5 348
Subscribers
No data24 hours
-307 days
-17230 days
Posts Archive
5 348
Repost from AURA Jobs
ለፕሮፋይል የሚሆኑ ገራሚ ገራሚ ፎቶዎችን ለማግኘት ከስር ጆይን ያድርጉ የፈለጉትን አይነት ያገኛሉ ይ🀄️ላ🀄️ሉን!👇
https://t.me/+UqU8zCoHqyw2NzQ0
5 348
5 348
የፍቅረኛችሁን ሰው ስም የመጀመርያ ፊደል በመጫን የምታገኙትን የፍቅር ቻናል ተጋበዙልኝ ❣︎❣
😍😍😍
ዳይ ለሁላችሁም ነው እንዳያመልጥዎ!!
5 348
Carrot music🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕🥕
የድሮ ዘፈን ከየት ላምጣ ወይንም እንዴት አገኝ ይሆን ብለው ተጨንቀው ነበር እንግዳውስ ትዝታ ምርጥ ምርጥ ዘፍኖችን በትንንሽ Size (Kb) በሳንቲም እንድታወዱ አዘጋጅተናል የማን ዘፍን መስማት ይፈልጋሉ ...?
1 ጥለሁን ገስስ
2 መሃሙድ አህመድ
3 ቴድሮስ ታደስ
4 ኤፍሬም ታምሩ
5 ፀሃዬ ይህዋንስ
6 አስቴር አወቅ
7 ብዝዋየው ደምሴ
8 ንዋይ ደበበ
See more....
5 348
#MoE
ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም በቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም #አጋማሽ ላይ የመውጫ ፈተናን ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ላሉ ተፈታኞች በሙሉ ፈተናው ከጥር 27- የካቲት 1/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል ብሏል።
በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተናውን ተፈትነው ያላለፉ እና ከጥር 27 - የካቲት 1/ 2016 ዓ.ም ድረስ የመውጫ ፈተናውን በድጋሚ (Re-exam) ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ያሉ ተፈታኞች በሙሉ ምዝገባ የሚያካሂዱት የመፈተኛ ተቋም (የመንግስት ዩኒቨርሲቲ) የሚመርጡት በዚህ ማስፈንጠሪያ (Link)
(https://exam.ethernet.edu.et) ነው።
ስለሆነ ከጥር 08 እስከ ጥር 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የምዝገባ ክፍያ 500.00 ብር በ " ቴሌ ብር " ብቻ በመክፈል መመዝገብ እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
አመልካቾች ተጨማሪ ድጋፍ የሚፈልጉ ከሆነ በስልክ ቁጥር +251 118 13 21 76 ወይም በኢሜይል registration@ethernet.edu.et በኩል ድጋፍ ማግኘት የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የመዉጫ ፈተና የሚፈቱ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የሚያካሂዱትና እና የአገልግሎት ክፍያ የሚፈፅሙት በተቋማቸው በኩል መሆኑን ገልጾ አስፈላጊው የመፈተኛ መረጃዎች በተቋማቸው በኩል እንደሚደርሳቸው አመልክቷል።
@tikvahethiopia
5 348
#WolkiteUniversity
በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳቹህ ለሪሚዲያል ፕሮግራም በ2016 የትምህርት ዘመን ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ጥር 27 እና 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
አጠቃላይ ገለፃ ጥር 29/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ትምህርት ጥር 30/2016 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡
ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➭ መሰናዶ ያጠናቀቃችሁበትን ሰርተፍኬት፣
➭ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
➭ የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
➭ አራት 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➭ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የትራስ ጨርቅ፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
5 348
Do you enjoy reading this channel?
Perhaps you have thought about placing ads on it?
To do this, follow three simple steps:
1) Sign up: https://telega.io/c/UniversitySchool
2) Top up the balance in a convenient way
3) Create an advertising post
If the topic of your post fits our channel, we will publish it with pleasure.
5 348
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ #በግል የማካካሻ ትምህርት በ2016 የትምህርት ዘመን በዩኒቨርሲቲው ለመማር የተመዘገባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ጥር 6/2016 ዓ.ም፣ የትምህርት ክፍያ የምትከፍሉት ጥር 6 እና 7/2016 ዓ.ም እና ትምህርት የሚጀመረው ጥር 8/2016 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲው የምግብ እና የመኝታ አገልግሎት ለሚፈልጉ ተማሪዎች በክፍያ የሚያስተናግድ መሆኑን አሳውቋል፡፡
@tikvahuniversity
5 348
ተጨማሪ ያለፉ ፈተናዎች, Short Notes, Practice Question እና የትምህርት ቪዲዮችን ለማግኝት ይከተሉን፡
🔠🔠🔠🔠 and 🔤🔤🅰️🔤🔤
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
✈️@Sturegion1Bot
5 348
✅Jimma university
➡️ All last year Final exams compiled🔗🔗(2013)
🔠🔠🔠🔠 and 🔤🔤🅰️🔤🔤
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
✈️@Sturegion1Bot
5 348
#BahirDarUniversity
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለነባር እና አዲስ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
የምዝገባ ጊዜ፦
➤ የ1ኛ ዓመት 2ኛ ወሰነ ትምህርት ተማሪዎች እንዲሁም የ3ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ነባር መደበኛ እና የማታ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች፦ ከጥር 15-17/2016 ዓ.ም
➤ በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ (Freshman፣ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያላችሁ ተማሪዎች)፦ ከጥር 21-23/2016 ዓ.ም
Note:
➭ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ለምዝገባ ስትሔዱ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይጠበቅባችኋል።
➭ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት እና የ12ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው እንዲሁም አራት ጉርድ ፎቶግራፍ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡
➭ በተለያየ ምክንያት ትምህርታችሁን አቋርጣችሁ ለመልሶ ቅበላ ውጤታችሁ የሚያበቃችሁና የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞላችሁ ተማሪዎች የምትገቡበት ባች በሚመዘገቡበት ቀን ማመልከት የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
5 348
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ማሥተማር ተግባር ቅድመ ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን አስታወቀ
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ጥር ወር ለሚጀምረው የመማር ማሥተማር ተግባር ቅድመ ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን አስታውቋል።
የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ታረቀኝ ትንታጉ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ ዩኒቨርሲቲው ጥር አንድና ሁለት ተማሪዎችን ለመቀበል ተዘጋጅቷል።
በተማሪዎች አገልግሎት በኩል የክሊኒክ፣ የመኝታ ክፍል፣ የመዝናኛ እና የቤተ መጽሐፍ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የምግብ አገልግሎት ግብዓት ማግኘት ፈታኝ ቢሆንም የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ለተማሪዎች የምግብ አገልግሎት በቂ ዝግጅት ተደርጓል ነው ያሉት።
ዩኒቨርሲቲው ባለፈው አመት በካምፓሱ ውጤታቸውን ያሻሻሉ 3 ሺህ 400 ተማሪዎች በዘንድሮው አመት የመግቢያ ውጤት ያመጡ 600 ተማሪዎች በጥቅሉ 4 ሺህ አዲስ ተማሪዎችን ይቀበላል ተብሏል፡፡
በዘንድሮው አመትም 3 ሺህ 600 የሪሜዲያል ተማሪዎች እንደሚማሩ ታረቀኝ ትንታጉ (ዶ/ር) ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ገልጸዋል፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
5 348
#BDU
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ሲጀመር ተማሪዎች ኃላፊነት ለመውሰድም ይዘጋጁ ብሏል።
በአማራ ክልል የሚገኙ 10 የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት 2 ሳምንታት መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀምሩ ትምህርት ሚኒስቴር ማስታወቁ ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድ ፖስት፣ የፀጥታ አደረጃጀቶች፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ፀጥታ አካላት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ተከታታይ ውይይቶችን ሲያደርግ ቆይቶ የውይይቶቹ የመጨረሻው ክፍል ሐሙስ ከተደረገ በኃላ ነው ውሳኔው የተላለፈው።
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
- ከመስከረም 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተማሪዎችን ለመቀበል ተዘጋጅተን የነበረ ቢሆንም፣ በክልሉ የፀጥታ ሁኔታ ሳቢያ ተሰናክሏል።
- በእኛ በኩል የዝግጅት ክፍተት የለብንም።
- በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቁጥጥር ሥር የሆነ የፀጥታ ሁኔታ አለ። ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆነም የፀጥታ ሁኔታ አለ። ከእኛ ውጪ በሆነው ጉዳይ ላይ ምንም ማድረግ አንችልም። ምንም ማድረግ ባልቻልንበት ሁኔታ የሰው ልጅ ጠርቼ አንድ መጥፎ ነገር ቢከሰት ምንድነው የምለው ? የሚለውን ተማሪዎችም፣ ወላጅንም ታሳቢ አድርገን ተማምነን ይቆይ የሚል አቋም ስለነበረን በዚህ ምክንያት ነው እስካሁን ቀስ እያልን የመጣነው።
- የመማር ማስተማሩ እንዲጀመር በነበረው ውይይት ሒደት አቅደን የነበረው ተመራቂ ተማሪዎችን ወደ የትምህርት ግቢያቸው ማስገባት ነበር።
- እስካሁን ባለን ልምድ ግጭቶች እዚህም እዚያም ሊቀሰቀሱ ይችላሉ። ቀጣይነታቸው ግን ብዙም አይደለም። አንድ ቀን ወይ ሁለት ቀን መስተጓጎል ሊፈጠር ይችላል ከዚያ ግን ያበቃል።
- ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ተጠርተው ሲመጡ ታሳቢ ማድረግ ያለባቸው ጉዳዮች አሉ ፤ ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሊያጋጥሙ የሚችሉ ዕክሎችን ከግምት በማስገባት ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው።
- ተማሪውም፣ ወላጅም፣ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብም እንደ አገር የሚመለከታቸውም አንድ ላይ ሆነን መደበኛ ትምህርት መጀመር አለብን ብለን ወስነናል።
- የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ተቋማቸው ከልደት (ገና) በዓል በኋላ ባሉት ቀናት ለተማሪዎቹ ጥሪ ያደርጋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ መሆኑን ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
5 348
የመፍትሄ ያለህ . . .
" መፍትሄ የሚባል ነገር ሳይሰጠን የትምህርት ዓመቱ 5ኛው ወር ሊገባ ነው " - ተማሪዎች
በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች እስካሁን ድረስ ወደ ሚማሩበት ዩኒቨርሲቲዎች አልተጠሩም።
ተማሪዎቹ መቼ እንደሚጠሩ አያውቁም ፤ መፍትሄም አልተሰጣቸውም።
ስለተማሪዎቹ ጉዳይ መፍትሄው ይሄ ነው ሳይባል የትምህርት ዘመኑ 5ኛ ወር ሊገባ ተቃርቧል።
ተማሪዎቹ ቤት ከዋሉ ወራት አልፈዋል። ከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና ላይ የሚገኙ ሲሆን የነሱ እኩዮች የትምህርት ዓመቱን አጋማሽ ለማጠናቀቅ ቀርበዋል።
ተማሪዎቹ እስካሁን ወደ ሚዲያ ወጥቶ መፍትሄ የሚናገር አካል ባለማግኘታቸው " በዚህ ዓመት ላንማር እንችላለን " የሚል ስጋት አድሮባቸዋል።
እነዚህ ተማሪዎች ፤ በቅድሚያ በኮሮና ቫይረስ ተፅዕኖ፣ በኃላም በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ይፈጠሩ በነበሩ የፀጥታ ችግሮችና አሁን ደግሞ በአማራ ክልል ባለው ወቅታዊ የሰላም መደፍረስ ምክንያት ትምህርታቸውን ባግባቡ መማር አልቻሉም።
ተማሪዎቹ በእነሱ ጉዳይ ተገቢ መረጃ የሚሰጥ አካል እንደሌለ ይናገራሉ።
በራሳቸው መንገድ እየደወሉ ይመለከታቸዋል የሚባሉ አካላት ሲጠይቁ " ምንም አናውቅም " ይሏቸዋል። አንዳንዶች ስልክ አያነሱም፣ አጭር የፅሁፍ መልዕክትም አይመልሱም ፤ ተስፋ የሚሰጥ ነገርም አይናገሩም ሲሉ ይወቅሳሉ።
ተማሪዎቹ የዚህ ጊዜ " ባች " ከአንደኛ ዓመት ጀምሮ ብዙ ተግዳሮቶችን እየተጋፈጠ የመጣ " ባች " ነው ብለዋል።
* በኮሮና ምክንያት ብዙ ጊዜ ግቢ ውስጥ ለመቆየት ተገደዋል።
* በተለያዩ አለመረጋጋቶች የትምህርት ክፍለጊዜዎች እየተጓተቱ፣ እየተቆራረጡ፣ አንድ ወሰነ ትምህርት በ45 ቀናት እየተማሩ ነው የመጡት።
* ብዙ የትምህርት ክፍሎች አልተሸፈኑም፣ እነዚህ ደግሞ የመውጫ ፈተና አካል ናቸው ተማሯቸውም አልተማሯቸውም " ተምረዋቸዋል "ተብሎ ነው የሚታሰበው።
* የተማሯቸው የትምህርት ክፍሎች እንኳ በበቂ አልተማሯቸውም።
* የመውጫ ፈተና ላይ እንዴት ልንሆን ነው የሚልም ሃሳብ አለባቸው።
አሁን ወደ ዩኒቨርሲቲ ቢገቡ ያልተሸፈነው ትምህርት እንዴት መሸፈን እንዳለባቸው ሲያስቡ ተማሪዎቹ ካሁኑ ጭንቅ ውስጥ እንደገቡ አስረድተዋል።
ተማሪዎቹ ያለትምህርት ረጅም ጊዜ ቤት መቀመጣቸው ለከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና እንደዳረጋቸውም ገልጸዋል።
ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ፤ ትምህርት ሚኒስቴር ድረስ ተማሪዎች ተወክለው ቢጠይቁም ፤ ብዙ አጥጋቢ ምላሽ እንዳላገኙ አመልክተዋል።
በተለይም የጤና ተማሪዎች ፤ ትምህርታቸው ተጨማሪ ኮርሶች ያሉት የትምህርት መስክ በመሆኑ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ትምህርቱ ካልተሰጠ አስቸጋሪ እንደሆነ አስገንዝበዋል።
ምናልባት ጊዜ ካለፈ በኋላ ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ በይድረስ ይድረስ ትምህርቱ የሚሰጥ ከሆነ ተማሪው በቂ እውቀት ይዞ አይወጣም ብለዋል።
በመጨረሻም ትምህርት ሚኒስቴር ትኩረት ሰጥቷቸው መፍትሄ የሚለውን ነገር በይፋ እንዲያሳውቃቸው ጥሪ አቅርበዋል። ሁኔታው ተስፋ እንዳስቆረጣቸውም አስገንዝበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተማሪዎችን ቃል የወሰደው ከዶቼ ቨለ ሬድዮ እንዲሁም በውስጥ ከመጡ መልዕክቶች ሲሆን ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ በእነዚህ ተማሪዎች ጉዳይ መሰል መልዕክት ማጋራታችን ይታወሳል።
የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ብዙ ጥረት ብናደርግም ይህ ነው ተብሎ ለተማሪና ወላጅ የሚነገር ምላሽ አላገኘንም።
🔠🔠🔠🔠 and 🔤🔤🅰️🔤🔤
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
✈️@Studregion1Bot
5 348
✨ትምህርት እድል በዱባይ ሀገር
University of Dubai Scholarships
The University of Dubai is offering undergraduate scholarships to international students who are open to all the subject areas. The scholarship fund allows students to partially cover their educational expenses. The students can apply for this grant after getting enrolled in one of the undergraduate programs taught at the university.
🌐Official Website: https://ud.ac.ae/admissions/scholarships-and-discounts/
🔠🔠🔠🔠 and 🔤🔤🅰️🔤🔤
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
✈️@Studregion1Bot
5 348
🆕 የሪሚዲያል ፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆኗል።
በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባችሁን ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ምደባችሁን ለማየት የቀረቡ አማራጮች፦
በድረ-ገፅ፦
https://placement.ethernet.edu.et
በቴሌግራም ቦት፦
https://t.me/moestudentbot
የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ #የማያስተናግድ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
🔠🔠🔠🔠 and 🔤🔤🅰️🔤🔤
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
✈️@Studregion1Bot
5 348
#ExitExam
📌ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች
📌ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባሉበት
ጉዳዩ፡- የመውጫ ፈተናን ድጋሚ የሚወስዱ ተፈታኞችን ይመለከታል፤
በ2015 የትምህርት ዘመን በሁሉም የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና ተግባራዊ መደረጉ ይታወቃል፡፡በተሰጡት ፈተናዎች የማለፊያ ነጥብ #ያላገኙ ተፈታኞች በጥር ወር መጨረሻ ላይ ለዳግም ፈተና እንዲቀመጡ ታቅዷል፡፡ ሆኖም ግን እነዚህ ተፈታኞች በተቋማት እየኖሩ ስላልሆነ ተገቢውን ዝግጅት ለማድረግ እየተቸገሩ መሆኑን በተለያዩ መንገዶች ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይገልፃሉ፡፡
በመሆኑም ተቋሞቻችሁ በሚችሉት መንገድ ተፈታኞቹ #ቤተመጽሐፍት መጠቀም እንዲችሉ አስፈላጊው ሁሉ ትብብር እንዲያደርጉላቸው እንጠይቃለን፡፡ [ትምህርት ሚኒስቴር]
🔠🔠🔠🔠 and 🔤🔤🅰️🔤🔤
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
✈️@Studregion1Bot
5 348
📚 Jimma University.
📚 Civics Final Exam.
🔠🔠🔠🔠 and 🔤🔤🅰️🔤🔤
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
@UniversitySchool🧡
✈️@Studregion1Bot
5 348
#RayaUniversity
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁ፤ ነገር ግን በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በራያ ዩኒቨርሲቲም ሆነ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ምንም ትምህርት ያልጀመራችሁ ተማሪዎች በሙሉ እስከ ታህሳስ 03/2016 ዓ.ም በራያ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራር ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ ሪፖርት እንድታደርጉ ራያ ዩኒቨርሲቲ ጥሪ አድርጓል፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
