en
Feedback
Tsegaye Demeke - Lawyer

Tsegaye Demeke - Lawyer

Open in Telegram

Legal Service

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
5 673
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ስለወለድ እና የወለድ ወለድ እና አራጣ የሕጉ ይዘት ምን ይላል? ===================== ሰዎች ንብረታቸውን የሚመለከቱ ጉዳዮችን በተመለከተ አንድን ግዴታ ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸው ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መካከል ስምምነት ሲፈፅሙ ውል እንዳደረጉ ከኢትዮጵያ የፍትሐብሄር ህግ ቁጥር 1675 መረዳት ይቻላል፡፡ አንድ ውል ከተደረገ በኋላ በአንደኛው ወይም በሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች ላይ ግዴታን ይጥላል፡፡ ይህንን ግዴታ በተባለው ጊዜ አለመፈፀም ወይም ጊዜ ካልተቀመጠ ደግሞ ማዘግየት የሚያስከትለውን ኪሳራ በተመለከተ ተዋዋይ ወገኖች ገደብ ወይም ቅጣት ወይም አንድ የተወሰነ ወለድ ግዴታውን ያልፈፀመ ተዋዋይ ወገን ውሉን ላከበረው ወገን እንዲከፍል ሲዋዋሉ መመልከት ወይም በፍርድ ቤቶች ሲወሰን ማየት የተለመደ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ወለድና የወለድ ወለድ (Interest on interest or compound interest) አስተሳሰብ ደንቦችን በተመለከተ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የኢትዩጵያ ህጎች ላይ ተመስርተን በጨረፍታ እንደሚከተለው እንዳስሳለን፡፡ ትርጓሜ ወለድ የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ስንመለከተው አንድ ገንዘብ ያበደረ ሰው ተበዳሪው ብድሩን በመጠቀሙ ላበዳሪው ወገን በበኩሉ የሚከፍለው ወይም አንድ የባንክ ደንበኛ ያለውን ገንዘብ በአንድ ባንክ ገንዘብ ተቀማጭ ሲያደርግ በመቶኛ የሚታሰብ ገንዘብን የሚመለከት ወይም ተበዳሪ የወሰደውን ገንዘብ ወይም እቃ በወቅቱ ባለመመለሱ የተነሳ የሚከፈል የገንዘብ ካሳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ወለድ ለገንዘብ ብድር ብቻ የሚከፈል ሳይሆን አንድ ግዴታን ባለመፈፀም ወይም በማዘግየት እና ይሄ ፍሬ ነገር ሲረጋገጥ የሚከፈል ጭምር ነው፡፡ በተጨማሪም ወለድ በስምምነት ወይም ያለስምምነት ማለትም በህግ አግባብ ሲወሰን ሊከፈል የሚችል ገንዘብ ነው፡፡ ለዚህ ፅሁፍ ዓላማ ሲባል በመቶኛ የሚታሰበውን ገንዘብን በሚመለከት ብቻ ያለውን እናያለን፡፡ የወለድ ወለድ ማለት በሚከፈል ወለድ ላይ በስምምነቱ ወይም በህግ መሰረት ወለዱን በወቅቱ ያልከፈለ ወገን በወለዱ ላይ የሚከፍለው ተጨማሪ የወለድ ወለድ እንደመቀጫ ያለ ገንዘብ ማለት ነው፡፡ ወለድ እና የወለድ ወለድ ከኢትዮጵያ ህግ አንፃር ወለድ ወለድን በተመለከተ የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 1751፣ 1803 እና 2478 በዋናነት ገዢ የሆኑ ድንጋጌዎች ሲሆኑ ሌሎች ህጋዊ ወለድን በሚመለከቱ በፍታብሄር ህጉ የተለያዩ መፅሀፎች ላይ ተመልክቷል፡፡ መሰረታዊ ወደሆኑት ድንጋጌዎች ስንመለስ የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 1751 ህጋዊ ወለድ (Legal Rate of Interest) ማለት በውል ያልተወሰነ ወለድ (ጥቅም) ከፋይ የሆነ ሰው በዓመት በመቶ ዘጠኝ (9%) ሂሳብ ይከፍላል በማለት በትርጓሜ መልክ ደንግጓል፡፡ ከዚህም ድንጋጌ መረዳት የሚቻለው አንደኛ በውል ያልተወሰነ የወለድ መጠንን በተመለከተ የወለድ መጠኑ የሚከፈለው ወይም የሚሰላው በዓመት ሆኖ ምጣኔውም በመቶ ዘጠኝ መሆኑን ነው፡፡ በአጭሩ ህጋዊ ወለድ በዓመት በመቶ ዘጠኝ የሚከፈልበት ገንዘብ ማለት ነው፡፡ ህጋዊ ወይም መደበኛው ወይም ደንበኛው ወለድ ማለት ይህ ከሆነ ተዋዋይ ወገኖች የወለድ መጠናቸውን መወሰን ይችላሉ ወይ? ከቻሉ ምን ያህል ድረስ? ተዋዋይ ወገኖች ውል ለመዋዋል ችሎታ ያላቸው (Capable) እና የሚዋዋሉበትን ጉዳይ በቂ በሆነ እርግጠኝነት የሚቻል (Possible)፣ ህጋዊ (Legal)፣ እንዲሁም ሞራላዊ ከሆነ የውላቸውን ጉዳይ (Object) የመወሰን መብት (FREEDOM OF CONTRACT) እንዳላቸው ከፍታብሄር ህጉ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል፡፡ ይህንን ማድረግ የሚችሉ ከሆነ ደግሞ የብድር ውል ሲዋዋሉ ውላቸው ያለወለድ ወይም በወለድ እንዲሆን ለማድረግ መብት አላቸው፡፡ ተዋዋዬቹ በመካከላቸው የሚያደርጉት ውል ከህግና ከሞራል የማይቃረንና የሚፈፀም ወይም የሚቻል ከሆነ በመካከላቸው እንደ ህግ ሆኖ እንደሚያገለግል ከፍ/ህ/ቁ 1731 መረዳት ይቻላል፡፡ ስለውሎች ውጤት በሚደነግገውና ስለውልን ስላለመፈፀም በሚያትተው የፍታብሄር የውል ህግ ክፍል አንቀፅ 1803 (2) ላይ የገንዘብ ዕዳን በማሳለፍ ስለሚከፈል ወለድ ሲያትት “በውለታው ውስጥ የበለጠ ወለድ የታሰበ እንደሆነ በዚሁ በከፍተኛው ወለድ መታሰቡ ይቀጥላል” በማለት ያስቀምጣል፡፡ ይህ ድንጋጌ የሚያስረዳው በውሉ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ሳይከፈል በቀረ የገንዘብ ዕዳ ላይ የሚታሰበውን የወለድ ምጣኔ ተዋዋዮቹ የተስማሙበት መጠን እንደሆነ የሚደነግግ ነው፡፡ በዚህም አግባብ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 81857 በቀን ጥር 13/2005 ዓ.ም በሰጠው አስገዳጅና ገዢ ውሳኔና የህግ ትርጉም አመልካች ለተጠሪ በውላቸው መሰረት በዋናው ገንዘብ ላይ የ14% ወለድ እንዲታሰብ መወሰኑ የፍ/ህ/ቁ 1803 (2) ያገናዘበ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ ይህም ማለት ማናቸውም ውሎች ከብድር ውል በስተቀር ተዋዋይ ወገኖች እስከፈለጉት የወለድ መጠን ድረስ መዋዋል ይችላሉ፣ ይህም ውላቸው በመካከላቸው በፍ/ህ/ቁ 1731 መሰረት የፀና ይሆናል፡፡ የዳኞች (ፍ/ቤቶች) የውሉን ሁኔታ በማየት ትርጓሜ የሚሰጡበትና ከውሉ በተቃራኒ ወለዱን የሚቀንሱበት ሁኔታ የለም ማለት አይቻልም፡፡ የብድር ውልን በተመለከተ ግን ተበዳሪው ወለድ እንዲከፍል የውል ቃል ከሌለ በቀር ላበዳሪው ወለድ መክፈል እንደሌለበት የፍ/ህ/ቁ 2479 ያስረዳል፡፡ ይህ ማለት ግን ባለእዳው ግዴታውን ባለመወጣቱና በውላቸው ላይ ወለድ ባይታሰብ እንኳን በፍ/ቤት ለሚቀርብበት ክስ ሀላፊ ሲሆን በከሳሽ የሚጠየቀውንና በፍ/ቤት የሚወሰነውን ህጋዊውን ወለድ ያስቀራል ማለት አይደለም፡፡ የብድር ውል ተዋዋዬች ውላቸውን በወለድ የማድረግ መብት አላቸው፡፡ በወለድ እንዲሆን ሲወስኑ የወለድ መጠኑንም እግረመንገዳቸውን የመወሰን መብትም አላቸው፡፡ በወለድ እንዲሆን ከወሰኑ ከህጋዊው ወለድ ማሳነስ ወይም ማስበለጥ ወይም እኩል ማድረግ ይችላሉ፡፡ የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 2479(1) የብድር ውል ተዋዋይ ወገኖች ተበዳሪው ሊከፍለው የሚገባው የወለድ መጠን በዓመት ከአስራ ሁለት በመቶ (12%) በላይ ሊበልጥ እንደማይችል ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ ሁለት ነገሮችን መገንዘብ ይቻላል፡፡ አንደኛው- ተዋዋይ ወገኖች የወለድ መጠኑን በተመለከተ እስከ 12% ድረስ መወሰን እንደሚችሉ መብትና ነፃነት ያላቸው መሆኑን ነው፡፡ It is also known as Contract Rate. ሁለተኛው- የክልከላ ይዘት ያለው ሲሆን እሱም ተዋዋዬቹ 12% በላይ መዋዋል እንደማይችሉና የወለድ መጠኑም በዓመት እንጂ በወር ወይም በሳምንት ወይም በሌላ ስሌት ማድረግ እንደማይችሉ ያስረዳል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ነገር የአራጣ ጉዳይ ነው፡፡ አራጣን በተመለከተ በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ የህሊናን ወይም የሰውን ችግር መሰረት በማድረግ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ስር በአንቀፅ 712 (1) (ሀ) ላይ እንደተመለከተው “ማንም ሰው የተበዳዩን ችግረኝነት፣ የበታችነቱን፣ ወይም የገንዘብ ችግሩን፣ ወይም መንፈሰ ደካማነቱን፣ ወይም ልምድ ወይም ችሎታ የሌለው መሆኑን መሰረት በማድረግ በህግ ከተፈቀደው ወለድ በላይ ገንዘብ ያበደረው እንደሆነ በቀላል እስራት፣ ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል” በማለት ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ የምንረዳው አራጣ ማለት ህጉ ከፈቀደው የብድር ወለድ መጠን በላይ ተዋውሎ ማበደር ማለት ነው፡፡ በአንቀፁ የተጠቀሱ ሌሎች ወንጀልን የሚያቋቁሙ

በው ክስ ለአንድ ፍርድ ቤት ከቀረበበት ቀን ጀምሮና ይኸውም ባለእዳው የአንድ ዓመት ሙሉ ሒሳብ ያለበት እንደሆነ ነው፡፡” ከዚህ የህግ ድንጋጌ የምንረዳው በወለድ ላይ ወለድ በመርህ ደረጃ የሌለ መሆኑን ነው፡፡ ነገር ግን ከላይ በድንጋጌው ውስጥ የተጠቀሱት ሁኔታዎች ሲሟሉ የወለድ ወለድ ሊኖር የሚችልበትን ሁኔታ ያስረዳል፡፡ እነዚህም ሁኔታዎች፡- ሀ) ባለእዳው በየጊዜው የሚከፍለው ገንዘብ እና ለባለገንዘቡ እንደገቢ (በተወሰነ ጊዜ የሚገኝ እንጂ የተከማቸ እዳን አያመለክትም) የሚያገለግል ሲሆን፤ ለ) እዳውን ለማስከፈል በፍ/ቤት በባለገንዘቡ ክስ ሲመሰረት፤ እና ሐ) ባለእዳው ለአንድ ዓመት ክፍያውን ሳይከፍል የቀረ እንደሆነ ወይም ባለገንዘቡ ባለእዳውን የሚጠይቀው የአንድ ዓመት ክፍያን ሲሆን ነው፡፡ በመሆኑም ህጉ የወለድ ወለድን በሁኔታ ላይ ብቻ ተመስርቶ እንዲኖር የፈቀደበት ሀተታ ዘምክንያት አንደኛው ባለገንዘቡ ገንዘቡን ለመቀበል በጣም የሚቸኩልበት ሁኔታ ላይ አይደለም ተብሎ ግምት ስለሚወሰድ ነው ምክንያቱም በየጊዜው የሚከፈል ገንዘብ በመሆኑ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት የወለድ ወለድ በመርህ ደረጃ ቢፈቀድ ባለእዳው በወለድ ወለዱ መጠራቀም ወይም መከማቸት እዳው በዝቶ ባለእዳውን አደጋ ውስጥ ላለመክተት በማሰብ ነው፡፡ ይህ የህጉ ግምትና ድንጋጌ ባለገንዘቡ ያለውን መብት እና ባለዕዳው ያለበትን ግዴታ በተነፃፃሪ ሁኔታ ባለዕዳው የአንድ ዓመት እዳ ካለበትና ይህንኑ ጥያቄ በፍ/ቤት ክስ ተመስርቶ በባለገንዘቡ ከተጠየቀ ባለገንዘቡ ባለዕዳው ላይ ካለው ያልተከፈለ እዳ እና ወለድ በተጨማሪ የወለድ ወለድ እንዲከፈለው የመጠየቅ መብት እንዳለው መደንገጉ ትክክለኛና አግባብ (Fair) ከሚባል በስተቀር የሚነቀፍ አይደለም፡፡ በወለድ ወለድ ላይ ሌላ ወለድ ማሰብ ፈፅሞ በህጋችን ቦታ የተሰጠው ጉዳይም አይደለም፡፡ መቋጫ ሌላኛውና የመጨረሻው ጉዳይ በብድር ለተሰጠ ወለድ የመጠየቂያ ጊዜ ምን ያህል ነው የሚለውን ተመልክተን ይህን ፅሁፍ እናበቃለን፡፡ በዚህም መሰረት የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 2024 እንደሚከተለው ይነበባል፡፡ ቁ. 2024. በሁለት ዓመት የተወሰነ ጊዜ እዳው እንዲከፈል መጠየቅ ከሚገባበት ቀን ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ሳይከፈል የቀረ ገንዘብ እንደተከፈለ የሚቆጠረው፤ (ረ) በብድር የተሰጠ የገንዘብ ወለድና በጠቅላላውም የዓመት ጊዜ ተወስኖለት በየዓመቱ ወይም ከዚህ ባነሰ የጊዜ ውሳኔ ውስጥ ሊከፈል የሚገባው ዕዳ የሆነ እንደሆነ ነው፡፡ በድንጋጌው ፊደል (ረ) ስር የተመለከተው ሲታይ በብድር የተሠጠ ወይም በማናቸውም የአከፋፈል ሁኔታ በየአመቱ ወይም ከአመት ባነሰ ጊዜ እየተከፈለ እንዲያልቅ ጊዜ ተቆርጦለት የተሰጠ ገንዘብ ላይ የሚታሰብ ወለድ እዳው ከበሰለበት ወይም በየተወሰነ ጊዜ የሚከፈል ገንዘብ ከሆነ ደግሞ ገንዘቡ ተከፍሎ ማለቅ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ ሁለት ዓመት ያለፈ እንደሆነ በእነዚህ ክፍያዎች (እዳዎች) ላይ ሊጠየቅ የሚችለው የወለድ ክፍያ እንደተከፈለ የህግ ግምት የሚወሰድ መሆኑን ያሳያል፡፡ በመሆኑም ይህ ድንጋጌ አስገዳጅ የሆነ የሕግ ግምት ያለው ሲሆን በተጨማሪ ደግሞ ማናቸውም የተፈጥሮም ሆነ የሕግ ሰው (ባንክና ሌሎች አበዳሪ ተቋማት) የገንዘብ ብድር ካበደረ በኋላ ብድሩ ተከፍሎ የሚያልቅበትን የጊዜ ገደብ ካበቃ ከሁለት ዓመት በኋላ የብድሩ የወለድ ይከፈለኝ ጥያቄ በሕግ እንደተከፈለ የሚገመት መሆኑን የሚደነግግ ድንጋጌ በመሆኑ ተበዳሪው ወለዱን የመክፈል ግዴታው በህግ ቀሪ ስለሚሆንለት አበዳሪውን በእጅጉ የሚጎዳ ጉዳይ በመሆኑ በጥንቃቄ ሊታይ ይገባል የሚል እምነት አለኝ፡፡ WRITTEN BY አብዱሰላም ሳዲቅ ሙክታር

lements) መሟላታቸውን ማረጋገጥ እንደተጠበቀ ሆኖ ማለት ነው፡፡ ከላይ እንደተመለከትነው ህጉ የፈቀደው የብድር ውል ወለድ መጠን በዓመት 12% ድረስ ብቻ ነው፡፡ ባንኮች ለደንበኞቻቸው የሚያበድሩትን ከፍተኛ መጠን ያለውን የወለድ መጠን አያካትትም፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በየካቲት 11 ቀን 2005 ዓ.ም በሰ.መ.ቁ 80119 በሰጠው ገዢ የህግ ትርጉምና ውሳኔ በቅፅ 15 እንደታተመው በወር 10% ወለድ ታስቦ እንዲከፈል በመስማማት ገንዘብ ማበደር በአራጣ የወንጀል ድርጊት የሚያስጠይቅ መሆኑን ትንታኔ በመስጠት ተከሳሹ በሁለት የአራጣ የወንጀል ድርጊቶች ጥፋተኛ ተብለው በሶስት አመት ፅኑ እስራትና በብር 4000.00 (አራት ሺህ) የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ በማለት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠውን ውሳኔ አፅንቶታል፡፡ በመሆኑም የብድር ውል ተዋዋዬች የወለድ መጠኑን በሚወስኑበት ሰዓት በህግ ከተፈቀደው በላይ ወለድ እንዳይዋዋሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ባንኮች ለደንበኞቻቸው የሚያበድሩበት አግባብ እንደተጠበቀ ነው፡፡ ከላይ የተመለከትነው የብድር ውል ወለድ መጠን ባንኮችን ይመለከታል ወይ? እንደሚታወቀው ባንኮች ከጥንስሳቸው ጀምሮ የደንበኞቻቸውን ተቀማጭ ገንዘብ በማስቀመጥ ደንበኞቻቸው ላስቀመጡት ገንዘብ ወለድ እንደሚሰጡ ይታወቃል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የገንዘብ ችግር ላጋጠመው ደንበኞቻቸው ወይም ኢንቨስትመንቱን ማስፋፋት ለሚፈልግ ባለሀብት ወይም ብድር ለሚፈልግ ማንኛውም ሰው ብድር በብድር ውል መያዣ በመያዝ ይሰጣሉ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ /እንደተሻሻለ/ አዋጅ ቁጥር 591/2000 አንቀፅ 5 (4) ስር እንደተመለከተው ብሔራዊ ባንኩ የገንዘብ ብድር አቅርቦት በተፈለገው መጠን መገኘትን፣ እንዲሁም የወለድ ተመንና ሌሎች ክፍያዎችን የመወሰንና የመቆጣጠር ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በዚሁ አዋጅ አንቀፅ 27 ብሔራዊ ባንኩ አዋጁንና አዋጁን ተመስርተው የሚወጡ ደንቦችን ለማስፈፀም የሚረዱ መመሪያዎችን ለማውጣት ስልጣን በአዋጁ ተሰጥቶታል፡፡ በዚህ አግባብ ብሔራዊ ባንኩ መመሪያ ቁጥር NBE/INT/11/2010 በማውጣት ንግድ ባንኮች የብድር ውል ለደንበኞቻቸው በሚሰጡበት ወቅት ላበደሩት ብድር የወለዱን ምጣኔ በራሳቸው እንዲወስኑ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል፡፡ በመሆኑም ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ የሚታሰበው የወለድ ምጣኔ ከላይ እንደተመለከተው በፍታብሄር ህጉ እንደተመለከተው የወለድ ጣራው በዓመት እስከ 12 % ብቻ ሳይሆን ከዛም በላይ ማድረግ እንደሚችሉ ነው፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ፀሀፊው በተመለከተው አንድ በሀገሪቱ ውስጥ በሚገኝ ባንክ እና በግለሰብ መካከል በተደረገ የብድር ውል ስምምነት ግለሰቡ የብር 364,000 (ሶስት መቶ ስልሳ አራት ሺ) ለመበደር ፈልጎ አበዳሪ ባንኩ በተሰጠው ብድር ላይ በዓመት አስራ ዘጠኝ ነጥብ አራት በመቶ (19.04 %) ወለድ በየእለቱ ቀሪ ገንዘብ ላይ በየቀኑ ይታሰባል፡፡ ይህ የወለድ መጠን ባንኩ በየጊዜው እያሻሻለ በሚያወጣው የወለድ ተመን (Interest Rate) የሚተካ ይሆናል በሚል ውላቸው ውስጥ አካተዋል፡፡ እዚህ ጋር መታየት ያለበት ጉዳይ ንግድ ባንኮች በህግ የሰውነት መብት የተሰጣቸውና ለትርፍ የተቋቋሙ ሆነው ሳለ ሌላኛው ተዋዋይ ወገን በመካከላቸው ያለውን ጉዳይ የመዋዋል ነፃነት ወደጎን የሚል እና ለባንኩ የመደራደር አቅሙን የሚጨምር (Bargaining power) ከመሆኑም በላይ ባንኩ በፈለገው ጊዜ (የብሔራዊ ባንክ ቁጥጥር እንደተጠበቀ ነው) የወለድ ተመኑን የማሻሻል ስልጣን ያለው መሆኑ የተበዳሪውን የገንዘብ ችግር ከግምት የማያስገባ ከመሆኑም በላይ ተበዳሪው ቅድሚያ ከተስማማበት የወለድ ምጣኔ የበለጠ እንዲከፍል “በቅድሚያ ስምምነት” ስም ብቻና የተበዳሪውን ችግር መሰረት በማድረግ ተበዳሪው ከባድ የውል ግዴታ ውስጥ የሚያስገባውን ሁኔታ ይፈጥራል፤ በህግ ፊት የተፈጥሮ ሰውና በህግ ሰውነት የተሰጣቸውን ሰዎች በአንድ አገር ህግ ውስጥ በእኩል አይን እንዳይታዩ ያደርጋል (በሌላ በኩል ውል የመዋዋል፣የመክሰስና የመከሰስ እኩል መብት እንዳላቸው ልብ ይሏል)፤ ባንኮች ላበደሩት ብድር ክፍያ በወቅቱ ተመላሽ ባይደረግላቸው በመያዣ የያዙትን የተበዳሪውን ንብረት የፍ/ቤት ሂደትን መከተል ሳያስፈልጋቸው (DUE PROCESS OF LAW) በራሳቸው ጊዜ በመሸጥ የሽያጩን ገንዘብ ለብድሩ እዳ ክፍያ የማዋልና ገዢ ካልተገኘም በፍ/ሥ/ሥ/ህጉ መሰረት ሁለት ጊዜ ጨረታ በማውጣት በመያዣ የተያዘውን ንብረት በጨረታው ላይ በወጣው መጠን የራሳቸው ንብረት ለማድረግ እንደሚችሉ ስልጣን የተሰጣቸው መሆኑን ስለ በባንክ በመያዣ ስለተያዘ የማይንቀሳቀሱና የሚንቀሳቀሱ ንብረቶች የወጣ አዋጅ ቁጥር 97/1990፣ ስለንግድ ተቋም የዋስትና መያዣ የወጣ አዋጅ ቁጥር 98/1990 እና በባንክ በመያዣ ስለተያዘ ንብረት የወጣውን አዋጅ ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ቁጥር 216/1992 “ን” ስንመለከት የግለሰቦችን ሰብዓዊና ህገ-መንግስታዊ ንብረት የማፍራት መብት “በህጋዊ” መንገድ የመንጠቅ አቅም ያላቸው በመሆኑ በህግ አውጪው አካል በጥንቃቄ ሊታዩ ይገባል፡፡ በአጠቃላይ ባንኩ ብድር በሚሰጥበት ጊዜ የሚያስከፍለው ወለድና ሌሎች ወጪዎች ተበዳሪው ከችግሩ የተነሳ ብድሩን መክፈል ሳይችል ቢቀር ከተበደረው ዋና ገንዘብ በላይ ወለዱና ሌሎች ወጪዎች እንደሚበዙ መገመት የማይከብድ ሆኖ ተበዳሪው እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ለግብር ከፋዩ ዜጋ እና ለመንግስት ሸክም ስለሚሆን ባንኮች በሚሰጡት የብድር ወለድ ምጣኔ ላይ በጥናት ላይ ተመስርቶ እንደፍታብሄር ህጉ በዓመት 12 % እንዲሆን በማድረግ በሀገሪቱ ላይ ወጥ የሆነ የብድር ወለድ ምጣኔ ህግ እንዲኖር ቢደረግ ወይም የተበዳሪዎችን አቅም ባገናዘበ መልኩ የብድር ወለዱ ምጣኔ ገደብ ቢበጅለት የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡ የወለድ ወለድ የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 1804 እና 2481 የወለድ ወለድን በተመለከተ ይደነግጋል፡፡ የወለድ ወለድን በሚመለከት በፍታብሄር ህጋችን ውስጥ አለ ወይስ የለም የሚለውን በተመለከተ የህግ ባለሙያዎች የተለያየ አቋም ያላቸው ሲሆን የፅሁፉ አንዱ ዓላማም ይህንን ፅሁፍ መነሻ በማድረግ ባለሙያዎችንና አንባብያንን ለውይይት መጋበዝ በመሆኑ የፀሀፊውን አቋም እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡ በብድር ውል ላይ ተዋዋይ ወገኖች ወለዱ ከዋናው ገንዘብ ጋራ ተጨማሪ ሆኖ ወለድ ይወልዳል ብለው አስቀድመው ለመዋዋል እንደማይችሉ የፍ/ህ/ቁ 2481 (1) በግልፅ ያመለክታል፡፡ በዚህ የህግ ድንጋጌ መሰረት በተሰጠው ብድርና በተስማሙት የወለድ መጠን ላይ ሁለቱ ገንዘቦች በአንድ ላይ ሁነው ሌላ ወለድ እንዲኖር መዋዋል የከለከለው አበዳሪው የተበዳሪውን የገንዘብ ችግር ምክንያት በማድረግ ያለአግባብ ሁለት ጊዜ ወለድ በማስከፈል እንዳይበለፅግ በማሰብ ሲሆን በሌላ በኩል ተበዳሪውን ሊሸከመው የማይችለው እዳ ውስጥ እንዳይገባ በማድረግ የማመዛዘን ስራ ነው ህጉ የሰራው፡፡ በዚህ የሕግ ድንጋጌ መሰረት በብድር ውል ግንኙነት ላይ የወለድ ወለድ በሀገራችን ህግ የተከለከለ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ሌላኛው የወለድ ወለድን የሚመለከተው የፍታብሄር ህግ ቁጥር 1804 ሲሆን ንዑስ ቁጥር 1 እንደሚከተለው ይነበባል፡፡ “ከባለእዳው ላይ ያለው ገንዘብ በየጊዜው የሚከፈል ሆኖ ለባለገንዘቡ በየጊዜው የሚገኘው ገቢ የሆነ እንደሆነ ለምሳሌ ኪራይ፣ የርስት አላባ፣ የዘወትር ጡረታ ወይም ለህይወቱ የተወሰነ ጡረታ፣ የአንድ ካፒታል ወለድ፣ ይህ የመሰለ ከሆነ ደንበኛው ወለድ የሚታሰ

ስለወለድ እና የወለድ ወለድ እና አራጣ የሕጉ ይዘት ምን ይላል? ============= ሰዎች ንብረታቸውን የሚመለከቱ ጉዳዮችን በተመለከተ አንድን ግዴታ ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸው ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መካከል ስምምነት ሲፈፅሙ ውል እንዳደረጉ ከኢትዮጵያ የፍትሐብሄር ህግ ቁጥር 1675 መረዳት ይቻላል፡፡ አንድ ውል ከተደረገ በኋላ በአንደኛው ወይም በሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች ላይ ግዴታን ይጥላል፡፡ ይህንን ግዴታ በተባለው ጊዜ አለመፈፀም ወይም ጊዜ ካልተቀመጠ ደግሞ ማዘግየት የሚያስከትለውን ኪሳራ በተመለከተ ተዋዋይ ወገኖች ገደብ ወይም ቅጣት ወይም አንድ የተወሰነ ወለድ ግዴታውን ያልፈፀመ ተዋዋይ ወገን ውሉን ላከበረው ወገን እንዲከፍል ሲዋዋሉ መመልከት ወይም በፍርድ ቤቶች ሲወሰን ማየት የተለመደ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ወለድና የወለድ ወለድ (Interest on interest or compound interest) አስተሳሰብ ደንቦችን በተመለከተ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የኢትዩጵያ ህጎች ላይ ተመስርተን በጨረፍታ እንደሚከተለው እንዳስሳለን፡፡ ትርጓሜ ወለድ የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ስንመለከተው አንድ ገንዘብ ያበደረ ሰው ተበዳሪው ብድሩን በመጠቀሙ ላበዳሪው ወገን በበኩሉ የሚከፍለው ወይም አንድ የባንክ ደንበኛ ያለውን ገንዘብ በአንድ ባንክ ገንዘብ ተቀማጭ ሲያደርግ በመቶኛ የሚታሰብ ገንዘብን የሚመለከት ወይም ተበዳሪ የወሰደውን ገንዘብ ወይም እቃ በወቅቱ ባለመመለሱ የተነሳ የሚከፈል የገንዘብ ካሳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ወለድ ለገንዘብ ብድር ብቻ የሚከፈል ሳይሆን አንድ ግዴታን ባለመፈፀም ወይም በማዘግየት እና ይሄ ፍሬ ነገር ሲረጋገጥ የሚከፈል ጭምር ነው፡፡ በተጨማሪም ወለድ በስምምነት ወይም ያለስምምነት ማለትም በህግ አግባብ ሲወሰን ሊከፈል የሚችል ገንዘብ ነው፡፡ ለዚህ ፅሁፍ ዓላማ ሲባል በመቶኛ የሚታሰበውን ገንዘብን በሚመለከት ብቻ ያለውን እናያለን፡፡ የወለድ ወለድ ማለት በሚከፈል ወለድ ላይ በስምምነቱ ወይም በህግ መሰረት ወለዱን በወቅቱ ያልከፈለ ወገን በወለዱ ላይ የሚከፍለው ተጨማሪ የወለድ ወለድ እንደመቀጫ ያለ ገንዘብ ማለት ነው፡፡ ወለድ እና የወለድ ወለድ ከኢትዮጵያ ህግ አንፃር ወለድ ወለድን በተመለከተ የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 1751፣ 1803 እና 2478 በዋናነት ገዢ የሆኑ ድንጋጌዎች ሲሆኑ ሌሎች ህጋዊ ወለድን በሚመለከቱ በፍታብሄር ህጉ የተለያዩ መፅሀፎች ላይ ተመልክቷል፡፡ መሰረታዊ ወደሆኑት ድንጋጌዎች ስንመለስ የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 1751 ህጋዊ ወለድ (Legal Rate of Interest) ማለት በውል ያልተወሰነ ወለድ (ጥቅም) ከፋይ የሆነ ሰው በዓመት በመቶ ዘጠኝ (9%) ሂሳብ ይከፍላል በማለት በትርጓሜ መልክ ደንግጓል፡፡ ከዚህም ድንጋጌ መረዳት የሚቻለው አንደኛ በውል ያልተወሰነ የወለድ መጠንን በተመለከተ የወለድ መጠኑ የሚከፈለው ወይም የሚሰላው በዓመት ሆኖ ምጣኔውም በመቶ ዘጠኝ መሆኑን ነው፡፡ በአጭሩ ህጋዊ ወለድ በዓመት በመቶ ዘጠኝ የሚከፈልበት ገንዘብ ማለት ነው፡፡ ህጋዊ ወይም መደበኛው ወይም ደንበኛው ወለድ ማለት ይህ ከሆነ ተዋዋይ ወገኖች የወለድ መጠናቸውን መወሰን ይችላሉ ወይ? ከቻሉ ምን ያህል ድረስ? ተዋዋይ ወገኖች ውል ለመዋዋል ችሎታ ያላቸው (Capable) እና የሚዋዋሉበትን ጉዳይ በቂ በሆነ እርግጠኝነት የሚቻል (Possible)፣ ህጋዊ (Legal)፣ እንዲሁም ሞራላዊ ከሆነ የውላቸውን ጉዳይ (Object) የመወሰን መብት (FREEDOM OF CONTRACT) እንዳላቸው ከፍታብሄር ህጉ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል፡፡ ይህንን ማድረግ የሚችሉ ከሆነ ደግሞ የብድር ውል ሲዋዋሉ ውላቸው ያለወለድ ወይም በወለድ እንዲሆን ለማድረግ መብት አላቸው፡፡ ተዋዋዬቹ በመካከላቸው የሚያደርጉት ውል ከህግና ከሞራል የማይቃረንና የሚፈፀም ወይም የሚቻል ከሆነ በመካከላቸው እንደ ህግ ሆኖ እንደሚያገለግል ከፍ/ህ/ቁ 1731 መረዳት ይቻላል፡፡ ስለውሎች ውጤት በሚደነግገውና ስለውልን ስላለመፈፀም በሚያትተው የፍታብሄር የውል ህግ ክፍል አንቀፅ 1803 (2) ላይ የገንዘብ ዕዳን በማሳለፍ ስለሚከፈል ወለድ ሲያትት “በውለታው ውስጥ የበለጠ ወለድ የታሰበ እንደሆነ በዚሁ በከፍተኛው ወለድ መታሰቡ ይቀጥላል” በማለት ያስቀምጣል፡፡ ይህ ድንጋጌ የሚያስረዳው በውሉ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ሳይከፈል በቀረ የገንዘብ ዕዳ ላይ የሚታሰበውን የወለድ ምጣኔ ተዋዋዮቹ የተስማሙበት መጠን እንደሆነ የሚደነግግ ነው፡፡ በዚህም አግባብ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 81857 በቀን ጥር 13/2005 ዓ.ም በሰጠው አስገዳጅና ገዢ ውሳኔና የህግ ትርጉም አመልካች ለተጠሪ በውላቸው መሰረት በዋናው ገንዘብ ላይ የ14% ወለድ እንዲታሰብ መወሰኑ የፍ/ህ/ቁ 1803 (2) ያገናዘበ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ ይህም ማለት ማናቸውም ውሎች ከብድር ውል በስተቀር ተዋዋይ ወገኖች እስከፈለጉት የወለድ መጠን ድረስ መዋዋል ይችላሉ፣ ይህም ውላቸው በመካከላቸው በፍ/ህ/ቁ 1731 መሰረት የፀና ይሆናል፡፡ የዳኞች (ፍ/ቤቶች) የውሉን ሁኔታ በማየት ትርጓሜ የሚሰጡበትና ከውሉ በተቃራኒ ወለዱን የሚቀንሱበት ሁኔታ የለም ማለት አይቻልም፡፡ የብድር ውልን በተመለከተ ግን ተበዳሪው ወለድ እንዲከፍል የውል ቃል ከሌለ በቀር ላበዳሪው ወለድ መክፈል እንደሌለበት የፍ/ህ/ቁ 2479 ያስረዳል፡፡ ይህ ማለት ግን ባለእዳው ግዴታውን ባለመወጣቱና በውላቸው ላይ ወለድ ባይታሰብ እንኳን በፍ/ቤት ለሚቀርብበት ክስ ሀላፊ ሲሆን በከሳሽ የሚጠየቀውንና በፍ/ቤት የሚወሰነውን ህጋዊውን ወለድ ያስቀራል ማለት አይደለም፡፡ የብድር ውል ተዋዋዬች ውላቸውን በወለድ የማድረግ መብት አላቸው፡፡ በወለድ እንዲሆን ሲወስኑ የወለድ መጠኑንም እግረመንገዳቸውን የመወሰን መብትም አላቸው፡፡ በወለድ እንዲሆን ከወሰኑ ከህጋዊው ወለድ ማሳነስ ወይም ማስበለጥ ወይም እኩል ማድረግ ይችላሉ፡፡ የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 2479(1) የብድር ውል ተዋዋይ ወገኖች ተበዳሪው ሊከፍለው የሚገባው የወለድ መጠን በዓመት ከአስራ ሁለት በመቶ (12%) በላይ ሊበልጥ እንደማይችል ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ ሁለት ነገሮችን መገንዘብ ይቻላል፡፡ አንደኛው- ተዋዋይ ወገኖች የወለድ መጠኑን በተመለከተ እስከ 12% ድረስ መወሰን እንደሚችሉ መብትና ነፃነት ያላቸው መሆኑን ነው፡፡ It is also known as Contract Rate. ሁለተኛው- የክልከላ ይዘት ያለው ሲሆን እሱም ተዋዋዬቹ 12% በላይ መዋዋል እንደማይችሉና የወለድ መጠኑም በዓመት እንጂ በወር ወይም በሳምንት ወይም በሌላ ስሌት ማድረግ እንደማይችሉ ያስረዳል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ነገር የአራጣ ጉዳይ ነው፡፡ አራጣን በተመለከተ በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ የህሊናን ወይም የሰውን ችግር መሰረት በማድረግ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ስር በአንቀፅ 712 (1) (ሀ) ላይ እንደተመለከተው “ማንም ሰው የተበዳዩን ችግረኝነት፣ የበታችነቱን፣ ወይም የገንዘብ ችግሩን፣ ወይም መንፈሰ ደካማነቱን፣ ወይም ልምድ ወይም ችሎታ የሌለው መሆኑን መሰረት በማድረግ በህግ ከተፈቀደው ወለድ በላይ ገንዘብ ያበደረው እንደሆነ በቀላል እስራት፣ ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል” በማለት ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ የምንረዳው አራጣ ማለት ህጉ ከፈቀደው የብድር ወለድ መጠን በላይ ተዋውሎ ማበደር ማለት ነው፡፡ በአንቀፁ የተጠቀሱ ሌሎች ወንጀልን የሚያቋቁሙ ነገሮች (E

ኑዛዜ ( Will ) =================== ኑዛዜ ማለት ሟች ከመሞቱ በፊት ንብረቱን በፍላጐቱ መሠረት ለተተኪዎቹ የሚያስተላልፍበት ሕጋዊ መንገድ ነው፡፡ እንዲሁም ኑዛዜ የሚደረገው ኑዛዜውን ለማድረግ በሕግ ችሎታ ባለው ሰው ብቻ በግሉ (በራሱ) የሚያደርገው ሕጋዊ ድርጊት ነው፡፡ ኑዛዜው የሚፀና እንዲሆን ኑዛዜውን በተመለተ መሙላት ያለባቸው ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነዚህም፡፡ 1ኛ. ኑዛዜው መፈፀም የሚችል መሆን አለበት፣ 2ኛ. የኑዛዜው ቃል ሕገ ወጥ መሆን የለበትም፣ 3ኛ. ኑዛዜ በሃይል የተደረገ መሆን የለበትም፣ 4ኛ. ኑዛዜው በመንፈስ ጫና ምክንያት የተደረገ መሆን የለበትም አንድ የኑዛዜ ቃል በማያሻማ መልኩ ተጠቃሚውን ወይም ጉዳዩን ካላመላከተ ፈራሽ ነው፡፡ በማንኛውም የኑዛዜ ቃል ላይ “ይህ ንብረት ለእገሌ” ተብሎ በግልጽ መቀመጥ አለበት፡፡(ፍ/ብ/ሕ/ቁ 865)፡፡ እንዲሁም አፈፃፀሙ የማይቻል ኑዛዜ ፈራሽ ነው፡፡ ለምሳሌ ሟቹ በሕይወት እያለ ሸጦ ገንዘቡን የተገለገለበትን መኪናውን አበበ የተባለ ልጄ ይውሰድ ቢል ይህ የኑዛዜ ቃል ሊፈፀም የማይችል ነው፡፡ በመሆኑም ተቀባይነት የለውም፡፡ የኑዛዜ ቃል ሕግን ወይም መልካም ጠባይን ተቃራኒ የሆነ እንደሆነ ፈራሽ ነው፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን የኑዛዜ ቃል ሕግን እና መልካም ጠባይን ያከበረ መሆን አለበት፡፡ ለምሳሌ ለምለም የተባለችው ልጅ አዲስ አበባ ያለውን ቤቴን የምትወስደው ጫላ የተባለውን ወዳጄን ስታገባ ነው በማለት በኑዛዜ ቃሉ አባቷ ቢገልፅ ይህ ኑዛዜ ከቤተሰብ ሕጉ ጋብቻ ተጋቢዎች ሲፈቅዱ ብቻ ነው የሚለው ስለሚቃረን ተቀባይነት የለውም፡፡ በኃይል ተገዶ የተናዘዘ ተናዛዥ በትክክል ለሚፈልገው ሰው በፍላጐቱ መሠረት ሊናዘዝ ይችላል ተብሎ አይገመትም፡፡ ስለዚህም በኃይል ተገዶ ወይም በፍርሃት የተደረገ ኑዛዜ ፈራሽ ነው፡፡(ፍ/ብ/ሕ/ቁ 867) ሟች ያደረገው ኑዛዜ በከፊል ወይም በሙሉ ፈራሽ የሚሆንበት ጊዜ አለ፡፡ ይህ ሁኔታ አለ የሚባለው የመንፈስ መጫን (undue influence) ሲኖር ነው፡፡ በመሠረቱ አንድን ኑዛዜ በኑዛዜው ተጠቃሚ የሆነ ሰው ባደረገው የመንፈስ ተፅዕኖ የተደረገ ነው ብሎ ውድቅ ለማድረግ አይቻልም፡፡ በአንፃሩ ግን የሥራ ወይም የሞያ ጠባያቸው ከሟች ጋር የቀረበ ግንኙነት እንዲኖራቸው የሚያደርጋቸው ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች በተለይም ሟች ጋር ዝምድና ከሌላቸው በሥራ ወይም በሞያ ግዴታቸው ሟችን ጣዕሩ በበረታበት ጊዜ ስላገለገሉት ብቻ አለአግባብ ንብረት እንዳያገኙ ቢናዘዝላቸው ሕግ ጣልቃ ይገባል፡፡ ዕድሜው ከሀያ ዓመት በታች የሆነ ሰው ለአሳዳሪው ወይም ለሞግዚቱ ጥቅም ያደረገው ኑዛዜ ሊቀነስ ወይም ሙሉ በሙሉ ሊሻር ይችላል፡፡ ነገር ግን ሞግዚት ወይም አሳዳሪው ወደ ላይ የሚቆጠሩ ወላጆቹ ከሆኑ ግን ኑዛዜው ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ (ፍ/ብ/ሕ/ቁ 869)፡፡ ሟችን ከመሞቱ በፊት ባሉት ስድስት ወራት ውስጥ የሕክምና እርዳታ ሲሰጡት የነበሩ ሀኪሟች ወይም በመንፈሳዊ አገልግሎት ሲሰጡት የነበሩ የእምነት አባቶች በአገልግሎታቸው ወቅት በሟች ላይ ከፍተኛ የመንፈስ ጫናን ሊያሳድሩ ይችላሉ ተብሎ ይገመታል፡፡ በመሆኑም ሟች በኑዛዜው ለነሱ የሰጠው ስጦታ እንደነገሩ ሁኔታ ሊቀነስ ወይ ሊሻር ይችላል፡፡ ነግር ግን እነዚህ ግለሰቦች ከሟች ጋር በትዳር የተሳሰሩ ወይም የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ካላቸው ይህ ደንብ ተፈፃሚ አይሆንም በማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 870 ተገልጿል፡፡ በኑዛዜው ላይ ምስክሮች ወይም አዋዋዮች ለነበሩ ሰዎች የተደረገ ኑዛዜም በተመሳሳይ ሊቀነስ ወይም ሊሻር ይችላል፡፡ ከላይ በተገለፀው መልኩ ኑዛዜውን ለመቀነስ ወይም ለመሻር ሥልጣን የተሰጣቸው ለዳኞች ብቻ ነው፡፡ ዳኞች በዚህ ስልጣናቸው ለመሥራት በኑዛዜው ተጠቃሚ የሆነው ሰው ኑዛዜው እንዲፈፀምለት ጥያቄ ካቀረበበት ቀን አንስቶ በሶስት ወራት ውስጥ በሕጉ መብት የተሰጣቸው ሰዎች ጥያቄ ሲቀርቡ ብቻ ነው፡፡ ዳኞች በዚህ በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት ኑዛዜውን በከፊል ወይም በሙሉ ሲሽሩ ከልቦና ፍርድና ከርትዕ ጋር የተስማማ ነው የሚባሉትን ምክንያት መግለጽ አለባቸው፡፡ ሟች የኑዛዜውን አንዳንድ ክፍሎች ሊናዘዝ የቻለው የኑዛዜው ተጠቃሚ በፈፀመው የተንኰል ወይም የማታለል ሥራ ነው በማለት የኑዛዜውን ቃል መሻር አይቻልም፡፡ ነገር ግን የኑዛዜው ቃል ላይ ስህተት ካለ ኑዛዜው ይሻራል፡፡ ይህም የሚሆነው ተናዛዡ የፈፀመው ስህተት ሀሳቡን ወደ አንድ አቅጣጫ እንዲያዘነብል ወሳኝ በሆነ መልኩ ተፅዕኖ ያደረገበት ለመሆኑ በኑዛዜው አነጋገር ላይ በግልጽ ሲታይ ወይም ኑዛዜውን በሚጠቅስ በአንድ ሰነድ ላይ በማያሳጣ መልኩ ተገልፆ ሲገኝ ብቻ እንደሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 877 ተደንግጓል፡፡ አንድ የኑዛዜ ቃል ፈራሽ በሚሆንበት ጊዜ በፈራሹ ቃልና በሌሎቹ ቃላት አፈፃፀም መካከል የሚያስተሳስር ነገር አለ ተብሎ ካልታሰበ በስተቀር በመርሕ ደረጃ ኑዛዜውን ሙሉ በሙሉ ፈራሽ የማድረግ ውጤት አይኖረውም፡፡ በተወሰኑ አጋጣሚዎች አንዳንድ ግለሰቦች ኑዛዜአቸውን ከአንድ መሟላት ካለት ሁኔታ ጋር አያይዘውት ይገኛሉ፡፡ ይህ ቅድመ ሁኔታ የማይቻል ወይም ለሕግ ወይም ለመልካም ፀባይ ተቃራኒ ከሆነ ግን በሕግ ፊት ተቀባይነት የለውም፡፡ (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 879)

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ሆነው የሚቆዩበትን ጊዜ ለተጨማሪ 30 የስራ ቀናት አራዘሙ ********************** የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶችና ም/ፕሬዝደንቶች የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ወቅታዊ ሁኔታ በመገምገም ፍርድ ቤቶቹ ከሰኔ 1 ቀን 2012 ጀምሮ እስከ ሀምሌ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ለተጨማሪ 30 የስራ ቀናት በከፊል ዝግ ሆነው አንዲቆዩ መወሰናቸውን ለኢቢሲ በላኩት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ስርጭት ለመግታት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከመጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን 2012 ዓ.ም በከፊል ዝግ ሆነው እንዲቆዩና አስቸኳይነት ያላቸውን ጉዳዮች ብቻ በተረኛ ችሎት እንዲመለከቱ መደረጉ ይታወቃል፡፡ የወረርሽኙ ስርጭት እየተስፋፋ በመምጣቱ ምክንያት ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር በየጊዜው እየጨመረና የስርጭት አድማስም እየሰፋ መምጣቱን የጤና ጥብቃ ሚኒስቴር በየጊዜው ከሚያስራጫቸው መረጃዎች የፍርድ ቤቱ አመራር መገንዘብ ችሏል፡፡ አመራሩ ባካሄደው ስብሰባ የዳኝነት አገልግሎት ለማግኘት ከክልሎች፣ ከአዲስ አበባና ከድሬዳዋ ከተሞች ወደ ፍርድ ቤቶች የሚመጡ ባለጉዳዮች ቁጥራቸው በርካታ በመሆኑና የእነዚህ ባለጉዳዮች ለቫይረሱ ስርጭት ያላቸወን ተጋላጭነት ለመቀነስ እንዲሁም ዳኞችና ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች ደህንነታቸው በተጠበቀ ሁኔታ ስራቸውን እንዲያከናውኑ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በማመን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከሰኔ 1 ቀን 2012 ጀምሮ እስከ ሀምሌ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ለተጨማሪ 30 የስራ ቀናት በከፊል ዝግ ሆነው አንዲቆዩ ወስኗል፡፡ ፍ/ቤቶች ዝግ ሆነው በሚቆዩበት ጊዜ በተረኛ ችሎት እንዲታዩ ከተለዩት ጉዳዮች በተጨማሪ አነስተኛ የተገልጋይ ቁጥር ያላቸው ሌሎች የዳኝነት አገልግሎት ሊሰጥባቸው የሚችሉ የጉዳዮችን በመለየት አገልግሎቱን በየጊዜው ቀስ በቀስ ለባለጉዳዮች ክፍት እየተደረገ እንዲሄድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም በአመራሩ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ ይህን መሰረት በማድረግም ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ሆነው በሚቆዩባቸው ጊዜ፡- 1. ከሰኔ 30/2011 ዓ/ም በፊት የተከፈቱ ዉዝፍ ይግባኝ መዝገቦችን ለመወሰን በችሎት ባለጉዳዮችን የመስማት አስፈላጊነት የታመኑባቸው ጉዳዮች ተለይተው ውሳኔ እንዲሰጣቸው ይደረጋል፡፡ 2. የወንጀል ይግባኝ ጉዳዮችን በተመለከተ ከማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጋር የቪዲዮ ኮንፈረንስ መርሃ ግብር በማዘጋጀት ተከራካሪ ወገኖች ይሰማሉ፤ እንደየሁኔታው ከባለጉዳዮች ጋር በመነጋገር የቃል ክርክራቸውን በጽሁፍ የሚያቀርቡ ሲሆን ወሳኔ እንዲያገኙም ይደረጋል፡፡ 3. የፍታብሔር ይግባኝ ጉዳዮችን በተመለከተ ባለጉዳዮችን መስማት አስፈላጊነቱ በዳኞች ከታመነባቸው ጉዳዮች ውጭ የሆኑ መዛግብት እልባት እንዲያገኙ ይደረጋል፡፡ 4. አስቸኳይ በሆኑ ጉዳችዮች በተረኛ ችሎት የተሰጠውን ትዕዛዝ፣ ብይን እና ውሳኔ መሰረት በማድረግ የሚቀርቡ የይግባኝ ጉዳዮች በአፋጣኝ እልባት የሚሰጣቸው ይሆናል፣ 5. አስቸኳነት ያላቸው ጉዳዮች ማለትም ከህጻናት ቀለብና አስተዳደግ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች፣ የዋስትና ጉዳይ፣ የአሰሪና ሰራተኞች ጉዳይ፣ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈጸሙ የቤት ውስጥ ጥቃቶች እና ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈጸሚያ መመሪያ ወይም ደንብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ይሆናሉ፡፡ 6. የፌዴራልና የክልል ጉዳዮች ውሳኔን መሰረት በማድረግ ተከፍተው በሂደት ላይ የነበሩ የአፈጻጸም ጉዳዮች የስራና አፈጻጸም አቅጣጫ እስከሚሰጥባቸው ጊዜ ድረስ በደረሱበት ደረጃ ቆመው የሚቆዩ ይሆናል፡፡ 7. በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች ተዘጋጅቶ በሚገለጸው መርሃ-ግብር መሰረት የውሳኔ፣ የትዕዛዝ፣ የብይንና የመዝገብ ግልባጭ የመስጠት ተግባር የሚከናወን ይሆናል፡፡ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ስርጭት ለመከላከል ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሆኑባቸው ጊዜያት ወደ ፍርድ ቤቶቹ ቅጥር ጊቢ የሚገቡና የሚስተናገዱት ባለጉዳዮቹ ብቻ ይሆናሉ፡፡ ባለጉዳዮች ለአገልግሎት ወደ ፍርድ ቤት ሲመጡም የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል መልበስ እንዲሁም በመግቢያ በር ላይ በተዘጋጀ እጅ መታጠቢያ እጃቸውን መታጠብ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የእርስ በእርስ ርቀታቸውንም ጠብቀው እንዲስተናገዱ የፍርድ ቤቱ አመራር አሳስቧል፡፡ የመከላከያ ጥንቃቄዎችን በአግባቡ በመተግበር ወረርሽኙ ከሚያደርሰው አስከፊ ጥቃት ህብረተሰቡ አራሱን እንዲከላከል የፌዴራል ፍርድ ቤቶች መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ Via:- EBC

የተደረገለት የአዕምሮ ንብረትንም (ኮፒ ራይት፣ ፓተንት፣ የንግድ ምልክት) ማዋጣት ይቻላል። ሰዎች የሽርክና ስምምነት አድርገው የንግድ ማህበር የሚመሰረትቱት በሕጉ አገላለጽ “የኢኮኖሚ ተግባር ያለው ሥራ ለማከናወን” ነው። ይህ አገላለጽ መሰረተ-ሰፊ ሲሆን፤ ማንኛውንም ትርፍ የሚያስገኙ በንግድ ሕጉ አንቀጽ 5 ስር የተዘረዘሩትንና ሌሎችንም የንግድ ተግባራት ሁሉ ያጠቃልላል። በንግድ ማህበራት ሥራ ላይ በተለይም ከሽርክና ስምምነቱ ጋር በተያያዘ ዋነኛው የሙግት መነሻ የትርፍና ኪሳራ ጉዳይ ነው። የሽርክና ስምምነት ሁሉም የማህበሩ አባላት ከሚገኘው ትርፍም ሆነ ከሚመጣው ዕዳ ተካፋይ ለመሆን የተስማሙ መሆናቸውን በግልጽ ማሳየት አለበት። ይሁንና በርካቶች ከሕግ የግንዛቤ እጥረት መነሻ ትርፍን በአንዱ እጅ ላይ፣ ዕዳን ደግሞ በሌላኛው ትከሻ ላይ የሚጭኑ ስምምነቶችን ሲያደርጉ ይስተዋላል። ሕጉ በግልጽ እንደሚያስቀምጠው ትርፉን ሁሉ ለአንደኛው ማህበርተኛ ብቻ የሚሰጥ ስምምነት ፈራሽ ነው። እንዲሁም የአንዱን ወይም የብዙዎቹን አባላት በማህበሩ ላይ ከሚመጣው ኪሳራ እንዳይነካው የሚያደርግ ስምምነትም ፍርስ ነው። ያም ሆኖ ተራ የሽርክና ማህበር በሆነ ጊዜ ግን በሥራ ችሎታው ብቻ ሸሪክ የሆነ ሰው የትርፍ ተካፋይ እንዲሆን፤ ኪሳራ ግን እንዳይነካው አድርጎ መዋዋል ሕጉ እንደሚፈቅድ ልብ ይሏል። በመርህ ደረጃ የሽርክና ስምምነት ሁሉንም አባላት (ያገቡት የመዋጮ ዓይነትና ዋጋው ከግምት ሳይገባ) እኩል የትርፉ ፍሬ ተቋዳሽ እና የኪሳራው ወይም የዕዳው ተጋሪ የሚያደረግ መሆን አለበት። ትርፍና ኪሳራው እንደመዋጯቸው ዓይነትና ዋጋ እንዲሁ የተለያየ ሊሆን ይችላል የሚል ስምምነት እንዳያደርጉ ግን ሸሪኮቹን የሚከለክላቸው ሕግ የለም። ከትርፍና ኪሳራ ጋር ተያይዞ ሳይጠቀስ መታለፍ የሌለበት ጉዳይ በህብረት ሽርክና ማህበር ውስጥ አንድ ማህበርተኛ የሌሎች ሸሪኮቹን ፈቃድ ሳይጠይቅ የድርሻውን መብቶችና ጥቅሞች (ትርፍን ጨምሮ) ሌላ ሦስተኛ ወገን (ለምሳሌ አበዳሪው) እንዲጠቀምባቸው አሳልፎ የመስጠት መብት ያለው መሆኑ ነው። ይህ ግን ለሦስተኛው ወገን የማህበርተኛነት መብት እንደማይሰጠው ልብ ይሏል።

የንግድ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ህግ ==================== ስለ ሽርክና ስምምነት ከመመልከታችን አስቀድሞ የንግድ ድርጅቶችን ማየቱ ጠቃሚ ነው። ምክንያቱም በመሰረቱ የሽርክና ስምምነት የሚባለው ነገር የሚያስፈልገው የንግድ ድርጅቶችን ለመመስረት ስለሆነ። በኢትዮጵያ ንግድን አብሮ መሥራት ዛሬም ድረስ ባይዳብርም በ1952 ዓ.ም ተደንግጎ እስከአሁንም በሥራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ የንግድ ሕግ ግን ከነውስንነቶቹ የንግድ ድርጅት መስርቶ አብሮ የመሥራት እንቅስቃሴን በስፋት ደንግጎ እናገኘዋለን። ሕጉ የንግድ ማህበርን (ድርጅትን) ሲተረጉም ማንኛውም በሽርክና ስምምነት መሰረት የሚቋቋም ማህበር የንግድ ድርጅት (ማህበር) ይሰኛል ሲል ይገልጸዋል። ከዚህ የምንረዳው የትኛውንም ዓይነት የንግድ ማህበር እውን ለማድረግ በቅድሚያ የሽርክና ስምምነት አስፈላጊ መሆኑን ነው። ባለንበት የነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ዘመን ከባድ፣ አትራፊና ሰፋፊ ንግድና ኢንቨስትመንቶችን በግል ለማከናወን ስለማይቻል ግለሰቦች ሰብሰብ ብለው የሽርክና ስምምነት በማድረግ የንግድ ድርጅቶችን ያቋቋማሉ። በንግድ ሕጋችን ውስጥ በሁለተኛው መጽሐፍ ከአንቀጽ 210 እስከ 560 ድረስ ያሉት ሰፊ ድንጋጌዎች ስለ ንግድ ድርጅቶች አመሰራረት፣ አነጋገድ፣ አደረጃጀት፣ ሂሳብ አያያዝ፣ የአባላትና የድርጅቶቹ ሕጋዊ ሰውነት ተጠያቂነት፣ የድርጅቶች መቀላለቀልና መፍረስ ጉዳዮችን የተመለከቱ ናቸው። በንግድ ሕጉ የንግድ ድርጅቶች በአጠቃላይ የሽርክና ማህበራት እና ኩባንያዎች ተብለው በሁለት ይከፈላሉ። የሽርክና ማህበራት በኩባንያ (በኮርፖሬሽን) ደረጃ ሊቋቋሙ የማይችሉ በንጽጽር አነስተኛ ድርጅቶች ናቸው። ዓይነተኛ መገለጫቸው ደግሞ ዋነኛ መዋጮዎቹ ግለሰቦቹ (አባላቱ) ራሳቸው መሆናቸው ነው። ይህ ማለት የሽርክና ማህበራት ምንም እንኳን ግለሰቦች ገንዘባቸውን፣ ሙያቸውን እና ሀብታቸውን አዋጥተው የሚመሰርቷቸው ቢሆኑም ግለሰቦቹ በሽርክና ማህበራቱ ሕልውና ላይ እጃቸው ረዥም ነው። ከሸሪኮቹ የአንዱ ችሎታ ማጣት (ሕፃንነት፣ እብደት፣ በሕግ ወይም በፍርድ የተጣለ ክልከላ)፤ ሞት፣ በግል ሥራቸው መክሰር ወይም በመካከላቸው የሚፈጠር አለመግባባት የማህበሩን መፍረስ ያስከትላል። ማንኛውም አባልም በራሱ ፈቃድ በፈለገው ጊዜ በማህበሩ ውስጥ ያለውን ድርሻ ለውጭ ሰው (ሦስተኛ ወገን) ማስተላለፍ አይችልም። ከዚህም በላይ አባላቱ አንዳቸው ለሌላኛው ወኪሎች ናቸው። ማህበሩ ከሦስተኛ ወገኖች ለሚጠየቀው ማናቸውም ዕዳ የአንድነትና የነጠላ ዋሶች ያለባቸውን ዓይነት ኃላፊነት አለባቸው። ኃላፊነታቸው ያልተወሰነ በመሆኑ ዕዳ ጠያቂው ድርጅቱ ቢፈርስ ወይም ዕዳውን መክፈል ቢሳነው እንኳ አባላቱን ሲፈልግ በተናጠል ሲያሰኘውም በጋራ ጠይቆ ገንዘቡን ከግል ንብረታቸው ላይ የማስመለስ ህጋዊ መብት አለው። ከእነዚህ ህጋዊ ባህርያት እንደምንረዳው የሽርክና ማህበራት በሚቀራረቡና በሚተማመኑ ወዳጅ ሸሪኮች አማካኝነት የሚመሰረቱ ናቸው። ከዚህም ሌላ ለአጭር ጊዜ እና ለተወሰነ የንግድ (የኢንቨስትመንት) ሥራ ጠቃሚዎችና ለአመራርም ቀላል ናቸው። በአገራችን ሕግ የሽርክና ማህበራት የሚባሉት ተራ የሽርክና ማህበር፣ የእሽሙር ማህበር፣ የሕብረት ሽርክና ማህበርና ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ያለበት የሽርክና ማህበር ናቸው። ከእሽሙር ማህበር በስተቀር ታዲያ ሁሉም የሽርክና ማህበራት ህጋዊ ሰውነት ያላቸው (በራሳቸው መክሰስ መከሰስ፤ የንብረት ባለቤት መሆን ወዘተ የሚችሉ) ናቸው። እነዚህ የሽርክና ማህበራት ዓይነቶች ከአመሰራረታቸው፣ ከማህበርተኞቹ መብትና ግዴታ፤ ከማህበራቱ ሥራ አመራር፣ በማህበራቱ እና በሦስተኛ ወገኖች እንዲሁም በአባላቱና በሦስተኛ ወገኖች መካከል ሊኖር ከሚገባው ግንኙነት እንዲሁም ከማህበራቱ የማፍረሻ ምክንያቶችና ከመፍረሳቸው ውጤቶች አንጻር የተለያየ የህግ አንድምታ አላቸው። ከሽርክና ማህበራት ሌላ ሕጋዊ እውቅና የተሰጣቸው የንግድ ድርጅቶች ኩባንያዎች ናቸው። ኩባንያዎች ሁለት ዓይነት ናቸው – የአክስዮን ማህበር እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር። ኩባንያዎች ሰፋፊና የረዥም ጊዜ ንግዶችን ለማከናወን ጠቃሚ ናቸው። የማህበራቱ ካፒታል በአክስዮን (በሼር) የተከፋፈለና አባላቱም እንደየመዋጯቸው ልክ የአክስዮን ድርሻ ያላቸው ባለአክስዮን ማህበርተኞች መሆናቸው የኩባንያዎች ልዩ ባህርይ ነው። ኩባንያዎችን የአባላቱ መክሰር፣ ሞት ወይም አለመግባባት አያፈርሳቸውም። የአባላቱ ኃላፊነት የተወሰነ በመሆኑ ለሦስተኛ ወገኖች ያለባቸው ተጠያቂነት በኩባንያው ውስጥ ባላቸው አክስዮን ልክ ነው። (እያንዳንዱን የሽርክና ማህበርና ኩባንያዎች የተመለከቱ ዝርዝር ሕጋዊ ጉዳዮችን በሌሎች ጊዜያት የምንዳስስ ይሆናል) የሽርክና ስምምነት የንግድ ማህበር ማለት ማንኛውም በሽርክና ስምምነት መሰረት የሚቋቋም ማህበር ነው ብለናል። የሽርክና ስምምነት ማለት ደግሞ ከንግድ ሕጉ አንቀጽ 211 ድንጋጌ ላይ ሰፍሮ እንደምናነበው ሁለት ወይም ብዙ ሰዎች መዋጮ አዋጥተው በአንድነትና በሕብረት የኢኮኖሚ ተግባር ያለው ሥራ ለመሥራትና ከሚገኘው ትርፍም ሆነ ከሚመጣው ዕዳ ተካፋይ ለመሆን የሚስማሙበት ውል ነው። ከድንጋጌው የምንረዳው ቀዳሚው ጭብጥ የሽርክና ስምምነት በመሰረቱ ውል መሆኑን ነው። ውል ከሆነ ደግሞ በሕግ ፊት ዋጋ የሚያወጣ እንዲሆን በፍትሐብሔር ህጋችን የተደነገጉትን አራት መለኪያዎች ማሟላት አለበት። እነዚህም የተዋዋዮች የመዋዋል ችሎታ፤ ፈቃዳቸው ጉድለት በሌለበት አኳኋን የተገለጸ መሆኑ፤ የተዋዋሉበት ፍሬ ጉዳይ በሕግና በመልካም ስነ ምግባር ቅቡልነት ያገኘ መሆኑ እንዲሁም ሕግ በሚጠይቅ ጊዜ የውሉ አቀራረጽ በህግ በተቀመጠው ሥርዓት (ፎርም) መሰረት የተደረገ መሆን አለበት የሚሉ ናቸው። የንግድ ሕጉ ከእሽሙር ማህበር በስተቀር ማንኛውም የንግድ ማህበር የሚቋቋምበት ውል በጽሑፍ ካልተደረገ በስተቀር አይጸናም ስለሚል የሽርክና ስምምነት በጽሑፍ መደረግ ይኖርበታል ማለት ነው። ተራ የሽርክና ማህበርን እና ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ያለበት የሽርክና ማህበርን ለመመስረት ስምምነቱ በጽሑፍ ይደረግ እንጂ የስምምነቱ ዓይነትና ቅርጽ ለሽርከኞቹ ምርጫ የተተወ ነው። የሕብረት ሽርክና ማህበር ደግሞ በህጉ በተገለጸው መልኩ በመመስረቻ ጽሑፍ ነው የሚመሰረተው። የአክስዮን ማህበርና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርም በመመስረቻ ጽሑፍና በመተዳደሪያ ደንብ የሚመሰረቱ ሲሆን ስምምነቱ ሊይዝ የሚገባውንም ፍሬ ነገር ሕጉ ዘርዝሮ አስቀምጧል። ሌላው የሽርክና ስምምነት መሰረታዊ ጉዳይ “ሁለት ወይም ብዙ ሰዎች” የሚለው አገላለጽ ነው። የተፈጥሮ ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው ድርጅት ሁሉ ሁለትና ከሁለት በላይ በመሆን የንግድ ማህበር መመስረት ይችላሉ። ከአክስዮን ማህበር በስተቀር ሁሉም የንግድ ድርጅቶች በትንሹ በሁለት ሰዎች ሊመሰረቱ ይችላሉ። የአክስዮን ማህበር ለመመስረት ግን በትንሹ አምስት ሰዎች ያስፈልጋሉ። አከራካሪ ቢሆንም አንዳንድ የበለጸጉት አገራት ሕጎች አንድ ሰው ብቻውን ኩባንያ እንዲመሰረት የሚፈቅዱ ሲሆን፤ እየተሻሻለ ያለው የእኛው የንግድ ሕግም ይህንኑ የሚፈቅድ ሆኖ ተቀርጿል። የመጨረሻውን የአባላት ቁጥር ስንመለከት ደግሞ ኃላፊነቱ ከተወሰነ የግል ማህበር በስተቀር ለሌሎቹ የንግድ ድርጅቶች ሕጉ ገደብ አላስቀመጠም። ኃላፊነቱ የተሰወነ የግል ማህበር አባላት ግን ከሃምሳ መብለጥ የለባቸውም። የመዋጮ ጉዳይ ሌላው የሽርክና ስምምነት ፍሬ ነገር ነው። መዋጮው በካሽ፣ በዓይነት ወይም በአገልግሎት ወይም በሥራ ችሎታ (Skill) ሊሆን ይችላል። በሕግ ጥበቃ

ቸው መሠረታዊ ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ መቃወሚያውን የሚያቀርበው ሰው የክሱ አካል መሆን ይችል የነበረ መሆን አለበት፡፡ በተሰጠው ፍርድ ምክንያት መብትና ጥቅሙ የተነካ መሆን እና የመቃወሚያ ማመልከቻው የቀረበው ውሳኔው ከመፈፀሙ በፊት መሆን ይጠበቅበታል፡፡ በዋነኛነት የዚህ የሕግ ሥርአት አላማ ፍርድ መሰጠቱን ሳያውቁ መብትና ጥቅማቸው ሊነካባቸው የሚችሉ ሰዎችን እድሉን በመሰጠት በፍርድ ሂደት ውስጥ ተካተው መብታቸውን እንዲያስጠብቁ ማስቻል ነው፡፡ የይግባኝ አቤቱታ (Appeal) የይግባኝ አቤቱታ ማለት በሥር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ቅር የተሰኘ ሰው ጉዳዩን ለበላይ ፍርድ ቤቶች ወይም ለይግባኝ ፍርድ ቤቶች ፍርዱ እንዲሰረዝለት ወይም እንዲሻሻል የሚጠይቅበት ማመልከቻ ነው፡፡ ማመልከቻው የቀረበለት ይግባኝ ፍርድ ቤት የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ የሕግም ሆነ የፍሬ-ነገር ሥሕተት የተፈፀመበት መሆኑን በመመርመር ፍርዱን የማፅናት፣ የመሻር አና የማሻሻል ሥልጣን ይኖረዋል፡፡ ይግባኝ የማለት መብት የዜጐችን ፍትህ የማግኘት መብት ከማስጠበቅ አንፃር ያለው ፋይዳ ጉልህ በመሆኑ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 20/6/ መሠረት ሕገ-መንግስታዊ እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 320 የይግባኝ አቤቱታ ሥለሚፈቀድበት ሁኔታ ይደነግጋል፡፡ በዚህ አንቀፅ መሠረት ይግባኝ እንዲፈቀድ ሶስት መሠረታዊ ቅድመ-ሁኔታዎች እንዲገኙ ያስፈልጋል፡፡ ሀ/ የመጨረሻ ፍርድ መሆን፡- ይህ ማለት ጉዳዩ ገና በበታች ፍርድ ቤት ታይቶ ያላለቀ ከሆነና የመጨረሻ ፍርድ ያልተሰጠበት ከሆነ የይግባኝ አቤቱታ ሊቀርብ አይችልም፡፡ ለ/ በሥር ፍርድ ቤት የሚገኙ መፍትሄዎችን አሟጦ መጠቀም፡- ከላይ በዳሰስናቸው ሶስት ምክንያቶች የተነሳ የሥር ፍርድ ቤት ጉዳዩን እንደገና መመልከት የሚችል ከሆነ የይግባኝ አቤቱታ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ለምሳሌ፡- የሥነ-ሥርአት ጉድለት በመገኘቱ ምክንያት የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔውን አንዲሰርዝ መጠይቅ ሲቻል የይግባኝ አቤቱታ ቢቀርብ የይግባኝ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ወደ ስር ፍርድ ቤት መመለስ ይችላል፡፡ ሐ/ በጊዚያዊ ትዕዛዞች ላይ ይግባኝ አለመፈቀዱ፡- ጊዜያዊ ትዕዛዞች (interlocutory decisions) ማለት የተያዘውን ጉዳይ ለመጨረሻ ጊዜ የማይቋጩ የፍርድ ቤት ግዜያዊ ፍርዶች ናቸው፡፡ ለምሳሌ፡- ቀነ- ቀጠሮ መወሰን፣ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ተገቢ መስሎ የታየውን ውሳኔ ሲሰጥ እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ ስለዚሀ በእነዚህ ጉዳዬች /ፍርዶች/ ላይ ይግባኝ ማለት አይፈቀድም፡፡ ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን ሦስት ሁኔታዎች በማሟላት የይግባኝ አቤቱታውን አንቀፅ 327 በሚያስቀምጣቸው መስፈርቶች መሠረት አዘጋጅቶ ማቅረብ የሚቻል ይሆናል፡፡ ይህም ሲሆን የይግባኝ ፍርድ ቤት ለጉዳዩ ቀነ- ቀጠሮ በመስጠት ጉዳዩን በይግባኝ ደረጃ ይመረምራል፡፡ በዚህም መሠረት የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ ጉድለት የሌለበት መሆኑን ከተረዳው መልስ ሰጪውን ሳይጠራ ይግባኙን ዘግቶ አቤት ባዩን ሊያሰናብት ይችላል /አንቀፅ 337ን ይመልከቱ/፡፡ ነገር ግን የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ጉዳዩ ይግባኝ ያስቀርባል ካለ የመጥሪያ ወረቀትና የይግባኝ አቤቱታውን አንድ ላይ በማድረግ ለመልስ ሰጪ ይልካል፡፡ በዚህ መሠረት መልስ ሰጪ በተባለበት ቀን ሲገኝ /በሌለበት ሊሆን ይችላል/ ጉዳዩ በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት መደበኛ አካሄድ መሠረት ዳግመኛ ይመረመራል፡፡ የሰበር ሰሚ ችሎት (casassion division) የሰበርን ትርጉም ከቃሉ በመነሳት መረዳት ይቻላል፣ ይኸውም አስቀድሞ የተሰጠ ውሳኔ ወይም ፍርድን መስበርን፣ ማፍረስን፣ መሰረዝን የሚመለከት ነው፡፡ አሁን ባለን አሰራር የሰበር ሥርዓት የመጨረሻ ፍርድ የተሰጠበት ጉዳይ በተለየ ሁኔታ እንደገና ታይቶ የሚታረምበት የዳኝነት ሥርዓት ነው፡፡ በአጠቃላይ የሰበር ሥርዓት ማለት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠበት ጉዳይ እንደገና ለመጨረሻ ጊዜ የሚታይበት እና እርምት ካሰፈለገው የሚታረምበት የተለየ የዳኝነት ሂደት ነው፡፡ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 80/3/ /ሀ/ እና /ለ/ መሠረት የፌዴራልና የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚኖራቸው በግልፅ ተደንግጓል፡፡ ሕገ-መንግስቱን ተከትሎ የፌ/ፍርድ ቤቶችን አደረጀጀትና አወቃቀር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀፅ 10 መሠረት የፌ/ጠ/ፍርድ ቤት/ሰ/ሰ/ችሎት የማከተሉትን ጉዳዬች በሰበር የማየት ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡ ሀ/ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በይግባኝ አይቶ የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዬች ለ/ የፌ/ጠ/ፍርድ ቤት መደበኛ ችሎት የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዬች ሐ/ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መደበኛ ችሎት ወይም በይግባኝ አይቶ የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዬች፡፡ በዚህም መሠረት ከተለያዩ አካላት የሚቀርቡትን የሰበር አቤቱታዎች ለመቀበል የሚከተሉት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት አለባቸው፡፡ መሠረታዊ የሕግ ስህተት መኖር ውሳኔው የመጨረሻ መሆኑን፣ አቤቱታው የመጨረሻ ውሳኔ በተሰጠ በ90 ቀናት ውስጥ የቀረበ መሆኑን ለፍትሐብሄር ጉዳዬች የዳኝነት ክፍያ የተፈፀመበት መሆን ወይም በደሃ ደንብ መሠረት የተከፈተ መሆን ናቸው፡፡ ከላይ የጠቀስናቸው አራት መሠረታዊ ቅድመ-ሁኔታዎች መሟላት ሲችሉ ጉዳዩ በሰበር ሰሚ ችሎት ፊት በድጋሚ የሚታይበት እድል ይፈጠራል፡፡ በሀገራችን የሕግ-ሥርዓት ውስጥ ጉዳዬች የመጨረሻ እልባት ሊያገኙ የሚችሉት በዚሁ የሰበር ሰሚ ችሎት ነው ነገር ግን ውሳኔው የህገ-መንግስት ጥያቄ ሲያስነሳ የፌዴሬሽን ም/ቤት በህገ-መንግስቱ አንቀፅ 83 በተሰጠው ሥልጣን መሰረት ጥያቄ የተነሳበትን የህገ-መንግሰት ክፍል የሚተረጉምበት ሁኔታ ይኖራል ይህ ሥርዓት ግን ከመደበኛው የዳኝነት ሂደት ውስጥ አይመደብም፡፡ በተጨማሪም ኢትዮጵያን የአፍሪካ የሰብአዊ መብቶች ቻርተር ፕሮቶኮልን ብታፀድቅ ኖሮ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች በአፍሪካ የሰብአዊ መብቶች ፍርድ ቤት በይግባኝ መልክ ሊታዩ የሚችልበት አጋጣሚ ይኖር ነበር፡፡

ፍርዶች ዳግመኛ ሰለሚታዩባቸው መንገዶች (Review of Judgments) ============================= ፍርድን እንደገና መመርመር ማለት ምን ማለት ነው? ፍርድን እንደገና መመርመር (Review of Judgments) ማለት በአንድ በተወሰነ ጉዳይ ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች የሰጡት ፍርድ /ውሳኔ/ የፍርድ ባለዕዳውን ወይም የፍርድ ባለመብቱን ቅር ሲያሰኘው ወይም አጥጋቢ ሆኖ ሳያገኘው ሲቀር ይህ የተሰጠው ፍርድ ዳግመኛ ይታይለት ዘንድ ሊጠቀምበት የሚችልበት ጠቃሚ የሥነ-ሥርዓት ሕግ አካል ነው፡፡ ፍርዶች ዳግመኛ ለምን ይታያሉ? የፍርድ ቤቶች ውሳኔ በተለያየ መንገድ የዜጐችን የአኗኗር ዘይቤ ጥሩም መጥፎም የማድረግ እድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ይህም ማለት ፍርድ ቤቶች ከሶሶቱ የመንግስት አካላቶች መካከል የዜጐች መብትና ነፃነት እንዲከበር እንዲሁም ፍትህን ከማስፈን አኳያ ያላቸው አስተዋፅኦ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ ጉዳዬችን የሚያጤኑበት ወይም የሚመረምሩበት መንገድ እጅግ ጥንቃቄ የተሞላበት እንዲሁም በሕግና በሥርአት የተደገፈ መሆን አንዳለበት ይታመናል፡፡ ከተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ፍርድ ቤቶች የሚሰጡት ውሳኔ ስህተት ሊሆን ወይም ደግሞ የሕጐችን አጠቃላይ መንፈስ ያልተከተለ የሚሆንባቸው አጋጣሚዎች እጅግ በርካታ ናቸው፡፡ ለዚህም በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን በይግባኝ ፍርድ ቤቶች እና በሰበር ሰሚ ችሎቶች ተከማችተው የሚገኙትን የጉዳዬች ብዛት መመልከት በቂ ነው፡፡ ተከራካሪ ወገኖች ልክ እንደማንኛውም ዜጋ ፍትህ የማግኘት ሕገ- መንግስታዊ መብት ባለቤት በመሆናቸው ትክክል አይደለም ብለው የሚያስቡትን ፍርድ የተሻለ ፍትህ እናገኝበታለን ብለው ወደሚያስቡት የፍትህ ተቋም ጉዳያቸው ዳግመኛ እንዲታይላቸው መጠየቅ ይችላሉ መንግስትም ይህ የዜጐች የተሻለ ፍትህ የማግኘት መብት አንዲከበር ሊያግዝ የሚችል ተቋማዊ መዋቅር መዘርጋት ይጠበቅበታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በአንድ ሀገር የሕግ ሥርአት (legal system) ውስጥ ወጥ (uniform) የሆነ የሕግ አተረጓጎም እንዲኖር ለማስቻል የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ እንደገና መመርመር የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ነው፡፡ የውጭ ሀገራት ተሞክሮ በተለያዩ የአለማችን ሀገሮች የሚገኙ ፍርድ ቤቶች አወቃቀራቸውና አደረጃጀታቸው ጉዳዬች በአንድ ፍርድ ቤት መታየት ጀምረው በተለያዩ የፍርድ ቤት ደረጃዎች በይግባኝና በሌሎች መሰል መንገዶች ዳግመኛ መታየት የሚችሉበትን መንገድ ታሳቢ ያደረጉ ናቸው፡፡ ለአብነት ያክል የአሜሪካን ሀገር የፍርድ ቤቶች አወቃቀር ብንመለከት በፌዴራልና በክልል ደረጃ ከመቋቋማቸው (Dual court structure) ባሻገር በእያንዳንዱ መንግስት ሥር ጉዳዬች ዳግመኛ የሚታዩባቸው ሁኔታ ይኖራል፡፡ ለምሳሌ፡- በአንድ የግዛት ክልል ውስጥ በታችኛው ፍርድ ቤት መታየት የጀመረ ጉዳይ በግዛቱ የይግባኝ ፍርድ ቤት ከታየ በኋላ እስከ ፌ/ጠ/ፍርድ ቤት ድረስ የሚታይበት አጋጣሚ ሊፈጠር ይችላል፡፡ በተመሳሳይ በፈረንሳይ ሀገር ዜጐች የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ በመቃወም ጉዳያቸው ዳግመኛ በሌሎች ፍርድ ቤቶች ይታይላቸው ዘንድ ከይግባኝ ፍርድ ቤቶች በተጨማሪ የሰበር ሰሚ ችሎት (cassation division) ተቋቁመዋል፡፡ በሌሎች የምዕራብ አውሮፓ ልክ እንደ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ስፔን እና ሌሎች ሀገራት ተመሳሳይ የሆነ የፍርድ ቤቶች ከአደረጃጀትን በመቅረፅ ባለጉዳዬችን ቅር ያሰኙ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ዳግመኛ የሚታዩበትን መንገድ መፍጠር ችለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ፍርዶች ዳግመኛ ስለሚታዩባቸው መንገዶች በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ውስጥ የተካተቱና በአሁኑ ሰዓት በሰፊው በተግባር ላይ የምንጠቀምባቸው ዳግመኛ ፍርድ የመመርመሪያ መንገዶች ሶስት ሲሆኑ እነርሱም፡- ጉዳዮን በሚመለከተው ፍርድ ቤት (Review by a court of rendition) የይግባኝ ፍርድ ቤቶች (Appellate courts) የሰበር ሰሚ ችሎት (Cassasion Division) ናቸው፡፡ ጉዳዩን በሚመለከተው ፍርድ ቤት እንደገና ስለሚታይበት ሁኔታ ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤት ምንም እንኳን ውሳኔ አስተላልፎ መዝገቡን የዘጋው ቢሆንም ይህንኑ ጉዳይ ዳግመኛ እንዲመለከተው የሚያስገድዱ እጅግ በጣም መሠረታዊ የሆኑ ሁኔታዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕጉ በጥልቀትና በሰፊው የተቀመጡ በመሆናቸው አንድ በአንድ ለማየት እንሞክራለን፡፡ የሥነ ሥርዓት መዛነፍ (Procedural irregularities) ይህ ማለት የፍርድ ሥርዓቱ በሚከናወንበት ወቅት ከፍርድ አካሄድ ደንብ ውጭ የሆነ ተግባር ሲፈፀም ዳኞች ባለማስተዋል ወይም በሌላ ምክንያት በማለፍ ፍርድ የሚሰጡበት አጋጣሚ ማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ የፍ/ሥ/ሥ/ሕግ በሥነ ሥርዓት መፃነፍ ምክንያት ጉዳዩ እንደገና የሚታይበትን ሁኔታ የሚደነግጉት የሕግ ክፍሎች ከአንቀፅ 207-212 በዝርዝር ተቀምጠዋል፡፡ ፍርዱን የሰጠው ፍርድ ቤት የሥነ-ሥርአት መዛነፍ መፈጠሩን ከተረዳና የሥነ-ሥርአት መዛነፉ የጉዳዮን ፍሰት ወደ ሌላኛው ተከራካሪ ወገን በእጅጉ ሊለውጥ የሚችል ሆኖ ከተገኘ በራሱ ተነሳሽነት ወይም በአንደኛው ተከራካሪ ወገን ጠያቂነት ይህ ከሥነ- ሥርአት ውጭ የቀረበው ነገር በከፊል ወይም በሙሉ እንዲሰረዝ፣ እንዲሻሻለ ትዕዛዝ መስጠት ይችላል /አንቀጽ 207 ይመልከቱ/፡፡ የስነ-ሥርአት ጉድለቱ የተከሰተው ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ከሆነና ይህ ጉድለት የተሰጠውን ፍርድ ሊለውጥ የሚችል ከሆነ ፍ/ቤቱ የሰጠውን ፍርድ የመሰረዝ ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ 1.2. የአዲስ ማስረጃ መገኘት (Newly Discovered Evidences) ፍርድ የተሰጠባቸው ጉዳዬች ዳግመኛ ከሚታዩባቸው ዋነኛ ምክንያቶች መካከል በአዲስ መልክ የሚገኙ ማስረጃዎች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 6 መሠረት አንድ ሰው አዲስ በተገኙ ማስረጃዎች ምክንያት ፍርድ የሰጠውን ፍርድ ቤት ጉዳዩን እንደገና እንዲያየው ለማመልከት የሚከተሉት መሠረታዊ ቅድመ ሁኔታዎች በአንድነት ሊገኙ ያስፈልጋል፡፡ ሀ/ ማስረጃው የተገኘው ፍርድ ከተሰጠ በኋላ መሆን አለበት ለ/ አዲስ የተገኘው ማስረጃ ውሳኔው ላይ ተፅዕኖ የሚያሳርፍ መሆን አለበት፡፡ ሐ/ የተገኘው ማስረጃ የመጨረሻው ፍርድ የተሰጠው በሐሰተኛ ሰነድ፣ በሐሰተኛ ምስክርነት ወይም መደለያን ወይም ወንጀል ጠቀስ የሆነ ተግባርን መሠረት በማድረግ መሆኑን ማስረዳት ሲችል መ/ አቤት ባዩም ፍርድ ከመስጠቱ በፊት ትጋት አድርጐ ለማወቅ ያለመቻሉን ለማስረዳት የቻለ እንደሆነ ሠ/ በተሰጠው ፍርድ ላይ ይግባኝ መባል አይኖርበትም ረ/ አቤት ባዩ ተገኝቷል የሚለውን አዲስ ማስረጃ ካገኘበት ወይም መኖሩን ካወቀበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አቤቱታውን ማቅረብ ሲችል እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ቅድመ-ሁኔታዎች መገኘት ሲችሉ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 6 መሠረት ጉዳዩ ዳግመኛ የሚታይ ይሆናል፡፡ ስለመቃወም (Opposition) ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤት ዳግመኛ ፍርዱን እንዲመረምር የሚገደድበት ሶስተኛው ምክንያት የመቃወሚያ ማመልከቻ መቅረብ ነው፡፡ መቃወሚያ ማለት በመደበኛው የፍርድ ክርክር ሂደት ጊዜ አካል ያልነበረ ሶሶተኛ ወገን የተሰጠው ፍርድ የእሱን መብትና ጥቅም የሚነካ ሆኖ ሲያገኘው ወደ ፍርድ ሥርአቱ በመግባት ጉዳዩ እንደገና አንዲታይለት የሚጠይቅበት ሥርአት ነው፡፡ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 358 መሠረት መቃወሚያ ለማቅረብ መሟላት የሚኖርባ

Welcome to this Telegram Channel.