒቨርሲቲው፤ ትምህርት ቤቱ ባለፉት ሦስት ዓመታት ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ገልጿል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል። 551.34 ከ 600
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል። 551.34 ከ 600 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ በትምህርት ቤቱ የተመዘገበ ሲሆን፣ ሰባት ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት አግኝተዋል። 392.84 ዝቅተኛው በትምህርት ቤቱ ተማሪዎች የተመዘገበ ውጤት መሆኑ ተገልጿል። ትምህርት ቤቱ ባለፉት ሦስት ዓመታት ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ገልጿል።

የራያ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ሼርድ ትምህርት ቤት የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ አገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ገልጿል። ተማሪ አርሴማ
+1
የራያ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ሼርድ ትምህርት ቤት የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ አገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በሙሉ ማለፋቸውን ገልጿል። ተማሪ አርሴማ ተስፋይ የትምህርት ቤቱን ከፍተኛ ውጤት 572 ነጥብ ማምጣቷ ተገልጿል። በትግራይ ክልል አራት ትምህርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች በሙሉ ማሳለፍ መቻላቸው በትምህርት ሚኒስቴር መገለፁ ይታወቃል።

የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው 103 ተማሪዎች 102 ተማሪዎች (99%) የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋ
+1
የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው 103 ተማሪዎች 102 ተማሪዎች (99%) የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል። ተማሪ ሌንጮ ዱራ የትምህርት ቤቱን ከፍተኛ ውጤት 564.64 ከ 600 ማምጣቱ ተገልጿል።

photo content

#KiburCollege ክቡር ኮሌጅ የአፍሪካ የቢዝነስ ስኩል ማኅበር አባል ተቋም ሲሆን ክህሎትን መሠረት ያደረገ ተግባራዊ የትምህርት አሰጣጥን የሚከተል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው። ✅ በመጀመሪያ
#KiburCollege ክቡር ኮሌጅ የአፍሪካ የቢዝነስ ስኩል ማኅበር አባል ተቋም ሲሆን ክህሎትን መሠረት ያደረገ ተግባራዊ የትምህርት አሰጣጥን የሚከተል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው። ✅ በመጀመሪያ ዲግሪ ✅ ቴክኒክና ሙያ (TVET) ✅ በ Remedial Program ✅ አጫጭር ስልጠናዎች በዳግም ምዝገባ ፍቃድ ባገኘንባቸው የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ለመቀበል በምዝገባ ላይ ነን!! Website: https://kibur.net አድራሻ፦ ጀሞ ሚካኤል ከአፍሪካ ህንፃ አጠገብ ☎️ 0113854042 / 0904848586 Telegram: https://t.me/kiburcollege Facebook:  https://www.facebook.com/kiburcollege