487
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
የህዳር ሚካኤል ወረቦች - ከአማርኛ ትርጉማቸው ጋር
(1) - አንተኑ ሚካኤል መና መና ዘአውረድከ፤
ወአንተኑ ለእስራኤል መና ዘአውረድከ።
ትርጉም፦ [እስራኤል ዘሥጋ ከግብጽ ባርነት ተላቅቀው ወደ ከነዓን ሲጓዙ በበረሃ መና ያወረድክላቸው መልአክ ሚካኤል አንተ ነህ!]
(2) - ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል ረዳኤ ምንዱባን፤
በከመ ከመ ታለምድ ዘልፈ።
ትርጉም፦ [የችግረኞች ረዳት ሚካኤል ሆይ ችግረኞችን መርዳትን እንዳስለመድክ እኔንም ለመርዳት ክንፍህን ዘርግተህ ፍጠን]
(3) - ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስኢለ፤
በብሂለ ኦሆ በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዓኒ ቃለ።
ትርጉም፦ [ከስዕልህ ፊት ቆሜ ዘወትር ልመናን ሳበዛ 'እሺ' በማለት ፈጥነህ ልመናዬን ወደ እግዚአብሔር ፊት አድርስ አሰማ]
(4) - እግዚኡ ረሰዮ ለውእቱ ሚካኤል፤
እምኲሎሙ መላእክት መላእክት ይትለዓል መንበሩ።
ትርጉም፦ [ከመላእክት ሁሉ ይልቅ ክብሩ(መንበሩ) ታላቅ እንዲሆን ሚካኤልን ጌታው እግዚአብሔር መረጠው]
(5) - በገዳም በገዳም በገዳም ዘሴሰይኮሙ፤
ለነገደ ለነገደ ኅሬ ደቂቅ።
ትርጉም፦ [የእስራኤልን ልጆች በበረሃ መና እንደመገብካቸው እኔንም የሕይወትን መብል መግበኝ።]
(6) - ባሕረ ግርምተ ዓረፍተ ገብር አርአየ ፍኖተ እግዚአብሔር
በእደ መልአኩ አቀቦሙ ለእስራኤል አርብዓ ዓመተ ለሕዝቡ በገዳም
ትርጉም፦ [ባሕር ከፍሎላቸው ዕረፍትን ሰጣቸው፥ የእግዚአብሔርንም መንገድ አሣያቸው። በመልአኩ እጅ የእስራኤልን ሕዝብ ለአርባ አመታት በበረሃ ጠበቃቸው!]
(7) - ተወከፍ ጸሎተነ ጸሎተነ ውስተ ኑኀ ሰማይ፤
ወስእለተነ ከመ መዓዛ ሠናይ ሊቀ መላእክት።
ትርጉም፦ [የመላእክት አለቃቸው ሆይ ጸሎታችንን በሰማይ ሆነህ ተቀበል፥ ልመናችንንም እንደ መልካም መዓዛ ተቀበል።]
የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃው አይለየን።
ህዳር 11/ 2014 ዓ.ም የተጻፈ
ዲ.ን አምደመስቀል ሙሉጌታ
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
በፍዳ ተይዘን ባየን ጊዜ ሰው ሆነልን። አስታረቀን። ሌላ አስታራቂ ያስነሣልን አይደለም። እርሱ ራሱ አስታረቀን እንጂ። እርሱ ራሱ ስለ እኛ ተሰቀለ። በመስቀሉም ጽናችን ቤዛችንና ድኅነታችን ተደረገልን። ይህም አዳኛን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ቅዱስ ሚካኤል - በመጽሐፍ ቅዱስ!
ያዕቆብን ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነው ልጆቹንም የባረከለት "ጠባቂና ባራኪ" መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ዘፍ 48:16)። እስራኤል ዘሥጋ ከግብጽ ባርነት ወጥተው ወደ ከነዓን ሲጓዙ ከፊታቸው ቀድሞ ይረዳቸው የነበረው ከፈርኦንና ከሠራዊቱም ያዳናቸው "ተራዳኢ" መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ዘጸ 14:19፥ ዘጸ 23:20፥ ዘኁ 20:16)። የበለዓምን አህያ ያናገረ በለዓምም የሰገደለት "ተአምራት አድራጊ" መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ዘኁ 22:23-35)።
ለኢያሱ የተገለጠለት እርሱንም የረዳው ቅዱስ ሚካኤል ነው(ኢያ 5:13-15)። ለጌድኦን ተገልጦ ያበረታው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(መሳ 6:12)። ለማኑሄና ለሚስቱ ያበሠረው 'ስሙ ድንቅ' የሆነው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(መሳ 13:3-20)። የኢየሩሣሌም ከተማ በአሦር ንጉሥ በሰናክሬም ሠራዊት በፈረስ በሰረገላ በተከበበች ጊዜ ከእግዚአብሔር ተልኮ መጥቶ ከአሦራዊያን ሰፈር መቶ ሰማኒያ አምስት ሺህ ሰው የገደለው ኃያል መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(2ነገ 19:35)።
ዳንኤልን ሊረዳው የመጣ የሚያጸናውም አጽናኝ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ዳን 10:13፥ ዳን 10:21)፥ በኋለኛው ዘመን ለሕዝብ ልጆች ሁሉ የሚቆመው ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ዳን 12:1)፥ እስራኤል ዘሥጋ በባቢሎናውያን እጅ ወድቀው በምርኮ ሰባ ዘመን በተገዙ ጊዜ ስለ እነርሱ ምልጃ ያቀረበው "አማላጅ" መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ዘካ 1:12)።
ስለ ሕዝበ እግዚአብሔር ''ይህቺን አመት ተዋት'' እያለ የሚማጸነው ጠባቂ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ሉቃ 13:8)። በቤተ ሳይዳ የመጠመቂያውን ውሃ የሚያናውጠው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ዮሐ 5:4)። ጴጥሮስን ከእስር ቤት ያስመለጠው ቅዱስ ሚካኤል ነው(ሐዋ 5:9፥ ሐዋ 12:11)። የቆርኔሌዎስን ጸሎትና ምጽዋት ቅድመ እግዚአብሔር ያሳረገው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ሐዋ 10: 1-4)። ስለ ሙሴ ስጋ ከዲያብሎስ ጋር የተከራከረው ቅዱስ ሚካኤል ነው(ይሁ 1:9)። ዘንዶ የተባለ ዲያብሎስን ከሰማይ የጣለው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ራእ 12:7)። ከክብሩ ብዛት የተነሣ ምድርን ያበራው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው(ራእ 18:1)።
ይህ ግሩም መልአክ ክርስቶሳዊያን የሆንን እኛንም ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን፥ በመንገዳችን ይቅደምልን፥ አማላጅነቱ አይለየን፥ በረከቱ ይደርብን አሜን።
የስሙ ትርጓሜ ማን እንደ እግዚአብሔር ነው፥
የሰውን ወደ አምላክ የአምላክን ወደ ሰው፥
እኛን የሚረዳን ዘወትር በምልጃው፥
የመልአክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነው።
ሰኔ 12 2011 ዓ.ም ተጽፎ የነበረ
ዲ.ን አምደመስቀል ሙሉጌታ
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
ንዒ ርግብየ ንዒ ርግብየ ምስለ ሚካኤል፤
ወንዒ ሠናይትየ ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ።
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
የቅዱሳንን ኃይል ከሞቱ በኋላ እንኳን አየህን?!
(የቁስጥንጥንያ ፀሓይ፥ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ(347 - 407) የቆሮንቶስን መልእክት ሲተረጉም ካስተማረው)
✔ 'ክርስቶስ ለደቀመዛሙርቱ በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ከሞቱ በኋላ እንኳ እንዲያበሩና እንዲሰለጥኑ አድርጓቸዋል። እስቲ ንገረኝ! የታላቁ የእስክንድር መቃብር የታለ?... የክርስቶስ አገልጋዮች ግን መቃብራቸው እንኳን ሳይቀር የተከበረ ነው፥ ያረፉበት ቀንም በሚገባ የታወቀ ነው፥ ዕረፍታቸው በመላው ዓለም በዓል ሆኖ ይከበራል። የተሰቀለው የክርስቶስ አገልጋዮች መቃብሮቻቸውም ከነገሥታት ቤተ መንግሥታት ይልቅ የከበረና የተወደዱ ናቸው።... ልብሰ መንግሥት የለበሰውና ዘውድ የደፋው ንጉሡ ራሱ ወደ እነዚያ የቅዱሳን መቃብራት ሄዶ እንዲራዱትና በእግዚአብሔር ፊት ጠበቃዎች ሊሆኑት ይለምናቸው ዘንድ የክብር ልብስ አውልቆ በዚያ ይቆማል። ልብሠ መንግስት ያለው እርሱ በሥጋ የሞቱ ቢሆኑም ረዳቶቹ ይሆኑት ዘንድ ድንኳን ሰፊዎችንና ዓሣ አጥማጆችን ይማጸናል።...
✔ ...የቅዱሳንን ኃይል ከሞቱ በኋላ እንኳን አየህን? የኃጥአንን ደካማነት ደግሞ በሕይወት እያሉ እንኳን አየህን? ከደካማነት ራቅ፥ በእነርሱ ኃይል ይኖርህ ዘንድ፥ የመልካም ሕይወትን ባለህ አቅም ሁሉ ተከተል። በዚህ ዓለም እንዲህ ከኾነ በሚመጣው ዓለም ምን ሊሆን እንደሚችል አስብ። ሁለንተናህ በዚህ ፍቅር የተቃኘና የተገዛ ይሁን! ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ባለው ፍቅር እናገኛለን ብለን ተስፋ የምናደርገውን ዘለዓለማዊ ሕይወት አጥብቀህ ያዝ! ምስጋና ለእርሱ ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ይሁን፥ ለዘለዓለሙ አሜን።'
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፥ ትርጓሜ ቆሮንቶስ ካልእ፥ ክፍለ ትምህርት(Homily) 26 ; 3)።
@OrthodoxConcepts
ይህ ወቅት "ዘመነ ጽጌ(የአበባ ወቅት)" ነው። ምድር በአበቦች የምታሸበርቅበት ወቅት። አበባ የክርስቶስ ምሳሌ ነው። በማኅሌታችን እርሱን "ነጭና ቀይ የሆነ አበባ" እንለዋለን። ስለ ንጽሐ ባሕርይነቱ "ነጭ"፥ ስለእኛ ደሙን በማፍሰሱ "ቀይ" አበባ የምንለው ንጉሣችን የእሾህ አክሊል ደፍቶ በቀራንዮ ዋለ። እርሱ አበባችን ነው። እርሱ ንጉሣችን ነው። እርሱ መድኃኒታችንም ነው።
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
"መስቀልህ የወደቁትን የሚያነሣቸው፥ ደካሞችንም እንደ ዋልያ የሚያሮጣቸው ነው። መስቀልህ ለሙሽራህ ለቤተ ክርስቲያን ጥሎሿ፥ በምኵራብ ለፈታሓትም ምልክቷ ነው።"
ውዳሴ መስቀል ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
#ነገረመስቀል(ክፍል ሦስት)
(3)፦ በዓለ መስቀሉ በዓለም ክርስቲያኖች ይከበራልን?
የቤተክርስቲያን የድኅነቷ ምልክት የሆነው ቅዱስ መስቀል በዓሉ በመላው ዓለም በሚገኙ ሐዋርያዊ መሠረትነት ባላቸው አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይከበራል። ይህም ስለ ሁለት ነገሮች ነው። የመጀመሪያው አዳኛችን ክርስቶስ ስለ እኛ በመስቀል ላይ የተቀበለውን መከራ ለማሰብ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን ድኅነተ ዓለምን የፈጸመበት ዕጸ መስቀል በ326 ዓ.ም በንግሥት ዕለኒ(St. Helene) አማካይነት ከተቀበረበት ስለመገኘቱ መታሰቢያ ይደረጋል።
➛ ሮማዊያን(Roman Catholic) 'The Triumph of the Cross’ ሲሉ ምሥራቃዊያን(Eastern Orthodox) አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ 'Exalation of Holy Cross' በማለት Sep. 14(በእኛ መስከረም 3) የመስቀሉን በዓል ያከብራሉ። የአንጾኪያ ቤተክርስቲያን(Antiochian Orthodox) ከዚህም በተጨማሪ የዐቢይ ጾም ሦስተኛውን እሑድ 'Sunday of the Veneration of the Holy cross.' በማለት ቅዱስ መስቀሉን ታስብበታለች። የአርመን ቤተክርስቲያን(Armenian Apostolic/Orthodox) በበኩሏ ከ(Sep. 10-14) ለተከታታይ አምስት ቀናት መስቀሉን አስባ Sep. 15&16 በዓላቱን ታከብራለች። ከዚህ አልፎ Oct. 24 ላይም ታከብራለች። ሦስቱ ኦርቶዶክሳዊያን(ግብጽ፥ ኢትዮጵያና ኤርትራ) ደግሞ በተመሳሳይ ቀን Sep. 27(በእኛ መስከረም 16)ና በነጋታው መስቀሉን ያስባሉ።
ከፕሮቴስታንቱ 'Anglican Protestant' ለሁለት ከፍለው May 3 'invention of cross' ደግሞም Sep. 14 'celebration of Holy cross day' በማለት ያከብራሉ።
@OrthodoxConcepts
#ነገረመስቀል(ክፍል ሁለት)
(2)- የመስቀሉ ምልክት ለቤተክርስቲያን ምኗ ነው?
በመስቀሉ በተፈጸመው ቤዛነት የተገኘችው ቅድስት ቤተክርስቲያን በመስቀሉ ስላገኘችው ድኅነት መስቀሉን አርማ፥ ድል መንሻ፥ የክርስቲያኖች መመኪያ፥ የክርስትና ምልክት፥ የቤተክርስቲያን ጌጥ አድርጋ ታከብረዋለች። አስቀድሞ ዳዊት 'ከቀስቱ ፊት ያመልጡ ዘንድ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠኻቸው።' ብሎ የተናገረው ስለ መስቀሉ እንደሆነ ታምናለች(መዝ. 59፥ 4-5)። በእሥራኤል ዘሥጋ ከግብጽ የመውጣት ታሪክ ሙሴ ባሕር የከፈለበት 'በትር' የእሥራኤል ዘነፍስ እረኛ ክርስቶስ ባሕረ እሳትን ለከፈለበት 'መስቀል' ምሳሌ መሆኑን ታስተምራለች(ዘጸ 14:16)። አማሌቃውያን ድል የተነሱበት የሙሴ የተዘረጋ እጅ ሰይጣናት የተሸነፉበት የክርስቶስ መስቀል ምሳሌ መሆኑንም ትመሰክራለች(ዘፀ 17:8-13)። ''ክፉ መንፈስ የተመታበትንና የቆሰለበትን ሰይፍ ካየ ወደ ሰይፉ ሊቀርብ አይችልም። ስለዚህ በቤታችን፥ በግድግዳችን፥ በግንባራችን፥ በክንዳችንና በደረታችን የመስቀል ምልክት ይኑረን። መስቀሉ ድላችን ነውና፥ ከተሰጡን በረከቶች ሁሉ ታላቁ በረከት ነው፥ የቤተክርስቲያን ጌጥ ነው፥ ስለዚህም በልባችሁ አትሙት።'' የሚለው የ4ኛው ክፍለ ዘመን ፀሓይ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር የቤተክርስቲያን ትምህርቷ ነው።
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
#ነገረመስቀል_(ክፍል 1)
(1) = "መስቀል" ስንል ምን ማለታችን ነው?
በኦርቶዶክሳዊ እሳቤ በቅዱሳት መጽሐፍት 'መስቀል' የሚሉ ቃላት እንደየአገባባቸው(Contextually) ሦስት ነገሮችን ይገልጣሉ። የመጀመሪያው 'መስቀል' ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ የተቀበለው መከራው ነው፥ ይህን መከራ 'መስቀል' እንለዋለን። ቅዱስ ያሬድ ''ዝንቱ መስቀል ለአዳም ዘአግብኦ ውስተ ገነት - አዳምን ወደ ገነት የመለሰው ይህ መስቀል ነው።'' ብሎ የተናገረው ስለ ጌታችን መከራ መስቀሉ ነው፥ መጽሐፈ ኪዳንም 'ይህ መስቀል በዓይን የሚታይ ሳይሆን በልብ የሚታሰብ ነው' ሲል የክርስቶስን መከራ ይገልጠዋል። ይህ የክርስቶስ መከራ መስቀል "ኃይላችን፥ ቤዛችን፥ ጽንዓችንና የነፍሳችን መዳኛ" ነው። ሁለተኛው 'መስቀል' ክርስቲያኖች የሚገጥማቸው መከራ ነው፥ ጌታችን 'መስቀሉን የማይሸከም...' እያለ ሲያሳስብ የነበረው ስለዚህ መከራ ነውና(ማቴ 10:38)። ሦስተኛው 'መስቀል' ክርስቶስ የተሰቀለበት 'ዕጸ መስቀል(የእንጨት መስቀል)' ሲሆን ለትምእርተ መስቀሉ(ለመስቀሉ ምልክት) መሠረት ሆኗል፥ ቅዱስ ቄርሎስም 'ይህ መስቀል በሕማማቱ ጊዜ የተዘረጋ የክርስቶስ መስቀሉ ምሳሌ እንደሆነ አምናለሁ።' በማለት ተናግሮታል።
ድጋሚ የተለጠፈ
ዲ.ን አምደመስቀል ሙሉጌታ
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
Repost from በአማን ወላዲተ አምላክ
#ነገረመስቀል_(ክፍል 1)
(1) = "መስቀል" ስንል ምን ማለታችን ነው?
በኦርቶዶክሳዊ እሳቤ በቅዱሳት መጽሐፍት 'መስቀል' የሚሉ ቃላት እንደየአገባባቸው(Contextually) ሦስት ነገሮችን ይገልጣሉ። የመጀመሪያው 'መስቀል' ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ የተቀበለው መከራው ነው፥ ይህን መከራ 'መስቀል' እንለዋለን። ቅዱስ ያሬድ ''ዝንቱ መስቀል ለአዳም ዘአግብኦ ውስተ ገነት - አዳምን ወደ ገነት የመለሰው ይህ መስቀል ነው።'' ብሎ የተናገረው ስለ ጌታችን መከራ መስቀሉ ነው፥ መጽሐፈ ኪዳንም 'ይህ መስቀል በዓይን የሚታይ ሳይሆን በልብ የሚታሰብ ነው' ሲል የክርስቶስን መከራ ይገልጠዋል። ይህ የክርስቶስ መከራ መስቀል "ኃይላችን፥ ቤዛችን፥ ጽንዓችንና የነፍሳችን መዳኛ" ነው። ሁለተኛው 'መስቀል' ክርስቲያኖች የሚገጥማቸው መከራ ነው፥ ጌታችን 'መስቀሉን የማይሸከም...' እያለ ሲያሳስብ የነበረው ስለዚህ መከራ ነውና(ማቴ 10:38)። ሦስተኛው 'መስቀል' ክርስቶስ የተሰቀለበት 'ዕጸ መስቀል(የእንጨት መስቀል)' ሲሆን ለትምእርተ መስቀሉ(ለመስቀሉ ምልክት) መሠረት ሆኗል፥ ቅዱስ ቄርሎስም 'ይህ መስቀል በሕማማቱ ጊዜ የተዘረጋ የክርስቶስ መስቀሉ ምሳሌ እንደሆነ አምናለሁ።' በማለት ተናግሮታል።
ድጋሚ የተለጠፈ
ዲ.ን አምደመስቀል ሙሉጌታ
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
እኛስ የተሰቀለው ክርስቶስን እንሰብካለን!
ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምዕመናን በጻፈላቸው መልእክቱ የመጀመሪያው ምዕራፍ[1ቆሮ 1:22] ''መቼም ቢሆን አይሁድ ምልክትን ይሻሉ'' ይላል፥ ሰው ሆኖ በቋንቋቸው በዕብራይስጥ ቢነግራቸው እንደ ሙሴ ባሕር ከፍለህ ጠላት ገድለህ መና አውርደህ ደመና ጋርደህ፥ እንደ ኢያሱ ፀሐይ አቁመህ በረድ አዝንመህ፥ እንደ ጌድዮን ጸምር ዘርግተህ፥ ጠል አውርደህ፥ እንደ ኤልያስ እሳት አዝንመህ ዝናም አቁመህ ምልክት ልታሳየን እንወዳለን ብለዋልና[ማቴ 12:38' ዮሐ 4:48' ሐዋ 17:18]። ቀጥሎም "የግሪክ ሰዎች ደግሞ ጥበብን ይሻሉ።'' ይላቸዋል። ፅርዓውያን ሙፃአ ነፋሳትን ምሕዋረ ክዋክብትን ሚጠተ ብርሃናትን እናውቃለን ባዮች ናቸውና።
ቅዱስ ጳውሎስ አይሁድ ምልክትን ፅርዓዊያን ሥጋዊ ጥበብን እንደሚሹ ካስረዳ በኋላ "ወንሕነሰ ንሰብክ ክርስቶስሃ ዘተሰቅለ - እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን።" በማለት ይመሰክራል።
እውነት ነው፥ እኛስ የተሰቀለው ክርስቶስን እንሰብካለን። ጥበብ የተባለ መድኃኒታችን እርሱ ነው እያልን፥ በመስቀሉ ጥልን የገደለና ሰላምን ያወጀ ንጉሣችን እርሱ ነው እያልን፥ ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበ ሊቀ ካህናት እርሱ ነው እያልን፥ የዓለምን ኃጢአት ሊያስወግድ የተሠዋ የእግዚአብሔር በግ እርሱ ነው እያልን፥ ከባሕርይ አባቱ ከአብና ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መሥዋዕቱን የተቀበለ የባሕርይ አምላክ እርሱ ነው እያልን። እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እናስተምራለን።
እንዲህ ብለን ብናስተምር ለአይሁድ የሳትን ይመስላቸዋል፥ 'እኚህ ሞኞች ሰማይ ምድር የማይችሉትን አምላክ ምን ቻለውና ተሰቀለ ይላሉ?' እያሉ፥ ለአረማዊያንም የምንሰንፍ ይመስላቸዋል፥ 'እኚህ ሞኞች ጌታን ቢደክም በረታ፥ ቢሸነፍ አሸነፈ ይሉታል እንጂ ታመመ ደከመ ጨርቅ ታጠቀ ግንድ ተሸከመ ይሉታል' ይላሉና። ከአይሁድ ከአረሚ ወገን ላመንን ለኛ፥ አንድም ከአይሁድ ከአረሚ ወገን ተለይተን ላመንን ለኛ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ኃይል ነው፥ በኃይል አንድ ስለሆነ ኃይሉም ስለተገለጸበት፥ የእግዚአብሔር ጥበብ ነው፥ በጥበብ አንድ ስለሆነ ጥበቡም ስለተገለጸበት።
[ማጣቀሻ ፦ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሐፍ ንባቡና ትርጓሜው፥ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት]
መስከረም 23/ 2014 ዓ.ም ተጽፎ የነበረ
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
ያለ ክርስቶስ ምንም ማድረግ አንችልም። እርሱ በወንጌል "ያለ እኔ ምንም ማድረግ አትችሉምና።" ብሎ እንደነገረን(ዮሐ. 15:5)። በክርስቶስ ግን ሁሉን ማድረግ አንችላለን። ሐዋርያው "ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።" እንዳለን(ፊልጵ 4:13)። ሁሉን የሚያስችለን ኃይላችን ክርስቶስ የተመሰገነ ነው።
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
#HappyNewYear
እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ በሰላም አሸጋገረን። መድኅን ክርስቶስ አዲሱን ዘመን የበረከትና የፍቅር ያድርግልን። መልካም አዲስ ዓመት።
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
እኔንስ የምትለውጠኝ መቼ ነው?
ጌታችን ሆይ... ቃል የገባልህንን መቼ ነው የምትፈጽምልን? ቃልህን ይዤ እጠይቅሃለው። ''አዲስ ልብን እሰጣችኋለሁ'' ብለሃል። ታዲያ የታለ አዲሱ ልብ? እኔ ራሴን ስመለከተው የድሮ ልቤ እንዳለ ነው። የትላንትናው መጥፎ ጠባዬ ልክ እንደ ትላንትናው ነው። የታለ ታዲያ ያ አዲሱ ልብ እሰጥሃለሁ ያልከኝ? እኔ ማወቅ እፈልጋለሁ፥ ከውስጥ እንድትቀይረው እፈልጋለሁ። አንተ አስተካክለኝ። ሥራብኝ፥ ደረቅ መሆኔን አስተካክለኝ። ስህተት አለብኝና ስህተቴን አስወግደው። ድርቅና አለብኝና ድርቅናዬን አስወግደው። ኃጢአት አለብኝና ኃጢአቴን አስወግደው።
ጌታ ሆይ... እኔ ውስጥ ሥራ፥ እናም ውስጤን አንጻው። መጋዙን መዶሻውን አንሳ፥ ሥራብኝ። ይህ መጥፎ እንጨት የተባለውን ለአንተ ወንበር አድርገው።
አዎ ጌታዬ ሆይ አስተካክለኝ።
[ከቅዱስነታቸው አቡነ ሺኖዳ ስብከት የተወሰደ]
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepta
በእርግጥ ድኅነታችን ከጎረቤቶቻችን ጋር ባለን ግንኙነት የተወሰነ ነው። ጎረቤቱን የሚወድ በብርሃን ይኖራል ማሰናከያም የለበትም። ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ያደርጋል። በቸርነቱ ብዛት መዳንን ገንዘብ ያደርጋታል።
ጎረቤቱን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል። የሚሄድበትንም አያውቅም፥ ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና። በጨለማ የሚኖር ደግሞ ከብርሃን እግዚአብሔር ተለይቷልና መንግሥተ ሰማያትን ሊያያት አይችልም።
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
''የተቤዣቸውን የሰው ልጆችን ለማሻገር መስቀሉን ድልድይ አድርጎ የሠራው አናጢ የተመሰገነ ነው።''
[St. Ephrem the syria, Homiliy on our Lord]
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
@OrthodoxConcepts
