en
Feedback
Tsegaye Demeke - Lawyer

Tsegaye Demeke - Lawyer

Open in Telegram

Legal Service

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
5 673
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#የዋስትና_መብትን_የሚያስነፍጉ_ሁኔታዎች #Share ያድርጉ 💪ዋስትና የማንም የተያዘ ሰው ህገ-መንግስታዊ መብት ቢሆንም በሚከተሉት ምክንያቶች ዋስትና ሊነፈግ ይችላል ፡፡ ❶. የፈፀሙት የወንጀል ድርጊት ከ 15 ዓመትና በላይ በ ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ ከሆነና በተለይ በወንጀል ድርጊቱ የሰው ህይወት የጠፋ ከሆነ የዋስትና መብቶን ያጣሉ ፡፡ የወ/መ/ስ/ስ ህግ ቁጥር 63/1/ ❷ በጠየቁት የዋስትና ጥያቄ መሰረት ዐቃቤ ህግ ስለ ዋስትናዎ አስመልክቶ ለፍ/ቤቱ አስተያየት ሲጠየቅ እርሶ በዋስ ቢወጡ በገቡት ስምምነት ግዴታዎን እንደማይወጡ በበቂ ሁኔታ በማስረጃ ካረጋገጠቦት ፤ የወ/ወ/ስ/ስ ህግ ቁጥር 67/ሀ/ ማለትም ፡- (በተደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚገኙ ከሆነ ፤አሁንም ወደ ህግ የመጡት በመያዣ ትእዛዝ ከሆነ ፤ ከዚህ በፊት በዋስ ወጥተው ይህንኑ ያላከበሩ ከሆነ ፤ የእርሶ መኖሪያ ቦታ ከፍ/ቤቱ አካባቢ ስልጣን እጅግ የራቀ ከሆነ ፤ በሚስጥር ከሀገር ሊወጡ ቢያዙ የመሳሰሉት ሊሆኑ ይችላሉ ፡፡ ❸ በዋስ ቢወጡ በድጋሚ የወንጀል ድርጊት ውስጥ እንደሚገቡ ዐቃቤ ህግ በአስተያየቱ / ከፖሊስ በሚደርሰው መረጃ መሰረት / አስተያየቱን በአሳማኝ ሁኔታ የሰጠ ከሆነ ፡ በ ወ/መ/ስ/ስ ህግ ቁጥር 67 /ለ/ መሰረት ዋስትና ይነፈጋሉ በዋስ ቢለቀቁ ምስክሮችን በማባበል / በመግዛት ተጽእኖ በማሳደር ወይም ሌሎች ማስረጃዎችን ያጠፉ ይሆናል የሚለውን በ ዐቃቤ ህግ ወይም በመርማሪ በፖሊስ ሲረጋገጥ ፡፡ የወ/መ/ስ/ስ ሕግ ቁጥር 67 /ሐ/ እንዲሁም ❹ የፈፀሙት ወንጀል የሙስና ወንጀል ከሆነ አስቀድሞ የዋስ መብት ሊፈቀድሎት እንደማይችል ይወቁ ፡፡ #Binimos

ቁም ኑዛዜ ስጦታ • ሟች ከሞተ በኋላ ተፈፃሚ የሚሆን ስጦታ ሟች ከአንድ በላይ የሆኑ ልጆች ወይም ወራሾች ቢኖሩትና ከነዚያ መካከል ለአንደኛው የኑዛዜ ስጦታ ቢያደርግ የሌሎችን ወራሾች ከሟች ውርስ መነቀል አያስከትልም፡፡ ይህንንም የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 913 የኑዛዜው ቃል የተናዛዡን ተቃራኒ ሀሳብ የሚገልጽ ካልሆነ በቀር ከውርስ ሀብት አንድ ድርሻ ወይም አንድ ንብረት ሟቹ ለወራሾቹ መስጠቱ ተራ የሆነ የክፍያ ደንብ እንጂ እንደ ኑዛዜ ስጦታ ነው ተብሎ አይቆጠርም በማለት ይደነግጋል፡፡ ሰ/መ/ቁ 32337 ቅጽ 5፣ ፍ/ህ/ቁ. 882፣ 913፣ 2428፣ 2443

የፌደራል ፍርድ ቤቶች በመስከረም ወር በከፊል ዝግ ሆነው ይቆያሉ ******************** የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በመስከረም ወር 2013 ዓ.ም በከፊል ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡ ይህም ፍርድ ቤቶች የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል ከመጋቢት 10 - እስከ ሐምሌ 10 ቀን 2012 ዓ.ም በከፊል ዝግ ሆነው ከቆዩብ ሁኔታ ለመውጣትና ተቋርጦው የነበሩት አገልግሎቶችን ደረጃ በደረጃ ለማስጀመር ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሐምሌ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ባወጣው መመሪያ መሰረት ዳኞች በመስከረም ወር እረፍት አንዲያደርጉ በመወሰኑ ነው ተብሏል፡፡ ዳኞች ዓመታዊ እረፍታቸውን በነሃሴ እና በመስከረም ወር የሚወስዱ በመሆኑ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አስቸኳይነት ያላቸውን ጉዳዮች ብቻ በተረኛ ችሎቶች በማስተናገድ በከፊል ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ ማድረግ የተለመደ አሰራር መሆኑን ያስታወሰው ጠቅላይ ፍርድ ቤት፤ በዚህ ዓመት ዳኞች አጭር የእረፍት ጊዜ እንደሚኖራቸው ገልጿል፡፡ ፍርድ ቤቶቹ በከፊል ዝግ ሆነው በሚቆዩባቸው የመስከረም ወር 20 የስራ ቀናት አስቸኳይና ጊዜ የማይሰጡ ከዜጎች መሰረታዊ መብቶች እንዲሁም ከአገር ሰላምና ፀጥታ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ጉዳዮች እንደሚመለከቱ ተገልጿል፡፡ ለአብነትም እንደ የጊዜ ቀጠሮ፣ የዋስትናና የዕግድ ጥያቄዎች፣ የመያዣና የብርበራ ትዕዛዞች፣ በተፋጠነ ስነ-ስርዓት የሚታዩ የእጅ ከፍንጅ ወንጀሎች እንዲሁም ከቤተሰብና ከሕፃናት ቀለብና አስተዳደግ ጋር የተያያዙ አጣዳፊ መሰረታዊ ጉዳዮች በተረኛ ችሎቶች የሚስተናገዱ መሆኑ ተነግሯል፡፡ የአዲሱ ዓመት የመጀመሪያው ወር ለዳኞች የእረፍት ጊዜያቸው አንዲሆን የተወሰነ ቢሆን በፍርድ ቤቶች የተለመደ አሰራር አብዛኛዎቹ ዳኞች በፈቃዳቸው ውዝፍ መዛግብትን በማጥራት ስራ ላይ የሚቆዩ መሆናቸውን ከፕሬዝደንት ጽ/ቤት ከተገኘው መረጃ ለመረዳት ተችሏል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤ ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ለዳኞች በስተላለፉት የምስጋና መግለጫ “መጪው አዲስ ዘመን ቃል የገባንለት ህጋዊና ፍትሃዊ ዳኝነት የመስጠት ተልዕኳችንን በእውቀትና በሙያ፤ በገለልተኝነትና በሐቀኝት፤ በቅልጥፍናና በጥራት፤ በነጻነትና በተጠያቂነት የምንወጣበት፤ ህብረተሰቡ በፍርድ ቤቶቻችን ላይ ያለው ዓመኔታ ከፍ የሚልበት እና ለሌላ ተጨማሪ ስኬት የምንበቃበት ዘመን እንዲሆንልን እመኛለሁ!!” ብለዋል፡፡ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

የመቀጮ ስምምነት ============= • አንደኛው ወገን ግዴታውን ያልፈጸመ ወይም አጉድሎ ወይም አዘግይቶ የፈፀመ እንደሆነ የሚከፍለውን የገንዘብ መጠን በግልጽ በመለየት ተዋዋዮቹ አስቀድመው በውላቸው ላይ የሚወስኑት የካሳ መጠን አንደኛው ወገን ግዴታውን ያልፈፀመ እንደሆነ ወይም አጉድሎ ወይም አዘግይቶ የፈፀመ እንደሆነ የሚከፍለውን መቀጮ ተዋዋዮች አስቀድመው በውላቸው ለመወሰን ይችላሉ፡፡ ባለገንዘቡ መቀጫ /ገደብ/ ሊቀበል የሚገባው ውሉ ባለመፈፀሙ ኪሣራ ለመጠየቅ በሚችልበት ጊዜ ሁሉ እንደሆነ ነው፡፡ ባለገንዘቡ ኪሣራ ባይደርስበትም የተዋዋለው መቀጫ /ገደብ/ ሊከፈለው ይገባል፡፡ ሰ/መ/ቁ. 58258 ቅጽ 12፣ ፍ/ህ/ቁ. 1889፣ 1891፣ 1892/1/ ባለዕዳው ለውሉ አለመፈፀም ምክንያት በመሆኑ የተነሣ በባለገንዘቡ ላይ የደረሰው ጉዳት በመቀጮ ስምምነቱ ከተወሰነው በላይ ሊሆን ቢችልም ባለዕዳው በመቀጮ ውሉ ከተመለከተው የጉዳት ኪሣራ ገንዘብ ጣሪያ በላይ ባለገንዘቡን እንዲክስ አይገደድም፡፡ ሰ/መ/ቁ. 69797 ቅጽ 14፣ ፍ/ህ/ቁ. 1731፣ 1889 በልዩ ሁኔታ የተደገነጉ ድንጋጌዎች ተዋዋዮች የሚያደርጉትን የመቀጮ ስምምነት መጠን የሚገድቡና የሚከለክሉ በሆነ ጊዜ የመቀጮ ስምምነትን የሚፈቅደው የፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 1889 ድንጋጌ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡ የብድር ገንዘብ አመላለስን አስመልክቶ ተበዳሪው የብድር ገንዘቡን በውሉ በተጠቀሰው ጊዜ ከመክፈል የዘገየ እንደሆነ ለአበዳሪው በኪሣራ መልክ የሚከፍለው በፍትሐብሔር ህጉ በተደነገገው መሠረት የወለድ ገንዘብ እንደሆነ በፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 2489 ንዑስ አንቀፅ 1 የተደነገገ ሲሆን በህግ ከተፈቀደው የወለድ መጠን በላይ ተበዳሪው መቀጫ እንዲከፍል የሚደረግ ስምምነት ፈራሸ እንደሆነ በፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 2489 ንዑስ አንቀፅ 2 በግልፅ ተደንግጓል፡፡ በተጨማሪም ብድሩ በውሉ ጊዜ ካልተመለሰ ተበዳሪው የተወሰነ የገንዘብ መጠን በመቀጮ እንዲከፍል የሚደረግ ስምምነት የየፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 2489 ንዑስ አንቀፅ 2 አስገዳጅ ድንጋጌን የሚጥስና ህጋዊ ውጤት የሌለው ነው፡፡ ሰ/መ/ቁ. 59882 ቅጽ 12፣ ፍ/ህ/ቁ. 1889፣ 2489 ተዋዋዮች በወለድ የሚከፈለውን ገንዘብ በዓመት በመቶ ከአስራ ሁለት በላይ እንዲሆን ለመዋዋል እንደማይቻል በፍ/ሕ/ቁጥር 2479/1/ የተመለከተ ከመሆኑም በላይ በወለድ የሚከፈለው ገንዘብ በመቶ አስራ ሁለት በላይ በዓመት እንዲሆን በጽሑፍ የተደረገ ውል ቢኖር እንኳ ተበዳሪው በመቶ ዘጠኝ ብቻ በዓመት ወለድ መክፈል እንዳለበት በፍ/ሕ/ቁ. 2479/3/ በአስገዳጅ ሁኔታ ተደንግጓል፡፡ ከዚህ አንፃር ተዋዋዮች የብድርን ገንዘብ እጥፍ አድርጐ ለመክፈል መስማማትን ሕጉ አይፈቅድም፡፡ ሰ/መ/ቁ. 43372 ቅጽ 8 ፣ ፍ/ህ/ቁ. 2479(1) እና (3)

ይግባኝ ማስፈቀጃ =============== • በህጉ የተቀመጠው የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በኋላ ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድ የሚቀርብ አቤቱታ አንድ ፍ/ቤት ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜው ያለፈበት ምክንያት በቂ መሆኑን ሲረዳ ይግባኙ እንዲቅርብ ሊፈቅድ እንደሚገባ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 326/1/ ስር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቱ የቀረበለት ምክንያት በቂ መሆን አለመሆኑን በአግባቡ ሊመረምረው ይገባል፡፡ በእርግጥ በቂ ምክንያት የሚባሉት ነገሮች ሕጉ ዘርዝሮ ያላስቀመጣቸው በመሆኑ ለመወሰን አስቸጋሪ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በመሆኑም የምክንያቱ በቂ መሆን አለመሆን በእያንዳንዱ ጉዳይ ከሚቀርቡ ፍሬ ነገሮች ጋር ተገናዝበው ሊመዘኑ ይገባል፡፡ ሰ/መ/ቁ. 38145 ቅጽ 8፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 326/1/ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ መሠረት ለአንድ ፍርድ ቤት መዝገብ ሹም የተሰጠው ሥልጣን ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ማለፍ አለማለፉን በመመልከት ይግባኝ መዝገቡ እንዲከፈት ማድረግ ሲሆን ይግባኙ ጊዜውን ጠብቆ ያልቀረበ ከሆነ ማመልከቻውን መመለስ፣ ማመልከቻው የተመለሰበት ወገን የይግባኝ ጊዜው ያለፈበት ሕጋዊ ምክንያት ካለው ማስፈቀጃ አቤቱታውን በማቅረብ ይኸው ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድለት ራሱን የቻለ አቤቱታ አቅርቦና ይህ መዝገብ ተከፍቶ ጉዳዩ ለችሎት ቀርቦ ችሎቱ የይግባኝ ማስፈቀጃውን በመመርመር በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 መሠረት ተገቢ ነው ያለውን ትእዛዝ የሚሰጥበት ነው፡፡ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ ከፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 ድንጋጌዎች ጋር አንድ ላይ ሲነበቡ የመዝገብ ቤት ሹም ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለችሎት እንዲቀርብ የመፍቀድ ስልጣን የሌለው መሆኑን የሚያሳዩ ሲሆን ፋይሉ ተከፍቶ ቀርቦ ከሆነም ችሎቱ ጉዳዩን መርምሮ ይግባኙ የቀረበው ጊዜው ከአለፈ በኋላ ነው በማለት መዝገቡን ከመዝጋት የሚከለክለው አይደለም፡፡ ሰ/መ/ቁ. 61843 ቅጽ 11፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 324-326

ሰቦቻችንንና ሃገራችን ከችግር እንታደግ!! ----------------------- // ---------------------------- የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከሀምሌ 13/2012 ዓ.ም ጀምሮ ስለሚሰጡ ተጨማሪ የዳኝነት አገልግሎቶች የተሰጠ መግለጫ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የኮሮና ቫይረስ (Covid-19) ወረርሽኝ በሀገራችን መኖሩ ከታወቀበት ጊዜ ጀምሮ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ ከመጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ዝግ በመሆን እና የከፊል ዝግ ውሳኔውን በማራዘም እስከ ሐምሌ 10/2012 ዓ.ም ድረስ በፍ/ቤቱ አመራር በተለዩ ጉዳዮች ላይ ብቻ አገልግሎት እየሰጡ ቆይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ባህሪና ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር ወረርሽኙ በአጭር ጊዜ በቁጥጥር ውስጥ ልናስገባውና ስርጭቱን ሙሉ በሙሉ ልንገታው የማንችል መሆኑን እንዲሁም አብሮን በተግዳሮትነት የሚቀጥል እንደሆነ ማስረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቶችን በከፊል በመዝጋት የዜጎች ፍትህ የማግኘት መብትን በውል ላልታወቀና ለተራዘመ ጊዜ ማቆየት የማይቻል መሆኑን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይረዳል፡፡ በተጨማሪም ከኮቪድ በኋላ ፍርድ ቤቶች መደበኛ ስራቸውን ይጀምሩ በሚባልበት ጊዜ ወደ ፍ/ቤት ሊመጣ የሚችለው ከፍተኛ የመዛግብት ፍሰት ፍርድ ቤቶች ስራቸውን መስራት የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሊያስገባቸው እንደሚችል በፍርድ ቤቱ የተከናወነው የመላምት ትንታኔ ያሳያል፡፡ ለእነዚህ ሁለት አበይት ችግሮች መፍትሄ መስጠት ያስችል ዘንድ ወረርሽኙን በከፍተኛ የመካላከልና የጥንቃቄ እርምጃዎችን በመውሰድ የተቋረጡትን አገልግሎቶች ደረጃ በደረጃ ማስጀመር አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ስለሆነም ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ሆነው እንዲቆዩ ከተደረጉበት ከሃምሌ 13 ቀን 2012 ዓ.ም በኋላ ደረጃ በደረጃ መደበኛ አገልግሎት መስጠት ስለሚጀምሩበት ሁኔታ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀፅ 16 (1) እና በዚሁ አዋጅ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 454/97 አንቀፅ 4 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ መመሪያ አውጥቷል፡፡ በመመሪያው መሰረት በየደረጃው ባሉ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከሃምሌ 13 2012 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጡ አገልግሎቶች እና የሚወሰዱ አስገዳጅ እርምጃዎች የሚከተሉት ይሆናሉ፡፡ 1. ከሐምሌ 13 - 30 /2012 ዓ.ም የሚሰጡ አገልግሎቶች  በሁሉም ደረጃ ባሉት ፍ/ቤቶች መልስ፣የመልስ መልስ፣ አስተያየቶች ፣የትዕዛዝ ውጤቶች ለመቀበል የተቀጠሩ፣ እልባት ለመስጠት ጥቂት ሂደት ብቻ የሚቀራቸው ጉዳዮች እንዲሁም እስረኛ ያላቸው መዛግብት በየቀጠሮ ቀናቸው የማስተናገድ፤  ማስረጃ ለመስማት' ክስ ለመስማት የተቀጠሩ መዝገቦች በጣም አስቸኳይነታቸዉ በዳኛው፣ በየፍርድ ቤቱ በየደረጃው በሚገኝ አመራር እስካልታመነ ድረስ ለቀጣይ የ2013 በጀት ዓመት የሚቀጠር ይሆናል ሆኖም ግን ከዚህ በፊት በተሰጡት መመሪያዎች መሰረት ሲከናወኑ የነበሩ ተረኛ ችሎቶችን በማደራጀት በአመራሩ የተለዩ ወሳኝ እና አንገብጋቢ ጉዳዮች በተለይም ከዜጐች የሰብዓዊ መብት ጋር የተቆራኙ ጉዳዮችን፣ ከቤት ውስጥ ጥቃት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን፣ እግድ፣ በስምምነት ፍች፣ ጥፋት ውስጥ ገብተው የተገኙ ወጣቶች (ወጣት ጥፋተኞች)፣ የልጆች አስተዳደግ እና ቀለብን የመሠሉ የቤተሰብ ጉዳዮች፣ አፋጣኝ የወንጀል ጉዳዮች (RTD) ከአስቸኳይ ግዜ አዋጅ አፈፃፀም ጋር የተያያዘ የወንጀል ጉዳዮችን፣ በስምምነት ክስን ማቋረጥ፣ ከትላልቅ ሜጋ ኘሮጀክቶች ጋር የተያያዙ የንግድ ኢንቨስትመንት ጉዳዮች፣ ከሀገር ፀጥታ እና ሠላም ጋር የተያያዙ የወንጀል ጉዳዮች እንዲሁም ብዙ ተካራካሪ የሌላቸው መዛግብትን የሚስተናገዱ ሲሆን በመደበኛ ችሎት ሲስተናገዱ የነበሩ የስራ ክርክር፣ የሴቶች እና ህፃናት ችሎቶች፣ የሁከት እና ሌሎች የአስተዳደር ጉዳዮች በመደበኛ ችሎት ዳኞች በየቀጠሯቸው የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡  በየደረጃው ያሉ የፍርድ አፈጻጸም ችሎቶች በአጭርና በቀላሉ የሚፈፀሙ የአፈፃፀም ጉዳዮችን ማስተናገድ የሚጀምሩ ይሆናል፡፡ ከዚህ በተያያዘም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት ከሐምሌ 13/2012ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ ስራውን የሚጀምር ሲሆን በፍርድ አፈፃፀም ምክንያት ከመኖሪያ ቤት ማስለቀቅ፣ የመኖሪያ ቤት ሽያጭ ማጫረት ማካሄድ ውስብስብነት ያላቸውና የሰዎች መሰባሰብ የሚጠይቁ የአፈፃፀም ጉዳዮች ተለዋጭ የስራ አቅጣጫ እስከሚሰጥ ድረስ ባሉበት ደረጃ እንዲቆዩ ይደረጋል፡፡  የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በአዲስ አበባ ከሚገኙ ባለጉዳዮች የሚቀርቡ የሰበር አቤቱታዎችን የሚያሥተናግድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ከአዲስ አበባ ውጪ የሚገኙ ባለጉዳዮችን በዚህ ወቅት ማስተናገድ ለኮቪድ 19 ወረርሽኝ ያላቸውን ተጋላጭነት የሚጨምር መሆኑን ታሳቢ በማድረግ የወረርሽኙ ስርጭት አስጊነት በቀነሰና ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ የስራ አቅጣጫ በሚሰጥበት ጊዜ የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡  በሁሉም ፍርድ ቤቶች የምርመራ መዛግብት የማጥራት ተግባር በተጨማሪነት የሚከናወን ይሆናል፡፡ 2. በነሀሴ ወር 2012 ዓ.ም የሚሰጡ አገልግሎቶች  በሁሉም ደረጃ ባሉት ፍ/ቤቶች አዲስ መዝገቦችን ማለትም ቀጥታ ክስ፣ ይግባኝ እና አፈፃፀም መዝገቦችን የመክፈት አገልግሎት ይጀመራል፡፡  ዳኞች በየዓመቱ በነሐሴ ወር እረፍት የሚወስዱ የነበረ ቢሆንም ወደፊት በዳኝነት ስራ ላይ የሚፈጠረውን የስራ ጫና ለማቃለል እንዲረዳ ዳኞች በስራ ገበታቸው በመገኘት አዲስ የሚከፈቱ መዝገቦችን በመመርመር በጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መርህ መሰረት ቀጠሮ ወይም ተገቢውን ትእዛዝ የሚሰጡ ይሆናል፡፡  አስቸኳይነት ያላቸው ጉዳዮች ማለትም ቀደም ሲል በተረኛ ችሎት ሲስተናገዱ የነበሩ ጉዳዮች በተረኛ ችሎት መስተናገዳቸውን ይቀጥላሉ፡፡  የምርመራ መዛግብት የማጥራት ስራ በተጨማሪነት የሚከናወን ይሆናል፡፡ 3. በመስከረም ወር 2013 ዓ.ም የሚሰጡ አገልግሎቶች  የመስከረም ወር 2013ዓ.ም የዳኞች የእረፍት ጊዜ ይሆናል፡፡  አስቸኳይ ጉዳዮች ማለትም በተረኛ ችሎት ሲስተናገዱ የነበሩ ጉዳዮች እስከ መስከረም 30/2013ዓ.ም በተረኛ ችሎት የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡ ፍርድ ቤቶች አብዛኛውን አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ተከትሎ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል በሁሉም ፍርድ ቤቶች በአስገዳጅነት ሊተገበሩ የሚገባቸዉ የጥንቃቄ እርምጃዎች 1. በቀጣይ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቢያንስ ሁለት ሜትር ርቀትን በጠበቀ ሁኔታ እንዲከናወን ማድረግ፤ 2. ሰራተኞችም ይሁኑ ተገልጋዮች የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ እንዲጠቀሙ ማድረግ፤ 3. ለፍ/ቤቱ ማህበረሰብና ለተገልጋይ የሚያገለግሉ የንፅህና መጠበቂያ ግብአቶችን እንደ የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ውሃ፣ ሳሙና፣ አልኮል እና ሳኒታይዘር የመሳሰሉትን ማሟላትና እንዲጠቀም ማድረግ፡፡ 4. ተገልጋይም ሆነ የፍ/ቤቱ ማህበረሰብ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊት የሙቀት መጠን እንዲለካ ማድረግና የሙቀት መጠኑ ከ38 ዲግሪ በላይ ከሆነ ተለይቶ ማቆየት እና በአቅራቢያው ለሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ማሳወቅ፡፡ 5. በየእለቱ ቀጠሮ ካላቸዉ ተከራካሪ ወገኖች እና የፍ/ቤቱን ሌሎች አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ ባለጉዳዮች ብቻ ወደ ፍ/ቤቱ ግቢ እንዲገቡ ማድረግ፡፡ 6. በየደረጃው ባሉ ፍ/ቤቶች በሚወሰን ግዜ በመደበኛነት የኮቪድ 19 ተጋላጭነት ለመከላከል የፀረ-ተሀዋሲያን ርጭት ማከናወን፡፡ 7. የፍ/ቤቱ አመራር የሚያወጣቸውን ተጨማሪ የጥንቃቄ እርምጃዎች በጥብቅ መተግበር ይሆናል፡፡ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመከላከል በጤና ባለሙያዎች የሚሰጡ ምክሮችን በጥብቅ በመተግበር ከወረርሽኙ ራሳችንን፤ ቤተ

Forgiveness .pdf7.77 KB

Urban-land-lease-proclamation-no-721-20111.pdf1.54 MB

All the followers of this channel, you are requested kindly to paricipate on the survey through the following link:- https://forms.gle/ZypsZjGBgUesSBbj9

ና በምን ሁኔታ እንደሚሾሙ የሚያመላክት እንዲሁም ምትክ ዳኞች ሊሰሩ ስለሚገባበት ሁኔታና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች የሚያመላክት ሕግ እንዲወጣ ማድረግና ድንጋጌዎቹም መፈፀማቸውን በአግባቡ መከታተል ለሕጉ ተፈፃሚነት መፍትሔ ይሆናል::

ምትክ ዳኞች ስለሚሾሙበት እና ስለሚሰሩበት ሁኔታ - የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 132 - 135 የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ ከቁጥር 132 እስከ 135 ድረስ ምትክ ዳኞች /Judicial Commissioners/ በፍርድ ቤቶች ስለሚሾሙበት፣ የሥራ ኃላፊነታቸው ምን እንደሆነና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦችን ያስቀምጣል፡፡ ለመሆኑ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ ምትክ ዳኞችን አስመልክቶ የሚያስቀምጣቸው ነጥቦች ምንድን ናቸው? ለተከራካሪ ወገኖች የምትክ ዳኞች መሾም አስፈላጊነቱ ምንድን ነው? ሕጉ በተግባር እየተፈፀመ ነው ወይ? የሚሉና ሌሎች ነጥቦችን እንዳስሳለን፡፡ ምትክ ዳኛ መሾም ለምን አስፈለገ? ፍርድ ቤቶች የሚመለከቷቸው ጉዳዮች ዘርፈ ብዙ እንደመሆናቸው መጠን እንደየጉዳዩ ሁኔታ በቀላሉ የቀረቡ ማስረጃዎችን እና የተከራካሪ ወገኖችን ክርክር በመስማት ብቻ ከሚወሰንባቸው መዛግብት አንስቶ እጅግ ጥልቅ የሆነ ምርመራ፣ ነባራዊ ሁኔታዎችን መመልከትና እውነትን ከችሎት ውጭ በሚደረግ ምልከታና ምርመራ ማፈላለግ እንዲሁም እንደጉዳዩ ዓይነት የሂሳብ ምርመራ ማድረግ የሚጠይቁ መዛግብቶች በርካታ ናቸው፡፡ ፍርድ ቤቶች (ዳኞች) ከሚመለከቷቸው መዛግብት ብዛትና ከሚኖርባቸው የሥራ ጫና አንፃር ከችሎት ሥራ በተጨማሪ ከችሎት ውጪ የክርክር ምክንያት የሆኑ ስፍራዎች ላይ እየተገኙ አስፈላጊ ማጣራትና ምርመራ ከሚያደርጉ ይልቅ ፍርድ ቤቶች በሚሾሟቸው ምትክ ዳኞች በኩል ሥራዎቹ ቢከናወኑ የፍርድ ቤቶችን/ዳኞችን የሥራ ጊዜና ጫና ይቀንሳል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎንም በሀሰት የሚቀርቡ ክሶችን ወይም ክርክሮችን ውድቅ ለማድረግ ለክርክር ምክንያት በሆኑ ስፍራዎች በመገኘትና በቂ ምርመራና ማጣራት በማድረግ በቀላሉ ለመወሰን ያግዛል፡፡ የምትክ ዳኞች የሥራ ኃላፊነት ምንድን ነው? ምትክ ዳኞች በፍርድ ቤት ከተሸሙ በኋላ የሚከተሉትን የሥራ ኃላፊነቶች መወጣት እንዳለባቸው የሥነ ሥርዓት ሕጉ ይጠቁማል፡፡ እነዚህም፡ - ክርክር ከሚደረግበት ጉዳይ ጋር በተያያዘ የክርክሩ ምክንያት በሆነው ስፍራ ላይ በመገኘት አስፈላጊ የሆኑና ከክርክሩ ጋር የተያያዙ ለፍርድ ቤት ውሳኔ አሠጣጥ የሚጠቅሙ ነጥቦችን ማጣራትና መመርመር፤ የክርክር ምክንያት በሆነ ስፍራ በመገኘት እንደአስፈላጊነቱ የምስክሮች ቃል መቀበል እና ማስረጃዎች መሠብሠብ፤ የክርክር ምክንያት በሆነ ስፍራ በመገኘት ከተደረገው ማጣራት፣ ምርመራ፣ የምስክሮች ቃልና የተሰባሰቡ ማስረጃዎች እንዲሁም ችሎቱ እንዲጣራለት ከፈለገውና ትዕዛዝ ከሠጠባቸው ነጥቦች አንፃር ለፍርድ ቤቱ በፅሁፍ መግለጫ /ራፖር/ የማቅረብ፤ ራፖር በቀረበበት ጉዳይ ላይ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የመሀላ ቃል በመስጠት በግልፅ ችሎት ከተከራካሪዎችና ከፍርድ ቤቱ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠት፤ በፍርድ ቤት ሲታዘዝ ሒሳብ ማጣራት አስፈላጊ በሆነባቸው ክርክር እና መዛግብት ላይ የሒሳብ ምርመራ አጣርቶ ከአስተያየት ጋር ራፖር የማቅረብ ኃላፊነቶች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ፍርድ ቤቶች/ዳኞች ከምትክ ዳኞች ጋር በተያያዘ የተጣለባቸው ኃላፊነት ምንድን ነው? ክርክር እየተደረገበት የሚገኝ ጉዳይ ላይ በስፍራው በመገኘት ነገሮችንና የክርክር መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን እንዲሁም ሂሳብ ማጣራትና መመርመር አስፈላጊና የሚጠቅም መሆን አለመሆኑን ተመልክቶ አስፈላጊና ጠቃሚ ሆኖ ሲገኝ ምትክ ዳኛ የመሾም ወይም እንዲሾም የማድረግ፤ ምትክ ዳኛ ሲሾም በስፍራ ተገኝቶ የሚጣራው ወይም ሒሳብን በተመለከተ የሚያጣራቸውን ነጥቦችና እንደአስፈላጊነቱ ሊሰበስባቸው የሚገቡ እና የማስረጃ ዓይነቶችንና ቃል ሊቀበላቸው የሚገባ ምስክሮችን ዓይነት በማመላከት ግልፅነት ያለው ትዕዛዝ መስጠት፤ ምትክ ዳኛው የሚያቀርበው ራፖር በተሠጠው ትዕዛዝ መሠረት ከምትክ ዳኛው አስተያየት ጋር መቅረቡን ማረጋገጥና የጎደለ ነገር ካለ በድጋሚ እንዲጣራ የማድረግ፤ በፍርድ ቤቱ ሲታመንበት ወይም ተከራካሪ ወገኖች ሲጠየቁ ምትክ ዳኛው በግልፅ ችሎት በመሐላ ቃል ስለራፖሩ ቃሉን እንዲሰጥ የማድረግ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ተከራካሪ ወገኖች ከምትክ ዳኞች አንፃር ለፍርድ ቤት ሊያነሱ የሚችሉት ምን ዓይነት ጥያቄዎች ናቸው? ተከራካሪ ወገኖች ክርክር በሚያደርጉበት ጉዳይ ላይ በፍርድ ቤት የተሾመ ምትክ ዳኛ በሚያቀርበው መግለጫ (ራፖር) ላይ በተለያዩ ምክንያቶች ምትክ ዳኛው ስላጣራው እና ስለመረመረው ጉዳይ የመሀላ ቃል ፈፅሞ በግልፅ ችሎት ስለ ሁኔታው እንዲያስረዳ ለመጠየቅ ይችላሉ፡፡ ምትክ ዳኛ ሊሾም የሚችለው በምን ዓይነት ጉዳዮች ላይ ነው? የዕለት የገበያ ሁኔታ ማወቅ በሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ፤ የካሣ ልክ ማረጋገጥ በሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ፤ ካንድ ሀብት የተገኘ የዓመት ትርፍ ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ በሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ፤ ያለአግባብ የተወሰደ ንብረት የሀብት ግምት ማጣራት በሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ፤ እንደ የመተላለፊያ መብቴ ተጣበበብኝ፣ ያለአግባብ የባለቤትነት መብቴ ተጣበበብኝ እና ይህን መሰል በሆኑ ለክርክር ምክንያት በሆነው ስፍራ ተገኝቶ ሁኔታዎችን ማጣራትና መመርመር የሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ፣ የሂሳብ ምርመራ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ በዋናነት ሊጠቀሱ የሚችሉ የምትክ ዳኞችን የሥራ ተሳትፎ የሚጠይቁ ጉዳዮች ናቸው፡፡ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 132፣ 133፣ 134 እና 135 ተግባራዊ አፈፃፀም ምን ይመስላል? ሥነ ሥርዓት ሕጉ ክርክር የተነሳባቸው ጉዳዮች ላይ በስፍራ ተገኝቶ ማጣራት እና መመርመር በሚያስፈልጋቸው እንዲሁም የሒሳብ ምርመራ በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ ምትክ ዳኛ መሾም እንዳለበት እና ምትክ ዳኛውም አስፈላጊውን ማጣራትና ምርመራ አድርጎ በሚያቀርበው መግለጫ /ራፖር/ መሠረት ፍርድ ቤቶች ሊወስኑ እንደሚገባ ቢያመለከትም በፌደራልም ሆነ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች በኩል ሕጉ ሲተገበር አይታይም፡፡ በሕጉ መሠረት በምትክ ዳኛ ማጣራትና ምርመራ ተደርጎባቸው በሚቀርቡ መግለጫዎች /ራፖር/ መሠረት ፍርድ ሊሰጥባቸው የሚገቡ በርካታ ጉዳዮች ላይ የምትክ ዳኛ ሳይሾም፣ ማጣራትና ምርመራ ሳይደረግ እንዲሁም መግለጫ ሳይቀርብባቸው ፍርድ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በፍርድ ቤቶች በኩልም በዕለት ተዕለት ሥራቸው ውስጥ ከዳኞች ውጪ ተያያዥ ሥራዎችን ሲያከናውኑ የሚታዩት ረዳት ዳኞች እንጂ ምትክ ዳኞች አይደሉም፡፡ ረዳት ዳኞችም በመዛግብት ላይ ክስ ሲሰሙ፣ ቀጠሮ ሲሰጡ እንዲሁም የምርመራ መዛግብት ላይ ፍርድ በመስጠት ዋና ዳኞችን ሲያግዙ አለፍ ሲልም የውርስ ሀብት የማጣራት ሥራ ሲሰሩ እንጂ በሥነ ሥርዓት ሕጉ የተቀመጠውን የምትክ ዳኛ ተግባራት ሲያከናውኑ አይታዩም፡፡ ፍርድ ቤቶች ክርክር ያስነሳ ንብረት ከሚገኝበት ስፍራ ተገኝቶ መመርመርና ማጣራት የሚጠይቁ ጉዳዮችን እንዲያጣሩ የሚያደርጉት በብዛት በክፍለ ከተማ አስተዳደር አካላት በኩል ተጣርቶ በፅሁፍ ይገለፅ በሚል መሆኑም ድንጋጌው ተግባራዊ አለመደረጉን ከማሳየቱ ባሻገር ከተዓማኒነት አንፃር በተከራካሪ ወገኖች ቅሬታ የሚያስነሳ አሠራር ነው፡፡ ድንጋጌዎቹ ተፈፃሚ ሊሆኑ ያልቻሉት በርግጥ ምትክ ዳኞችን ሊያስሾሙ የሚችሉ ጉዳዮች ስለሌሉ? ወይስ ፍርድ ቤቶች ምትክ ዳኞችን ለመሾም የሚያስችል መዋቅርና አሠራር ስለሌላቸው? የሚሉ ጥያቄች በዳኞች ወይም ፍርድ ቤቶች ሊታዩ የሚገባቸው ናቸው፡፡ የመፍትሔ ሀሳቦች የሕግ አውጪው ወይም ፍርድ ቤቶች የምትክ ዳኞችን ተሳትፎ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ዓይነት፣ ምትክ ዳኞች ሊኖራቸው ስለሚገባው የትምህርት ደረጃና የሥራ ልምድ፣ ምትክ ዳኞች እንዴት፣ በማን

ች ምክር ቤት በሽታውን ለመቆጣጠር ያግዘው ዘንድ እነዚህን የንግድ ውድድር እና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ የሕግ ክፍተቶች የሚሞላ ድንጋጌን ቢያወጣ የተሻለ አፈፃፀም ይኖረዋል። ማጠቃለያ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የወረርሽኝ አደጋ ሲከሰት በሀገራት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ የሚያደርሰው ጫና ቀላል የሚባል አይደለም። አሁን ላይ አለማችን ያጋጠማት እና በሀገራችን መከሰቱ የተረጋገጠው የኮረና ወረርሽኝም ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ሀገራት ላይ እያደረሰው ያለው ሰብዓዊ እና ማህበራዊ ኪሳራም በጣም ከፍተኛ ነው። እንደዚህ አይነት አደጋዎች በሚከሰቱበት ወቅት በጣም ፈታኝ እና እልህ አስጨራሽ ከሚሆኑ ህገወጥ ተግባራት መካከል የነጋዴዎች ከአደጋ የማትረፍ እሩጫ ትልቁን ድርሻ ይይዛል። ይህ የነጋዴው ማህበረሰብ ኢሞራላዊ እና ህገወጥ እንቅስቃሴ በሀገር ላይ በተለይ ደሞ በሸማቹ ማህበረሰብ ላይ የሚያደርሰው ሰብዓዊ እና ማህበራዊ ቀውስ በጣም ከባድ ነው። ይህንን ቀውስ ለመከላከል ወይም ለመቀነስ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ጠንካራ የሕግ ሥርዓት መዘርጋት ትልቁን ድርሻ ይወስደዋል። ሀገራት እንደዚህ አይነት ችግሮችን ለመቀነስ የሸማቾች ጥበቃ ሕግን በብዛት ሲጠቀሙ ይስተዋላል። ኢትዮጵያም ለሸማቾች ጥበቃ ልዪ ትኩረት መስጠት ከጀመረችበት 2002 ዓ.ም ጀምሮ ሁለት የሸማቾች ጥበቃን የሚመለከቱ ህጎችን ያወጣች ሲሆን አሁን በስራ ላይ ያለው የንግድ ውድድር እና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ከአካተታቸው ድንጋጌዎች መካከል የንግድ እቃዎችን ማከማቸት እና መደበቅን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች ይገኙበታል። የአዋጁ አንቀፅ 24 ለነጋዴዎች በገቢያ ላይ ከተለመደው መጠን ውጭ እንዲሁም ነጋዴ ላልሆኑ ግለሰቦች ለግል ወይም የቤተሰብ ፍጆታ ከሚያስፈልግ በላይ በንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስተር እጥረት እንዳለበት የተገለፀን እቃ ይዞ መገኘት የተከለከለ መሆኑን ይደነግጋል። ነጋዴዎችን በተመለከተ አዋጁ የመጠን እና የጊዜ መስፈርት የአስቀመጠ ሲሆን ከነጋዴ ውጭ የሆኑ ግለሰቦችን በተመለከተ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የመወሰን ስልጣን ተሰጦታል። ከተፈቀደ መስመር ውጭ ሲጓጓዝ የተገኘ እቃም ምንም እንኳ መስፈርቶችን ባያሟላም እንደ ተከማቸ እቃ እንደሚቆጠር አዋጁ ያስቀምጣል። የአዋጁን ድንጋጌዎች ጥሶ እቃ አከማችቶ የተገኘ ነጋዴም እቃ የመወረስ፣የገንዘብ እና የስር ቅጣቶች ይጠብቁታል። አሁን በዓለም ላይ እንዲሁም በሀገራችን የተከሰተውን ኮረና ወረርሽኝ አደጋን ተከትሎ እየተስተዋሉ ያሉ የነጋዴዎች እንቅስቃሴን ከመግታት አንፃር የዚህን ሕግ ጥንካሬ ስንገመግም በተለይ የተቀመጡት የመጠን መነሻ መስፈርቶች እና የእፎይታ ጊዜዎች የነጋዴውን ማህበረሰብ የአልተገባ እንቅስቃሴ የሚደግፉ እና ህዝብን ለከባድ ችግር የሚያጋልጡ ስለሆኑ ማስተካከያ ሊደረግባቸው እና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በሚያስችል መንገድ ሊቃኙ ይገባል። ይህንም ለማድረግ ወረርሽኙን ለመከላከል የፌደራል መንግስቱ የአወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 3/2012 መሰረት አድርጎ እነዚህን ገደቦች የሚያነሳ መመሪያ ማውጣት ያስፈልጋል። https://t.me/Consultancy2012 Source:- ፍኖተ ህግ

ቅ ክልክል ነው። እዚህ ላይ በመጀመሪያ ደረጃ የንግድ ሚኒስተር እጥረት ያለበትን እቃ በዝርዝር በህዝብ ማስታወቂያ የማሳወቅ ሀላፊነት ያለበት ሲሆን ይህንም ተከትሎ ነጋዴዎች እና ለግል ወይም የቤተሰብ ፍጆታ የሚሸምቱ ግለሰቦች ከመደበኛ መጠን ያለፈ እቃን ማከማቸት ወይም መደበቅ አይችሉም። ነጋዴውን ማህበረሰብ ወይም ሌሎችን ግለሰቦች ከእነዚህ ተግባሮች እንዲቆጠቡ ለማድረግ ሚኒስተሩ በመጀመሪያ የራሱን ሀላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ መገንዘብ ይገባል። የህዝብ ማስታወቂያዎች ለህዝቡ ተደራሽ በሆኑ የብሮድካስት ወይም የህትመት ሚዲያዎች እንዲሁም የህዝብ ማስታወቂያ መለጠፊያ ቦርዶችን እንደአግባብነቱ በመጠቀም ሊገለፅ ይችላል። በተመሳሳይ አንቀጽ ላይ አዋጁ የአስፈፃሚ አካላት ሕግን የማስከበር ስራ በሚሰሩበት ወቅት ችግር እንዳይፈጠር እንዲሁም የትርጉም ክፍተቶችን በመቀነስ የሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ለማስቻል በንዑስ አንቀፅ ሁለት ላይ ከመደበኛ የግብይት አሰራር ውጭ እቃ ተከማችቷል ወይም ተደብቋል የሚያስብሉ መስፈርቶችን አስቀምጧል። መጀመሪያ ላይ የሰፈረው ነጋዴውን ማህበረሰብ የተመለከተ ሲሆን አንድ ነጋዴ ግምቱ ከነጋዴው ካፒታል 25% የማያንስ እቃ ከውጭ የመጣ ሲሆን አስመጭው ራሱ ለቀጣይ የምርት ሂደት በጥሬ እቃነት ወይም በግብይት የሚጠቀምበት ካልሆነ በስተቀር የጉምሩክ ፎርማሊቲ ከተጠናቀቀለት በኋላ በሶስት ወራት ውስጥ፤ በሀገር ውስጥ የተመረተ የንግድ እቃ ሲሆን በተመሳሳይ አምራቹ ለእራሱ የምርት ግብዐት ካልተጠቀመበት በሁለት ወራት ውስጥ ወይም በጅምላ ሻጭ እና በችርቻሮ ሻጭ የተገዛ እቃ ሲሆን ከተገዛበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ውስጥ ለሽያጭ ካልቀረበ ነጋዴው እጥረት ያለበትን እቃ የማከማቸት እና የመደበቅ ክልከላን እንደጣሰ ይቆጠራል። እነዚህ መስፈርቶች ባይሟሉም እንኳ በማንኛቸውም መጓጓዣ ከተፈቀደው የስርጭት መስመር ውጭ ሲጓጓዝ የተገኘ እቃ እንደ ተከማቸ እና አንደተደበቀ ይቆጠራል። ይህ ድንጋጌ ለነጋዴው ማህበረሰብ ብቻ ሳይሆን ከንግድ ውጭ ላሉ ማህበረሰቦች ተፈፃሚነት አለው። እንደፃፊው አረዳድ የተፈቀደ የጉዞ መስመር የሚለውን ሀረግ የሚያመላክተው የጉምሩክ መመሪያን መሰረት የአደረገ እንቅስቃሴን አለመከተል ወይም የእቃ እጥረት ማጋጠሚን ተከትሎ በመንግስት የሚወጡ የጉዞ መስመር መመሪያዎችን የተመለከተ ሊሆን ይችላል። ከነጋዴ ማህበረሰቦች ውጭ ያሉትን ግለሰቦች በተመለከተ ተቀባይነት ያለውን የግል ወይም የቤተሰብ ፍጆታ ሁኔታዎችን ታሳቢ አድርጎ እንዲወስን ለንግድ ሚኒስትር በአዋጁ ስልጣን ተሰጦታል። የማከማቸት እንዲሁም የመደበቅ ተግባራት ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦችን በተመለከተ የአዋጁ አንቀፅ 43 ንዑስ አንቀፅ 4 እና 5 ላይ የተቀመጡ ድንጋጋጌዎች የተከማቸውን እቃ እንዲሁም ማጎጓዣን መውረስን ጨምሮ እስከ አምስት አመት የሚደርስ ፅኑ እስራትን እና የገንዘብ ቅጣቶችን አስቀምጠዋል። የንግድ ውድድር እና ሸማቾች ባለስልጣን በአንቀፅ 36 ንዑስ አንቀፅ 1(ለ) መሰረት በአዲስአበባ እና በድሬደዋ ከተማ የሚፈጠሩ እቃ የማከማቸት ወይም የመደበቅ ወንጀሎችን የመመርመር እና ክስ የማቅረብ ስልጣን የተሰጠው ሲሆን በክልልሎች የሚፈጠሩ ችግሮችን በተመለከተ በአንቀፅ 23(5) መሰረት ለክልል የንግድ ቢሮዎች ስልጣን ተሰጠዋል። ከዚህ በተጨማሪም በአንቀፅ 23(5) መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃዎችን በተመለከተ ለባለስልጣኑ አዋጁ በግልፅ ስልጣን ስላልሰጠው የእቃ ማከማቸት እና መደበቅን በተመለከተ የሚያስፈልጉ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን የመውሰድ ስልጣንም በንግድ ሚኒስተር እና ቢሮዎች ስር የሚወድቅ ይሆናል። ይህ የንግድ እቃን ማከማቸት እና መደበቅን የተመለከተ ድንጋጌ በተወሰነ ጊዜ ወይም ሁኔታ የተገደበ ሳይሆን በማንኛውም ጊዜ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስተር የእቃ እጥረት መከሰቱን ሲረዳ ሊከተለው እና ሊያስፈፅመው የሚገባ ድንጋጌ ነው። በማንኛውም ጊዜ አስፈላጊ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ሀገር ለከባድ የተፈጥሮ ወይም ሰው ሰራሽ አደጋ(በሽታ ወረርሽኝን ጨምሮ) ስትጋለጥ አስፈላጊነቱ ከምንም በላይ ይሆናል። በዚህ ወቅትም ዓለም በኮረና ወረርሽኝ አደጋ በተጨነቀችበት ወቅት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለማቃለል iA´Xu} ከምንጠቀምባቸው ህጎች መካከል የንግድ ውድድር እና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ላይ የተቀመጠው ይህ የንግድ እቃወችን ማከማቸት እና መደበቅን መቆጣጠሪያ ድንጋጌ አንዱ እና ዋነኛው ነው። ይህንንም ለማድረግ የወረርሽኙን መከሰት ተከትሎ እጥረት የተከሰተባቸውን የእቃ አይነቶች የንግድ ሚኒስትር በተከታታይ ይፋ ሊያደርግ እና የተቀመጡ ሂደቶችን ተከትሎ ሊቆጣጠር ይገባል። ሌሎች በአዋጁ ሀላፊነት የተሰጣቸው የክልል እና የፌደራል መስሪያቤቶችም ሀላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል። አሁን ከተከሰተው የኮረና ወረርሽ አደጋ አንፃር የአዋጁን ድንጋጌዎች ከአየናቸው ግን አንዳንድ ክፍተቶችን መገንዘብ እንችላለን። በአዋጁ አንቀፅ 24 ላይ እንደተመለከተው ከተፈቀደ መስመር ውጭ ሲጓጓዙ የተያዙ እና በግለሰቦች እጅ የተከማቹ እቃዎች ውጭ ያሉ ሁሉም የማከማቸት እና የመደበቅ ድርጊቶች በየደረጃው ከአንድ ወር እስከ ሶስት ወር የሚደርስ የእፎይታ ጊዜን ተሰጦአቸዋል። ከዚህ በተጨማሪ የንግድ እቃዎችን በተመለከተ አንድ ነጋዴ እስከ 25% ካፒታሉ ድረስ የማከማቸት ስልጣን መሰጠቱን ከወቅቱ የኮረና ወረርሽኝ አጣዳፊነት አንፃር ስንመለከተው አዋጁ ታሳቢ ያደረገው በመደበኛ ጊዜ የሚፈጠር እጥረትን ብቻ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል። እስከ 3 ወር የሚደርስ እፎይታን እና አስከ 25% ካፒታሉ የሚደርስ እቃን የማከማቸት መብት ለነጋዴው የምንሰጥ ከሆነ እቃው በተሎ ለገቢያ መድረስ እየቻለ የህጉን ክፍተት ተጠቅሞ እንዲያከማች ለነጋዴው እድል እየሰጠነው እና በመካከል ብዙ የሰብዓዊ ኪሳራ እንዲያጋጥም እያደረግን ነው። ስለዚህ ይህ ክፍተት ወቅቱን ታሳቢ አድርጎ የሚሞላበትን አቅጣጫ መጠቆም አስፈላጊ ይሆናል። በፀሃፊው አረዳድ ይህን ክፍተት መሙላት የሚቻለው በህገመንግስቱ መንግስት መደበኛውን የሕግ አሰራር ወደ ጎን በመተው ነገሮችን እንዲያስተካክል የሚፈቅድለትን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የማወጅ ስልጣን መጠቀም ነው። በኢፌዴሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 93(4) መሰረት በሀገር ደረጃ ወይም በክልልሎች የወረርሽኝ በሽታ በሚከሰትበት ወቅት የፌደራል መንግስት ወይም የክልል መንግስታት እንደተዋረዱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማውጣት በመደበኛ የሕግ ስርዐቱ ማስፈፀም ያልቻሉአቸውን ጉዳዮች እንዲያስፈፅሙ እና ዜጎችን ከመጣው ወረርሽኝ እንዲከላከሉ ስልጣን ሰጧቸውአል። ይህንንም ተከትሎ የኮረና ቫይረስ ወርሽኝ የሚያመጣቸውን ችግሮች ከመደበኛው የሕግ ሥርዓት በተለየ መልኩ ተንቀሳቅሶ በሚገባ ለመመከት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 3/2012ን አወጥቷል። ከላይ እንደገለፅኩት በትክክለኛው የሕግ አሰራር የኮረና ወረርሽኝን ተከትሎ መንግስት ሊያስፈፅማቸው ከማይችላቸው ነገሮች መካከል እስከ 25% ካፒታላቸው ያከማቹ ነጋዴዎችን ምርታቸውን ወደ ገቢያ እንዲያወጡ ማድረግ እና ከአንድ ወር እስከ ሶስት ወር የሚደርሱ በየደረጃው የተሰጡ የእፎይታ ጊዜዎችን በመጣስ ነጋዴዎች ያላቸውን ምርት ለገቢያ እንዲያቀርቡ ማስገደድ ይገኙበታል። እነዚህ ደግሞ በአንፃሩ የነጋዴውን ማህበረሰብ የማከማቸት እና የመደበቅ ተግባር የሚያግዙ እና የመንግስትን ወረርሽኙን የመመከት እንቅስቃሴ የሚጎዱ የሕግ ክፍተቶች ናቸው። ስለሆነም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ክልከላዎችን እንዲያስፈፅም ስልጣን የተሰጠው የሚኒስትሮ

የንግድ እቃን ማከማቸት፣ መደበቅ፣ ዋጋ ጨምሮ መሸጥ እና የኮረና ወረርሽኝ ከኢትዮጵያ ሕግ አንፃር ======================= መግቢያ በአገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ ሲከሰት የሰዎች ህይወትን ከመቅሰፉ በተጨማሪ የንግድ እንቅስቃሴዎችንም አደጋ ላይ ይጥላል። ንግድ የተሳለጠ እና ለሁሉ ተደራሽ የሚሆነው የተረጋጋ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ሲኖር ብቻ ነው። በንግድ ዓለም ውስጥ የነጋዴዎች ዋነኛ ግብ ተደርጎ የሚወሰደው በአጭር ጊዜ ወይም በረጅም ጊዜ ውስጥ ትርፋማ መሆን ነው። ነገር ግን ይህ ትርፋመነታቸውን የሚያሳኩት ሕግ እና ሥርዓትን በአከበረ መንገድ በሚደረግ እንቅስቃሴ ሊሆን ይገባል። ከሕግ እና ሥርዓት ውጭ ትርፍ ለማጋበስ የሚንቀሳቀስ ነጋዴ የተመሰረተበት አላማ ማትረፍ ስለሆነ በሚል ተልካሻ ምክንያት ዝም ተብሎ ሊታለፍ አይገባም። ይህንም መሰረት ለማስያዝ ሕግ እና ሥርዓት አስፈፃሚ አካላት ትልቅ ድርሻ አላቸው። ትርፍ ለማግኘት ከሚደረጉ ጥረቶች ጎን ለጎን ማህበራዊ ሀላፊነትን መወጣትንም መዘንጋት አይገባም። የነጋዴዎች ትርፍን ለማሳደግ የሚያርጉት እሩጫ ሕግ እና ሥርዓትን ለማስከበር ከተቋቋመ አካል ጋር በጥብቅ ከሚካረሩባቸው ወቅቶች አንዱ ወረርሺኝ የሚከሰትበት ወቅት ነው። ወረርሽኝ በሚከሰትበት ወቅት ሁሉም ከወረርሽኙ ለመዳን በሚያደርገው እሩጫ ወቅቱ የሚፈልጋቸው እቃዎች እና አገልግሎቶች እጥረት ሊከሰት ይችላል። በዚህ ጊዜ ማህበራዊ ሀላፊነትታቸውን ለመወጣት ደፋ ቀና የሚሉ ነጋዴዎች የሚኖሩትን ያክል አጋጣሚውን ተጠቅመው ሀብት ለማካበት እና ከችግር ለማትረፍ የሚሯሯጡም አሉ። እነዚህ ከችግር ለማትረፍ የሚሯሯጡ ነጋዴዎች ከሚተገብሯቸው ነገሮች መካከል እጥረት ያለበትን እቃ ማከማቸት እና በተፈላጊ እቃዎች ላይ አለአግባብ ዋጋ መጨመር ይገኙበታል። እነዚህ ተግባራት በሸማቹ ማህበረሰብ ላይ ከቀላል እስከ ከባድ አደጋዎችን ሊያስከትሉ ይችላሉ። ይህንንም ታሳቢ በማድረግ ሀገራት የሸመቾች ጥበቃ ሕግን በማውጣት ሸማቹን ማህበረሰብ ከእንደዚህ አይነት ችግር ለመጠበቅ ጥረት ሲያደርጉ ይስተዋላል። ሀገራችን ኢትዮጵያም ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ለሸማቾች መብት ጥበቃ ልዩ ትኩረትን የሰጠች ሲሆን በመካከልም ሁለት ህጎችን አርቅቃለች። አሁን ላይ በስራ ላይ ያለው የንግድ ውድድር እና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006 ትኩረት ከሰጣቸው ነገሮች መካከል እጥረት ያለባቸውን እቃዎች ማከማቸት እና ተፈላጊ እቃዎችን ወይም አገልግሎቶችን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች ይገኙበታል። በሀገራችን ዓለም አቀፍ የሆነው የኮረና ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ ከወረርሽኙ እኩል በሚባል ደረጃ የመገናኛ ብዙሀንን ትኩረት የሳበው ጉዳይ የነጋዴዎች እጥረት ያለባቸውን እቃዎች ማከማቸት ተግባር እና የተፈላጊ እቃዎችን ዋጋ ጨምሮ መሸጥ ይገኙበታል። የዚች አጭር ፅሁፍ አላማም እነዚህን የነጋዴው ማህበረሰብ ተግባራት ከኢትዮጵያ የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ አንፃር መተንተን እና መወሰድ ያለባቸውን ተግባራት መጠቆም ነው። የኮረና ወረርሽኝ እና እጥረት የተከሰተባቸው እቃዎች የኮረና ወረርሽኝን ለመከላከል ከሚደረጉ ጥረቶች መካከል የህክምና መሳሪያዎች አቅርቦት የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል። የዓለም ጤና ድርጅት በሰጠው መመሪያ መሰረት ሀገራት ሊከተሏቸው ከሚገቡ የመከላከያ መንገዶች አካላዊ እርቀት፣ ማስክ መጠቀም ፣አለመጨባበጥ እና እጅን በተደጋጋሚ መታጠብ ዋነኞቹ ናቸው። ከእነዚህም ውስጥ ማስክ መጠቀም የማስክ አቅርቦትን እንዲሁም እጅን በተደጋጋሚ መታጠብ ደግሞ የሳሙና እና የሳኒታይዘር አቅርቦትን ይጠይቃሉ። በአሁኑ ሰዓት በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ እነዚህ በሽታውን ለመከላከል የሚረዱ እቃዎች እጥረት የመንግስታት እና የህዝብ ጭንቀት ከሆኑ ውሎ አድሯል። ከዚህ በተጨማሪ እነዚህን እጥረት ያለባቸውን ቁሳቁስ በአገኙት አጋጣሚ የሚሰበስቡ እና በውድ ለመሸጥ የሚያከማቹ ነጋዴዎች እንዲሁም ከእራሳቸው እና ከቤተሰባቸው ፍጆታ በላይ የሚገዙ ግለሰቦች መበራከት ሌላ ትልቅ የእራስ ምታት ሆኗል። ከህክምና ቁሳቁሶች በተጨመሪ ለእለት ፍጆታ የሚውሉ እቃዎችም ለዚሁ ችግር ሰለባ ሆነዋል። መንግስት የሚያወጣውን መመሪያ ተከትሎ ዜጎች እቤት ውስጥ ለመቀመጥ ከሚገዙት ከመጠን ያለፈ የምግብ እቃዎች በተጨማሪ ወደፊት የዋጋ ጭማሪ ሊከሰት እንደሚችል በመተንበይ ዜጎች ሊገዙ የሚፈልጉአቸውን እቃዎች አከማችቶ የለም iማለት ወይም አላግባብ ዋጋ በመጨመር የሸማቹን የመግዛት አቅም የመቀነስ ተግባር በነጋዴው ማህበረሰብ ዘንድ ይስተዋላል። እነዚህ ተግባራት በወቅቱ ተገቢ የሆነ ህጋዊ እርምጃ ካልተወሰደባቸው በጊዜ ሂደት የሚያስከትሉት አደጋ በጣም ከባድ ይሆናል። የህክምና ቁሳቁሶች ላይም ሆነ የእለት ፍጆታ እቃዎች ላይ የሚደረገው የማከማት እና ሰው ሰራሽ የእቃ እጥረት ችግር ሸማቹን ማህብረሰብ ለርሀብ ብሎም ለሞት የሚዳርግ ችግር ውስጥ ሊከተው ይችላል። ወረርሽኙን ለመከላከል የሚረዱ እቃዎች በአግባቡ እንዲሰራጩ ከአልተደረገ ከእለት ወደ እለት ወረርሽኙ እየተስፋፋ ከሚያስከትለው ሰብዓዊ ኪሳራ በተጨማሪ የእለት ከእለት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን በመገደብ ሀገርን ከባድ የማትወጣው አዘቅት ውስጥ ሊከት ይችላል። የእለት ፍጆታ አቅርቦቶችን መገደብም በእራሱ ዜጎችን ለርሀበ እና ሲቃይ በመዳረግ ወረርሽኙ ሊያስከትል ከሚችለው አደጋ የበለጠ ችግር ሊያመጣ ይችላል። እነዚህን ከባድ ችግሮች መቋቋም የሚቻለው ሕግን መሰረት አድርጎ በእንደዚህ አይነት ተግባራት ላይ የተሰማሩ አካላትን ማስተካከል እና አስፈላጊ እርምጃዎች ሲወሰዱ ብቻ ነው። የንግድ እቃን ማከማቸት እና ሰው ሰራሽ እጥረት መፍጠር በኢትዮጵያ ሕግ እቃን ማከማቸት እና ሰው ሰራሽ እጥረት መፍጠር የገቢያ አለመረጋጋት እና የዋጋ ንረትን ከሚያስከትሉ ተግባራት መካከል የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል። በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች የእቃውን በገቢያ ላይ ያለውን ተፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የአቅርቦት ችግር በሌለበት ሁኔታ የአቅርቦት ችግር ያለ በማስመሰል በግለሰብ ወይም በቡድን ደረጃ ሊያከማቹ እና ሰው ሰራሽ እጥረት ፈጥረው በትልቅ ዋጋ የመሸጥ ተግባር ሊፈፅሙ ይችላሉ። ነጋዴዎች እቃውን አከማችተው የሚያስቀጡበት ዋነኛ አላማቸው ጊዜውን ጠብቆ ከተገቢው በላይ ትርፍን ለማጋበስ ነው። ከነጋዴው ማህበረሰብ በተጨማሪ የሸማቹ ማህበረሰብም በእንደዚህ አይነት ተግባራት ተሰማርቶ ሊገኝ ይችላል። የሸማቹ ማህበረሰብ በዋነኝነት እንደዚህ አይነት ተግባር ውስጥ የሚሰማራው እቃው ከገቢያ ላይ ይጠፋል የሚል ፍራቻ ሲያድርበት ነው። ይህ የንግዱ ማህበረሰብም ሆነ የሸማቹ የማከማቸት ተግባር በዜጎች ላይ ወይም እንደ አጠቃላይ በሀገር ላይ የሚያደርሰው ኪሳራ በጣም ከባድ የሆነ ነው። ይህንም ተግባር ለመከላከል ይረዳ ዘንድ የኢትዮጵያ ንግድ ውድድር እና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006 እቃን ስለማከማቸት እና ሰው ሰራሽ እጥረት መፍጠርን አስመልክቶ ድንጋጌዎችን የአካተተ ሲሆን የማስፈፀም ሀላፊነቱንም ለንግድ ሚኒስትር፤ ለንግድ ዉድድር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን እና ለንግድ ቢሮዎች ሰጥቷል። በአዋጁ አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት አንድ ነጋዴ ከመደበኛ የግብይት ስርዐት ውጭ ወይም ነጋዴ ያልሆነ ሰው ለግል ወይም ለቤተሰብ ፍጆታ ከሚውል መጠን በላይ በንግድ እና ኢንደስትሪ ሚኒስተር በገቢያ ላይ እጥረት ያለበት መሆኑ በሚኒስተሩ በወጣ የህዝብ ማስታወቂያ የተገለፀ የንግድ እቃን ማከማቸት ወይም መደበ

ባለሀብትነት ስለሚተላለፍበት መንገድ ========================== ሀብትን በእጁ ያደረገ ማንኛውም ባለሀብት ንብረቱን የመያዝ እና የመገልገል መብት እንዳለው ሁሉ ንብረቱን ለሌላ ሰው እንዳያስተላልፍ ከልካይ ሊኖረው አይችልም፡፡ንብረትን ለማስተላለፍ የምንጠቀምባቸው መንገዶች እንደ ንብረቱ ባህሪ የሚለያይ ሲሆን የሚንቀሳቀሱ እና የማይንቀሰዋቀሱ ንብረቶች የሚተላለፉበት መንገድ አንድ አይነት አይደለም፡፡የሚንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ ግዙፋዊነት ያላቸውን ተንቀሳቃሽ ነገረሮች(corporeal things or chattels) ባለሀብቱ ሀብቱን ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ በማሰብ ንብረቱን በሽያጭ ወይም በስጦታም ሆነ በውርስ ያስረከበ ወይም በሚተላለፍለት ሰው እጅ ካደረገ ንብረቱ እንደተላለፈ ይቆጠራል፡፡ ይህ አይነቱ የንብረት ማስተላለፍያ መንገድ ልዩ ተንቀሳቃሽ ለሆኑ እንደ መኪና ላሉ ንብረቶች የሚያገለግል አይደለም፡፡ በሌላ በኩል የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች የሚተላለፉት ባለሀብቱ ንብረቱን የሚመለከቱ ሰነዶችን/የባለቤትንት ማረጋገጫ ም/ወረቀቶችን/ ለሌላ ሰው አሳልፎ በመስጠት ነው፡፡በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረቶችን ክፍያ በመፈጸም ግዢ በመፈጸሙ ብቻ ንብረቱ ተላልፎልኛለው ሊባል አይችልም፡፡ በመሆኑም ንብረቱ በገዢው እጅ ቢገባም ባይገባም በገቡት ውል አማካኝነት ውልን ለማዋዋል እና ለመመዝገብ ስልጣን ባለው የመንግስት አካል ዘንድ በመቅረብ ከተዋዋሉ እና ይህው ባለስልጣን ንብረት ከነባሩ ባለሀብት ወደ አዲሱ ባለሀብት የተሸጋገረ መሆኑን የሚያረጋግጥ ም/ወረቀት ይሰጠዋል፡፡ሰነዱ እጁ እንደገባም ንብረቱ የተላለፈለት ሰው ከንብረቱ ጋር ተያይዘው የሚገኙ መብት እና ግዴታዎች አብረው የሚተላለፉለት /የሚተላለፉበት ይሆናል፡፡ በዚህ ምክንያት ንብረቱን ያስተላለፈው የቀድሞ ባለሀብት መብቱን የሚያጣ ሲሆን ከንብረቱ ጋር ተያይዞ የሚገኙ ንብረትን የመያዝ(ይዞታ ስር ማድረግ) እና ፍሬን የመሰብሰብ እና የመጠቀም መብት አይኖረውም፡፡በተቃራኒው መብቶቹ ወደ አዲሱ ባለሀብት የሚተላለፉ ይሆናሉ፡፡ https://t.me/Consultancy2012

የባለይዞታነት እና ባለሀብትነት መብት ማስከበርያ መንገዶች =================== በህግ እውቅና የተሰጣቸው ሁለት መብት ማስከበርያ መንገዶች አሉ የመጀመርያው ከፍርድ በፊት የሚደረግ ሀይልን ተጠቅሞ ንብረትን ማስመለስ እና ሌላኛው ደግሞ በፍ/ቤቶች ውሳኔ መሰረት መብትን ማስከበር ናቸው፡፡በመሰረቱ ከላይ እንደጠቀስነው ማናኛውም ዜጋ በንብረት መብቱ ላይ ከሚፈጸም የመብት ጥሰት በህግ ጥበቃ ይደረግለታል፡፡ የመጀመርያው መንገድ ለራሱም ሆነ ለሌላ ሰው ሲል በያዘው ንብረት መብት ላይ ጥሰት ወይም ሁከት የተነሳበትን ማንኛውም ሰው ሀይል በመጠቀም ንብረቱን ከማንኛውም ጣልቃ ገብነት መከላከል ወይም ማስመለስ ይችላል፡፡ይህን ለማድረግ ባለንብረቱ የፍ/ቤት ውሳኔ ሳይጠብቅ በራሱ መብቱን የሚያስከብርበት መንገድ ነው(extra judicial remedy) ::ይህንን መፍትሄ በፍ/ብሄር ህጉ አንቀጽ 1148(1)ስር እናገኘዋለን፡፡ከዚህ ድንጋጌ የምንረዳው ሁለት ባህርያት ያሉት ሀይል አጠቃቀሞች ናቸው፡፡ የመጀመርያው ንብረቱን ለመንጠቅ ወይም ለመውሰድ የመጣውን ሰው ንብረቱን እንዳይወስድ በሀይል መከላከል እና ሌላኛው ደግሞ ንብረቱ በተወሰደ ጊዜ ባለመብቱ ባለመመልከቱ ወይም በስውር የተከናወነ ከሆነ እየሸሸ ያለውን ወሳጅ ወይም ነጣቂ ወድያውኑ ተከታትሎ በሀይል ማስመለስ ናቸው፡፡(የፍ/ህግ አንቀጽ 1148(2)) ከዚህ ድንጋጌ አላማ አንጻር ሀይልን መጠቀም የሚቻለው ንብረቱ እየተወሰደ ባለበት ወይም ከተወሰደ በኋላ ባለ ቅጽበት ወይም ድርጊቱ ሳይቋረጥ መሆን ይገባዋል፡፡ምክንያቱም ህጉ ወድያውኑ በሚል የገለጸው በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ትኩረት ሊደረግበት የሚገባው ጉዳይ የሀይል አጠቃቀም ልክ ነው፡፡በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው የሚጠቀመው ሀይል ድርጊቱን ለማቋራጥ ወይም ውጤቱን ለማስቀረት በሚያስችል ብቻ መሆን አለበት፡፡በመሆኑም የሚጠቀመው ሀይል ግለሰቡ ከሚጠቀመው ሀይል ጋር ወይም አደገኝነቱ ጋር ተመጣጣኝ መሆን ይገባዋል፡፡በዚህ ረገድ የወንጀል ህጋችን በአንቀጽ 78 ስር ህገ ወጥ ከሆነ ጥቃት…ሌላ መንገድ ሳይኖር ከሁኔታው መጠን ባለማለፍ የተፈጸመ ድርጊት የወንጀል ተጠያቂነትን የማያሥከትል መሆኑን ሲያስቀምጥ የዚሁ ድንጋጌ የእንግሊዝኛ ቅጂ …if the deffence was proportional to the needs of the case’ ሲል ያስቀምጣል፡፡ ይሁንና ይህንን ወሰን በማለፍ ከድርጊቱ ጋር የማይመጣጠን ሀይልን የተጠቀሙ ባለይዞታዎች ወይም ባለሀብቶች ከወንጀል ተጠያቂነት የማያመልጡ መሆኑን መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ ነገር ግን ድርጊቱን ለመፈጸም ያነሳሳው ምክንያት ምክንያት በቅጣት ማቅለያነት ሊይዝለት ይችላል፡፡ይህንኑ ለማጠናከር በፍ/ብሄር ህጉ አንቀጽ 1148(3) ባለመብቱ በወቅቱ አስገዳጅ ሁኔታ ካላገጠመው በስተቀርየእጅ እልፊት ከመፈጸም መቆጠብ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ንብረቱን የወሰደው ሰው ንብረቱን በፍቃዱ ለመመልስ ፍቃደኛ ከሆነ ሀይልን መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ከላይ የተጠቀሰው መፍትሄ ከፍ/ቤት ውሳኔ ውጪ ተግባር ላይ የሚውል የባለይዞታነት መብት ማስከበርያ ነው፡፡ ይሁንና ባለይዞታው በመብቱ ላይ የተቃጣውን ገደብ ወይም ጣልቃ ገብነት ወይም የጠነሳበትን ሁከት ወድያውኑ ማስወገድ የማይችል ከሆነና በዚህ ምክንያት ሀይልን ተጠቅም ንብረቱን ማስመለስ የማይችል በሚሆንበት ጊዜ ሊጠቀም የሚገባው ሌላኛው መፍትሄ የፍ/ቤት ውሳኔ ነው፡፡በመሆኑም የፍ/ብሄር ህጉ አንቀጽ 1149 በሚያስቀምጠው መንገድ የንብረት መብቱ የተጣሰበት ሰው ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ላለው ፍ/ቤት ክስ በማቅረብ መብቱን ማስከበር እና የተነጠቀው ንብረት እንዲመለስለት የተፈጠረበት ሁከት እንዲወገድለት ማድረግ ይችላል፡፡ለምሳሌ በተፈጸመበት የስርቆት ወንጀል ምክንያት ከእጁ የወጣውን ንብረት የወሰደውን ሰው ወይም ከወሳጁ ላይ በሽያጭም ሆነ በሌላ ማንኛውም መንገድ በመቀበል በእጁ ካደረገው ሰው ላይ ከሶ መቀበል የሚችል ይሆናል፡፡ ይህንን መብት ከማስከበር አንጻር የወንጀል ህጉ በአንቀጽ 665 እና 682 ስር በስርቆት እና መሸሸግ ወንጀል የሚጠየቁ መሆኑን የደነገገው፡፡ ይሁንና ይዞታዬን ወይም ሀብቴን ተነጥቄያለው የሚለው ሰው የንብረት ይመለስልኝ ጥያቄውን ማቅረብ የሚችለው ንብረቱ ከተወሰደበት ወይም ሁከቱ ከተነሳበት እለት አንስቶ በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ከዚህ ጊዜ በኋላ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል፡፡ በመሆኑም ይህ የይርጋ ጊዜ ከማለፉ በፊት ክስ ከቀረበ ተከሳሽ ንብረቱ የሚገባው ስለመሆኑ በበቂ ማስረዳት ካልቻለ ለባለመብቱ እንዲሰጠው ይወሰንለታል፡፡

የተፋጠነ የፍርድ ሥነሥርዓት እና አጭር ሥነ ሥርዓት ልዩነታቸው ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣ የተፋጠነ የፍርድ ሥነሥርዓት ከሳሽ በመደበኛው የሙግት አመራር የማይመራ ክስን በመመስረት ጉዳዩ በፍጥነት ታይቶ እንዲወሰን ለማድረግ የሚችልበት ሥነ ሥርዓት ሲሆን በውስጡም በአጭር ሥነ ሥርዓት የሚወሰኑ ጉዳዮችን አጠቃሎ የያዘ ነው። አጭር ሥነ ሥርዓት ማለት ከሳሽ የተሟላ የክስ ሂደትን ማለፍ ሳያስፈልገው ውሳኔ የሚያገኝበት ሥነሥርዓት ነው። የተፋጠነ ሥነሥርዓት ማለት ደግሞ ከጉዳዩ አይነት የተነሳ ክሱ በፍጥነትና የተሟላ የክስ ሂደትን ሳያልፍ የሚወሰንበት ሥነሥርዓት ነው። በመሆኑም አጭር እና የተፋጠነ ሥነሥርዓት የተለያዩና ተፈፃሚነታቸውም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሲሆን በሁለቱም ጊዜ ግን ጉዳዩ የሚታየው መደበኛውን የክስ ሥነሥርዓትን ባለመጠበቅ ወዲያውኑ በመሆኑ ተመሳሳይነትም አላቸው። @Consultancy2012

ወለድ የሚታሰበው ክስ ለአንድ ፍርድ ቤት ከቀረበበት ቀን ጀምሮና ይኸውም ባለእዳው የአንድ ዓመት ሙሉ ሒሳብ ያለበት እንደሆነ ነው፡፡” ከዚህ የህግ ድንጋጌ የምንረዳው በወለድ ላይ ወለድ በመርህ ደረጃ የሌለ መሆኑን ነው፡፡ ነገር ግን ከላይ በድንጋጌው ውስጥ የተጠቀሱት ሁኔታዎች ሲሟሉ የወለድ ወለድ ሊኖር የሚችልበትን ሁኔታ ያስረዳል፡፡ እነዚህም ሁኔታዎች፡- ሀ) ባለእዳው በየጊዜው የሚከፍለው ገንዘብ እና ለባለገንዘቡ እንደገቢ (በተወሰነ ጊዜ የሚገኝ እንጂ የተከማቸ እዳን አያመለክትም) የሚያገለግል ሲሆን፤ ለ) እዳውን ለማስከፈል በፍ/ቤት በባለገንዘቡ ክስ ሲመሰረት፤ እና ሐ) ባለእዳው ለአንድ ዓመት ክፍያውን ሳይከፍል የቀረ እንደሆነ ወይም ባለገንዘቡ ባለእዳውን የሚጠይቀው የአንድ ዓመት ክፍያን ሲሆን ነው፡፡ በመሆኑም ህጉ የወለድ ወለድን በሁኔታ ላይ ብቻ ተመስርቶ እንዲኖር የፈቀደበት ሀተታ ዘምክንያት አንደኛው ባለገንዘቡ ገንዘቡን ለመቀበል በጣም የሚቸኩልበት ሁኔታ ላይ አይደለም ተብሎ ግምት ስለሚወሰድ ነው ምክንያቱም በየጊዜው የሚከፈል ገንዘብ በመሆኑ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት የወለድ ወለድ በመርህ ደረጃ ቢፈቀድ ባለእዳው በወለድ ወለዱ መጠራቀም ወይም መከማቸት እዳው በዝቶ ባለእዳውን አደጋ ውስጥ ላለመክተት በማሰብ ነው፡፡ ይህ የህጉ ግምትና ድንጋጌ ባለገንዘቡ ያለውን መብት እና ባለዕዳው ያለበትን ግዴታ በተነፃፃሪ ሁኔታ ባለዕዳው የአንድ ዓመት እዳ ካለበትና ይህንኑ ጥያቄ በፍ/ቤት ክስ ተመስርቶ በባለገንዘቡ ከተጠየቀ ባለገንዘቡ ባለዕዳው ላይ ካለው ያልተከፈለ እዳ እና ወለድ በተጨማሪ የወለድ ወለድ እንዲከፈለው የመጠየቅ መብት እንዳለው መደንገጉ ትክክለኛና አግባብ (Fair) ከሚባል በስተቀር የሚነቀፍ አይደለም፡፡ በወለድ ወለድ ላይ ሌላ ወለድ ማሰብ ፈፅሞ በህጋችን ቦታ የተሰጠው ጉዳይም አይደለም፡፡ መቋጫ ሌላኛውና የመጨረሻው ጉዳይ በብድር ለተሰጠ ወለድ የመጠየቂያ ጊዜ ምን ያህል ነው የሚለውን ተመልክተን ይህን ፅሁፍ እናበቃለን፡፡ በዚህም መሰረት የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 2024 እንደሚከተለው ይነበባል፡፡ ቁ. 2024. በሁለት ዓመት የተወሰነ ጊዜ እዳው እንዲከፈል መጠየቅ ከሚገባበት ቀን ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ሳይከፈል የቀረ ገንዘብ እንደተከፈለ የሚቆጠረው፤ (ረ) በብድር የተሰጠ የገንዘብ ወለድና በጠቅላላውም የዓመት ጊዜ ተወስኖለት በየዓመቱ ወይም ከዚህ ባነሰ የጊዜ ውሳኔ ውስጥ ሊከፈል የሚገባው ዕዳ የሆነ እንደሆነ ነው፡፡ በድንጋጌው ፊደል (ረ) ስር የተመለከተው ሲታይ በብድር የተሠጠ ወይም በማናቸውም የአከፋፈል ሁኔታ በየአመቱ ወይም ከአመት ባነሰ ጊዜ እየተከፈለ እንዲያልቅ ጊዜ ተቆርጦለት የተሰጠ ገንዘብ ላይ የሚታሰብ ወለድ እዳው ከበሰለበት ወይም በየተወሰነ ጊዜ የሚከፈል ገንዘብ ከሆነ ደግሞ ገንዘቡ ተከፍሎ ማለቅ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ ሁለት ዓመት ያለፈ እንደሆነ በእነዚህ ክፍያዎች (እዳዎች) ላይ ሊጠየቅ የሚችለው የወለድ ክፍያ እንደተከፈለ የህግ ግምት የሚወሰድ መሆኑን ያሳያል፡፡ በመሆኑም ይህ ድንጋጌ አስገዳጅ የሆነ የሕግ ግምት ያለው ሲሆን በተጨማሪ ደግሞ ማናቸውም የተፈጥሮም ሆነ የሕግ ሰው (ባንክና ሌሎች አበዳሪ ተቋማት) የገንዘብ ብድር ካበደረ በኋላ ብድሩ ተከፍሎ የሚያልቅበትን የጊዜ ገደብ ካበቃ ከሁለት ዓመት በኋላ የብድሩ የወለድ ይከፈለኝ ጥያቄ በሕግ እንደተከፈለ የሚገመት መሆኑን የሚደነግግ ድንጋጌ በመሆኑ ተበዳሪው ወለዱን የመክፈል ግዴታው በህግ ቀሪ ስለሚሆንለት አበዳሪውን በእጅጉ የሚጎዳ ጉዳይ በመሆኑ በጥንቃቄ ሊታይ ይገባል የሚል እምነት አለኝ፡፡ WRITTEN BY አብዱሰላም ሳዲቅ ሙክታር

ነገሮች (Elements) መሟላታቸውን ማረጋገጥ እንደተጠበቀ ሆኖ ማለት ነው፡፡ ከላይ እንደተመለከትነው ህጉ የፈቀደው የብድር ውል ወለድ መጠን በዓመት 12% ድረስ ብቻ ነው፡፡ ባንኮች ለደንበኞቻቸው የሚያበድሩትን ከፍተኛ መጠን ያለውን የወለድ መጠን አያካትትም፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በየካቲት 11 ቀን 2005 ዓ.ም በሰ.መ.ቁ 80119 በሰጠው ገዢ የህግ ትርጉምና ውሳኔ በቅፅ 15 እንደታተመው በወር 10% ወለድ ታስቦ እንዲከፈል በመስማማት ገንዘብ ማበደር በአራጣ የወንጀል ድርጊት የሚያስጠይቅ መሆኑን ትንታኔ በመስጠት ተከሳሹ በሁለት የአራጣ የወንጀል ድርጊቶች ጥፋተኛ ተብለው በሶስት አመት ፅኑ እስራትና በብር 4000.00 (አራት ሺህ) የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ በማለት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠውን ውሳኔ አፅንቶታል፡፡ በመሆኑም የብድር ውል ተዋዋዬች የወለድ መጠኑን በሚወስኑበት ሰዓት በህግ ከተፈቀደው በላይ ወለድ እንዳይዋዋሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ባንኮች ለደንበኞቻቸው የሚያበድሩበት አግባብ እንደተጠበቀ ነው፡፡ ከላይ የተመለከትነው የብድር ውል ወለድ መጠን ባንኮችን ይመለከታል ወይ? እንደሚታወቀው ባንኮች ከጥንስሳቸው ጀምሮ የደንበኞቻቸውን ተቀማጭ ገንዘብ በማስቀመጥ ደንበኞቻቸው ላስቀመጡት ገንዘብ ወለድ እንደሚሰጡ ይታወቃል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የገንዘብ ችግር ላጋጠመው ደንበኞቻቸው ወይም ኢንቨስትመንቱን ማስፋፋት ለሚፈልግ ባለሀብት ወይም ብድር ለሚፈልግ ማንኛውም ሰው ብድር በብድር ውል መያዣ በመያዝ ይሰጣሉ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ /እንደተሻሻለ/ አዋጅ ቁጥር 591/2000 አንቀፅ 5 (4) ስር እንደተመለከተው ብሔራዊ ባንኩ የገንዘብ ብድር አቅርቦት በተፈለገው መጠን መገኘትን፣ እንዲሁም የወለድ ተመንና ሌሎች ክፍያዎችን የመወሰንና የመቆጣጠር ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በዚሁ አዋጅ አንቀፅ 27 ብሔራዊ ባንኩ አዋጁንና አዋጁን ተመስርተው የሚወጡ ደንቦችን ለማስፈፀም የሚረዱ መመሪያዎችን ለማውጣት ስልጣን በአዋጁ ተሰጥቶታል፡፡ በዚህ አግባብ ብሔራዊ ባንኩ መመሪያ ቁጥር NBE/INT/11/2010 በማውጣት ንግድ ባንኮች የብድር ውል ለደንበኞቻቸው በሚሰጡበት ወቅት ላበደሩት ብድር የወለዱን ምጣኔ በራሳቸው እንዲወስኑ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል፡፡ በመሆኑም ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ የሚታሰበው የወለድ ምጣኔ ከላይ እንደተመለከተው በፍታብሄር ህጉ እንደተመለከተው የወለድ ጣራው በዓመት እስከ 12 % ብቻ ሳይሆን ከዛም በላይ ማድረግ እንደሚችሉ ነው፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ፀሀፊው በተመለከተው አንድ በሀገሪቱ ውስጥ በሚገኝ ባንክ እና በግለሰብ መካከል በተደረገ የብድር ውል ስምምነት ግለሰቡ የብር 364,000 (ሶስት መቶ ስልሳ አራት ሺ) ለመበደር ፈልጎ አበዳሪ ባንኩ በተሰጠው ብድር ላይ በዓመት አስራ ዘጠኝ ነጥብ አራት በመቶ (19.04 %) ወለድ በየእለቱ ቀሪ ገንዘብ ላይ በየቀኑ ይታሰባል፡፡ ይህ የወለድ መጠን ባንኩ በየጊዜው እያሻሻለ በሚያወጣው የወለድ ተመን (Interest Rate) የሚተካ ይሆናል በሚል ውላቸው ውስጥ አካተዋል፡፡ እዚህ ጋር መታየት ያለበት ጉዳይ ንግድ ባንኮች በህግ የሰውነት መብት የተሰጣቸውና ለትርፍ የተቋቋሙ ሆነው ሳለ ሌላኛው ተዋዋይ ወገን በመካከላቸው ያለውን ጉዳይ የመዋዋል ነፃነት ወደጎን የሚል እና ለባንኩ የመደራደር አቅሙን የሚጨምር (Bargaining power) ከመሆኑም በላይ ባንኩ በፈለገው ጊዜ (የብሔራዊ ባንክ ቁጥጥር እንደተጠበቀ ነው) የወለድ ተመኑን የማሻሻል ስልጣን ያለው መሆኑ የተበዳሪውን የገንዘብ ችግር ከግምት የማያስገባ ከመሆኑም በላይ ተበዳሪው ቅድሚያ ከተስማማበት የወለድ ምጣኔ የበለጠ እንዲከፍል “በቅድሚያ ስምምነት” ስም ብቻና የተበዳሪውን ችግር መሰረት በማድረግ ተበዳሪው ከባድ የውል ግዴታ ውስጥ የሚያስገባውን ሁኔታ ይፈጥራል፤ በህግ ፊት የተፈጥሮ ሰውና በህግ ሰውነት የተሰጣቸውን ሰዎች በአንድ አገር ህግ ውስጥ በእኩል አይን እንዳይታዩ ያደርጋል (በሌላ በኩል ውል የመዋዋል፣የመክሰስና የመከሰስ እኩል መብት እንዳላቸው ልብ ይሏል)፤ ባንኮች ላበደሩት ብድር ክፍያ በወቅቱ ተመላሽ ባይደረግላቸው በመያዣ የያዙትን የተበዳሪውን ንብረት የፍ/ቤት ሂደትን መከተል ሳያስፈልጋቸው (DUE PROCESS OF LAW) በራሳቸው ጊዜ በመሸጥ የሽያጩን ገንዘብ ለብድሩ እዳ ክፍያ የማዋልና ገዢ ካልተገኘም በፍ/ሥ/ሥ/ህጉ መሰረት ሁለት ጊዜ ጨረታ በማውጣት በመያዣ የተያዘውን ንብረት በጨረታው ላይ በወጣው መጠን የራሳቸው ንብረት ለማድረግ እንደሚችሉ ስልጣን የተሰጣቸው መሆኑን ስለ በባንክ በመያዣ ስለተያዘ የማይንቀሳቀሱና የሚንቀሳቀሱ ንብረቶች የወጣ አዋጅ ቁጥር 97/1990፣ ስለንግድ ተቋም የዋስትና መያዣ የወጣ አዋጅ ቁጥር 98/1990 እና በባንክ በመያዣ ስለተያዘ ንብረት የወጣውን አዋጅ ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ቁጥር 216/1992 “ን” ስንመለከት የግለሰቦችን ሰብዓዊና ህገ-መንግስታዊ ንብረት የማፍራት መብት “በህጋዊ” መንገድ የመንጠቅ አቅም ያላቸው በመሆኑ በህግ አውጪው አካል በጥንቃቄ ሊታዩ ይገባል፡፡ በአጠቃላይ ባንኩ ብድር በሚሰጥበት ጊዜ የሚያስከፍለው ወለድና ሌሎች ወጪዎች ተበዳሪው ከችግሩ የተነሳ ብድሩን መክፈል ሳይችል ቢቀር ከተበደረው ዋና ገንዘብ በላይ ወለዱና ሌሎች ወጪዎች እንደሚበዙ መገመት የማይከብድ ሆኖ ተበዳሪው እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ለግብር ከፋዩ ዜጋ እና ለመንግስት ሸክም ስለሚሆን ባንኮች በሚሰጡት የብድር ወለድ ምጣኔ ላይ በጥናት ላይ ተመስርቶ እንደፍታብሄር ህጉ በዓመት 12 % እንዲሆን በማድረግ በሀገሪቱ ላይ ወጥ የሆነ የብድር ወለድ ምጣኔ ህግ እንዲኖር ቢደረግ ወይም የተበዳሪዎችን አቅም ባገናዘበ መልኩ የብድር ወለዱ ምጣኔ ገደብ ቢበጅለት የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡ የወለድ ወለድ የፍታብሄር ህጉ አንቀፅ 1804 እና 2481 የወለድ ወለድን በተመለከተ ይደነግጋል፡፡ የወለድ ወለድን በሚመለከት በፍታብሄር ህጋችን ውስጥ አለ ወይስ የለም የሚለውን በተመለከተ የህግ ባለሙያዎች የተለያየ አቋም ያላቸው ሲሆን የፅሁፉ አንዱ ዓላማም ይህንን ፅሁፍ መነሻ በማድረግ ባለሙያዎችንና አንባብያንን ለውይይት መጋበዝ በመሆኑ የፀሀፊውን አቋም እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡ በብድር ውል ላይ ተዋዋይ ወገኖች ወለዱ ከዋናው ገንዘብ ጋራ ተጨማሪ ሆኖ ወለድ ይወልዳል ብለው አስቀድመው ለመዋዋል እንደማይችሉ የፍ/ህ/ቁ 2481 (1) በግልፅ ያመለክታል፡፡ በዚህ የህግ ድንጋጌ መሰረት በተሰጠው ብድርና በተስማሙት የወለድ መጠን ላይ ሁለቱ ገንዘቦች በአንድ ላይ ሁነው ሌላ ወለድ እንዲኖር መዋዋል የከለከለው አበዳሪው የተበዳሪውን የገንዘብ ችግር ምክንያት በማድረግ ያለአግባብ ሁለት ጊዜ ወለድ በማስከፈል እንዳይበለፅግ በማሰብ ሲሆን በሌላ በኩል ተበዳሪውን ሊሸከመው የማይችለው እዳ ውስጥ እንዳይገባ በማድረግ የማመዛዘን ስራ ነው ህጉ የሰራው፡፡ በዚህ የሕግ ድንጋጌ መሰረት በብድር ውል ግንኙነት ላይ የወለድ ወለድ በሀገራችን ህግ የተከለከለ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ሌላኛው የወለድ ወለድን የሚመለከተው የፍታብሄር ህግ ቁጥር 1804 ሲሆን ንዑስ ቁጥር 1 እንደሚከተለው ይነበባል፡፡ “ከባለእዳው ላይ ያለው ገንዘብ በየጊዜው የሚከፈል ሆኖ ለባለገንዘቡ በየጊዜው የሚገኘው ገቢ የሆነ እንደሆነ ለምሳሌ ኪራይ፣ የርስት አላባ፣ የዘወትር ጡረታ ወይም ለህይወቱ የተወሰነ ጡረታ፣ የአንድ ካፒታል ወለድ፣ ይህ የመሰለ ከሆነ ደንበኛው