en
Feedback
Tesfaye Woldesilassie

Tesfaye Woldesilassie

Open in Telegram

Tesfaye Woldesilassie

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Tesfaye Woldesilassie

Channel Tesfaye Woldesilassie (@tesfayewoldesilassie) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 12 995 subscribers, ranking 15 469 in the News & Media category and 2 626 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 12 995 subscribers.

According to the latest data from 09 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -135 over the last 30 days and by 40 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 28.81%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 13.24% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 744 views. Within the first day, a publication typically gains 1 721 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 16.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Tesfaye Woldesilassie

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

12 995
Subscribers
+4024 hours
-57 days
-13530 days
Posts Archive
ተከታታዩ የፋኖ ወታደራዊ እርምጃ በሰራዊቱ ላይ የማይነሳ ኪሳራ አስከትሎበታል። “ዘመቻ መሐመድ ቢሆነኝ” በላቀ ድል መጠናቀቁ ተገለፀ። በጎጃም  መርዓዊ ከተማ ከባድ የድሮን ጥቃት ሲፈፀም  በወሎ የአገዛዙ ሰራዊት የመከላከያ ምሽጉ ተደርምሶ ሰራዊቱ ከፍተኛ ወታደራዊ ውድቀትና ኪሳራ ማስተናገዱን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ  ይፋ አደረገ። የዕዙ ሰብሳቡ በወታደራዊ ድሉ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ሰጥተዋል፡፡ በወለጋ ነዳጅ ጫኝ ቦቴዎች ተቃጠሉ፤ በርካታ አሽከርካሪዎች ታግተው ተወሰዱ። አሽከርካሪዎች የሚጠብቃቸው አካል አለመኖሩን በመገንዘብ ይህን ድርጊት እያየ ዝምታና እያስፈጸመ ያለው አገዛዝ ስርዓታዊ ለውጥ እንዲመጣ ራሳቸውን ከጉዞ በማቀብ የጋራ ትግል ማድረግ እንዳለባቸው ተጠቁሟል። አገዛዙ የጦር መሣሪያ እያከማቸ ነው ሲባል የዲፕሎማሲ ውድቀቱ መባባሱ ተመላከተ፡፡ ሀገረ ኢትዮጵያ በውስጥ ግጭትና በውጭ ከበባ መካከል መሆኑዋም ተጠቁሟል፡፡  የሰላም ማስከበር ስልጣንን እንደ መሳሪያ የሚጠቀሙ የውጭ ኃይሎችን ለመመከት እና ሉዓላዊነትን ለማስከበር የአቀራረብና የስልት ለውጥ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል። በኬንያ በርካታ ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ፤ በፕሬዚዳንት ሩቶ አዲስ መመሪያ ምክንያት በንግድ ማህበረሰቡ ዘንድ ስጋት አንዣቧል፡፡ በሌላ በኩል በሱዳን ሰሜን ኮርዶፋን ግዛት በፍርድ ቤት ላይ በተፈፀመ የሰው አልባ አውሮፕላን ድሮን ጥቃት ንፁሃን ሰዎች መገደላቸውን ጠበቆች አስታወቁ። https://youtu.be/AjPo-RPrvyo?si=wcxA3rk3hlUaa9IK

በበርካታ ግንባሮች አውደ ውጊያዎች ተከፍተው ውለዋል፡፡ የሰራዊቱ ሁለት አዛዦች ሲሞቱ በርካቶች ተማርከዋል፡፡ የአፋብን ዕዞች በተለያዩ ግንባሮች ከፍተኛ ወታደራዊ ድል ተቀዳጀተዋል፡፡ በአገዛዙ ሠራዊት ላይ ከፍተኛ የሰውና ቁሳቁስ ኪሳራ አስተናግዷል፡፡ በትግራይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት የንፁሃኑን ህይወት ሲበላ በኦሮሚያ የማዕድን ማውጫ ጥቃት ስጋት መደቀኑና ተቋማቱ ስራ ማቆማቸው ተጠቆመ፡፡ በሌላ በኩል ፋኖ ከአውደ ውጊያ ጎን ለጎን ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ውይይቶችን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በመንዝ እና ግሼ አውራጃ ህዝባዊ ውይይት ሲደረግ የአባት አርበኞች ክፍለ ጦር ምስረታ ተጠናቋል፡፡ በመካከለኛው ምስራቅ ለወራት ሲያያንዣብብ የቆየው የጸጥታ ስጋት አዲስ እና አደገኛ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። በየመን አብዛኛውን የአገሪቱን ክፍል የሚቆጣጠሩት የሁቲ አማፂያን በሳዑዲ አረቢያ ላይ የፈጸሙት የተቀናጀ ጥቃት እንዲሁም ኢራን በደቡብ ኮሪያ ላይ ያወጣችው ቀጥተኛ የጦርነት ማስጠንቀቂያ የቀጣናውን ነዳጅ መስመር እና ዓለም አቀፍ ንግድ ለአደጋ ዳርገውታል። https://youtu.be/w20rD7iJwlI?si=eEWzU5o0gCdObkU0

በሸዋና ጎንደር አዳዲስ ግንባሮች ተከፈቱ። በቀጠናዎቹ ከባድ ውጊያ እየተደረገ ነው። የአገዛዙ ሪፕብሊካን ጋርድ ያላሰበውን ኪሳራ ተከናንቧል። በጎንደር ተጨማሪ ድል ተበስሯል። ፓርቲው አደራዳሪውን አልፈልግም ለድርድር ግን ዝግጁ ነኝ ማለቱ መነጋገሪያ ሁኗል። ውስብስብ ኩነቶችን እያስተናገደ ያለው የኢትዮጵያ የውስጥ ፍትጊያ አዲስ ክስተት አሰምቷል። በጽምዶ እየታማ ያለው ህወሃት ሽማግሌውን አደራዳሪ አትድረሱብኝ ብሏል። ፋኖ በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ምዝገባ እንዲያከናውኑ አዘዘ። አፋብን ከውጊያ ጎን ለጎን የተማረ ትውልድ ክፍተት እንዳይከሰት እየሰራ ነው። የአለምን ቀውስ እያናጋ ያለው ነዳጅ ከፍተኛ ጭማሪ  አሳየ።  የአሜሪካ ኢራን የወታደራዊ ልውውጥ እየጨመረ በመጣበት በዚህን ሰዓት የነዳጅ ዋጋ የማይቀመስ ሁኗል። የቀጠናው ውጥረትም ተባብሷል። https://youtu.be/cx1FZfMWbfs?si=Z4K38RP1X8UfeHRi

ፋኖ ድል መቀዳጀቱን አበሰረ። ጥምር ሀይሉ ያላሰበው የደፈጣ ጥቃት ደርሶበታል። በርካቶች በሞት ሲሸኙ ቀሪዎቹ ሆስፒታል ገብተዋል።  ደህንነቶቹ ተይዘዋል።  አርበኞቹ በድል ታጀበው እየገሰገሱ ናቸው ጦሩ ወሳኝ የጦር እስትራቴጂ ከተማዋን ተቆጣጠረ። በቀጠናው አሁንም ውጊያው ሲቀጥል ሰራዊቱ ወደ ፊት እየገሰገሰ ነው። የድንበር ላይ ውጥረቱም አይሏል። ከ140 በላይ ወታደሮች ሞት ተሰማ። በወታደሮቹና  ታጣቂዎቹ መካከል ከባድ ውጊያ እየተደረገ ነው።  ውጊያው በአየር ድብደባ ታጅቦ ቀጥሏል። https://youtu.be/CCJ_n3fWmxI?si=JpPhZdcUCBird2n3

አገዛዙ ትምህርት ቤት ላይ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን ቀጥሎበታል። ብልፅግና በንፁሐን ዜጎች ላይ የሚፈፅመውን ፍጅት አባብሶ ቀጥሎበታል። ዛሬ ጳጉሜ 02/13/2018/ዓ.ም ጎንደር ደራ ወረዳ ሳና ከተማ ላይ ሳና አንደኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ት/ቤት እና ሜጮ ትምህርት ቤት ላይ በጥዋቱ ድሮን በመጣል በትምህርት ቤቶች እና በንፁሀን ላይ ጉዳት አድርሷል። አርበኛ መንግስቱ አማረ

የፋኖ አርበኞቹ  በሰሜን ጎንደር ከፍተኛ ድል ማስመዝገባቸውና ተቋማዊ አንድነታቸውን የሚያጠናክር ውይይት ማካሄዳቸው ተገለጸ።  በሸዋ ግንባር  አፄ ዳዊት ክፍለ ጦርና ካራ ምሽግ አርበኞች ጦር በመርሀቤቴ ባካሄዱት የተቀናጀ የእጅ ለእጅ ውጊያ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦርን ኪሳራ አደረሱበት። ትልቁ የገበያ ማዕከል ሲነድ አድሯል። አገዛዙ የንግድ ተቋማትን በሴራ ፖለቲካ በእሳት እንዱወድሙ እያደረገ መሆኑ ተሰማ። በመርካቶ የደረሰው ጉዳት የብልጽግና አገዛዝ እጅ አዙር ተልዕኮ ያለበት መሆኑ ተመላክቷል። በወለጋ ያለው ቀውስ እየተባባሰ ሲሆን ሰራዊቱ በንጹሃኑ ላይ ግድያና እልቂቱን አሁንም ቀጥሎበታል። የአብይ አህመድ አገዛዝ የጦርነት ጉዞና የዲፕሎማሲ  ውድቀት ለግብጽ ማንሰራራት ውሳኝ እየሆነ መምጣቱ ተጠቆመ:: ግብጽ በቀጠናው ሀገራት እጅ አዙር ኢትዮጵያ ላይ ጦሯን እያዘመተች ነው። https://youtu.be/PbszB7bOh-Q?si=9G1Y-LgahF3icBK4

የብልጽግና ሰራዊት ወታደራዊ ቁመና እየሳሳ ነው። ወታደራዊ መሪዎ ጦራቸውን ይዘው ከካምፕ የሚያደርጉት መውጣት በቤተ መንግስት ተጨማሪ ስጋት ሁኗል። የፋኖ አርበኞች ከውጊያ የበላይነት ባሻገር የአገዛዙን ጦር ከካምፕ እያፈራረሱት ቀጥለዋል። አንድ ሙሉ ሪጂመንት ጦር ሲያልቅ የሰራዊቱ ዘመቻ መሪ ፋኖን ተቀላቅለዋል።  ባለስልጣናቱ ሊባረሩ ናቸው። ከሀገር እንዳይወጡ የታገዱ መኖራቸውም ተሰምቷል። ከብልጽግና የስልጣን ጥማቸው ሳይቆርጥላቸው የሚባረሩ ሚንስትሮች የአገዛዙን መረጃዎች እዳያወጡ ክትትል ይደረግባቸዋል ተብሏል። አብይ አህመድ ሚስጥራዊ ስብሰባ ላይ ናቸው ቴዎድሮስ 2ተኛ ዕዝ አዳዲስ መመሪያዎችንና ስራ አስፈጻሚዎችን በማዋቀር ውሳኔዎችን አሳለፈ። በጎጃም ቀጠና ወታደራዊ ድሎችን ለማስጠበቅ አሁናዊ ግምገማና ትዕዛዝ ወርዶል። ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖስት ውስጥ ድብቅ መረጃ ወጣ። የአብይ አህመድ አገዛዝ በኤርፖርቱ በኩል እየፈጸመ ያለው አለም አቀፍ ትኩረት የሳበው መረጃ በተጓዦች ላይ ስጋትን ደቅኗል። በርካታ የጦር አውሮፕላኖች እየተመላለሱ ናቸው። https://youtu.be/q8fRArVKIYw?si=tohviMxK0Gzx0D6N

በማዕከላዊ ጎንደር አፀደ ማርያም ቀጠና በአገዛዙ ጦር ላይ ከፍተኛ ውድመት ደረሰ፤ ሰራዊቱ በተለያዩ አቅጣጫዎች አካባቢውን ለቆ በመውጣት ላይ ነው። አዳዲስ ውጊያዎች ተከፍተዋል። የብልፅግና አገዛዝ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ውድቀት እያስተናገደ ሲመጣ በውጊያ ሜዳ ሽንፈት ገጥሞታል።  በአገር ውስጥ የንጹሃን  ጭፍጨፋ ላይ የተጠመዱት ወታደራዊ መሪዎች በቀጠናዊ ጦርነት የደካሞች ዛቻ እያሰሙ ቀጥለዋል። ኮሎኔሉ ኤርትራ ትወድማለች ሲሉ ተደምጠዋል። በርካታ የአማራ ንጹሃን በወለጋ ቀጠና እንዲጨፈጨፉ መመሪያ እያወረደ ያለው ፖለቲከኛው በርካታ ተቃውሞና ትችት እያተናገደ ነው። አቶ ልደቱ አያሌው ለጃዋር መሀመድ አሁናዊ ደብዳቤ ጽፈዋል። አቅም ያለውና እውነተኛ የሆነ ይሞግተኝ ብለዋል። የጃዋርን ድብቅ ሚስጥርም አውጥተዋል። https://youtu.be/rEKyZg7Fs5w?si=4fRcSAd5XiEt2x4z

መጽሐፉ በደኅንነት አባላት ተሰበሰበ ትናንት ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ «የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ» የተሰኘው መጽሐፌ ማከፋፈያ
+1
መጽሐፉ በደኅንነት አባላት ተሰበሰበ ትናንት ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ «የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ» የተሰኘው መጽሐፌ ማከፋፈያ ድርጅት በበርካታ የደኅንነት አባላት ከተከበበ በኋላ፣ በመጋዘን ውስጥ የነበሩ መጻሕፍት ተሰብስበው መወሰዳቸውንና ደንበኞችን በማስተናገድ ላይ የነበረ ሠራተኛ «ለጥያቄ ትፈለጋለህ» በሚል መወሰዱን የመጽሐፉ ደራሲ ቀሲስ ዶ/ር መንግስቱ ጎበዜ በይፋዊ ማህበራዊ ገጻቸው ተናገሩ። መጽሐፉ ቤተ ክርስቲያንን እና ተያያዥ የሀገራችንን ታሪክ ብቻ መሠረት ያደረገ ሙያዊ ሥራ በመሆኑ ለምን በዚህ ደረጃ የመንግሥትን ትኩረት እንደሳበ እንዳስገረማቸው ተናግረዋል። መጽሐፉ ከኢትዮጵያ የአእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን (ጉዳዩ ከሚመለከተው ከፍተኛ የመንግሥት መሥሪያ ቤት) ፈቃድ አግኝቶ የታተመ መሆኑን የተናገሩት ቀሲስ ዶ/ር መንግስቱ የፈቃዱ የምስክር ወረቀትም አብሮ ስለታተመ ከመጽሐፉ የመጨረሻ ገጽ ላይ ማዬት እንደሚቻል አረጋግጠዋል። የመናገርና ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ ሕገመንግስታዊ መብትን የጣሰ በመሆኑ መጽሐፉንም የተያዙት ሠራተኛ እንዲለቀቁ እጠይቃለሁ። ቀሲስ ዶክተር መንግስቱ ጎበዜ

ካምፑ ተሰበረ። ከ100 በላይ ወታደሮች እዛው ወደቁ። የፋኖ አርበኞቹ የማያዳግም እርምጃ በድል ተጠናቋል። በሌላ ዜና አፋብን መመሪያ ሰጠ። መመሪያው በሁሉም የክልሉ ቀጠናዎች ወደ ተግባር ተገብቶበታል።  የአገዛዙ የደህንነት ሀይሎች በአዲስ አበባ ተቋሙን መዝረፋቸውና የተቋሙ ሰራተኞችን ማፈናቸው ተገለጸ:: ደራሲው  አሁናዊ ምላሽ ሰጥተዋል። ምስራቅ ወለጋ ያልተቋረጠው የአገዛዙ ጭፍጨፋ እንደቀጠለ ነው። ደራሽ ያጡት ንጹሃኖች ከገዳ ኮማንዶ በትር ባለፈ በርሃብ አለጋ እየተገረፉ ናቸው። የደህንነት መሪው ቁጥጥር ስር መዋሉ ሲሰማ ከባድ ኦፕሬሽን እንደቀጠለ ነው። የኢራን አሜሪካ የተኩስ ልውውጥ ዳግም አለም አቀፍ ትኩረት ስቧል። https://youtu.be/lh7_YggtJ5Y?si=nffCkzZJBmQaSXQH

የፋኖ ሀይሎች አመርቂ ድል አስመዘገቡ። አርበኞቹ በሸዋና ወሎ ቀጠናዎች አሁንም ውጊያውን አስቀጥለውታል። የብልጽግና ጦር ከባድ ሽንፈት ገጥሞታል። ጦርነትን እና የአገዛዙን የብሄርተኝነት አስተዳደር ሽሽት የተሰደዱ ኢትዮጵያዊያን በስደታቸው አሳዛኝ ግጭት ገጥሟቸዋል። በሀገራቸው ልጆች ጥቃት የደረሰባቸው ስደተኞች ጉዳይ መነጋገሪያ ሁኗል። ከ100 በላይ ፅንፈኞች ተይዘዋል። ሚዲያዎች ራሳቸውን ሳንሱር ለማድረግ መገደዳቸው ተሰማ። አገዛዙ የሀሳብ ነጻነትን ሙሉ በሙሉ በመዝጋቱ የግል ሚዲያዎች አደጋ ላይ መውደቃቸው ተመላክቷል። በሌላ ዜና የአፍሪካ ህብረት በሱዳን ጉዳይ ክስ ቀርቦበታል።  በመካከለኛው ምስራቅ የሀያላኑ ፍጥጫ ወደ ከፋ  ደረጃ ተሸጋግሯል። https://youtu.be/wrWgyhHn7fM?si=Rq4K2GKQOY4eb73D

በበላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ስር የሚገኙ ክፍለ ጦሮች በጠላት ላይ ከፍተኛ ውድመት በማድረስ በስኬት የተጠናቀቀ የደፈጣና የማጥቃት እርምጃ ወሰዱ፡፡ በአውደ ውጊያው ፋኖ በድል ገብቷል፡፡ በሌላ ዜና የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጤና መምሪያ ኃላፊ በቅርቡ በጃዋር መሐመድ አስተያየት ላይ አሁናዊ ምላሽ ሰጡ፡፡ አማራውንና ህዝበ ሙስሊሙን ለማጥቃት የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው ሲሉም ተችተዋል፡፡ ፋኖ በአለም አቀፉ መድረክ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ስቦ ዋለ፡፡ የአርበኞቹና የተራራዎቹ ዝምድና የህዝቡና የፋኖ ቁርኝት ከአማራ ክልል ፈረንሳይ ደርሶ አለም አቀፍ አይኖችን ስቦ ውሏል፡፡ ታላላቅ ሚዲያዎች የታደሙበት የፈረንሳዩ ኩቫን ዴ ሚኒም አዳራሽ የፋኖን ትግል አስተጋብቷል፡፡ ኢሕአፓ አገራዊ የምክክር ሂደቱን እና የአገዛዙን ፖሊሲዎች «ተጨማሪ ቀውስ ፈጣሪ» ሲል ኮንኗል፡፡ ከውጭ ኢራን አሜሪካ ወደ ስምምነቱ ከተመለሰች የመግባቢያ ሰነዱን ሙሉ በሙሉ ለመተግበር ዝግጁ መሆኗን አስታውቃለች፡፡ https://youtu.be/pcy9OJgt5e8?si=1lIQK3zne2TQrzo2

አርበኛው ለኢትዮጵያዊያን ጥሪ አቀረበ። እየተባባሰ የመጣውን የዜጎች እልቂትና ፊት ለፊት የተጋረጠውን ህዝባዊ እልቂት በጋራ እንታገል ሲል አሳስቧል። አገዛዙ በጭፍን ሀገር የማፍረስ ተግባሩን አጠናክሯል። ወደ ወሎ ተሻግረው የገቡት በአገዛዙ የተደገፉት የኦነግ ታጣቂዎች በርካታ ውድመት አደረሱ። ወሎን አሻግሮ እያየ ያለው ኦሆዴድ በቀጠናው ንጹሃኑ ላይ ጭፍጨፋ አስፈጽሟል። ከወለጋ እስከ ወሎ የተዘረጋው ጥቃት ሀይ ባይ አላገኘም። ወታደራዊ አፈሳውና ጦርነት ያሳቀቃቸው ወጣቶች ስደት ተበራክቷል። የሀገር ተስፋ ያጡት ወጣቶች በስደታቸውም ሌላ አደጋ ተደቅኖባቸዋል። ስደት ዳግም ሞት አምጥቷል። የሱዳን ወታደራዊ ፍጥጫ ድንበር ተሻጋሪ ሁኗል።  የRSF ሀይሎችን እየደገፉ ያሉት ኢትዮጵያና ቻድ የድንበር ተሻጋሪ ጥቃቱ ሰለባ እየሆኑ ናቸው። ዝርዝሩን ይከታተሉ! https://youtu.be/kliGyeu5IjU?is=BziVQ7pTaeymXm44

በጎንደርና በሸዋ የፋኖ  አሀዶች የጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሳቸውን  መምሪያዎቹ አስታወቁ። የግንባር ውጊያዎቹ እንደቀጠሉ ናቸው፡፡ በምስራቅ ወለጋ ቀጠናዎች የተቀናጀ የጥቃት እና የዘረፋ ጭፍጨፋው ተባብሷል። በመዲናዋ የታፈኑት ወጣቶች አስደንጋጭ መረጃ ወጣ፡፡ ማጎሪያ ቤቱ ሌላ ውስብስብ የህይወት መቋጫ ሁኗል፡፡ በሌላ ዜና በጃናሞራ ወረዳ በድርቅና በትኩረት ማጣት ምክንያት የተከሰተው አስከፊ ሰብአዊ ቀውስ፤ በህዝብ ላይ የተደራረበ መከራ ደቅኗል። RSF ንጹሃንን መግደሉን እና በሺዎች የሚቆጠሩትን ማፈናቀሉን ጦሩ አስታወቀ፡፡ ቀጣናዊ ውጥረቶችና የአካባቢው ፖለቲካዊ ዛቻ ምልልሶች ተጠናክረዋል። ከውጭ የአሜሪካ ጦር ከሐምሌ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢራን ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመ። https://youtu.be/MKIbO7DHaTo?si=e13HQHEN6HIogVgm