en
Feedback
Ethiopian Muslim Network

Ethiopian Muslim Network

Open in Telegram

ስህተት ላይ አይቶህ ከማይመክርህ ⇨ ተቸግረህ አይቶህ ከማይረዳህ ⇨ ተዘናግተህ አይቶህ ከማያስታውስህ ጓደኛ ምንም ኸይር አትጠብቅ https://t.me/joinchat/AAAAAEiwq-sMQEIRM7VWqg

Show more
2 026
Subscribers
+124 hours
-27 days
-2430 days
Posts Archive
#ሴቶች_ካለ_ሒጃብ_በፍፁም_መንቀሳቀስ_የማይችሉባት_ኢራን !! ጊዜው ከ 60 አመት በፊት ገደማ ነው ያኔ ሳኡዲ አረቢያና ኢራን ክንፍ ያሉ ወዳጆች ነበሩ ። የኢራኑ ንጉስ ሻህ ሙሀመድ ሬዛ ፓህላዊ ለሳኡዲው ወዳጃቸው ንጉስ ፈይሰል ቢን አብዱልአዚዝ አልሳኡዲ እንደዚህ ሲሉ የወዳጅነታቸውን መከሯቸው ። " የተከበርክ ወንድሜ ፈይሰል ሆይ እባክህን ሳኡዲ እንዲትሰለጥን ለምእራባዊያን ስልጣኔ በሯን እንድትከፍት አድርጋት ሴቶቻችሁም በነፃነት የፈለጉትን እንዲለብሱ ፍቀዱላቸው ያኔ ህዝቡም ስልጡን ይሆናል " ሲሉ መከሯቸው ። ንጉስ ፈይሰልም በአምላሹ " ወንድሜ ሻህ ሙሀመድ ለምክርህና ለሳኡዲ ላለህ መልካም ሀሳብ አመሰግናለሁ ግና ሳኡዲ ኢስላማዊ እሴቶቿን ጥላ የምእራቡን ፀረኢስላማዊ ባህል አትቀበልም " ሲሉ መለሱለት ። ያኔ የያኔዋ ኢራን የዛሬዋ ሳኡዲ ነበረች የዛሬዋ ሳኡዲ ደግሞ የያኔዋ ኢራን ! ነገሩ የተገላቢጦሽ መሆኑ ነው ! በኢራን ኢስላማዊ አብዮት ፈንድቶ የአብዮቱ አቀጣጣይ ኢማም አያቱሏህ ኹመይኒ የንጉስ ሻህ ሙሀመድ ሬዛን መንበር አሽቀንጥረው ሲጥሉ ኢማሙ የምእራባውያን ስልጣኔ ሰይ*ጣ*ናዊ ነውና ከእንግድህ በኢራን ቦታ የለውም ኢራን እሴቷም ህገመንግስቷም ባህሏም ሼሪአ ብቻ ነው ሲሉ አወጁ ! የእርሳቸው ተተኪ አያቱሏህ አሊ ኻምንኢ የቀድማቸውን የኹመይኒን ሌጋሲ አጠኑና ኢራንን በአለማችን ላይ እጅግ ወግ አጥባቂዋ ሀገር አደረጓት ። ከዚያ በሗላ ኢራን እየከረረች ሳኡዲ እየላላች ሁለቱ ኦየተጠላሉ እየተጠላለፉ እየተፎካከሩ እየተዛዛቱ ሲሻቸው ፀባቸውን ሀይማኖታዊ ሲያሻቸው አረባዊና ፐርሺያዊ ሲያሻቸው ፖለታካዊና ወታደራዊ እያደረጉ እስከዛሬ ቀጠሉ ። ዛሬ ሳኡዲ ካለሂጃብ እንደፈለጉ የሚኬድባት የሙዚቃ ኮንሰርቶች የሚደገሱባት ስቴዳየሞች በሴትና በወንድ ጭፈራዎች የሚደምቁባቶ ምእራባውያንን ለመሆን ቢሊዮን ዶላሮችን እየከሰከሰች በክብረወሰን የእግርኳስ ከዋክብትን ፤ የሙዚቃው አለም ፈርጦችን ፤ የፊልሙ አለም አይከኖችን እያመጣች የባህል ንቅለተከላ ላይ ያለች ሀገር ሆናለች ! ኢራን በበኩሏ ከተቸከሉኩበት አይንቀለኝ ፤ የምእራባውያንን እሴት ሀገሬ ላይ ከማመጣ ፈርሼ ያስገኘኝ ብላ ከውጭም ጠላቶቿ ከውስጥም ነፃነት ፈላጊዎቿ ጋር እየተላተመች እነሆ ባለችበት አለች ! ኢራን ጭራሽ ይባስ ብሎ ሂጃብ የማያደርጉ ሴቶችን ለመቆጣጠር በየከተማው ካሜራዎችን ከመግጠምም አልፋ የመንገድ ላይና የትራፊክ ካሜራዎችን በየአደባባዩ ገጥማ ትገኛለች ። ኢራን አይደለም በእግር ካለሂጃብ መሄድና በመኪና ውስጥ እንኳ ሂጃብ ሳያደርጉ መንቀሳቀስ የማይቻልባት ሀገር ሆናለች ። ይህም በትራፊክ ካሜራዎች የመኪና አሽከርካሪዎችን መከታተል በመጀመሯ ነው ። አንድት ሴት በመኪናዋ ውስጥ ሆና ሂጃብ ካላደረገች በመጀመሪያ የማስጠንቀቂያ መልእክት የሚላክላት ሲሆን ሁለተኛ ከተገኘች በቁጥጥር ስር ሆና የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ይሰጣታል ይህን አልፋ ለሶስተኛ ጊዜ ከተገኘች ግን የእርምጃ ሰለባ ትሆንና ከርቼሌ ትወርዳለች ። አሁን ኢራን ውስጥ ሴቶች በዚህ መልኩ ብቻ የሚኖሩባት ሀገር ናት ። በአሁኑ ሰአት ሴቶች ካለሂጃብ መንቀሳቀስ የማይችሉባቸው ሀገራት ሁለት ብቻ እነርሱም ኢራንና በታሊባን የምትመራው አፍጋኒስታን ብቻ ናቸው ። የአፍጋኒስታንን ለየት የሚያደርገው ሴቶች ፊታቸውንም ጭምር እንዲሸፍኑ መደረጋቸው ነው ። #Seid_Mohammed_Alhabeshiy ቴሌግራም 👉 t.me/Seidsocial

📚 ዚክራችንን ምሉዕ የሚያደርጉ 2 ቁልፍ እምነቶች | አላህን በወጉ የማመሥገን ጣምራ ገጽታ | በኡስታዝ ኑዕማን ዓሊ ኻን [ NAK Amharic Studios ] . 📌 ማክሰኞና ቅዳሜ ተርጉመን የምናቀርበውን የቁርኣን ድንቃድንቆች ፕሮግራም እነሆ! አይተው ለሌሎች ቢያጋሩ የአጅሩ ተካፋይ ይሆናሉ! ቻነላችንንም ያግዛሉ! . 🔗 [ https://youtu.be/J60d6u3YQDE ]

📚 ስሜታችንን መከተል ይብቃን! | የተመቸንን እየመረጡ የመከተል ዝንባሌ በቁርኣን | በኡስታዝ ኑዕማን ዓሊ ኻን [ NAK Amharic Studios ] . 📌 ማክሰኞና ቅዳሜ ተርጉመን የምናቀርበውን የቁርኣን ድንቃድንቆች ፕሮግራም እነሆ! አይተው ለሌሎች ቢያጋሩ የአጅሩ ተካፋይ ይሆናሉ! ቻነላችንንም ያግዛሉ! . 🔗 [ https://youtu.be/Llu9IEeFFjg ]

photo content

የአሹራ ፆም! ዐሹራእ ተብሎ የሚጠራው ይህ የሙሃረም አስረኛ ቀን ነው፡፡ በዚህ ቀን አላህ ነብዩላህ ሙሳንና ተከታዮቻቸውን ከአምባገነኑ ከፊርዐውን አደጋ ባህሩን በማሻገር ያዳነበት ቀን በመሆኑ፡ እኛም ሙስሊሞች ከአይሁዶች ይልቅ ለሙሳ (ዐለይሂ ሰላም) ወንድምነት የተገባን በመሆናችን ልንጾመው ይገባል በማለት ነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ቀኑን በፆም እንድናሳልፈው አሳውቀውናል፡፡ በተለይ ይህን 10ኛውን ቀን (ዐሹራእ) መጾም ያለውን ጥቅም ተጠይቀው ሲመልሱ፡- ‹‹አላህ ያለፈውን አንድ ዓመት (ትናንሽ) ኃጢአት እንዲምር ተስፋ አደርጋለሁ›› ብለዋል(ሙስሊም ዘግበውታል )፡፡ ከአይሁዶች ጋርም ለመለየት ሲባል ቀደም ተብሎ የሙሃረምን ዘጠነኛውን ቀን ጨምሮ መፆም አልያ ደግሞ የሙሃረም 11ኛ ቀኑን ጨምሮ መፆም ሱና ነው፡፡ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል “አሏህ ካለ የሚመጣው ዓመት ላይ 9ኛውንም ቀን እንጾማለን “ ብለዋል ከዚህም በመነሳት ዑለማዎች ዘጠነኛውንም ቀን መጾም ሱና ነው ብለዋል። በመሆኑም ነገ ሐሙስ ሙሃረም 9 እና የሙሃረም 10. ዕለተ ጁምኣ የአሹራ ፆም ቤተሰቦቻችን፣ወዳጆቻችን እና ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁሉ ቀኑን በመፆም በኢባዳ እንዲያሳልፉት እናስታውሳቸው:: ለሃገራችን ሰላም እና መረጋጋትም ዱዓ ማድረግ አንዘንጋ መልካም ስራ እንዲሰራ ማስታወስ የሰሪውን ያህል ሙሉ ምንዳ ከአላህ (ሱ.ወ) ያስገኝልናል፡፡ አላህ ቀኑን ፆመው የአንድ አመት ወንጀላቸው ከሚማርላቸው ያድርገን አሚን

sticker.webp0.15 KB

አዲሱ 1445ኛው አመተ-ሂጅራ ከሰአታት በኋላ ይቆጠራል። ሂጅራ የነፃነት አየር ፍለጋ የተደረገ ስደት ነው፤ ያ ነፃነት የአላህን መንገድ የመከተል እውነተኛ ነፃነት ነው። ሂጅራን ስናስብ ነፃነትን እናስባለን፤ ነፃነትን ስናስብ ከመሬት ስበት ከፍ ብሎ ለአንድ አምላክ አላህ(ሱ.ወ.) ታዛዥ መሆንን እናስባለን። “ሙእሚን ማለት ሰዎች በንብረታቸው የሚያምኑት ሰው ነው፤ ስደተኛ(ሙሃጅር) ማለት ወንጀሎችንና ኃጢአቶችን የሚርቅ ሰው ነው።” ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዓ.ወ.) ባለፉት አመታት የሰራናቸውን መልካም ተግባራት ይበልጥ የምናጠናክርበት፣  አስበን ያላሳካናቸውን እቅዶቻችንን የምንከልስበትና የምንተገብርበት፥ በአጠቃላይ ከፈጣሪና ከፍጡራን ጋር እርቅ ፈጥረን በምድር ላይ መልካም አሻራችንን የምናሳርፍበት ዓመት ይሆንልን ዘንድ እመኛለሁ።

sticker.webp0.15 KB

sticker.webp0.15 KB

አስሩን የዙልሒጃ  ቀናት እንዴት እናሳልፍቻው? 1-እውነተኛ  ተውበት ማድረግ እነዚህንም ሆነ  ሌሎች የዒባዳ ቀናትን ለመቀበል ከሰራናቸው ወንጀሎች በመጸጸት ወደ አላህ መመለስ አለብን። አላህ እንዲ ብሏል:- { ምእምናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ።﴿ [ሱረ አል-ኑር፣31] 2- ቀኖቹን በአግባቡ ለመጠቀም ቁርጠኛ  መሆን በዙልሒጃ 10 ቀናት  ውስጥ ልዩ ትኩረት ሰጥተን አላህ በደነገጋቸው ኢባዳዎች ለማሳለፍ ከወዲሁ ራስን እና ያግዘናል ያልነውን ነገሮች በሙሉ ማዘጋጀ ተገቢ ነው። አላህ እንዲ ብሏል:- {እነዚያም በኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፤ አላህም በእርግጥ ክበጎ ሠሪዎች ጋር ነው።﴿[ሱረቱ አል-ዐንከቡት፣69] 3- ከወንጀል መራቅ የአላህን  ተእዛዛት መፈጸም ወደርሱ እንደሚያቃርብ ሁሉ የከለከላቸውን እና እርም ያደረጋቸውን ነገሮች መዳፈር ከርሱ መራቅን እና ከእዝነቱ ለመባረር ምክንያቶች ናቸው። 🕋 አስሩ የዙልሒጃ ቀናት ያላቸው ደረጃ 1-አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ  በነዚህ  ቀናት ምሏል አላህ በሆነ  ነገር ሲምል የዛን ነገር ትልቅነት እና  ደረጃ ያመለክታል፤ አላህ በትልቅ ነገር እንጅ አይምልም። አላህ እንዲህ ብሏል:- ﴾በጎህ እምላለሁ።በዐሥር ሌሊቶችም።﴿ [አል-ፈጅር፣1-2] ኢብን ከሢርን ጨምሮ አብዛኞች ሙፈሲሮች እንዳሉት ‘አስሩ ሌሊቶች’ የዙልሒጃ  የመጀመሪያዎቹ ናቸው። 2-አላህ በርሱ ውስጥ እሱን ማውሳትን የደነገገባት “የታወቁ ቀናት” መሆናቸው። አላህ እንዲህ ብሏል:- ﴾በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከማለዳ እንሰሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ፣ (ይመጡሃል)﴿ [አል-ሐጅ፣28] ኢብን ዐባስ እንዳሉት የታወቁ ቀኖች የተባሉት የዙሒጃ የመጀመሪያዎቹ አስሩ ቀኖች ናቸው። 3- ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከዱንያ ቀኖች በላጭ መሆኗን ተናግረዋል ከዐብደላህ ቢን ዐባስ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው ነቢዩ( ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:- [ከነዚህ አስርት(ከዙልሒጃ  የመጀመሪያዎቹ) ቀናት ይበልጥ አላህ ዘንድ በውስጣቸው የሚሰሩ መልካም ስራዎች ተወዳጅ የሚሆኑበት ቀን የለም።] ብለው ሲናገሩ ሶሐቦች፡- ”የአላህ መልእክተኛ ሆ! በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን?“ በማለት ጠየቁ፤ ነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም):- [ (አዎን!)ነፍሱንና ንብረቱን ይዞ የወጣ፣ ከዚያም አንዱንም ይዞ ያልተመለሰ ሰው ካልሆነ በስተቀር፣ በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን(አይበልጥም።)] አሉ። (አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።) 4- በአስሩ ቀናት ውስጥ የዐረፋ ቀን አለ። ዐረፋ ከዙልሒጃ የዘጠነኛው ቀን ነው። አላህ ﴾ ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ። ለናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ﴿የሚለውን አያህ ያወረደበት፣ወንጀሎች የሚማሩበት፣ የአላህ ባሮች ከእሳት ነጻ የሚባሉበት ቀን ነው። 5- በአስሩ ቀናት ውስጥ የእርድ ቀን (ዒደል-አድሐ) አለ። የዙሒጃ አስረኛው የውመነሕር(የእርድ ቀን)የዒድ ቀን  ነው። ከቀናቶች ሁሉ ታላቅ ቀን ነው። ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:-(አላህ ዘንድ ከቀናት ሁሉ ትልቁ የእርዱ(ዒደል-አድሐ) ቀን ነው።(አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።) 6-ዋና ዋና የዒባዳ አይነቶች በነዚህ ቀናት ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ። ኢብን ሐጀር(አላህ ይዘንላቸው እና) እንዲህ አሉ:- “የዙልሒጃ  አስሩ ቀናት ልዩ የሆኑበት ምክንያት ዋና ዋና የአምልኮ አይነቶች እነሱም:ሶላት፣ ጾም፣ ሶደቃ እና ሐጅ በውስጧ  ስለተሰበሰቡ ነው። ይህ(ስብስብ) በሌሎቹ ውስጥ አይገኝም።” 🕋በአስሩ የዙልሒጃ  ቀናት ውስጥ ከሚሰሩ ታላላቅ ዒባዳዎች:- ሐጅ እና ዑምራ፣ ጾም፣ ሶላት፣ ዚክር እና ደቃ ማብዛት ይገኙበታል። 🔖ሐዲስ በአማርኛ:- Telegram: t.me/HadithAmharic Instagram: instagram.com/HadithAmharic FB: fb.com/HadithAmharic

ኸሊፋው ዑመር (ረዐ) አንድ ቀን ሰዎችን ሰበሰበ። ወደ ሚንበሩም ወጣና እንዲህ አለ፦ «እኔ በጃሂሊያ ዘመን ለአዳዴዎቼ ፍየል አግድላቸው ነበር።እፍኝ ተምርን ወይም ዘቢብን ይከፍሉኝ ነበር። ለቀናት እርሷን አየተመገብኩ የምቆይ ሰው ነበርኩ።» ብሎ ንግግሩን ጨርሶ ከሚንበሩ ከወረደ በኋላ ዐብዱረሕማን ኢብኑ ዐውፍ (ረዐ) ፦ «ያ አሚረል ሙእሚኒን! ራስህን ከማቃለል ውጭ ምንም አልጨመርክም!»አለው። ዑመርም አለው ፦ « የዐውፍ ልጅ ሆይ! ወየውልህ! ለብቻዬ ስሆን ነፍሴ የሙእሚኖች መሪና የረሱል ኸሊፋ መሆኔን ነገረችኝ ፤ ስርአት ላሲዛት ፈልጌ ነው!» (አጥጦበቃቱል ኩብራ 3/293) አላህ ዑመርን ስራውን ይውደድለት፤በጀነትም ከርሱ ጋር ያጎራብተን! ነፍስያ እንዲህ ነች፤ መቀጣት ያስፈልጋታል። ቤትህ ስትገባ «አንተኮ የኡማው መከታ ነህ!» «ኡስታዝ ነህ!» «ለኡማው ተሰቃይተህ»፣ «ሀይላንድ ተንጠልጥሎብህ»፣ «አንተ የጀነት ሙሽራ»፣ «በቁስልህ ኡማው ተፈወሰ!» ፣ «የሙስሊሙ ተቆርቋሪ»፣ «ባለ ራእይ አክቲቪስት» ትልሀለች። በዚህ ሰአት የዑመርን መድሀኒት መጠቀም ፍቱን ነው። ወጣ ብለህ ለሰዎች «እኔኮ ሊስትሮ እየሰራሁ ያደግኩና የቀን ስራ እየሰራሁ ጉርሴን ስለቅም የነበርኩ ሰው ነኝ» ማለት ግድ ይላል። እኔም በፃፍኩት እናንተም ባነበባችሁት ተጠቃሚዎች ያድርገን!

الحمد الله: የዙል-ሒጃ ወር ጀምሯል። ዙል-ሒጃ በእስልምና ወር አቆጣጠር አስራ ሁለተኛው (የመጨረሻው) ወር ነው፡፡ በዚህ ወር ውስጥ ካሉት 29/30 ቀናት ውስጥ የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት እጅግ የተከበሩ ቀናቶች ናቸው፡፡ የፈለገ ሙሉውን ዘጠኝ ቀን: ካልሆነም የቻለውን ያክል መጾም ይችላል፡፡ዐብደላ ኢብኑ አባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- "መልካም ስራ ከዙል-ሒጃ አስርቱ ቀናት በልጦ አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነበት ቀናት የለም፡፡" በዚህ ሐዲሥ መሠረት ጾም "መልካም ሥራ" የተባለው ሐዲሥ ውስጥ ስለሚካተት በጾሙ የቻለውን ያክል መበርታት ይችላል፡፡ አላህን በነዚህ ቀናት ማውሳት: መዘከር እንዳለብን ይነግረናል፡፡ ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ባስተላለፉት ሐዲሥ ላይ ነቢዩ (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) እንዲህ ብለዋል፡- "በነዚህ ቀናት ውስጥ ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢልለሏህ)፤ተክቢር (አላሁ አክበር)፤ተሕሚድ (አል-ሐምዱ ሊላህ) ማለትን አብዙ" (አህመድ 7/224)

ታላቁ ዳዒ ሼይኽ ሙሀመድ አልአንሲ ብርሃናማ ቀናት በሚል ርእስ በሼይኽ ሆጄሌ መስጅድ በዛሬው እለት ያቀረቡትን ምርጥ ዳእዋ ሃሩን ሚዲያ ይዞላችሁ ቀርቧል ይከታተሉ https://youtu.be/buZyyOfdVfg

የዙልሒጃ ወር ነገ ሰኞ አንድ ብሎ ይጀምራል የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል ሰኔ 21 ዕለተ ረቡዕ ላይ ይውላል ። ከነገ ጀምሮ ያሉትን 10ቱን ቀናት በኢባዳ ማሳለፍ በሌላ ግዜ ከሚደረገው በብዙ ይበልጣል !

ስለ ረሱል ምን ያህል እናውቃለን 1 ─────────── ነብዩ ሙሀመድ صل الله عليه وسلم የኢብራሂም የዳዕዋ ፍሬ እና የዒሳ ብስራት ናቸው። ራሱን ለእርድ ዝግጁ ያደረገው የኢስማዔል ልጅም ናቸው። ከአባታቸው እስከ ዐድናን ድረስ ያለው የዘር ሀረግ በትክክለኛ መረጃዎች የፀደቀ ሲሆን ከዐድናን እስከ ኢስማዔል ድረስ ያሉት አያቶቻቸው ስም ግን ምንም አይነት አሳማኝ መረጃ ስላልተገኘላቸው በታሪክ አጥኚዎች መካከል ልዩነት እንደተንፀባረቀበት ኢማሙ አልበገዊይ፣ ኢብኑ ቀይም አልጀውዚይ፣ ኢማሙ አዝዘሀቢይና ሌሎችም ጠቅሰዋል። በጥቅሉ ነብዩ ምንም አይነት ብልግና ካልተቀላቀለበት የዘር ሀረግ፣ ከምርጥ ጎሳ እና ከልዩ ቤተሰብ የተመዘዙ ናቸው። ──────────

Audio from Zinet Ahmed

የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች አሁናዊ ችግሮችና መፍትሔዎቹ.pdf

★ ከመሪ ተቋማችን ጎን መሆን ግዴታ የሆነ ኢባዳ ነው ። -————————— ★ አዎ መሪ ተቋሟችን በመጥፎ ነገር እስካላዘዘን ድረስ መርሀባ ማለት ለአላህም ለመልእክተኛውም መርሀባ እንደማለት ነው ። ★ አቢ ሁረይራ ረዲየላሁ አንሁ ባወሩት ሀዲስ ነብያችን ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል ፣ (( እኔን የታዘዘ ለአላህ ታዟል : እኔን ያመፀ በአላህም አምጿል ፣ ለአሚር /መሪ ድርጅት/ ታዘዘ እኔን ታዟል ፣ አሚርን ያመፀ እኔንም አምጿል ።)) ሙስሊም ዘግቦታል ። عن أبي هريرة - رضي الله عنه - أن رسول الله - صلى الله عليه وسلم - قال: ((من أطاعني فقد أطاع الله، ومن يعصني فقد عصى الله، ومن يطع الأمير فقد أطاعني، ومن يعص الأمير فقد عصاني))؛ رواه مسلم.