Tsegaye Demeke - Lawyer
Open in Telegram
Legal Service
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
5 673
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ (Stop Payment Order) የሚሰጠው መቼ እና እንዴት ነው?
===================
መግቢያ
ቼክ ጥሬ ገንዘብን ተክቶ በመገበያያነት አገልግሎት ላይ የሚውል የሚተላለፍ የንግድ ወረቀት አይነት ነው። በሀገራችን በቼክ መገበያየት እጅግ የተለመደ ተግባር ሲሆን ቼክም ሌሎች የሚተላለፉ የንግድ ሰነዶች ካላቸው እውቅናና ተቀባይነት በላቀ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለ እና በህብረተሰቡም ዘንድ እውቅና ያለው ሰነድ ነው። በሰነዱ ላይ ህብረተሰቡ የጣለው እምነትና በስፋት አገልግሎት ላይ መዋሉም በሰነዱ ላይ በተለያዩ ጊዜያት እና በስፋት የፍርድ ቤት ክርክሮች እንዲነሱ አንዱ ምክንያት እንደሆነ እሙን ነው። ታዲያ በዚህ ሰነድ በስፋት አገልግሎት ላይ መዋልና በሕጋችን ውስጥ ሰነዱን አስመልክቶ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን ማሻሻል እና ክፍተቱን መሙላት አስፈላጊና ለሰነዱ ቀጣይነትም አስተማማኝ ዋስትና ነው።
በዚህ አጭር ጽሑፍ ውስጥም በተለይም ቼክን በተመለከተ በስፋት የሚያጋጥመውንና በሕጋችን ሽፋን የተሰጠውን የቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ (Stop Payment Order) በተመለከተ ጥቂት ምልከታ ለማድረግ ነው። በጉዳዩ ላይ በስፋት አንባቢዎች ግንዛቤን ከፈለጉ ጸሐፊው የኢትዮጵያ የባንክ እና የሚተላለፉ የንግድ ሰነዶች ሕግ በሚል የታተመውን መጽሀፍ ማንበብ እንደሚችሉ በዚሁ ለመግለጽ እወዳለሁ።
የቼክ ክፍያ ባንክ አልፈጽምም ሊል የሚችለው መቼ ነው
ቼክ ህጉ የሚፈልገውን ፎርማሊቲዎች(የንግድ ሕግ አንቀጽ 827ን ይመለከቷል) አሟልቶ ለከፋዩ ባንክ ክፍያ እንዲፈጸም ከቀረበ በኋላ ከፋዩ ባንክ ለአምጪው ክፍያ አልፈጽምም ሊል ከሚችልባቸው ምክንያቶች ውስጥ አንዱ የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ በአውጪው ለባንኩ የተሰጠ እንደሆነ ነው(የኢትዮጽያ የባንክ እና የሚተላለፉ የንግድ ሰነዶች ሕግ መጽሐፍ፣ ገጽ 179)። በንግድ ሕጋችን አንቀጽ 857 የእንግሊዝኛው ቅጂ እንደተመለከተውም በአውጪው የሚሰጥ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ የቼኩ ከፋይ ባንክ ቼኩን ክፍያ አልፈጽምም ለማለት በቂ ምክንያት(sufficient authority) ነው በማለት ያሰቀምጣል። በተመሳሳይ መልኩ የአማርኛው የንግድ ሕግ አንቀጽ 857 ቅጂ ቼኩ ከመከፈሉ በፊት አውጪው እንዳትከፍል ብሎ የነገረው እንደሆነ ባንኩ የቼኩን ዋጋ አልከፍልም ለማለት ይችላል ይላል። እነዚህ የንግድ ሕጉ ድንጋጌዎች አንደኛ በጣም ጥቅል የሆነ ሀሳብ የያዙ በመሆኑ የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝን የሚያስፈጽሙት ባንኮች በምን በምን ምክንያት ክፍያ ይቁም ትዕዛዝን ተቀብለው ማስፈጸም እንዳለባቸው ባለመግለጹ ለቼክ ተገልጋዮችም ሆነ ለባንኮች የራሱን አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥር ይሆናል። ሁለተኛውና ዋናው ችግር አንቀጹ የቼክ ከፋይ ባንኮች የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝን እንደ ግዴታ መፈጸም እንዳለባቸው ሳይሆን አልከፍልም ለማለት ይችላል እና በቂ ምክንያት ነው በሚሉ የላሉ ቃላቶች በማስቀመጡ ባንኮችም ቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝን መቀበልና ያለመቀበል መብት ያላቸው እና በባንኮች በጎ ፈቃድ(ስልጣን)(Discretion) ላይ የተመሰረተ እንደሆነ የሚያሳብቅ የህግ አንቀጽ ነው።
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ መስጠት የሚቻልበት መንገድ
ሌላው ጉዳይ ህጉ የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ በምን በምን መንገዶች ይሰጥ( ማለትም በቃል ይሁን፣ በጽሑፍ፣ በስልክ፣ በፋክስ ወይም በሌሎች የመገናኛ መንገዶች) ያስቀመጠው ነገር ባለመኖሩ አንዱ የክርክርና የውዝግብ በር የሚከፍት ጉዳይ ይሆናል ማለት ነው( ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ የሌሎች አገሮችን ተሞክሮ ጨምሮ ማብራሪያ የሚሰጠውን የኢትዮጽያ የባንክና የሚተላለፉ የንግድ ሰነዶች ህግ መጽሐፍን በማጣቀሻነት ቢያነቡት የተሻለ ግንዛቤ ማግኘት ይችላሉ)። ከዚህ በዘለለ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ የሚሰጠው ቼኩን የጻፈው አውጪው ብቻ እንደሆነ በህጉ ላይ መቀመጡ በቀጣይነት ቼክ የሚተላለፍ ሰነድ በመሆኑና በጀርባ በመፈረም የተላለፈላቸው ቀጣይ የቼኩ ተጠቃሚዎች የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ እንዳይሰጡና መብታቸው የተገደበ እንዲሆን ያደርግባቸዋል። ከዚህ በተጨማሪም በቼኩ ላይ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ለማሰጠትም አውጪው መፈለግና አውጪው ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ማስደረግ ያለባቸው በመሆኑ በዚህ ሂደት አላስፈላጊና ከፍተኛ መጉላላት እንዲሁም በዚሁ የፍለጋ ጊዜ ውስጥ ቼኩ እንደቀረበ የሚከፈል የክፍያ ሰነድ በመሆኑ ቼኩ ከነጭራሹ ተከፍሎ መብታቸውን እስከማጣት የሚያደርስ ጉዳት ሊደርስባቸው ስለሚችል በዚህ ረገድ ህጉ ያለበትን ክፍተት መሙላት ይጠበቅበታል።
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ አንጻር
ከቼክ ጋር ተያይዞ ያሉ ጉዳዮችን ለመዳኘት ብሔራዊ ባንክ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ መመሪያዎችን አውጥቷል። ይሁንና ግን እነዚህ መመሪያዎች የቼክ እንቅስቃሴን፣ የቼክ ሂሳብ መክፈትን፣ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ መጻፍንና ሌሎች የተንቀሳቃሽ ሂሳብ ጉዳዮችን ከሚመለከቱ ውጪ ስለ ቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ የሚመለከት አንድም ድንጋጌዎች አልነበሯቸውም። በቅርቡ የወጣው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ፣ መመሪያ ቁጥር SBB/61/2016 ግን በአንቀጽ 6 የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝን የተመለከቱ አንቀጾችን አስቀምጧል። ይህ መመሪያም ቢሆን ስለቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ያስቀመጣቸው ድንጋጌዎች አሁንም ቢሆን ብዙውን የአሰራርና የህግ ክፍተት የሸፈኑ አይደሉም። ይሁንና ግን መመሪያው በአንቀጽ 6 ላይ እንዳስቀመጠው ከሆነ አንድ ቼከን የጻፈው አውጪው የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ቢደርሰው እንኳን የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዙ ለከፋዩ ባንክ የተሰጠው በዚሁ መመሪያ አንቀጽ 5 ላይ የተቀመጠውንና በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ መጻፍ የሚያስከትለውን አስተዳደራዊ ሀላፊነት ወይም የወንጀል ተጠያቂነት ለማምለጥ በማሰብ ከሆነ ላይቀበለው ይችላል ይላል።( በአውጪው ላይ በቂ ሂሳብ ሳይኖር ቼክ በመጻፉ የሚጣሉ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እና የወንጀል ተጠያቂነት ምንድናቸው የሚለውን ለመመልከት የኢትዮጽያ የባንክ እና የሚተላለፉ የንግድ ሰነዶች ሕግ መጽሐፍን ይመልከቱ) በመመሪያው ላይም የቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ በመመሪያው ላይ የተቀመጠውን ቅጣት ለመሸሽ ተደርጓል ተብሎ የሚታሰብባቸውን መሰረቶች አስቀምጧል። እነዚህ መሰረቶችና የህግ ግምቶችም አንደኛ የቼክ ክፍያ ይቁም ጥያቄው ለባንኮች ሲቀርብ የአውጪው ሂሳብ ውስጥ የተጻፈውንና ለተከፋዩ የሚከፈለውን የገንዘብ መጠን ሊሸፍን የሚችል በቂ ስንቅ(ሂሳብ) ቼኩ በሚጻፍበት እና ወይም ለክፍያ በሚቀርብበት ጊዜ( ይህ አገላለጽ በራሱ ግልጽነት ይጎድለዋል። ምክንያቱም በንግድ ሕጉ አንቀጽ 830 ላይ የተቀመጠው አውጪው ቼኩን በሚጽፍበት ጊዜ በሂሳቡ ውስጥ ሊያዝበት የሚችል በቂ ሂሳብ እና ይህንኑ ሂሳብ የማንቀሳቀስ መብት ጭምርም ያለው መሆኑን ማረጋገጥ ያለበት መሆኑን እንጂ መመሪያው እንደሚነግረን ለክፍያ በሚቀርብበት ጊዜ በቂ ስንቅ እስካለው ድረስ የሚል አይደለም። በመሆኑም መመሪያው የንግድ ሕጉን ድንጋጌዎች እስካልተሻሻለ ድረስ የመጠበቅ የህግ መስመር መከተል ነበረበት።) ሌላው አውጪው የቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ሰጥቶ በ15 ቀናት ውስጥ ለቼኩ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ መስጠት ምክንያት የሆነው ጉዳይ የቼኩ መጥፋት ወይም መሰረቅ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል።
ክስ መቀጠል/ ክስ ያቀረበ ከሳሽ ሲሞት የወራሾች በክርክር ውስጥ መግባት
===================
Our telegram:- https://t.me/Consultancy2012
======================
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 49(1) ድንጋጌ መሰረት ክሱን ለመቀጠል መብት አለኝ የሚሉ ወገኖች ዋናው ከሳሽ ወይንም ከሳሾች በሞቱ በአንድ አመት ውስጥ ክሱን ለመቀጠል እንዲፈቀድላቸው ሳያመለክቱ የቀሩ እንደሆነ የተጀመረው ክርክር ውድቅ እንደሚሆን የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 49(2) ድንጋጌ በግልፅ ያሳያል፡፡ ይህ ድንጋጌ ክሱን ለመቀጠል መብት አለኝ የሚል ወገን ክሱን ለመቀጠል እንዲፈቀድለት ማመልከቻውን የሚያቀርብበትን የጊዜ ገደብ የሚመለከት ሲሆን ከሳሽ ወይም ከሳሾች በሞቱ በአንድ አመት ውስጥ ክሱን ለመቀጠል ሳያመለክቱ መቅረታቸው ከተረጋገጠ የተጀመረው ክርክር ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ የሚደነገግ ሲሆን ከዚህ ጊዜ በኋላም ጥያቄው ሲቀርብ ተቀባይነት የሚያገኝበት አግባብ መኖሩን የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 55(2) ድንጋጌ ያሳያል፡፡
በዚህም መሰረት ከሳሹ ራሱ ወይም ከሳሽ የነበረው የሟቹ ንብረት አስተዳዳሪ ነኝ የሚል ባለአደራ ወይም የከሰረው ከሳሽ ንብረት አስተዳዳሪ የሆነ ሰው ወይም የዋናው ከሳሽ መብት ተላልፍልኛል የሚል ሰው ክሱ ቀሪ በሆነ ወይም በተሰረዘ በስድስት ወር ውስጥ የቀረበው ክስ እንዲቀጥል ወይም መሰረዙ እንዲነሳለት ለማመልከት የሚችል ስለመሆኑ የተደነገገ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ክሱ ቀሪ የሆነው ወይም የተሰረዘው በከሳሹ ጉድለት ያለመሆኑን የተረዳው እንደሆነ ይህ ምክንያት ስለደረሰው ኪሳራ ተገቢ መስሎ የታየውን ወስኖ የቀረው ወይም የተሰረዘው ክስ እንዲቀጥል ለማዘዝ የሚችል ስለመሆኑ የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 55(3) ድንጋጌ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡ ይህ ድንጋጌ አቤቱታው ክሱ ቀሪ በሆነ ጊዜ ውስጥ በሚቆጠር ስድስት ወራት ውስጥ መቅረብ እንዳለበትና በበቂ ምክንያት መደገፍ እንዳለበት የሚደነግግ ሲሆን በቂ ምክንያት የሚለውን ሐረግ ግን መመዘኛው ምን እንደሆነ በግልጽ ያስቀመጠው ነገር የለም፡፡ ይሁን እንጂ በቂ ምክንያት አለ ወይስ የለም? የሚለው ጥያቄ አመልካቹ በተገቢው ጊዜ አስፈላጊውን ስርዓት ያልፈፀመበት ምክንያት ተገቢ የሆነ ምክንያት ስለነበረው ነው? ወይስ አይደለም? የሚለውን በመመልከት በፍርድ ቤቱ አዎንታዊ ምላሽ ከአገኘ በቂ ምክንያት አለ ብሎ ለመደምደም የሚችልበትን አግባብ የሚያሳይ ነው፡፡
በመሆኑም የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 49 እና 55(2) እንዲሁም 55(3) ድንጋጌዎች ሲታዩ ክርክሩን ለመቀጠል የአንድ አመት ጊዜ ከአለፈ ጥያቄው ተቀባይነት የሌለው መሆኑንና ይህ የጊዜ ገደብ በማለፍ መዝገቡ ከተዘጋ ወይም ክሱ ቀሪ ከሆነ በኋላ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ክርክሩ እንዲቀጥል ወይም ቀሪ የሆነ ክስ እንዲንቀሳቀስ በቂ ምክንያት ያለው መሆኑን አቤቱታ አቅራቢው ከገለፀ እና ፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅራቢው አስፈላጊውን ስርዓት ያልፈፀመበት ምክንያት ተገቢ በሆነ ምክንያት መሆኑን ከተረዳው ክርክሩ እንዱቀጥል ማድረግ የግድ የሚል መሆኑን የሚያስገነዝቡን ናቸው፡፡
ከዚህ አንፃር ሲታይ ከሳሽ በመሞቱ ምክንያት የተዘጋ መዝገብን ለማንቀሳቀስ ፍጹም የሆነ ይርጋ የአንድ አመት ስድስት ወራት ጊዜ ነው ቢባል እንኳ ፍርድ ቤት መዝገቡ ተዘግቶ የቆየበትን ጊዜ በማስላት ብቻ ጊዜውን መቁጠር ያለበት ሳይሆን በጊዜ ገደቡ ውስጥ ጥያቄውን ያቀረበው አቤቱታ አቅራቢ የቆየበትን ሁኔታ ሁሉ አግባብነት ካላቸው ሌሎች የመሰረታዊ ህግ ድንጋጌዎችና አንድ ሰው ከሳሽ ለመሆን መሟላት ያለባቸውን የስነ ሥርዓት ሕግ መስፈርቶች ማየትን የግድ የሚል ነው፡፡
የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 49 እና 55(3) ሥነ-ሥርዓታዊ ድንጋጌዎች እንደመሆናቸው መጠንም የይርጋ ጊዜው መቆጠር የሚጀምረው መቼ ነው? ከሚለው ጥያቄ አንጻር ጉዳዩ መታየት ያለበት ነው፡፡ ይህንኑ ጥያቄ ለመመለስ ደግሞ የፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1846 እና የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 48 ድንጋጌዎችን ይዘት መመልከት ተገቢ ይሆናል፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1846 ድንጋጌ መሰረት የይርጋ ጊዜ መነሻው በመብት መስራት የሚቻልበት ጊዜ ነው፡፡ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 48 ድንጋጌ መሰረት ደግሞ ክርክሩ እንዲቀጥል የሚያስችለው መብት የማይቋረጥ ከሆነ የከሳሽ ወይም የተከሳሽ መሞት ክርክሩን እንዲቆም አያደርገውም በሚል ተቀምጧል፡፡ ከዚህ የስነ ስርዓት ድንጋጌ ውስጥ "ክርክሩ እንዲቀጥል የሚያስችለው መብት የማይቋረጥ ከሆነ" የሚለው ሐረግ ከፍ/ብ/ሕ/ቁ. 826(2) እና ከፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1986 ድንጋጌ ጋር ተጣምሮ የሚታይ ነው፡፡
በዚህም መሰረት በዚህ መብት አንድ ሰው ሊሰራ ይችላል ተብሎ የሚታሰበው ተገቢውን የወራሽነት ማስረጃ ከያዘ በኋላ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 62452 ቅጽ 13፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 48፣ 49(1)፣ 55(2)፣ 55(3) ፍ/ህ/ቁ. 826(2)፣ 1846፣ 1986
ክርክር አመራር ስርዓት
====================
Our telegram channel:- https://t.me/Consultancy2012
=====================
• ፍርድ ቤት ተከሳሹ ከጠየቀው የተለየ ወይም በላይ ዳኝነት ሊሰጥ አይችልም፡፡
ውል ባለመፈጸሙ ምክንያት ተከሳሽ የወሰደውን ቅድሚያ ክፍያ እጥፍ እንዲመለስ ዳኝነት ከጠየቀ መፍትሔ ሊሰጠው የሚችለው ቀብድ ስለሚከፈልበት ሁኔታ አስመልክቶ በተቀመጡት ድንጋጌዎች እንጂ የመቀጮ ስምምነት ላይ ተፈጻሚ በሚሆኑት የህግ ድንጋጌዎች መሰረት አይደለም፡፡
ክርክር የሚመራውና ዳኝነት የሚሰጠው በህጉ በተዘረጋው ስርዓት መሰረት ነው፡፡ በህጉ ከተዘረጋው የክርክር አመራርና የዳኝነት አሰጣት ስርዓት ውጪ ክርክር የመምራትና ዳኝነት የመስጠት አካሄድ የዳኝነት ሰጪ አካሉን ገለልተኝነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑ የሚታመን ነው፡፡ አንድ ፍርድ ቤት ዳኝነት የሚሰጠው በተከራካሪ ወገን የተጠየቀ ሁኖ በሕጉና በውሉ የተፈቀደ መሆኑን በጥንቃቄ አረጋግጦ ሲሆን ተከራካሪ ወገን በሕጉ ወይም በውሉ የተፈቀደለትን መፍትሔ ለማግኘት በግልጽ ዳኝነት መጠየቅ የሚገባው መሆኑን ስለክስ አመሰራረትና የመከላከያ መልስ አቀራረብን የሚደነግጉት የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 222፣ 234፣ 235፣ 236 እና 83 ድንጋጌዎች ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 224 እና 182 ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ ጋር ተዳምረው ሲታዩ የምንረዳው ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህ ድንጋጌዎች የዳኝነት ጥያቄ አይነትና መጠኑን በክሱ ማመልከቻ በግልጽ መስፈር ያለበት መሆኑን ያሳያል፡፡
የፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 224 ድንጋጌ ጠቅላላ ይዘቱ ሲታይም ከሳሹ በጉዳዩ ላይ የሚጠይቀው ዳኝነት ፍርድ ቤቱ የክሱን ጭብጥና የማስረጃውን አካባቢ ሁኔታ መሰረት በማድረግ ትክክለኛ መስሎ የታየውን ፍርድ ሊሰጥ እንደሚችል ያስገነዝባል፡፡ የፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 241 ድንጋጌ መሰረታዊ አላማ ተከራካሪ ወገኖች በጽሑፍ ያቀረቡትን ክርክር ለማብራራትና በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 246-248 ድንጋጌዎች አግባብ ጭብጥ ለመመስረት እንዲያግዝ ሲሆን በጽሑፍ ማመልከቻው ላይ ያልሰፈረን ዳኝነት ለመጠየቅ የሚያስችል ያለመሆኑን የድንጋጌው ይዘትና መንፈስ ያስረዳል፡፡ ተከራካሪ ወገኖች በመጀመሪያው ክርክር ላይ ካቀረቡት በቀር ሌላ ተጨማሪ ሙግት ወይም ሌላ ማስረጃ ማስቀረብና መመርመር የሚያስፈልግ ከሆነ ወይም ቀድሞ የተያዘው ጭብጥ የሚሻሻል ወይም ተጨማሪ ጭብጥ የሚያዝ መሆኑ ከታመነም በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 255 እና 251 አግባብ የሚፈፀም እንጂ ያለህጋዊ ምክንያት በማናቸውም የክርክር ደረጃ የቀረበ ክርክር ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት የክርክር አመራር የለም፡፡
ሰ/መ/ቁ 86510 ቅጽ 15፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 83፣ 182፣ 222፣ 224፣ 234፣ 235፣ 241፣ 236፣ 246-248፣ 251፣ 255
የክስ አቀራረብ ስርዓት
====================
Our telegram channel:- https://t.me/Consultancy2012
================
• ማናቸውም ለፍርድ ቤት የሚቀርብ ክስ ሁሉ ክሱ የቀረበለት ፍ/ቤት ጉዳዩን በሚገባ መርምሮ ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት በሚያስችለው በዚያው ነገር ሌላ አከራካሪ ጉዳይ በማያስከትል ሁኔታ ግልጽ በሆነ አጻጻፍ መቅረብ አለበት።
ማናቸውም ለፍርድ ቤት የሚቀርብ ክስ ሁሉ ክሱ የቀረበለት ፍ/ቤት ጉዳዩን በሚገባ መርምሮ ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት በሚያስችለው በዚያው ነገር ሌላ አከራካሪ ጉዳይ በማያስከትል ሁኔታ ግልጽ በሆነ አጻጻፍ መቅረብ እንዳለበት፣ በክስ ማመልከቻ ላይ መገለጽ ከሚገባቸው ነገሮች መካከልም አንዱ የክሱ ምክንያት እና ለክሱ ምክንያት የሆኑት ነገሮችና እነዚሁ የተፈጠሩበት ጊዜና ስፍራ እንደሆነ የክስ አቀራረብን ከሚመለከቱ የፍ.ስ.ስ.ሕ. ቁ 8ዐ(2)፣ 213(1)፣ 216(1)፣ 222(1)(ረ) እና ሌሎችም ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡
የእነዚህ ድንጋጌዎች ዓላማም የፍትሐብሄር ጉዳዮችን በተመለከተ በሰዎች መካከል የሚፈጠሩት የግንኙነት ዓይነቶች፣ እንዲሁም እነዚህ ግንኙነቶች የሚገዙባቸው የህግ ድንጋጌዎች፣ ግንኙነቶቹን አስመልክቶ የሚነሱ ክርክሮች የሚመሩበት ስርዓትም ሆነ የተለያዩ ግንኙነቶችን አስመልክቶ ከተከራካሪ ወገኖች የሚቀርቡት የክርክር ነጥቦች የተለያዩ በመሆናቸው ምክንያት እንደየግንኙነቱ እና ክርክሩ ዓይነትና ሁኔታ ለፍ/ቤት የሚቀርቡትን ክርክሮች በተቀላጠፈ ሁኔታ እና በተገቢው ስነ ስርዓታዊ አግባብ መርቶ እልባት ለመስጠት ማስቻል እንደሆነ የሚታመን ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 91329 ቅጽ 16፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 8ዐ(2)፣ 213(1)፣ 216(1)፣ 222(1) ረ
አንድ ክስ ለፍርድ ቤት የሚያቀርብ ሰው ክሱን የሚያቀርበበት ስርዓት በሕጉ የተዘረጋ ሲሆን ክሱ የቀረበለት ፍርድ ቤትም ሌላኛውን ወገን ከመጥራቱ በፊት ክሱ ህጋዊ ፎርማሊቲ ያሟላ መሆን ያለመሆኑ መመርመር ያለበት መሆኑን ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 33፣ 80፣ 222፣ 225፣ 226፣ እና 231 ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህ ድንጋጌዎች በህጉ መሰረት ያልቀረበ ክስ ተከሳሽ የሆነውን ተከራከሪ ወገን መጥራት ሳያስፈልግ ሊዘጋ የሚችልበት አግባብ መኖሩን የሚያሳዩ ናቸው፡፡ በህጉ አግባብ መቅረቡ ከተረጋገጠ ደግሞ የግራ ቀኙ የመሰማት መብት በሕጉ አግባብ መጠበቅ ያለበት መሆኑን 223፣ 234፣ 241 እና ተከታይ ድንጋጌዎች ያሳያሉ፡፡
ሰ/መ/ቁ. 83915 ቅጽ 15፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 33፣ 80፣ 222፣ 225፣ 226፣ 231፣ 223፣ 234፣ 241
ክስ ይዛወርልኝ
• በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያለ ጉዳይ የግዛት ስልጣን በሌለው ሌላ ፍርድ ቤት ወይም በዛው ፍርድ ቤት በሌላ ችሎት ተዛውሮ እንዲታይ በመጠየቅ በተከራካሪዎች የሚቀርብ አቤቱታ
በአንድ ወረዳ ፍ/ቤት በመታየት ላይ ያለ ጉዳይ ወደ ሌላ ወረዳ ፍ/ቤት ተዛውሮ እንዲታይ አንደኛው ወገን ሲያመለክት ተገቢ ምክንያቶች መኖራቸው ተረጋግጦ በክስ ይዛወርልኝ አቤቱታው እንደየሁኔታው አግባብነት ያለው ውሳኔ ሊሰጥ የሚችል ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 31 ተመልክቷል፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት የክስ ይዛወርልኝ አቤቱታ ለማቅረብ ጉዳዩ በክርክር ሂደት ላይ የሚገኝ መሆን ይኖርበታል፡፡ በስር ፍ/ቤት ክስ ተመስርቶ ፋይል ባልተከፈተበት ወይም ቀድሞ የተዘጋ መዝገብ ባልተንቀሳቀሰበት ሁኔታ የሚቀርብ የክስ ይዛወርልኝ አቤቱታ የክስ ምክንያት የለውም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 93171 ቅጽ 16፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 31
የክስ ይዛወርልኝ ጥያቄ /Change of Venue/ የሚስተናገድበትን አግባብ ህጉ የዘረጋው ስርዓት ያለ ሲሆን በ1958ቱ የፍትሐብሔር ስነ ሥርዓት ህግ አንቀጽ 31 ስር የተመለከተው አንዱ ነው፡፡ ከዚህ ህግ በኋላ በፌደራልም ሆነ በክልሎች የወጡት የፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጆች ተመሣሣይ ይዘት ያለውን ድንጋጌ ስራ ላይ አውለው ይገኛል፡፡ አንድ ክስ ወደ ሌላ ስፍራ ሊዛወር የሚችልበትን አግባብ ከሚደነግጉት የስነ ስርዓት ህግ ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ መገንዘብ የሚቻለው ደግሞ ጥያቄው ከተከራካሪ ወገኖች የሚቀርብ መሆኑና ህጋዊ ምክንያቶች ተብለው በህጉ ከተመለከቱት ሁኔታዎች ውስጥ አንዱ መሟላት ያለበት መሆኑን ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 66945 ቅጽ 11፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 31
ዕቃውን ዋጋ ከፍ ለማድረግ ያወጣው ወጪ እንዲመለስለት የሚከተሉትን ነገሮች ማስረዳት ይጠበቅበታል፡-
• በዕቃው ላይ ወጪ ያወጣ መሆኑን፤
• የዕቃውን ዋጋ መጨመሩን እና የዕቃው ዋጋ የጨመረው እሱ ባወጣው ወጪ ምክንያት መሆኑን፤
• የዕቃው ዋጋ መጨመር ንብረቱ እንዲመለስ በተጠየቀመት ግዜ የሚታይ መሆኑን፡፡
ነገር ግን እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ተሟሉ ማለት ሰውየው በዕቃው ላይ ያወጣው ወጪ በእርግጠኝነት ይመለስለታል ማለት አይደለም፡ ከነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች በተጨማሪ የቅን ልቦና መኖር አስፈላጊ ነው፡፡ ምንም እንኳን ወጪውን በማውጣት ሂደት ቅን ልቦና አለ የሚለው ግምት የሚወሰድበት ቢሆንም ይህ ግን ተቃራኒ ማስረጃ ሊቀርብበት የሚችል ነው፡፡ የፍታብሔር ህጉም በቁጥር 2172 ስር ወጪው በተፈፀመበት ግዜ ዕቃውን እንዲመልስ የተገደደው ሰው ዕቃውን የመመለስ ግዴታ ያለበት መሆኑን ያውቅ እንደነበር ወይም የማወቅ ግዴታ ያለበት መሆኑን ማስረዳት ከተቻለ የወጪው ኪሳራ እንዳይከፈል ወይም የንብረቱ ባለቤት ኪሳራውን የመክፈያ እስከ ሁለት ዓመት የሚደርስ ግዜ እንዲሰጠው ዳኞች ለመወሰን እንደሚችሉ አስቀምጧል፡፡
Source:- Legal Training and Research Institute
ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል፡፡ በዚህ መሰረት ከውል ውጭ ሃላፊነትን በተመለከተ ተበዳዩ ክስ ማቅረብ የሚችለው ካሣ የሚጠይቅበት ጉዳት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ እስከ 2 አመት ድረስ መሆኑ በፍ/ህ/ቁ 2143/1/ ሥር ተመልክቷል፡፡ ስለሆነም ተከሳሽ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ወደ ኋላ ላሉት ሁለት አመታት አላግባብ በቤቱ በተገለገሉበት መጠን እንዲከፈሉ የተጠየቁት ካሣ በይጋ የሚታገድ አይሆንም:: ሆኖም ከዛ በፊት ያሉት ግዜያት የተጠቀሙት ክፍያ ግን በይርጋ ቀሪ የሚሆኑ ናቸው በማለት ወስኗል፡፡
ሌላው መታየት ያለ ጉዳይ አንድ ሰው ያለአግባብ በልፅጓል ተብሎ ክስ በሚቀርብበት ወቅት ይህ አለመሆኑን ስለሚያሳይበት መንገድ ነው፡፡ የፍታብሔር ህጋችን በቁጥር 2163 ያለአግባብ መበልፀግ ስለሚቀርበት ሁኔታዎች የሚደነግግ ሲሆን በዚህም መሰረት ያለአግባብ በልፅገሃል ተብሎ የተከሰሰ ሰው ንብረቱን መልስ በሚባልበት ግዜ ላለመበልፀጉ ማስረጃ ያቀረበ እንደሆነ ማሰረጃ ባቀረበበት ልክ ኪሳራ እንዲከፍል አይጠበቅበትም፡፡ ይህም ማለት ምንም እንኳን ከሳሽ ተከሳሽ በእርሱ ኪሳራ መበልፀጉን ማስረዳት ቢችልም ተከሳሽ ክሱ በቀረበበት ወቅት የተገኘው ብልፅግና ከእርሱ ጋር እንደሌለ (ወይም ለሌላ ሰው የተላለፈ መሆኑን) ማስረዳት ከቻለ ካሳ መክፈል ላይኖርበት ይችላል፡፡ ሆኖም ተከሳሹ በክፉ ልቦና ተነሳስቶ ወይም መመለስ እንዳለበት እያወቀ ንብረቱን ወይም ዕቃውን ሌላ ሰው አስተላልፎ ከሆነ ምንም እንኳን የተገኘው ብልፅግና እርሱ ጋር የሌለ ቢሆንም ካሳ የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርበት የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2163(2) ስር ያስቀምጣል፡፡ ነገር ግን ተከሳሽ ያለአግባብ የበለፀገበትን ሀብት ለሶስተኛ ወገን ያስተላለፈው ያለ ዋጋ እንደሆነ ከሳሽ ይህን ሶስተኛ ወገን ያለ ዋጋ የወሰደውን ንብረት እንዲመልስለት ሊጠይቀው ይችላል፡፡
መክፈል የማይገባውን ክፍያ ስለመክፈል
ማንኛውም ሰው ሊከፍል የማይገባውን ነገር የከፈለ እንደሆነ ያለአግባብ የከፈለው ክፍያ እንዲመለስለት መጠየቅ ይችላል፡፡ ይህም ማለት ማንም ሰው በስዕተት ሊከፍል የማይገባውን ክፍያ የፈፀመ እንደሆነ ይህ የከፈለው ገንዘብ እንዲመለስልት ካሳ መጠየቅ የሚችል ሲሆን ክፍያውን የተቀበለው ሰው በእምነት ማጉደል ሀሳብ ተነሳስቶ የተቀበለ እንደሆነ ክፍያውን የፈፀመው ሰው ክፍያው ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ የከፈለው ነገር የሰጠውን ፍሬ ወይም ህጋዊ ወለድ ጨምሮ መጠየቅ እንደሚችል ህጉ ይደነግጋል፡፡ ሆኖም ሰውየው የከፈለው መክፈል የማይጠበቅበትን ክፍያ ቢሆንም እንኳን በሚከተሉት ሁኔታዎች የከፈለው ክፍያ እንዲመለስለት መጠየቅ አይችልም፡-
• ክፍያውን የፈፀመው ዕዳ እንደሌለበት እያወቀ ወይም ይህን ሁኔታ በግልፅ እየተረዳ በፍቃደኝነት ከሆነ፤
• ግለሰቡ የሚከፈለውን ነገር ያለዋጋ የመስጠት የህግ ችሎታ ያለው ሆኖ ክፍያውን የፈፀመው በይርጋ የታገደውን ዕዳውን ወይም የሕሊና ግዴታውን እና የበጎ አድራጎት መንፈሱን ተከትሎ እንደሆነ፤
ክፍያውን ከፈፀመለት ሰው የከፈለው እንዲመለስለት መጠየቅ እንደማይችል የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2165 እና 2166 ስር ያስቀምጣል፡፡
በሌላ በኩል ያለአግባብ የተከፈለውን ክፍያ የተቀበለ ሰው የተከፈለውን ነገር ከመመለስ የሚድንበት መንገድ ህጉ በቁጥር 2168 ስር ያስቀመጠ ሲሆን በዚህም መሰረት የማይገባውን ገንዘብ የተቀበለ ሰው በሌላ ሰው ላይ ያለው ገንዘቡ የተከፈለው መስሎት በቅን ልቦና የብድሩን ሰነድ አበላሽቶ ወይም ዋሶቹን ከዕዳው ነፃ አድርጎ ወይም ከእውነተኛ ባለዕዳ ሊቀበል የሚገባውን ገንዘብ በይርጋ አሳልፎ እንደሆነ፤ ያለአግባብ የተቀበለውን ገንዘብ የመመለስ ግዴታ ማይኖርበት ሲሆን እንዲህ ባለው ሁኔታ ክፍያውን ያለአግባብ የከፈለው ግለሰብ ክፍያው እንዲመለስለት ለመጠየቅ የሚችለው ከዋናው ባለዕዳ ብቻ ነው፡፡
በሌላ ሰው ንብረት ላይ የወጣ ወጪን ስለማስመለስ
ይህ የህግ ክፍል የሌላ ሰው ንብረት ያየዘ ሰው ንብረቱ በሚመልስበት ግዜ ንብረቱን ለመጠበቅ ያወጣውን ወጪ እንዲመለስለት ስለሚጠይቅበት አግባብ ወይም ንብረቱ በግለሰቡ ቁጥጥር በነበረበት ወቅት ያስገኘውን ጥቅም የራሱ ስለሚያደርግበት መንገድ የሚደነግግ የህግ ክፍል ነው፡፡ ዋናው ያለአግባብ መበልፀግ ህግ አላማ ማንኛውም ሰው መክፈል የማይገባውን ክፍያ እንዳይከፍል ወይም ማውጣት የሌለበትን ወጪ እንዳያወጣ ይህን ካደረገም ተገቢው ካሳ ተከፍሎት ፍትሀዊነት እንዲሰፍን ማድረግ ነው፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ሰው የራሱ ባልሆነ ንብረት ላይ በቀና ልቦና ያወጣው ወጪ ሳይቀናነስ ንብረቱን ለባለቤቱ መልስ መባሉ ተገቢ አይደለም፡፡ የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2168 ስር አንድ ሰው ለተወሰነ ግዜ በእጁ የቆየውን ዕቃ እንዲመለስ የተገደደ እንደሆነ የሕግ ወይም የውል ተቃራኒ የሚሆን ድንጋጌ ከሌለ በቀር ይህ ሰው የተባለውን ዕቃ ከመለዋወጥ የተነሳ ያሉት መብቶችና ግዴታዎች በዚህ የህግ ክፍል እንደሚገዛ ያደነግጋል፡፡
በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው በእጁ የነበረውን የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ በሚገደድበት ወቅት ዕቃው እንዳይጠፋ ወይም እንዳይበላሽ ለማድረግ ያወጣውን ወጪ እንዲመለስለት ለመጠየቅ እንደሚችል በቁጥር 2168 ስር ተቀምጧል፡፡ ሆኖም ይህ ወጪ የወጣው ዕቃውን እንዲመልስ በተገደደው ሰው ወይም እርሱ ሃላፊነትን በሚወስድለት ሰው ጥፋት ምክንያት ከሆነ ወጪው እንዲመለስለት ለመጠየቅ አይችልም፡፡ በመሆኑም አንድ ሰው በውል ህግ መሰረት በተቃራኒው ካልተዋዋሉ ወይም ወጪው አላስፈላጊ ካልሆነ ወይም ወጪው ዕቃውን እንዲመልስ በተገደደው ሰው ጥፋት ምክንያት የተፈፀመ እስካልሆነ ድረስ የሌላን ሰው ንብረት እንዳይጠፋ ወይም እንዳይበላሽ ለማድረግ ያወጣው ወጪ እንዲመለስለት የመጠየቅ መብት እንዳለው ህጉ ያስቀምጣል፡፡
ነገርግን ይህ የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ የተገደደ ሰው በውል በሌላ መልኩ ካልተዋዋሉ በስተቀር በማንኛውም መልኩ ለዕቃው አጠባበቅ ያወጣው ወጪ ወይም በንብረቱ ይዞታ ምክንያት የከፈለው ግብር እንዲመለስለት ለመጠየቅ አይችልም፡፡ ይህ መርህ መሰረት ያደረገው ህጉ የሌላ ሰው ንብረትን የያዘ ሰው ንብረቱን በእጁ በሚያስገባበት ወቅት ምንም አይነት መብት የሌለው መሆኑን የሚያውቅ ካልሆነ በስተቀር ንብረቱ ከሚያፈራው ፍሬ እንዲጠቀም መብት የሚሰጥ በመሆኑ ይህ ግለሰብ ፍሬ ያፈራለትን ንብረት ለመጠበቅ ያወጣው ወጪ ይመለሰልኝ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ካለመሆኑ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ ስለሆነም በእጁ ያለው ዕቃ እንዲመልስ የተገደደ ሰው የተቀበለው ዕቃ ያፈራውን ፍሬ የማስቀረት ህጋዊ መብት ያለው ሲሆን ዕቃውን በይዞታው ስር ባደረገበት ወቅት በዕቃው ላይ ምንም ዓይነት የውልም ሆነ የህግ መብት እንደሌለው እያወቀ ድርጊቱን ከፈፀመ ግን ይህን የንብረቱን ፍሬ ለራሱ የማስቀረት መብቱ ቀርቶ ለትክክለኛው የንብረቱ ባለቤት ዕቃው በእሱ ይዞታ ስር በነበረበት ወቅት ያፈራው ፍሬ ግምት ልክ የመክፈል ግዴታ ይኖርበታል፡፡
ሌላው የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ ከተገደደ ሰው መብት ጋር ተያይዞ የሚነሳው ይህ ግለሰብ ንብረቱ በእጁ በነበረበት ወቅት በቅን ልቦና በመነሳሳት ወጪ አውጥቶ የዕቃውን ዋጋ ከፍ በሚያደርግበት ግዜ ስለሚኖረው ህጋዊ መብት ነው፡፡ የፍታብሔር ህጉም በቁጥር 2171 ስር በሌላ ሰው ዕቃ ላይ የተደረገ ወጪ የዕቃውን ግምት ከፍ አድርጎት ከሆነ ዕቃውን እንዲመልስ የተገደደው ሰው ለዚሁ ጉዳይ ያወጣው ወጪ የዕቃውን ዋጋ ከፍ ባደረገው መጠን ብቻ ሊመለስለት እንደሚገባ ያስቀምጣል፡፡ በዚህም መሰረት ይህ ንብረቱን እንዲመልስ የተገደደ ሰው የ
ያለግባብ መበልፀግ
===================
ያለአግባብ መበልፀግ ህግ የውል፣ የንብረት እና ከውል ውጭ ያለ ሃላፊነት ህግ ክፍል በተጨማሪ የፍታብሔር ግንኙነትን የሚገዛ የህግ ክፍል ነው፡፡ ይህ የህግ ክፍል የውል፣ የንብረት እና ከውል ውጪ ያለ ሃላፊነት ህጎች የማይገዙትን የሰው ግንኝኑነት ክፍተት ለመሙላት በስፋት ጥቅም ላይ የሚውል ህግ ሲሆን ከዚህ ባሻገር ይህ የህግ ክፍል የሰዎችን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ከመግዛት አኳያ ሰፊ ድርሻ ያለው ነው፡፡
ያለአግባብ መልፀግ ህግ በመሰረታዊነት የሚመነጨው ማንኛውም ሰው በሌላ ሰው ኪሳራ ወይም ጉዳት ምክንያት መበልፀግ የለበትም ከሚለው መርህ ነው፡፡ ስለሆነም ማንኛው ሰው በሌላ ሰው ጉዳት ወይም ኪሳራ ምክንያት ያለአግባብ የበለፀገ እንደሆነ ጉዳት ወይም ኪሳራ ለደረሰበት ሰው ካሳ የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርበት ይህ የህግ ክፍል ያስገድዳል፡፡
አጠቃላይ መርሆዎች
የዚህ ህግ ዋንኛ አላማ ሰዎች በገንዘባቸው፣ በንብረታቸው እና በጉልበታቸው ላይ ሚኖራቸውን ህጋዊ መብት መጠበቅ ነው፡፡ ስለሆነም የፍታብሔር ህጋችን በቁጥር 2162 ስር ማንኛውም ሰው በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም የሌላ ሰው ሀብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ እና ባለሀብቱ ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ጥቅም ባገኘበት ልክ ለባለሀብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ካሳ የመክፈል ግዴታ እንዳለበት ያስቀምጣል፡፡ ይህ ድንጋጌ በስሩ የያዛቸው ነጥቦችን ስንመለከት ያለአግባብ የመበልጸግ ህግ ማንኛውም ሰው (ማለትም የተፈጥሮ ወይም የህግ ሰውነት ያለው ሰው) ላይ ተፈፃሚ የሚሆን ሲሆን እንደመጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ በዚህ ህግ ተጠያቂ የሚሆን ሰው የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም ሊያገኝ ይገባል፡፡ ይህም ማለት ጥቅሙ በንብት ላይ የተቋቋመ (right in rem) ወይም ከሌላ ሰው የሚጠየቅ መብት (right in personam) ወይም የነበረ እዳ የመሰረዝ፣ ግዴታ የመቅረት አይነት ወይም የኪሳራ መቅረት አይነት ጥቅም ሊሆን የሚችል ሲሆን ይህ ጥቅም ያለአግባብ የመበልፀግ የህግ ክፍል ስር ሊያስቀጣ የሚችለው ጥቅሙ የህሊና እርካታ ሊያስገኝ የሚችል ብቻ ሳይሆን በገንዘብ ሊለካ የሚችል ሲሆን ብቻ ነው፡፡ በተጨማሪም ይህ የተገኘው የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም በሌላ ሰው የሚንቀሳቀስ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ወይም ስራ ምክንያት የተገኘ መሆን ያለበት ሲሆን ጥቅሙን ያገኘው ሰው ጥቅሙን ላገኘበት ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት የሌለው መሆን ይኖርበታል፡፡ ስለሆንም በዚህ የህግ ክፍል ተጠያቂ የሚያደርግ ክስ የቀረበበት ሰው ጥቅሙን ላገኘበት ማንኛውም ህጋዊ ምክንያት ያቀረበ እንደሆነ ካሳ መክፈል ግዴታ አይኖርበትም፡፡ ሌላው በህጉ የተቀመጠው ቅድመሁኔታ በተከሳሽ ድርጊት ምክንያት ከሳሽ የሚታወቅ ኪሳራ ወይም ድህነት ሊደርስበት ሚገባ ሲሆን የከሳሽ ጥቅም ማጣት (ኪሳራ) እና የተከሳሽ ጥቅም ማግኘት ምክንያት አንድ መሆን አለበት፡፡ ይህም ማለት በደረሰው ኪሳራ እና በተገኘው ጥቅም መካከል የውጤት እና የምክንያት ግንኝነት መኖር አለበት፡፡
ከላይ የተዘረዘሩ ሁኔታዎች ከተሟሉ በኋላ ሃላፊነትን የሚወስድ ሰው በምን ያህል መጠን ከሳሽን የመካስ ግዴታ አለበት የሚለውን በተመለከተ የተገኘው ጥቅም እና የደረሰው ኪሳራ እኩል በሚሆንበት ግዜ ምንም አይነት ችግር ሊገጥም አይችልም ምክንያቱም ተከሳሽ አለአግባብ የበለፀገበት መጠን እና ከሳሽ ላይ የደረሰው ጉዳት እኩል ስለሆነ በዚሁ ልክ ካሳ እንዲከፍ ይደረጋል፡፡ ሆኖም በአንዳንድ ሁኔታዎች ያለአግባብ የተገኘው ብልፅግና ከደረሰው ጉዳት ሊያንስ ወይም ሊበልጥ ይችላል፡፡ እንዲህ አይነት ሁኔታ በሚያጋጥምበት ግዜ ምንም እንኳን የደረሰው ጉዳት ከተገኘው ብልፅግና የሚያንስ ቢሆንም ህጉ በግልፅ ተከሳሽ መክፈል ያለበት ኪሳራ ያለአግባብ ባገኘው ብልፅግና መጠን መሆን እንደሚገባው ያስቀምጣል፡፡ በተመሳሳይ ያለአግባብ የተገኘው ብልፅግና ከደረሰው ጉዳት የሚያንስ ከሆነ ወይም ጉዳቱ ከብፅግናው የሚበልጥ በሚሆንበት ግዜ የተከሳሽ ተጠያቂነት መጠን በተገኘው ብልፅግና ልክ ብቻ በመሆኑ ካሳ እንዲከፍል የሚገደደውም በዚሁ መጠን ብቻ ይሆናል፡፡
በአጠቃላይ ያአለአግባብ መበልፀግ በመሰረታዊነት ሶስት ሁኔታዎችን ያካተተ ሲሆን አንድን ሰው በዚህ የህግ ክፍል በመክሰስ ካሳ ለማስከፈል እነዚህ ሶስት ሁኔታዎች በድምር መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ የመጀመሪያው ተከሳሽ በገንዘብ ሊለካ የሚችል ጥቅም ያገኘ መሆኑ ሁለተኛው ይህ ጥቅም የተገኘው በከሳሽ ኪሳራ ወይም ጉዳት ምክንያት መሆኑ እንዲሁም ሶስተኛው የተገኘበት መንገድ አለአግባብ ወይም ምንም አይነት ህጋዊ መንገድ/ምክንያት የማይቀርብበት መንገድ መሆኑ ናቸው፡፡
ያለአግባብ የመበልፅ ክሶችን ይበልጥ ለመረዳት ፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 34406 የሰጠውን ውሳኔ መመልከት ይቻልል፡፡ በዚህ መዝገብ በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ የሆኑት ሰዎች ባለቤት እና አባት የሆኑት ግለሰብ መኖሪያ ቤታቸውን ያከራዩት ሰው ለተከሳሽ ቤቱን አስረክቦ ይጠፋል፡፡ የቤቱ ህጋዊ ዋራሽ ከሳሾች ቤቱን ለተረከቡት ግለሰብ ቤቱን ለቀው እንዲያስረክቧቸው ቢጠይቋቸውም ፍቃደኛ ባለመሆናቸው አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲያስረክቡ እና ንብረቱን በያዙበት ወቅት ያለክራይ በመኖር ያገኙትን ያለአግባብ ብልፅግና እንዲከፍሉ ክስ አቅርበዋል፡፡ ተከሳሽም በሰጡት መልስ ቤቱን ያለአግባብ ይዛለች ከተባለ እንኳን ይህን ካወቁ 10 ዓመት በላይ ስለሆነ በይርጋ ይታገዳል፣ የደረሰባቸው የጥቅም ጉዳት ከውል ውጪ እንደመሆኑ የኪራይ ማስከፈል ጥያቄአቸው ሁለት አመት ካለፈው በይርጋ ይታገዳል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል፡፡ የስር ፍርድ ቤቶች ጉዳዩን ከመረመሩ በኋላ ተከሳሽ ያለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲመልሱ እና ከንብረቱ ያለአግባብ የተጠቀሙትን መጠን ካሳ እንዲከፍሉ ወስነው ተከሳሽም በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ለሰበር ሰሚ ችሎቱ አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ የሰበር ሰሚ ችሎቱም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ የሆኑት ግለሰቦች ይዞታችን በሃይል ተወስዷል ወይም በይዞታችን ላይ ሁከት ተፈጥሯል በማለት ያቀረቡት ክስ የለም ክሣቸው በኪራይ የተረከቡትን ቤት ተከሳሽ መብት ሣይኖራቸው ገብተው አልወጣም ብለዋልና አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲለቁ የቀረበ ክስ ስለሆነ 10 ዓመት ቢያልፈው እንኳን በይርጋ አይታገድም፡፡ በጨማሪም ተከሳሽ የቀረበው የካሣ ጥያቄም ቢሆን በይርጋ ቀሪ ይሆናል በሚል ያቀረቡት ክርክር በተመለከተ ማንኛውም በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም በሌላ ሰው ሃብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ ሰው ጥቅም ባገኘበት መጠን ለባለሃብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ኪሣራ መክፈል እንዳለበት በፍ/ህ/ቁ. 2162 ሥር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ከሳሽ በቤቱ አላግባብ በበለፀጉበት መጠን ኪሣራ እንዲከፈላቸው መጠየቃቸው ህጉን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የካሣ ጥያቄ ሊቀርብ የሚገባበት የጊዜ ገደብ በተመለከተ ክርክር ቀርቧል፡፡ ያለአግባብ ስለመበልፀግ የሚናገረው ምእራፍ የካሣ ጥያቄ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ አይናገርም፡፡ ነገር ግን አላግባብ ስለመበልፀግና ከውል ውጪ ስለሚደርስ ሃላፊነት የሚናገሩት ድንጋጌዎች በአንድ አንቀጽ ውስጥ ተካትተው መገኘታቸው እንዲሁም ያለአግባብ መበልፀግም ከውል ውጪ የሚደርስ ሃላፊነት በመሆኑ ከውል ውጭ የሚደርስ ሃላፊነት ሥር የተመለከተው የይርጋ ዘመን በተመሣሣይ አላግባብ መበልፀግ በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅድመ ሙግት መስማት (pre-trial stage)
1. የክስ አቤቱታ (ከሰነድና ከፅሐፍ ማስረጃ እንዲሁም ከማስረጃ ዝርዝር ጋር) ይቀርባል፡፡
2. ተከሳሹ የመከላከያ መልሱን ይዞ እንዲቀርብ ይታዘዛል፡፡
3. የመከላከያ መልስ (ከሰነድና ከፅሐፍ ማስረጃ እንዲሁም ከማስረጃ ዝርዝር ጋር) ይቀርባል፡፡
4. የመከላከያ መልሱ ከቀረበ በኃለ የጽሐፍ ክርክሩ ይቆማል፡፡
5. የፅሐፍ ክርክሩ ካቆመ በኃለ ክሱን ለመስማት ይቀጠራል፡፡
6. በተቀጠረው ቀን በላጉዳዮች ራሳቸው ወይም ወኪልቻቻው ይቀርባሉ፡፡
7. ባለጉዳዮች ከፅሐፍ አቤቱታቸው ጋር ያላቀረቡትን የፅሐፍ ማስረጃ ይዘው ይቀርባል፡፡
8. የጽሐፍ ማስረጃ ሁሉ በባለጉዳዮች ወይም በፍርድ ቤቱ ትፅዛዝ ተጠቃሎ ይገባል፡፡
9. ፍርድ ቤቱ ባለጉዳዮቹን ወይም ወኪልቻቸውን ይመረምራል፡፡
10. የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ከቀረበ ውሳኔ ይሰጥበታል፡፡
11. በተገረገው ምርመራ ተከሳሹ የቀረበበትን ክስ ካመነ ወዲያው ውሳኔ ይሰጣል፡፡
12. ተከሳሹ የቀረበበትን ክስ ካላመነ የክርክሩ ጭብጥ ይያዛል፡፡
ሙግት መስማት (trial stage)
13. ጭበጡ ከተመሠረተ በኃላ ክርክሩን መስማትና ማስረጃ መመርመር ይቀጥላል፡፡
14. ለሁለቱም ወገን ምስክሮች መጥሪያ ይላካል፡፡
15. የሁለቱም ወገን ምስክሮች ተሟልተው ይቀርባለ፡፡
16. ከሳሹ (በተወሰኑ ሁኔታዎች ተከሳሹ) ሙግቱን ይከፍታል፡፡
17. ሙግቱን የጀመረው ወገን ምስክሮቹ የሚመስክሩለትን ነጥብ በአጭሩ ያስረዳል፡፡
18. ምስክሮች እውነት ለመናገር ይምላሉ ወይም እውነት እንደሚናገሩ ያረጋግጣሉ፡፡
19. ሙግቱን የጀመረው ሰው ምስክሮቹን አንድ በአንድ አቅርቦ ዋና ጥያቄ ይጠይቃል፡፡ ሌለው ወገን መስቀለኛ ጥያቄ ያቀርባል፡፡ የጀመረው ወገን የማጣሪያ ጥያቄ ይጠይቃል፡፡ ፍርድ ቤቱ በማንኛውም ሰዓት አስፈላጊ የሆነ ጥያቄ ይጠይቃል፡፡
20. ሙግቱን የከፈተው ወገን ምስክሮቹን አሰምቶ ከጨረሰ በኋለ ሌላኛው ወገን ምስክሮቹ የሚያስረደለትን የመከላከያ ነጥብ በአጭሩ አስረድቶ በተመሳሳይ ሁኔታ ምስክሮቹን ያሰማል፡፡
21. ማስረጃ የመስማቱ ሂደት ሲጠናቀቅ ግራ ቀኙ የመዝጊያ ቃላቸውን ይሰጣለ፡፡
22. በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ የፍርድ ውሳኔውን ይሰጣል፡፡
ምንጭ፡- ለቅድመ ስራ ስልጠና ሰልጣኞች ከተዘጋጀ የስልጠና ማኑዋል የተወሰደ
ለውን ካሳ የመክፈል ሃላፊነት የተወሰነ መሆንን መሰረት በማድረግ ስናየው ኮንቬንሽኑ ካስቀመጠው የካሳ መጠን በላይ ተዋዋይ ወገኖች ለመስማማት እንደሚችሉ ቢፈቅድም በኮንቬንሽኑ አንቀፅ 22(1) ከተደነገገው 125,000 ፍራንክ ወይም 10,000 ዶላር በታች መስማማት ግን ኣይፈቀድም፡፡ ይህ የካሳ መጠን በመንገደኛ ላይ የደረሰን ጉዳት መሰረት ያደረገ ሲሆን ሻንጣና ዕቃን በተመለከተ የደረሰ ጉዳት በሚኖርበት ጊዜ 250 ፍራንክ ማለትም 20 ዶላር ገደማ በጥቅል እንደሚከፈል የሚደነግግ ነው፡፡ ከፍ ብሎ የተገለፀው ለተመዘገቡ ጓዞች ወይም እቃዎች የሚያገለግል ሆኖ መንገደኛው በእጁ ለያዘው ጓዝ ወይም እቃ ደግሞ 5,000 ፍራንክ ወይም 400 ዶላር ገደማ በካሳ ሊከፈል እንደሚችል የሚወሰን ነው፡፡ ሆኖም ግን የዋርሶ ኮንቬንሽን በሰው ላይ ለሚደርስ ጉዳት ወይም መዘግየት ከተጠቀሰው ጣርያ በላይ ሊከፈልበት የሚችልን ሁኔታም ስለሚያካትት ኮንቬንሽኑ በመርህ ደረጃ የተወሰነ ሃላፊነትን የሚከተል ሲሆን በልዩ ሁኔታ (Exception) ደግሞ ያልተወሰነ ሃላፊነትን (unlimited liability) የሚከተል መሆኑ ግልፅ ሊሆን ይገባል፡፡ በአገራችን ያለው የጉዳት ካሳ አከፋፈል ኢትዮጵያ ኣየር መንገድ የ1999 ሞንትሪል ኮንቬንሽን የፈረመ በመሆኑ ይህ ኮንቬንሽን ደግሞ በመንገደኛ ላይ ለሚደርስ የኣካል ጉዳት ወይም ሞት የሚከፈለውን የካሳ መጠን ህጋዊ ክፍያዎችን( legal fees) እና ወጪዎችን (costs) የሚጨምር ከሆነ 75,000 የአሜሪካ ዶላር እነዚህን ወጪዎች የማይጨምር ከሆነ ግን 58,000 የኣሜሪካን ዶላር እንደሚከፈል ከነበረው በእጅጉ የተሻለ የካሳ ክፍያን የሚደነግግ ነው፡፡ ይህን መሰረት በማድረግ የኣገር ውስጥ በረራን ወደሚገዛውና መሰረቱ የዋርሶ ኮንቬንሽን ወደ ሆነው የኢትዮጵያ ንግድ ህግ በምንመጣበት ጊዜ ደግሞ በመንገደኛ ኣካል ላይ ለሚደርስ ጉዳት ወይም ሞት ን/ህ/ቁ 636(1) አጓዥ ለአንድ መንገደኛ የሚከፍለው የካሳ መጠን ከ40 ሺ ብር መብለጥ እንደሌለበት የሚደግግ ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው በአገር ውስጥ በረራና ዓለም ኣቀፍ በረራ የኢትዮጵያ ኣየር መንገድ ለመንገደኞች ያለው ሃላፊነት የተለያየ መሆኑን ነው፡፡ የተለያየ መሆኑ ብቻም ኣይደለም ኣሁን ባለው የውጭ ምንዛሪ በዓለም አቀፍ በረራ የሚከፈለው የካሳ መጠን ከግማሽ ሚልዬን ብር በላይ ሲሆን በአገር ውስጥ በረራ የሚከፈለው 40,000 ብር መሆኑ በእጅጉ የተራራቀ የካሳ ኣከፋፈል ስርዓት ያለ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የዋርሶ 1929 ዓ.ም ኮንቬንሽንን ያሻሻለው የ1955 ሄግ ፕሮተኮል ኣልፈረመችም ኣላፀደቀችምም እዚህ ላይ ሊነሳ የሚችለው ይህንን ሰነድ ሳትፈርም ሳታፀድቅ እንዴት ነው ከዓለም ጋር አብራ እየሰራች ያለችው? የሚል ጥያቄ ነው፡፡ ዓለም አቀፍ በረራን በሚመለከት ኢትዮጵያ ከገበያው ያልወጣችበት ምክንያት የ1955 ሄግ ፕሮቶኮል የአጓዥ ሃላፊነትን በማስመልከት በዋርሶ ኮንቬንሽን የተደነገጉትን አንቀፅ 17፣ 18 እና 19 ሳያሻሽላቸው በማለፉና አሁን ድረስ እነዚህ ህጎች በስራ ላይ ስላሉ ነው፡፡ የ1955 ሄግ ፕሮተኮልን ተከትሎ የመጣው የ1999 ሞንትሪል ኮንቬንሽን ያሻሸለው የካሳ መጠኑን ስለሆነ ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስለፈረመ ኢትዮጵያን እስካሁን ድረስ በዘርፉ የዓለም ገበያ እንድትቆይ ኣሰችሏቷል፡፡
የተወሰነ ሃላፊነት (limited liability) በሚመለከት የኢትዮጵያ ንግድ ህግ የአጓዥ ሃላፊነት በመወሰን መንገደኛን በሚመለከት በን/ህ/ቁ 636(1) የሚከፈለው ከሳ ከ40,000 ብር መብለጥ እንደሌለበት በን/ህ/ቁ 637(1) ላይ ደግሞ የጓዝ ወይም ዕቃ መጥፋት ወይም መበላሸት ሲኖር የሚከፈለው የካሳ መጠን በኪሎ ግራም ከ40.00 ብር መበለጥ እንደሌለበት የሚደነግግ ነው፡፡
በዚህ ድንጋጌ እንደ ኣንድ የተለየ ሁኔታ (exception) የተቀመጠ ነገር ቢኖር መንገደኛው ገና ከመጀመርያው ከአጓዡ ጋር በዚያ ንብረት ልዩ ጥቅም ኣለኝ በሚል ስምምነት ላይ ደርሰው ከሆነ አጓዥ በን/ህ/ቁ 637(2) (3) መሰረት የተስማሙበትን የጉዳት ካሳ መጠን ለመክፈል ሃላፊ የሚሆንበት ሁኔታ መኖሩ ነው፡፡ ን/ህ/ቁ 637(4) በዋርሶ ኮንቬንሽን ለውዝግብ ይዳርግ የነበረውን የጉዳት ካሳው የሚሰላው በጠፋው ጓዝ ወይም ዕቃ ክብደት ነው ወይስ በኣየር ትኬቱ ባለው የክደት መጠን የሚለው አከራካሪ ጉዳይ በሚቀርፍ መልኩ የሚሰላው “… የነዚህኑ ጓዞች፣ ዕቃዎች ወይም በውስጣቸው ያሉ እቃዎች ጠቅላላ ክብደት በማሰብ ነው፡፡” በማለት ስለሚደነግግ ከዋርሳ ኮንቪንሽን የተሻለ ግልፅነት ያለው ድንጋጌ ነው፡፡
ከዚህ ጋር የታይዞ የሚነሳው ጉዳይ ኢትዮጵያ የዋርሶ ኮንቬንሽንን ብቻ ተከትላ መሄዷ ወይም ለአገር ውስጥ በረራ የንግድ ህጉን መሰረት በማድረጓ የቱን ያህል ተቀባይነት ያለው ነው? የሚል ሲሆን የዋርሶ ኮንቬንሽን በወጣበት ጊዜ የነበረው የገንዘብ ምንዛሪና አሁን ያለው የዋጋ ገሽበትን መሰረት አድርገን ብቻ እንኳን ብናየው በኢትዮጵያ ያለው የአጓዥ ሃላፊነት በእጅጉ ዝቅተኛ ሆኖ ነው የምናገኘው፡፡ ዓለም አቀፍ በረራን በተመለከተም ኢትዮጵያ ኣየር መንገድ የፈረመው የሞንትሪል ኮንቬንሽን በራሱ አሁን በርካታ ኣየር መንገዶች እሱን ውድቅ እያደረጉ ሌላ ‘’IATA’’ ውልን ተከትለው የተሻለ የካሳ ኣከፋፈል ስርዓትን በመከተል ባሉበት ጊዜ የድሮውን ኮንቬንሽንና የሄግ ፕሮተኮል መሰረት በማድረግ የወጣውን የኢትዮጵያ ንግድ ህግን ብቻ መሰረት በማድረግ የጉዳት ካሳ መክፈል የዘርፉን ተወዳዳሪነት ሊቀንሰው ይችላል፡፡ ስለሆነም ጊዜው የውድድር ነውና ኣርቆ ማሰብን የሚጠይቅ ነው፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያ የኣየር ማጓጓዣን በተመለከተ የዋርሶ ኮንቬንሽን፣ የሄግ ፕሮቶኮል ሞንትሪል ኮንቬንሽንና የንግድ ህጉን መሰረት በማድረግ ከዚህ የኢኮኖሚ ዘርፍ ተጠቃሚ ለመሆን እየሰራች ያለች ስትሆን በነዚህ ህጎች ያለው የመንገደኞቹ መብትና ግዴታ ግን በየጊዜው እየተሻሻሉ ከመጡት 1955 ሄግ ፕሮቶኮል፣ የ1971 ጓቲማላ ሲቲ ፕሮቶኮል፣ የ1978 ጓዳላጃራ ፐሮቶኮል እና የ1999 ሞንትሪል ኮንቬንሽን አንፃር ሲታይበእጅጉ ዝቅተኛ ትኩረት የተሰጠው ይመስላል፡፡
**የየብስ ማጓጓዥ ውል (Carriage by Land) )የአጓዥ የተወሰነ ሃላፊነት (Limited Liabilities of air carrier)
(ይቀጥላል •••)
ሀላፊነትን የመወሰን ህጎች (liability limiting laws) ( ክፍል 1
****
በዳንኤል ፍቃዱ( ጠበቃ እና የህግ አማካሪ)
****
በመሰረቱ ለደረሰ ጉዳት ሀላፊ ሆነ ሰው የሚከፍለው ካሳ በተበዳዩ ላ ከደረሰው ጉዳት ጋር እኩል መሆን እንዳለበት ህግ ይነግረናል፡፡( የፍ/ሕ/ቁ 2090 እና ተከታዮቹ) ሆኖም የህግ መርህ (principle) ባብዛኛው በስተቀር( ልዩ ሁኔታ)(exception) ደግሞ አሉ፡፡
ሀላፊነት በህግ ወይም በውል ሊወሰን ( ሊገደብ ) እንደሚችል ብላክስ ሎው የተባለው የህግ መዝገበ ቃላት ይገልጻል፡፡
ሀላፊነትን መወሰን የሚስፈልገው ሀላፊነቱ የተገደበለት ወገንን ለማበረታታት ፣ በስራው የሚገኘው ጥቅም ውሱን በመሆኑ ስራውን እንዳይተው እና በስራው እንዲቀጥል ለማበረታታት እንዲሁም የደረሰው ጉዳት ትክክለኛ ግምቱን (exact amount of the damage) ለማወቅ የሚስቸግር በመሆኑ ጉዳቱ ሲደርስ የሚከፈለው የካሳ መጠን አስቀድሞ የታወቀ እንዲሆን ነው፡፡
* የኣየር ማጓጓዣ (Air Carriage)የአጓዥ የተወሰነ ሃላፊነት (Limited Liabilities of air carrier)
•የአጓዥ ሃላፊነቶች ከዋርሶ ኮንቬንንና የኢትዮጵያ ንግድ ህግ ኣንፃር
የሃላፊነቶቹን ይዘት ለመረዳት ያስችለን ዘንድ በሶስት ማለትም፤-
1.. በመንገደኞቹ ለደረሰ ጉዳት ስለሚኖረው ሃላፊነት (liability for carriage of passengers)
2.በዕቃዎችና ሻንጣዎች ለደረሰ ጉዳትና፣ መጥፋት ስለሚኖረው ሃላፊነት (liability for the carriage of goods and baggage’s)
3. በመዘግየት ምክንያት የሚመጣ ሃላፊነት (liability for delay)በሚል ከፍለን ልናየው የሚችል ነው፡፡ በመጀመርያው ከአጓዥ ሃላፊነት ብንጀምር አጓዥ ለመንገደኛው የኣካል ጉዳት ወይም መሞት ሃላፊ የሚሆነው በኣውሮፕላኑ ውስጥ በመጓዝ
ላይ ሳለ ወይም በኣውሮፕላን ለመጓዝ ሲሳፈር ወይም ሲወርድ አደጋ ከደረሰበት ነው፡፡ ለዚህ
የዋርሶ ኮንቬንሽን አንቀፅ 17 በግልፅ “Physical or bodily injury or death are recoverable” በማለት ሲደነግግ የኢትዮጵያ ንግድ ህግም በአንቀፅ 630 ላይ “መንገደኛው
በአውሮፕላን ጉዞ ላይ እንዳለ ወይም ለመጓዝ ሲሳፈር ወይም ሲወርድ የሞት አደጋ ወይም ሌላ የኣካል ጉዳት ቢደርስበት አጓዥ ሃላፊ ይሆናል፡፡” በማለት ይደነግጋል፡፡ እዚህ ላይ አንድ ግልፅ መሆን ያለበት ጉዳይ ኣጓዥ ለደረሰው የኣካል ጉዳትም ሆነ ሞት ሃላፊ የሚሆነው ለጉዳቱ መንስኤ የሆነ” አደጋ” (accident) የደረሰ መሆኑ ሊረጋገጥ እንደሚገባና
ሃላፊነቱ ለማንኛውም ጉዳት እንዳልሆነ ነው (ን/ህ/ቁ 630)፡፡ ሁለተኛውን የአጓዥ ሃላፊነት በተመለከተ የዋርሶ ኮንቬንሽን አንቀፅ 18 ”The carrier is liable for damages sustained in the event of the destruction or loss of damage to any registered luggage or any good, if the occurrence which caused the damage so sustained took place during the carriage by air.” በማለት የኣጓዥን ሃላፊነት ሲገልፅ የኢትዮጵያ ንግድ ህግ
ቁጥር 631 ላይ “የተመዘገቡ ጓዞች ወይም ዕቃዎች በኣየር ጉዞ ጊዜ በሆነ ነገር ቢጠፋ ወይም ቢበላሹ አጓዥ በሃላፊነት ይጠየቅበታል፡፡” ሲል ተመሳሳይ በሆነ መንገድ ይደነግጋል፡፡ ሶስተኛው ሃላፊነት በሚመለከት የዋርሶ ኮንቬንሽን በአንቀፅ 19 ላይ “The carrier is Liable for damage occasioned by delay in the carriage by air of passengers or goods.” ሲል የኢትዮጵያ ንግድ ህግ በቁጥር 633 ላይ “በኣየር ጉዞ በሚደረግበት ጊዜ በመንገዶኞቹ፣ በጓዞቹ ወይም በእቃዎች ዘገይቶ በመድረስ ምክንያት ለደረሰው ጉዳት አጓዥ ሃላፊ ነው፡፡” በማለት ይደነግጋል፡፡
በእነዚህ ድንጋገጌዎች ዙርያ የሚነሱት አከራካሪ ጉዳዮች የዋርሶ ኮንቬንሽን አንቀፅ 17 እና የን/ህ/ቁ 630 “accident” “አደጋ ” ሲሉ ቃሉ በራሱ ምን ማለት ነው? ለሚለው ፍች ኣይሰጡም በመሆኑም ያልተጠበቀ ነገር (Unexpected event) ወይስ ያልተለመደ ከውጭ የሚመጣ ችግር? የሚል ሲሆን የተለያዩ የውጭ አገር ፍ/ቤቶች የተለያየ ትርጉም ሲሰጡት ይስተዋላል፡፡
ለምሳሌ በ padilla V. Olympia Air Lines ጉዳይ መንገደኛው Padilla በበረራ ላይ እያለ ከ6-7 ቢራ ጠጥቶ ሽንት ቤት (Lavatory) ውስጥ ወድቆ ለደረሰበት የኣካል ጉዳት ካሳ ኣይገባውም ምክንያቱም ይህ አደጋ ኣይደለም በራሱ ፈቃድ (voluntarily) ያመጣው የኣካል ጉዳት ነው በማለት ኣሰናብቶታል፡፡ ሌላው ከዚህ ጋር በተያይዞ ሊነሳ የሚችለው ኣወዛጋቢ ጉዳይ “bodily injury” የሚለው ኣባባል የኣእምሮ ጉዳትን ይጨምራል ወይስ ኣይጨምርም? የሚል ሲሆን ኣብዛኞቹ የውጭ አገር ፍ/ቤቶች “bodily injury” is inclusive to mental or psychic injuries በሚል አተረጓጎም ውሳኔ ሲሰጡ ይታያል፡፡
ከእቃዎች ወይም ጓዞች መጥፋትና መበላሸት ጋር ተያይዞ የሚነሳው ክርከር የዋርሶ ኮንቬንሽን አንቀፅ 18 “… during carriage by air.” ከሚለውና የን/ህ/ቁ 631”….whilst such Luggage or goods were carried by air.” ከሚሉት ኣባበሎች ጋር ተያይዞ የሚነሳው ዕቃው ወይም ሻንጣው በኣየር ጉዞ ላይ ሳለ የሚለው ኣባባል መነሻና መድረሻው የት ነው? ወይም ይህ ንብረት በአየር ጉዞ ላይ ነው የሚባለው መቼ ነው? የሚል ሲሆን በነዚህ ርእሰ ጉዳዮች ዙርያ የአገር ውስጥ የፍ/ቤቶች ጉዳይ የሌለ ቢሆንም በውጪው ዓለም ያለው አተረጓጎም ለምሳሌ በ Fovie V.Sabena ጉዳይ Fovie ከስዊዘርላንድ ወደ ብራስለስ ስርዓቶችን ይዛ ለመሄድ ተነስታ ኣየር መንገድ ውስጥ የጉምሩክ ቀረጥ ለመክፈል ኣስቀምጣቸው ሳለች ጠፍቶባት ፍ/ቤቱ ኣየር መንገዱን ሃላፊ ኣይደለም ብሎ አሰናብቶታል፡፡ ሌላ ፍ/ቤት በሌላ ጉዳይ Westminster Bank V. Imperial Airways በተከራከሩበት መዝገብ ከሳሽ ባንክ ከፓሪስ ወደ ለንደን ለመጓዝ በዝግጅት ሳለ በኣየር መንገዱ የደህንነት ሳጥን (security box) ውስጥ ያስቀመጠው ወርቅ ስለጠፋበት ፍ/ቤቱ ኣየር መንገድ ሃላፊ እንደሆነ ወስኗል፡፡ ከነዚህ ውሳኔዎች ለመገንዘብ የሚቻለው የኮንቬንሽኑም ሆነ የንግድ ህጉ ኣባባል ለትርጉም የተጋለጠ መሆኑን ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የኮንቬንሽኑ አንቀፅ 19 “in the carriage by air” የሚል ኣባባልና ን/ህ/ቁ 633 “in carriage” የሚል ሓረግ ስለሚጠቀሙ ይህ ሁኔታ ኣለ የሚባለው መቼ ነው? የሚለው ጥያቄ እንዲነሳ ምክንያት ሲሆን ይታያል፡፡ ለዚህ አንዳንድ ፀሃፍት የሚሰጡት አስተያየት የኮንቬንሽኑ አንቀፅ መነበብና መተርጎም ያለበት ከኮንቬሽኑ አንቀፅ 17፣ 18፣ 22እና 24 ጋር ነው በማለት አስተያየት የሚሰጡ ሲሆን ተመሳሳይ ጉዳይ በአገራችን በሚያጋጥምበት የነዚህ የዋርሶ ኮንቬንሽን ድንጋጌ ኣቻዎች የሆኑትን ህጎች በስራ ላይ ማዋልን የሚጠይቅ ነው፡፡
የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረን የተወሰነ ሃላፊነትን ከዓለም አቀፍ ኮንቬንሽንና የኢትዮጵያ ንግድ ህግ ኣንፃር ስንመለከት በዋርሶ ኮንቬንሽን ኋላም የኢትዮጵያ ኣየር መንገድ በፈረመይ የ1999 ሞንትሪል ኮንቬንሽን ያ
ቀለብ የመስጠት ግዴታ በተሸሻለው የፌዴራል የቤተሰብ ህግ
------------------------------
በማህበራዊ ህይወት ውስጥ አስፈላጊ በሆነ ጊዜ መረዳዳት ያለ እና በህግ የሚጣሉ ግዴታዎች እንዳሉ ሆነው በዋናነት ከሞራል የሚመነጭ ተግባር ነው፡፡ በችግር ጊዜ ከሚደጋገፉ እና ከሚረዳዱ ሰዎች ውስጥ ደግሞ በዝምድና ወይም በጓደኝነት የሚተዋወቁ ሰዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ቀለብ መስጠት ዝምድና ያለቸው ሰዎች ካለባቸው ህጋዊ ግዴታ ውስጥ አንዱ ሲሆን የተለያዩ ሀገራት ህጎች በተለይ በቤተሰብ ህጋቸው ውስጥ ቀለብ የማግኘት መብት የእነማን አንደሆነ፣ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለባቸውን ሰዎች እንዲሁም ቀለብ የሚሰጥበትን ዝርዝር ሁኔታዎች አካተው ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያም የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ ቀለብ የመስጠት ግዴታን ዝርዝር ሁኔታዎች የሚደነግጉ አንቀፆችን ይዟል፡፡ቀለብ የመስጠት ግዴታ የሚኖረው በህግ ቀለብ የማግኘት መብት ያለው ሰው ለመስራት እና ለኑሮው አስፈላጊውን ገቢ ለማግኘት አቅም የሌለውና በችግር ላይ የወደቀ ሲሆን ብቻ ነው፡፡በመሆኑም ቀለብ የመጠየቅ መብት ያላቸው ሰዎች እነማን ናቸው የሚለው መሰረታዊ ጥያቄ ነው፡፡ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች ከወላጆቻቸው ወይም በእድሜ ወይም በጤና ችግር ምክንያት እራሳቸውን ማስተዳደር ያልቻሉ ሰዎች ቀለብ የመስጠት ግዴታ ከተጣለባቸው ዘመዶቻቸው ቀለብ መጠየቅ እንደሚችሉ ግንዛቤ መውሰድ ይቻላል፡፡ እንዲሁም ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለበት ሰው ቀለብ ለማቅረብ የሚችል መሆኑ ለቀለብ መስጠት ግዴታ ተፈፃሚነት ጠቃሚ ነው፡፡
በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 197 መሰረት ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለበት ሰው እንደ ባለጉዳዮቹ ሁኔታ እና እንደ አካባቢው ልማድ የሚስማማውን በመከተል ለቀለብ ተቀባዩ ምግብ፣መኖሪያ፣ልብስ፣ጤናውን የሚጠብቅበትና እንደሁኔታው ለትምህርት አስፈላጊ የሆነውን ነገር መስጠት አለበት፡፡ይህም የሚያመለክተው ቀለብ የሚሰጠው ለመኖር አስፈላጊ የሆኑ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ብቻ ለማሟላት እንጂ የቅንጦት ፍላጎቶችን እንደማያካትት ነው፡፡
ቀለብ የማቅብ ግዴታ በቀጥታ የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዳሞች መካከል ያለ ሲሆን በባል ወይም በሚስት፣በቀጥታ ወላጆችና ተወላጆች እንዲሁም በወንድማማቾች እና በእህትማማቾች መካከል ግዴታ አለ(አንቀፅ 49 እና 198/1/2 )፡፡ በተያያዘም አንቀጽ 199 በጋብቻ ለሚፈጠር ቀለብ የመስጠት ግዴታ የሚቀርበትን ሁኔታ አስቀምጧል፡፡ ይህም ጋብቻው የፈረሰው በሞት ምክንያት ካልሆነ በስተቀር፤ በጋብቻ ዘመዳሞች መካከል ያለው ቀለብ የመስጠት ግዴታ ቀሪ ይሆናል፡፡
ምንም እንኳን እንቀፅ 198/1/2 ስር በግልፅ ባይደነገግም አንደ ሁኔታው በጉዳፈቻ አድራጊ እና ተደራጊ መካከል ግዴታው ይኖራል፡፡ምክንይቱም በተሸሻለው የቤተሰብ ህግ እንቀፅ 181 መሰረት የጉዲፈቻ ልጅ በማናቸውም ረገድ ቢሆን እንደ ጉዲፈቻ አድራጊው ልጅ ስለሚቆጠር በወላጅ እና በተወላጅ መካከል የሚኖረው ቀለብ የማቅረብ ግዴታ በጉዲፈቻ ቤተሰብም ተፋፃሚ ይሆናል ማለት ነው፡
የጉዲፈቻ ግንኙነት በሚኖር ጊዜ በመሰረቱ በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 212(1) እንደሚያትተው የጉዲፈቻ ልጅ፣ ባል ወይም ሚስትና የቀጥታ ጋብቻ ተወላጆች የጉዲፈቻ አድራጊው ቤተዘመዶች ቀለቡን መስጠት በማይችሉበት ሁኔታ ካልተገኙ በስተቀር፤ የሥር ወላጆቹን ቤተዘመዶች ቀለብ መጠየቅ አይችሉም፡፡
እንዲሁም ንዑስ አንቀጽ ሁለት የቀደምት ቤተሰቦቹ ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆች ቀለብ ለማግኘት ከዘመዶቻቸው አንዱን ለመጠየቅ የማይችሉ ካልሆነ በስተቀር በጉዲፈቻ የሰጡትን ልጅ ቀለብ ሊጠይቁት አይችሉም በማለት ያትታል፡፡
በአጠቃላይ በህጉ ቀለብ የማስጠት ግዴታ የተጣለባቸው ዘመዳማቾች ከላይ የተገለፁት ብቻ ስለሆኑ ሰዎች ከአጎት ፣ከአክስት፣ከአጎት ልጅ ወይም ከሌላ ዘመዶቻቸው ቀለብ መጠየቅ አይችሉም ማለት ነው፡፡
በመሰረቱ(as a rule) ቀለብ የመስጠት ግዴታ የሚፈፀመው ቀለብ ሰጪው ለቀለብ ተቀባዩ ገንዘብ በመስጠት ሲሆን የቀለቡ መጠን የሚወሰነው ቀለብ ጠያቂው ያለበትን ችግር እና የቀለብ ሰጪውን አቅም በማመዛዘን ነው፡፡እንዲሁም ቀለብ ሰጪው ቀለብ ተቀባዩን በመኖሪያ ቤቱ በማኖር ግዴታውን ሊፈፅም የሚችል ሲሆን የቀለቡ መጠን ወይም ስለ ቀለብ ተቀባዩ መኖሪያ የተሰጠው ውሳኔ በቀለብ ሰጪው ወይም ቀለብ ተቀባዩ በሚያቀርቡት ጥያቄ መሰረት ሊሻሻል (ሊቀነስ ወይም ሊጨመር) ይችላል(አንቀፅ 202 እና 203)፡፡
ለቀለብ የሚከፈል ገንዘብ የቀለብ ተቀባዩ ህይወት መቀጠል እጅግ አስፈላጊ ነው ተብሎ ስለሚታመን ገንዘቡ ሊተላለፍ ወይም ሊያዝ አይችልም፡፡ይሁንና ይህ መርህ ለቀለብ ተቀባዩ ኑሮ አስፈላጊ የሆነውን ነገር ያበደሩ ሌሎች ሰዎችን በተመለከት ተፈፃሚነት አይኖረውም(አንቀፅ 205)፡፡ በተጨማሪም ቀለብ ተቀባዩ ለኑሮው አስፈላጊ መሆኑን ካላረጋገጠ በስተቀር የቀለቡን ገንዘብ መቀበል ካለበት ቀን ጀምሮ በተከታዮቹ ሦስት ወራት ውስጥ ያልተቀበለው ወይም ሳይጠይቀው የቀረ እንደሆነ የተጠራቀመውን ቀለብ እንዲሰጠው መጠየቅ አይችልም፡፡
ለቀለብ ተቀባዩ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው ሰዎች ብዙ የሆኑ እንደሆነ ቀለብ ተቀባዩ ከእነርሱ መካከል አንዱ ቀለቡን እንዲሰጠው ሊጠይቀው ይችላል፡፡ ነገር ግን ቀለብ የመስጠት ግዴታ ካለባቸው ሰዎች አንዱ ሙሉውን የከፈለ እንደሆነ፤ ከፋዩ ራሱን በቀለብ ተቀባዩ ቦታ በመተካት ቀሪ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለባቸውን ሰዎች ወጪውን እንዲተኩለት መጠየቅ ይችላል ሲል የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 208 እና 209 ደንግጓል፡፡
ምንም እንኳን ተገላቢጦሽ(reciprocal) ቀለብ የመስጠት ግዴታ (ልጅ ያሳደጉትን ወላጆቹን በእርጅና ወራት የመጦር፣ባል ሚስቱን ሚስት ባሏን የመንከባከብ ሀላፊነት ወ.ዘ.ተ.) ቢኖርም አንቀጽ 210 የቀለብ ሰጪዎች ተራ ቅደም ተከተል አስቀምጧል፡፡
በዚህም መሰረት ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው ሰዎች ቅደም ተከተል፤
1. ባል ወይም ሚስት
2. ተወላጆች እንደየደረጃቸው(ልጅ፣የልጅ ልጅ፣….)
3. ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆች እንደየደረጃቸው(አባት ወይም እናት፣አያት፣ቅድመ አያት…..)
4. ወንድማማችና እህትማማቾች
5. የጋብቻ ተወላጆች እንደየደረጃቸው(የባል ወይም የሚስት ልጆች፣የልጅ ልጆች…)
6. የጋብቻ ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆች እንደየደረጃቸው ናቸው፡፡(የባለ ወይም የሚስት እናት ወይም አባት፣አያት ቅድመ አያት…)
በተጨማሪም በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 213 ንዑስ አንቅጽ/1 እና 2/ ስር እንደተደነገገው ቀለብ ሰጪው ለቀለብ ተቀባዩ ቀብር ማስፈፀሚያ ወጪ እንዲከፍል የሚገደድ ሲሆን እንዲሁም ይህን የቀብር ማስፈፀሚያ ወጪ ሌላ ሦስተኛ ወገን ከከፈለ ደግሞ በአበዳሪው ቦታ ራሱን በመተካት ባለዕዳው ወጪውን እንዲተካለት መጠየቅ ይችላል፡፡
በመጨረሻም በቀለብ ሰጪ እና ቀለብ ተቀባይ መካከል በሚደረግ ስምምነት፣ቀለብ ሰጪው እራሱን የሚያስተዳድርበት ገቢ ማግኘቱ፣ቀለብ ሰጪው ግዴታውን መወጣት አለመቻሉ፣ጋብቻው በፍቺ ምክንያት ከፈረሰ እና ቀለብ ተቀባዩ በቀለብ ሰጪው ወይም በዚህ ሰው ወደ ላይና ወደታች በሚቆጠሩ ወላጆች ወይም ተወላጆች ወይም ባል ወይም ሚስት ሕይወት ወይም ንብረት ላይ የወንጀል ድርጊት ከፈፀመ ወይም ለመፈፀም ከሞከረ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ቀሪ ይሆናል፡፡
FDRE GENERAL ATTORNEY
የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት የሚሰጥባቸው የአገልግሎት ዓይነቶች
=======================
1. የንግድ ስራ ፈቃድ ወይም የሙያ ፈቃድ ለማደስ ወይም ለመመለስ፣
2. በጨረታ ለመካፈል ወይም ለመሳተፍ፣
3. ለተሸከርካሪዎች ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ዓመታዊ ማዝገባና ምርመራ /ከላውዶ/ ለማድረግ፣
4. የባንክ ብድር ለማግኘት፣
5. ለተሸከርካሪ ቅሪት የመድን ካሳ ለማግኘትና የሰሌዳ ለውጥ ለማግኘት፣
6. የድርጅት ስም ወይም አድራሻ ለመለወጥ፣
7. ጥቅም የሚከፈልበት የካፒታል ሀብት ለማስተላለፍ፣
8. ድርጅት በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለመዝጋት ወይም ዘርፍ ለመቀየር፣
9. የባለቤትነት ስም ምዝገባ የሚያስፈልገውን የንግድ ስራ ሀብት ለመሸጥ ወይም ለማስተላለፍ፣
10. ህጋዊ ህልውና የነበራቸው ድርጅቶች በአንድ ላይ ለማደራጀት ወይም ለማዋሀድ፣
11. የንግድ መደብር ለሌላ አካል በሽያጭ፣በስጦታ፣በውርስ ወይም በመሳሰሉት ለማስተላለፍ፣
12. ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ ግብር ስለመከፈሉ ለተቀጣሪው የሚሰጥ ማረጋገጫ፣
13. የከፍተኛ ትምህርት የወጪ መጋራት ተጠቃሚ በትምህርት ዘመኑ የተጋራውን ወጪ በአገልግሎት ወይም በክፍያ ስለመወጣቱ የሚሰጥ ማረጋገጫ፣
14. ሌሎች ተመሳሳይ አገልግሎቶችን ለማግኘት፣
Source:- Munistry of Revenues
አዋጅ ቁጥር 1185/2012 - የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣ አዋጅ
http://negari.abyssinialaw.com/laws?id=1762
