cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

SING unto Christ

" መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።" (የዮሐንስ ራእይ 5:9-10)

Show more
Advertising posts
781
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1830 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

The Scripture says, “Call on the name of the Lord and He will answer you.” Sometimes, we call on people, call on our friends, call on our relatives. They can only do so much, but when you call on the Source, the Creator of the Universe, that’s when things happen that you couldn’t make happen. God wants us to depend on Him.
Show all...
የኢየሱስ ውልደት የፍጥረት ተስፋ የተፈጸመበት ነው።በዘፍጥረት የተሰጠው ተስፋ በውልደቱ ተፈጸመ።ጌታ እኮ የሰጠውን ተስፋ የሚጠብቅ ነው። ተባረክ
Show all...
#የእግዚአብሔርን ፍቅር መረዳት የቀን ጌጥህ ሲዋብ በእቅፍህ ዙፋን ላይ በክብር ለዋሉ አያውቀኝም ብዬ ለማማህ ለሁሉ አፍንጫ የለውም ቁመተ ኩራዝ ነው ብለህ ንገራቸው በፃድቅ ገፅህ ላይ የፅልመቴን ግድፈት ስለህ አሳያቸው ይወደኝ ነበረ ይንገበገብልኝ እኔነቴ ማርኮት ሰው አልሆን ሲለኝ ነው ከእቅፌ ያሸሸሁት ኧረ ያሳፍረኛል......... አይነ ልምነቱ ከሰው አይን ያሰቃል የገፁ ጥፉነት አመድ ያስመርቃል ብለህ ንገርብኝ ከእርዛቴ ገፈህ ከራብ ጥሜ ገፈህ አጀብ ደርብበት በረከሰ ክብሬ ነበረኝ እያልኩኝ ሞቴን ላዝግምበት። በፍቅርህ አድባር ይዤሀለሁ በገደልከው በቀኔ አጥንት አላውቀውም ብለህ ንገር አንተን መክዳት ታሪኬ ነው ከእራፊ ዝተት ልባሼ ወርቅ አልማዝ ቢከምሩበት በአለም ውብ ሳቅ የማይፋቅ የእንባዬ ጠባሳ አለበት ከቶ ሚወደኝ የለም እኔን ሚያፈቅር ከቶ በምድር በሰማይ ተጠላሁ ሀጢያቴ እንደ ጉም በዝቶ አምላክም አይቶኝ ከሰማይ በእነዚያ የፍቅር አይኖቹ ውራ ሆኜ ከምኖርበት ከዚያ የእሪያ ሰፈር የፍቅር ደብዳቤ ደረሰኝ ውድነቴን የሚያበስረኝ መልዕክቱን ከፍቼ ሳደምጥ ለካ ከቅድመ አለም በፊት እኛ ራሳችንን ሳንወደውም በፊት ሳናውቀውም በፊት ይች አለም ሳታውቀን እናት አባታችን ሳይወልዱንም በፊት ሳይወዱንም በፊት ገና በፊት በፊት አለም ሳይፈጠር ሳንወደውም ወዶን ነበር ባንወደውም ይወደናል ብንወደውም ይወደናል እንደገና ብንጠላው..... ባንወደውም ይወደናል ደሞ ታርቀን ብንመለስ ብንወደውም ይወደናል አሻፈረኝ ሄድኩኝ ብንል ባንወደውም ይወደናል ብንወደውም ይወደናል ባንወደውም ይወደናል ወደነው አይተናል ከድተነው አይተናል ፍቅሩ ሳይለወጥ አዎ ይወደናል የዕድሜው ዘመን ፣ የማይቆጠር ፊቱ ሰዎች ላይ ፣ የማይቋጠር በሞቱ ሞትን ፣ ወግቶ የገደለ ከዲያብሎስ አፍ ፣ እኔን ያስጣለ ለሟች ለመሞት ፣ ለነፍሱ ያልሳሳ ባሪያ ለማድረግ ፣ ጆሮ 'ማይበሳ ሰይጣን ሲያዘጋጅ ፣ የመስቀልን ሞት እንደሚነሳ ፣ ተናግሮ 'ሚሞት ያለምን ብልጠት በሞኝነቱ፣ ሞኝነት 'ሚያደርግ ፣ ድል በመንሳቱ ሲክዱት ጊዜ ፣ በቀል 'ማያስብ ሄዶ እንደገና ፣ የሚሰበስብ "ባለፈው እኮ" ፣ ብሎ 'ማይጠቅስ በቸርነቱ ፣ ሰው የሚመልስ ሽታው የፍቅር♥♥♥ ድምፁ የፍቅር♥♥♥ መጠሪያው ፍቅር♥♥♥ ምግባሩ ፍቅር♥♥♥ እራሱ ፍቅር የጠጡት ጊዜ ፣ ሰው የሚያሰክር ምን ውድ አለኝና ፣ ውዱን ሰጥሀለሁ ለኔ ውድ አንተ ነህ ፣ ባንተ ውድ ሆኛለሁ የኔ አልባስጥሮስ ፣ ልዩ ነው መአዛህ ሰማይን አውዷል ፣ ያ መልካሙ ሽታህ የኔ ውድ ሽቱ ፣ በላዬ የፈሰስከው ኃጢአት ቆሻሻዬን ፣ በደምህ ያጠብከው ቤቴን የሞላኸው ፣ በሚስብ ጠረንህ መለኪያ የለውም ፣ ለኔስ ውድነትህ እዩት የእኔን ወዳጅ ድፍረቴ ሊሆነኝ ሀፍረቴን ሊሸፍን እርቃኔን ሊያለብሰኝ እርሱ እርቃኑን ሲሆን በአደባባይ ሲያፍር በእሾህ ጉንጉን ሲነግስ እዩት የእኔን ፍቅር። እዩልኝ እዩልኝ ሲወጋልኝ ጎኑ ሲደማ ያ ደሙ ጻድቅ ሀጥያት ሲባል ተቀይሮ ስሙ ህመሜን ሲታመም ሲያቃስት ጌታዬ ጩኸቴን ሲጮኸው በእርሱ እፎይ ብዬ ተጠማሁ ብሎ ሲል እኔን እያረካኝ ስጋውን ቆራርሶ ደሙን ሲያፈስልኝ እዩትማ እዩልኝ በዳይ ሆኜ ሳለሁ ሊታረቀኝ ወዶ ልጁን በመቆጣት ቁጣውን አብርዶ ሀጥያቴ እንዲወገድ በጉን ያረደልኝ ያለምንም ምክንያት ሲወደኝ እዩልኝ። ታዲያ ፍቅር ማለት እንደዚህም አይደል የመውደድ ትርጉሙ ያልፍ የለ ከፊደል አዎን በደንብ ያልፋል ፍቅር ለሚወደው አንድ ልጁን አርዶ በደሙ ይፅፋል አዎን በደንብ ያልፋል የበዳዩን በደል በክቡር ልጁ ደም አጥቦ ያነፃዋል አዎን በደንብ ያልፋል ይቅር ካለ ወዲህ እንደባሪያ ሳይሆን እንደ ልጅ ያቅፈዋል አዎን በደንብ ያልፋል ከህግ ያፋታውን ፀጋውን አልብሶ ቀኙ ያስቀምጠዋል። ወድሀለው ብሎ ፊደል የማይሰድር በነጭ ወረቀት ላይ ቃላት የማያኖር ልብ ቅርፅ ስሎ በጦር የማይወጋ ይልቅ ለሚወደኝ ወዶ የተወጋ መውደዱን አይቼ እኔም የወደድኩት ወዳጄ ኢየሱስ ነው ውዴን እርሱን እዩት። TEMESGEN NEWCREATION
Show all...
ስለ መዝሙር ሳስብ... (while listening to Yidnu’s new Album) አሁን አሁን የ"መዝሙር" ክብደት በትውልዱ ዘንድ ዜሮ የገባ ይመስለኛል:: መዝሙር ሲሰራ መታሰቢያነቱ ለTikTok የሆነ ይመስል በ"እግዚያብሄርን በቲክቶክ ማምለክ" ስም ብዙ መራቆቶችንና አላግባብ ውዝዋዜን  እያየን እንገኛለን:: የወጣው መዝሙር ምን ያህል ሰዎችን ወደጌታ ቤት አመጣ የሚለው ጥያቄ ተረስቶ ምን ያህል ሰው ቲክቶክ ላይ ዙጥዙጥ አለበት ሆኗል ጥያቄው! አንዳንዴማ እዛ ቦታ ላይ ከቶ ሊገኝ የማይገባው መዝሙር ሁሉ ለዳንስ ወጥቶ ሳይ ይበሰጨኛል 🤦🏽‍♀️😒 ውጥንቅጡ የጠፋበት ዘመን! እና ሰሞኑን (አልበሙ ከወጣበት ቀን አንስቶ) ይድነቃቸውን እየሰማሁ ስለነበር ስገረም ነበር:: ኢየሱስን እንዴት እንዴት አድርጎ እንደሚሸላልመው... ታድሎ... BTW በዚሁ አጋጣሚ ይድኑ እግዚአብሔር ይባርክህ ማለት ፈልጋለሁ አንተን የሰጠን ይባረክ!! እና መዝሙሮቹ ሁሉ ልቤ ውስጥ ስለከረሙ በእርሱ መዝሙር ምሳሌ ብሰጥ መቼም ይዱ አይቀየመኝም ብዬ አምናለሁ... እና ለምሳሌ፦ ከ(ብቸኝነት አይሰማኝም) ውስጥ "ፍቅርህ ልቤ ውስጥ አለ ፍቅርህ አጥንቴ ውስጥ ፍቅርህ መንፈሴን ዘልቋል ፍቅርህ አጥለቅልቆኛል" ይህን የመሰለ ስንኝ አሁን እንዴት ሆኖ በምንስ መስፈርት ለቲክ ቶክ ይመጥን ይሆን? ምንስ ለብሰን ፣ ምንስ አይነት Facial expressions ኖሮን ደግሞስ በምን አይነት እንቅስቃሴ ይሆን ምንሰራው? መዝሙሩ ፍቅርን መግለጫም አይደል? ፍቅር ሊገለጥለት ለሚገባውም አይደል የተዘመረው? ኢየሱስን እንደምንወድ ለመናገር የግድ ቲክቶክ ላይ እንባችን እስኪመጣ ጠብቀን ፣ ቪድዮ አብርተን ፣ ድንገት ስህተት ቢኖር ቪዲዮውን እንደገና ቀድተን ( እንባ አሁንም እስኪመጣ ተጠብቆ😁) ይህ ማስመሰል ውስጥ እየከተተን አይመስላችሁም? እንደባለአይምሮ ስናስበው ይህ እውነተኛ አምልኮ ነው? እውነት እንደው ሁሉም የቲክቶክ ቪድዮ Genuine ነው? አልመሰለኝም! ለማንኛውም ዋናው ሃሳቤ በልባችን ጏዳ ለእግዚአብሔር ከምናቀርበው እውነተኛ አምልኮ ይልቅ ካሜራ ፊት የምናጠፋው ግዜ በልጦ ከስረን እንዳንገኝ ሰጋለሁ:: ትውልድ ሆይ ህይወትህ የኪሳራ እንዳይሆን ቆም በል ፣ አሰብ አድርግ እናም አስተውል:: ግዜ እኛን ለሰከንድ እንኳ ሳይጠብቅ ይነጉዳልና በጉብዝና ወራት ወንጌልን ሳንሰራ በካሜራ ፊት ስንወዛወዝ ዘመናችን እንዳያልቅ:: ባካችሁ እናስተውል! ስህተታችን ብዙዎችን አሸሸ የሸሹትን አይተን ከስህተታችንም ተምረን ሽሽታቸው በጎ እንዳይደለ በተግባር በማስገንዘብ ገንዘባችን እናድርጋቸው:: ልብ በሉ የአንድ ነፍስ መዳን በሰማይ ታላቅን ደስታ ያመጣል እባካችሁ ለአምላካችን ደስታው እንሁን!! ተባረኩ! እንግዲህ የ7ወር እርጉዝ ሴት እምቢ አትባልምና እባካችሁ ምክሬን ተቀበሉ! 😀😊❤️🙏🏽 ከነዓን አብይ #speakthetruthwithboldness 💪🏾
Show all...
I recommended this song
Show all...
መንፍስን ማሰልጠን | Apostle Tamrat T. | Discipleship Class | CJTv2022
Show all...
Are you striving or are you abiding? There are plenty of opportunities to strive. We can all live worried, stressed, trying to fix everything in our own strength. But that’s overwhelming. Come back to a place of peace. The Scripture says, “Your Father knows what you need.” He knows what you’re facing. He knows the dreams He’s placed in your heart. He sees the struggles, the unfair situations, the times you were put at a disadvantage. You don’t have to do life on your own, trying to make up for it, trying to accomplish that goal. Jesus said, “Come to Me and I will give you rest.” Stop your striving, depending on your own efforts, your own ability. That’s draining. If you’ll start depending on Him, relying on Him, you’ll feel that load lift off of you.
Show all...