cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ልዩ መዝናኛ

መዝናኛ ~New music ~Natural picture ~Amazing fact ~Tik Tok ~Loves poem ~Meme FROM LEYU MEZNAGNA @leyumeznagna 🥀

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
179
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ሼር አድርጉ እናት ለዘላለም ትኑር😘😘😍😍😍😍
Show all...
🌹 ፍቅር ብቻ🌹 🌊የወጀቡ ጥግ🌊 🔥ክፍል 5 ✍ደራሲ ሸረፈዲን የእናቱ ልጅ(ምትኩ) . . #እኔ በመፃፍ ልበርታ እናንተ ሼር በማድረግ በርቱልኝ። . . እግሮቿን ብርክ እየያዛቸዉ ነዉ..ሰዉነቷ ቅርዝዝ ብሎባታል ስትራመድ እግሮቿ እርስ በእርስ ይማቱባታል..ደስ ብሏታል ግን ደግሞ ፈርታለች.. ከቀኑ 11 ሰአት ሆኗል...ትእግስት አለምነህን ልታገኘዉ እየሄደች ነዉ..ደርሳ ከላይብረሪዉ በስተጀርባ ማሰስ ጀምራለች..."ፈለግሽኝ እንዴ ቲጂ ምን ልርዳሽ" ቢላት የምትመልሰዉ መልስ የላትም ብቻ ግን እየፈለገችዉ ነዉ...ብዙም ሳትደክም አገኘችዉ..አለምነህ ብቻዉን ተቀምጦ ይፅፋል...ቦታዉ ላይ ሌላ ማንም ሰዉ የለም..ፍፁም ፀፅታ የሰፈነበት ነዉ..ከፊት ለፊቱ በእኩል እርዝመት ችምችም ብለዉ ያደጉ አረንጓዴ ሳሮች ይታያሉ...በስፍራዉ ያሉት ብዛት ያላቸዉ ትልልቅ ዛፎች ንፁህ እና ያልተበከለ አየር እንዲዘዋወር አስተዋፅኦ አድርገዋል...አለምነህ የመረጠዉ ቦታ እራስን ለማዳመጥ ምቹ ነዉ...መንፈስን ያድሳል... ትእግስት አየሩን ደጋግማ ወደ ዉስጧ ማገችዉ...በቀረበች ቁጥር የልብ ምቷ ጨመረ...ዝብርቅርቅ ያለ ድዉታ እና ብዉታ....(ብዉ..ብዉ መልሶ ደግሞ ድዉ...ድዉ) ይላል "ቲጂ ነይ ተቀመጭ እንኳን ወደ ግዛቴ በሰላም መጣሽ" አላት አለምነህ ወረቀቱ ላይ እንደተደፋ...ትግስት አመዷ ቡን አለ ከፉኛ ደነገጠች..ግራ እና ቀኟን ገልመጥ ገልመጥ ብላ ተመለከተችና አማተበች..ልቧ ከድዉታ ወደ መዝለል ተሸጋገረ.. "አለምነህ አስደነገጥከኝኮ" አለችዉ "ይቅርታ በጣም ኮቴሽን ስሰማ አንቺ እንደሆንሽ ስለገባኝ ነው አላት" ካቀረቀረበት ቀና እያለ "ቢሆንስ እንዴ ልቤን ቀጥ አርገሀት ልትገለኝ ነበረኮ"ትግስት ከአለምነህ ጎን ተመቻችታ ተቀመጠች... አለምነህ ደብተሩን አስቀመጠው እና ፈገግ አለላት... "ይሄን ቦታ ለምን መረጥከው..? ዝም ያለ ነው በጣም" "አዎ ዝም ያለ ነገር ይመቸኛል...በጫጫታ ከምናሳልፈዉ 24 ሰዓት ውስጥ ጥቂት ሰዓታትን ቆርሰን እንዲህ ዝም ስንል መንፈሳችን ይታደሳል..ካልተመቸሽ ግን መራመድ እንችላለን" አላት ፍላጎቷን ለማወቅ በሚመስል ሁኔታ ቀና ብሎ እየተመለከታት... "አይ አይሆንም እንዲሁ ተመችቶኛል እንደውም ወደ ግዛትህ እንድገባ የጥገኝነት ጥያቄ እያቀረቡ ነው ትቀበለኛለህ...?" አለችው ፈገግ እያለች "ለቆንጆ ሴቶች አይሆንማ የኔ ግዛት..ትሰለቺያለሽ በዛ ላይ ቤቴ ጠባብ ነው" አላት ሳቅ እያለ... "አላማርርም... ተፈቅዶልኛላ" አለችው ቅብጥብጥ እያለች.. "አንቺን ካልጨነቀሽ በደስታ ነዋ" "እስኪ ስለ አለምነህ ንገረኝ..አለምነህ ማን ነው ብል ማን ነው ትለኛለህ"..ትግስት ጉልበቶቿን እጥፍ አድርጋ አገጯን አስደግፈቻቸው..ፊቷን ወደ አለምነህ አዙራ በአይኖቿ ትከታትለው ጀመር.... አለምነህ አይኖቿን የፈራቸው ይመስል አንገቱን ሰበር አደረገ.. "አለምነህ ምንም የሚነገር ታሪክ የለዉም..አለምነህ የኮምቦልቻ ልጅ ነው.. ወሎ ኮምቦልቻ ስሟን ሲጠሯት ሰምተሻል ይሆናል...ሌላዉ ደሞ አለምነህ የ3ተኛ አመት የcivil ኢንጅነሪንግ ተማሪ ነዉ" አላትና ዝም አለ....አለምነህ እንዲህ ነዉ.. ራሱን ብዙ መግለጽ አይፈልግም ስለ ሰዉ ህይወትም ማወቅ እና መጎርጎር አይፈልግም.... "እእ ወሎ የቆንጆዎች አገር..ብዙ ይዘፈንላችኋል በቁንጅናችሁ" "አንቺም በጣም ቆንጆ ነሽ..እጅግ በጣም ውብ ነሽ" አላት አይን አይኗን እያየ ትግስት ድንብርብሯ ወጣ...አለምነህ ቆንጆ ነሽ ሰላላት ዉስጧ እረክቷል ቆንጆ እንደሆነች ታውቃለች ግን ቃሉ ከአለምነህ አፍ ሲወጣ አቁነጠነጣት...ልቧን ሲሞቃት ተሰማት..ፊቶቿና የእጆቿ የውስጥ መዳፎች ቀሉ...የምትለው የምታደርገው ጠፍቷት እጆቿን ታፋትጋለች... "እእ አላውቅም ነበር አመሰግናለሁ" አለችው.. "ሌሎች ሰዎችም እንደኔዉ እንዳሉሽ አስባለሁ" አላትና ሳቀ "ምንድነዉ የምትጽፈው" አለችዉ..ወሬውን ለማስቀየር የፈለገች ትመስላለች "ዝም ብሎ ሙንጭርጭር ነዉ..ደስ ሲለኝ ሲከፋኝ ዝም ብዬ እፅፋለሁ..,ቤት መታም አልመታም ስሜት ሰጠም አልሰጠም ዝብርቅርቅ ያለዉን ሀሳቤን አሰፍረዋለሁ".. "ኦህ ጥሩ ነገር ነዉኮ ይሄ...ችሎታህን ከማዳበር ባለፈ ጥሩ የህይወት መማሪያ ይሆንሃል በዛ ላይ እያንዳንዱን የህይወትህን ክፍሎች እዚህ ስታስቀምጣቸዉ ትዝታዎችህ ይሆኑሃል...እንደምትፅፍ ቀድሞዉኑም ገምቼ ነበር..በል አሁን እስኪ አንድ ግጥም አንብብልኝ እንደዉም ግጠምልኝ" "ግጥም ትወጂያለሽ...?" አለምነህ ደስ ብሎት ጠየቃት... "አዎ በጣም እንደዉም እንዳቅሚቲ እሞክራለሁ" "በይልኛ ቲጂ..እንደዉም አንቺ ቅደሚ" አለ አለምነህ ያነሳዉን ደብተር መልሶ እያስቀመጠዉ.. ትእግስት ከንፈሯን በምላሷ ሞዠቀችዉና አረጠበችዉ..ሰዉየቷን ወደ አለምነህ አዙራ ተመቻችታ ተቀመጠች.. በህልሜ የማልምህ አልሜም የሳልኩህ፣ አይኖቼ የተራቡህ ልቤ የሚመታልህ፣ ስእልህን ስዬ ጠዋት ማታ ማመልክህ፣ ድርሳን ምደርስልህ ቅኔ ምቀኝልህ፣ አገኘችህ መሰል ሚስኪኗ ሄዋንህ። እቅፍህ ልወሸቅ ዝንት አለም ይሙቀኝ በል እጄ ይሄዉልህ ይዘህ እንዳትለቀኝ። ትእግስት አይኗን ከአለምነህ ላይ ሳትነቅል ያነበነበችዉ ግጥም ነበር..አለምነህ እጅግ ደስ አለዉ..ትእግስትን እያያት ከልቡ ፈገግ አለላት..የሚጨንቀዉ የአለምነህ ዝምታ በትእግስት ስንኞች ተሰበረ...አለምነህ ትእግስትን ፈለጋት...ሊያቀርባት ሁሉ ነገሩን ሊያጋራት ተመኘ..."ግጥምሽም እንዳንቺዉ ቆንጆ ነዉ ተገርሜብሻለሁ አላት በፈገግታ ተሞልቶ... "እዉነት...? በል እሺ ተራዉ ያንተ ነዉ አሁን..ቶሎ በል አፍጥነዉ" አለችዉ እነደመቅበጥ እያደረጋት.. አንቺ ስትመጪ ነገረ አለሙ ዝም ፀፅ ረጭ ይላሉ፣ ሁሉም ባንቺ ዙሪያ ይሽከረከራሉ። ተራራዉ ተንዶ መሬት ይነጠፋል፣ ምድር ያለዉ ሁሉ ስላንቺ ያዜማል፣ ከወደ ሰማይ ቤት ነጋሪት ይጎሰማል፣ መላእክቶች ቁመዉ ያቆላምጡሻል፣ በፍቅር ሰረገላ ወደኔ ይሸኙሻል። ደመናዉን ቀዝፈሽ ጉሙንም በትነሽ፣ ፍቅሬን ብቻ ይዘሽ መዉደድን ሰንቀሽ፣ ትመጪልኛለሽ አምሮብሽ ተዉበሽ። ትእግስ በአለምነህ ግጥም ሰማየ ሰማያት አርጋለች..አይኖቿን ስልምልም እያደረገች አለምነህን በፍቅር ትመለከተዋለች..ከአለምነህ አፍ የሚወጡት ስንኞች በጆሮዋ ተንቆርቁረዉ እዛዉ አልቀሩም...ታንቡሯን ጥሰዉ አልፈዉ ልቧን ሲያሞቋት ልቧን ሲያረጥቧት ይሰማታል...በዉስጧ ባላቆመ ስትል ተመኝታለች...አለምነህ አነብንቦ እንደጨረሰ የትእግስት ጭብጨባ ተቀበለዉ... "አለምነህ ምንም ማለት አልቻልኩም ስላወቅኩህ ደስ ብሎኛል" አለችዉ አይኖቿን ከአይኑ ላይ ሳትነቅል... "አመሰግናለሁ እኔም ስላወቅኩሽ ደስ ብሎኛል" አላት አለምነህ ከአይኖቿ ለመሸሽ እየሞከረ.. "ሁሌም ትገጥምልኛለሃ..ማለቴ ታነብልኛለህ..?" ትእግስት ፊቷን አሳዛኝ አድርጋዉ በልምምጥ ጠየቀችዉ... "ሁለታችንም እንገጥማለን በሚለዉ ይስተካከል...እኔም እንድታነቢልኝ እፈልጋለሁ" አላት ፈገግ ብሎ.. "ተስማምተናል..እሺ አሁን ላዉንች እራት ልጋብዝህ..እንደማስበዉ ከሆነ አልበላህም..እኔም እርቦኛል" ትእግስት ዉስጧ እየቦረቀ ነዉ... "አዎ አልበላሁም..
Show all...
​​የማይቋጥረዉ የማይፈታዉ ምንም ነገር ሊኖር አይችልምና...](https://t.me/joinchat/UVDSxnieQg-2OsJO) እኛ ብንቆምም ጊዜዉ አይቆምም ይቆጥራል (እሮብ..ሀሙስ..አርብ...ቅዳሜ..) የትእግስት የዶርም አጋሮች ሁሉም ገብተዋል..ጭር ያለዉ ክፍል ደምቋል..ዝም ያለዉ ክፍል ጫጫታ በርትቶበታል...በመጡላት አጋሮቿ ምክንያት ብቻዋን ማዉራት አቁማ ከእነሱ ጋር ማዉራት ጀምራለች። ዉስጧ ግን ዝም ብሏል..አለምነህ አሳስቧታል ከዛም በላይ ናፍቋታል...ነገር ግን አለምነህን ልታገኘዉም ሆነ ልታየዉ አልቻለችም።.. 4 ቀን ሙሉ ሳትሰለች ጠብቃዋለች..ደከመኝ ሳትል ግቢዉን አስሳለች..አለምነህ ግን በድንገት ተሰወረ...ለተቸገሩ የሚደርስ ከሰማይ ቤት የሚወርድ ታዛዠ መላእክ ወይስ ድንገት ታይቶ የሚሰለብ ደግ እና ቆንጅዬ ሰይጣን..? እለተ ቅዳሜ ምሽት 12:45 ላይ ትእግስት ከሶስት ቀን በፊት ካወቀቻት የዶርም ጓደኛዋ ቤተልሄም(ቤቲ) ጋር ሁነዉ ከግቢ ዉጪ መመገብ ስላሰኛቸዉ ወደ ዉጪ እየወጡ ነዉ... "እያቸዉ ሲያፈጡብን...ይሄ ደሞ እንዴት አባቱ ያምራል!! የዚህማ የባሰ ነዉኮ ሊበላሽ ነዉ መሰል ቡዳ..እረ ሊደፋ ነዉ"...ጓደኛዋ ቤቲ ናት የሚያፈጡባቸዉን ወንዶች እያየች ድምጿን ቀነስ አርጋ ለትእግስት ምታንሾካሽከዉ... ትእግስት ግን ቀልቧ ሌላ ቦታ ነዉ "ተያቸዉ ባክሽ" አለችና ዝም አለች... አይኖቿ ሌላን አይፈልጉም አለምነህን ቢሆን እንጂ...አይኖቿ ሚንከራተቱት ደጉን ሰዉ ፍለጋ ብቻ ነዉ... ወደ ግቢዉ መዉጫ እንደተቃረቡ ትእግስት እርምጃዋን ገታ አድርጋ ቆመች...ደርቃ የቀረች ሁሉ ይመስላል...አይኖቿ የተራቡት አለምነህ ወደ ግቢዉ ለመግባት ID ካርዱን(የተማሪነት መታወቂያዉን) በማሳየት ላይ ነዉ..ወገቡ ላይ ፎጣ ነገር ጣል አርጓል... አዎ አለምነህ እና በዉል የማታዉቃቸዉ ሶስት ወንዶች አጅበዉት እየገቡ ነዉ...ወትሮዉንም እሱን በፍለጋ የተጠመዱት አይኖቿ አለምነህ እንደሆነ ለመለየት ጊዜ አልፈጀባቸዉም... ነፍሷ በደስታ ቦረቀች...የጭንቀቷ ፍርሃት በደስታ ፍርሃት በቅፅበት ተቀየረ...ተጨምቶ የነበረዉ ፊቷ በፈገግታ ተሞላ... "እህ እንሂድ እንጂ ቲጂ" አለቻት የትእግስት በድንገት መሃል መንገድ ላይ መቆም አስገርሟት..ቤቲ አላስተዋለችም እንጂ "ምን አግኝተሽ ነዉ እንዲህ ዉበቱን የደፋብሽ..እንዴት ነዉ ድንገት እንዲህ ፊትሽ የወዛዉ...እንዴት ነዉ እንዲህ ማንፀባረቅ የያዝሽዉ..?" ነበር ልትላት ሚገባዉ... ትእግስት ምንም አልመለሰችላትም ብቻ ወደ አንድ አቅጣጫ እየተመለከተች ፈገግ ትላለች.. "እንሂድ እንጂ ምን ሁነሽ ነዉ" አንድ እጇን ይዛ እየነቀነቀቻት... "ቆይ አንዴ ቤቲዬ" ትእግስት ወደ አለምነህ ገሰገሰች..ምን እየተካሄደ እንዳለ የማታዉቀዉ ቤቲም ከኋላዋ ተከተለቻት... ትእግስት ደርሳ ከአለምነህ ፊት ለፊት ተገተረችበት...አለምነህ የረዳት ቀን እንዳገኘችዉ ንቁዉ እና ጠንካራዉ አለምነህ አልነበረም...ጠይም ፊቱ ግርጥት ብሏል ከናፍሮቹ ደራርቀዋል..ደከም ያለ ይመስላል...ለትእግስት ግን የሚታያት ደግነቱ ነዉ..የሚታያት ቅንነቱ ነዉ.. ዘለሽ ተጠምጠሚበት የሚል ስሜት ተፈታተናት..ለምን ይሄን ሁሉ ቀን ጠፋህብኝ..?ለምን አስጨነከኝ...? ለምን አሰቃየኸኝ...? ልትለዉ ፈለገች..ግን ልቧ የሻተዉን አእምሮዋ ያሰበዉን ለማድረግ መብቱ የላትም...ምንድን ነኝ ብላስ ነዉ ምታደርገዉ...አየር በረዥሙ አስገብታ አስወጣች "ተረጋጊ ትእግስት ተረጋጊ ቲጂ" ስትል በዉስጧ አነበነበች... "ወንድም አለምነህ ድጋሜ ላስቸግርህ ፈልጌ ጠፋህብኝ" አለችዉ ፍልቅልቅ እያለች... "ቲጂ ፈልገሽኝ አጣሽኝ..? ይቅርታ በጣም ትንሽ የግል ጉዳይ ገጥሞኝ ነዉ...ግን ደህና ነሻ" አላት አለምነህ በተራዉ ፈገግ ለማለት እየሞከረ... የአለምነህ ጓደኞች እና ቤቲ ምቾት ለመስጠት አስበዉ ፈንጠር አሉላቸዉ.. "ደህና ነኝ...አለምነህ አመመህ እንዴ..?" "ኖ አላመመኝም እንዲሁ ሌላ ጉዳይ ነዉ..አሁን የምረዳሽ ነገር ይኖራልን" አላት በትህትና "ለጊዜዉ የለም ፈትቼዋለሁ እንደምንም..ግን ድጋሜ ብቸገር የማምነዉ አንተን ነዉ...ላገኝህ የምችልበትን መንገድ ልትነግረኝ አትችልም..? አለችዉ እየተቅለሰለሰች... "ከላይብረሪዉ በስተጀርባ የራሴ የሆነች ቦታ አለችኝ በሊዝ ነዉ የያዝኳት ሁሌም ከ11 ሰአት በኋላ እዛች ቦታ ታገኚኛለሽ" አላት እየሳቀ.. "ከዚህ ሰአት ዉጪ ላገኝህ ብፈልግስ..?" ሌላ ጥያቄ አስከተለች.. "ጓደኞቼን በደንብ እያቸዉ..አስቸኳይ ሲሆን ከእነሱ ለአንደኛዉ ከነገርሻቸዉ መልእክትሽ ይደርሰኛል" "ድጋሜ ከግቢ ብጠፋስ...?" ትእግስት መጠየቋን አላቆመችም.... "ድጋሜ አልጠፋም አታስቢ" ፈገግ ብሎ መለሰላት... "ሰላም አምሽ እሺ አለምነህ...በድጋሚ ስላየሁህ ደስ ብሎኛል" ትእግስት ከዚህ በላይ ልታቆመዉ አልፈለገችም ተሰናብታዉ ወደ ቤቲ ሄደች... ጓደኛዋ ቤቲ የጥያቄ መአት ታዘንብባታለች...ትእግስት ግን ምንም አትመልስም .. "ማናት ባክህ እቺ ቆንጆ ልጅ...አንተማ ድምፅህን አጥፍተህ ስራ ይዘህልን የለ እንዴ" የሹክሹክታ ያህል በጆሮዋ የሚሰሟት የአለምነህ ጓደኞች ድምፆች ነበሩ... ይ.................. ቀ.................... ጥ.................... ላ.................... ል........................ ሀሳብ እና አስተያየታችሁን 😋 👇👇👇👇👇👇👇👇 @Mesfinlov Owner by 👌 Mesfin @Mesfinlov 🌹🍃✨JOIN US 💌SHAER✨🍃🌹 ⚡️ @leyumeznaga ⚡️ 🔥 🌸 😍 ልዩ መዝናኛ 😍🌸🔥
Show all...

🌹ልዩ መዝናኛ 🌹 🌊የወጀቡ ጥግ🌊 🔥ክፍል 4 ✍ደራሲ ሸረፈዲን የእናቱ ልጅ(ምትኩ) . . . የአዉራ ዶሮ ጩኸት የንጋት ዜናን እያበሰረ ነዉ...አዲስ ቀን ተጨምሮናል አዲስ ተስፋ ተሰጥቶናል..ሰማዩ ጥርት ብሎ ለእይታ ማራኪ ነዉ..ለስለስ ያለች ሰዉነት የማታቃጥል የፀዋት ፀሀይ ምድርን ልታበራ ከማህፀኗ ጨረሮቿን አለም ላይ በትናለች..ፍንትዉ ብላ ደምቃ በስተምስራቅ ትታያለች.... እዚህ ጋር ደሞ ሌላ ንጋት ሌላ ፀሀይ የሆነችዉ ትእግስት...ዉበቷ ከአድማስ እስከ አድማስ የሚናኘዉ ትእግስት...በዉበቷ ምድረ አዳምን ብርክ ምታሲዘዉ ትእግስት...ከዶርሟ ወጥታ የሬጅስትራል ጽ/ቤት ፊት ለፊት ቆማለች... ተማሪዎች ለምዝገባ እየተዋከቡ ነዉ እዛ እዚህ ይሯሯጣሉ.. ሬጅስትራሉ በሰዎች ጢም ብሎ ሞልቷል... ትእግስት ምኑን ከምኑ እንደምታደርገዉ ጭንቅ አላት....ለመመዝገብ ከየት እንደምትጀምር እንኳን አታዉቅም...ለእንደሷ አይነት አይን አፋርና ሁሉን ተጠራጣሪ ሴት ደግሞ እጅግ ከባድ ነዉ...የምዝገባ ሂደቶቹ ግቢ ዉስጥ አሰልቺ ከሆኑት ነገሮች መካከል ዋናኛዉ ነዉ..ካፌ ለመመገብ ምትሰለፈዉ ሰልፍ በምን ጣእሙ....ምዝገባዉ ብዙ ሂደቶች አሉት ሂደቶቹ ብቻ ሳይሆኑ የሰራተኞቹም ቸልተኝነት ለተማሪ እንግልት ዋነኛ ተዋንያኖቹ ናቸዉ... ኮስት ሼሪንግ ሙላ ይሉሃል እሱን ሞልተህ ስትጨርስ ዲፓርትመንትህ እላይኛዉ ፎቅ ብረር ይሉሃል..ደረስኩ ጨረስኩ ብለህ እፎይ ስትል ታችኛዉ ፍሎር ተወርወር ይልሃል...በፍጥነት ደርሰህ ተገላገልኩ ስትል 3ተኛ ፎቅ ላይ ዉጣ...ወደ ጎን ሂድ 4ተኛ ፎቅ ላይ ማህተም አስመታ እንዲሁ ሲያሰቃዩህ ይዉላሉ የሆነ ሰአት ላይ ድክም ብለህ ደረጃዉን በደረትህ አየተሳብክ መዉጣት ትጀምራለህ.... በትእግስት ዉበት የተቁነጠነጡ ወንዶች አጠገቧ ሁነዉ ሊረዷት በሚል ምክንያት ከእሷ ጋር ማዉራትን ቢፈልጉትም..እሷን ለማሳቅ ቢሞክሩም ሊቀርቧት ጥረት ቢያደርጉም እሷ ግን ትላንት የረዳትን መንገድ አሳይ መላእኳን ፈለገችዉ...ዝምተኛዉን አለምነህን ድጋሜ ልታስቸግረዉ ፈለገች.... "ደጉን ሰዉ የት ላግኘዉ" ስትል አሰበች.. ወዲያዉ የተኮሳተረዉ ግንባሯ ፈታ አለ..ሳይታወቃት ፈገግ አለች..አለምነህን የት ልታገኘዉ እንደምትችል አዉቃለች..ዛሬም ተማሪዎች ገብተዉ አላለቁም ስለዚህ አለምነህ እንደተለመደዉ እነሱን እየረዳ ነዉ..ወደዛዉ መሄድ አለባት...እግሯን አንቀሳቀሰች አለምነህን ፍለጋ የግቢዉ መዉጫና መግቢያ አመራች... ነፍስን ከስጋ ነጥለዉ ሲፈልጉ ባህር የሚከቱ ሲያሻቸዉ ህዋ ላየ የሚያንሳፍፉ አይኖቿን በቅርብም በሩቅም ላከቻቸዉ።...አይኖቿ አለምነህን ተራቡት..አይኖቿ አለምነህን ፈለጉት..አለምነህ ግን በስፍራዉ የለም። ሀሞቷ ፍስስ ሲል ተሰማት..ሀሳቧ እንደ ጉም ብትንትን አለባት... እዉነት አለምነህ እንዲረዳት ፈልጋ ነዉ..? ወይስ በምክንያቶች የአለምነህን ከጎኗ መሆን ፈልጋዉ ነዉ...? እንጃ ለእራሷም ስሜቷ አልገባትም..ግራ የሚያጋባ ማህበረሰብ ፤ ግራ ሚያጋባ ስሜት ፤ ግራ የሆነ ልጅ.... "ምናልባት ተማሪዎችን ወደ ዶርማቸዉ ሊያስገባ ሂዶ ይሆናል እስኪመለስ ልጠብቀዉ" ስትል አሰበች...ልትጠብቀዉ ወስና ለእይታዋ ምቹ የሆነ ጥላ ቦታ ፈለገች..ወዲህ ወዲያ ስታማትር የጠረጴዛ ቴኒስ የሚጫወቱ ልጆች ያሉበት ስፍራን ምቹ ሆኖ አገኘችዉ... አግዳሚ ወንበሩን ደገፍ ብላ ተቀምጣ አንዴ የቴኒስ ጨዋታዉን ስትመለከት አንዴ ደግሞ ቀልቧን ሰብሰብ አድርጋ አለምነህ ይመጣበታል ብላ ያሰበችዉን አስባም በሀሳቧ የሳለችዉ መንገድ ላይ አይኗን ስትወረዉር ሰአቱ ነጎደ...አለምነህ ግን የለም... ደጉ ሰዉ ሊመጣ አልቻለም... ቴኒስ የሚጫወቱት ልጆች እንድትጫወት ቢጋብዟትም...ተጫዉታ እንደማታዉቅ ገልፃለቸዉ ሌላ ቀን እንደምትሞክር በትህትና ነግራቸዉ አለምነህን በተስፋን መጠበቋን ተያያዘችዉ...አለምነህ ግን ዝር አላለም.. ሰአቱ እየቆጠረ ነዉ 3:00...3:30...4:00...5:00 የምሳ ሰአት ደረሰ ምዝገባዉ ላይ ሳትሳተፍ ሬጅስትራል ጽ/ቤቱ ለምሳ ተዘጋ..ሰራተኞቹ እየተንጠባጠቡ መዉጣት ጀመሩ...ለሷ ግን ይሄ ግድ አልሰጣትም እረ ከነ አካቴዉም ትዝ አላላትም..እየተጨነቀች ያለችዉ ትላንትን ብቻ ስላወቀችዉ ሰዉ ነዉ..የሰአቱ መርፈድ ጉዳዩዋ አልነበረም ብዙ ሰአቶችን ተቀምጣ ስለጠበቀችዉም አልቆጫትም እነዚህ ሁሉ ተራ ትርክሚኪዎች ናቸዉ..ሀሳቧ አለምነህ እና አለምነህ ብቻ ናቸዉ።.. "ለምን ሊቀር ቻለ..? ለምንስ ዛሬ ተማሪዎችን አልረዳም...ክፉ ነገር አጋጥሞት ይሆን..?" ባዶ ጭንቀት ብቻ...ጓደኞቹን አታዉቅ...የዶርሙን መገኛ አድራሻ እንኳን አታዉቅም...ምንድነዉ ማድረግ ያለባት...? ጭንቀቷን ሚያስተነፍስላት ነገር ፈለገች..ፍቱን መድሀኒቷ ደሞ ቀዝቃዛ ዉሃ ዉስጥ መነከር ነዉ...ከተቀመጠችበት ተነሳች ቅርዝዝ እንዳለች ወደ ዶርሟ አመራች..ፍሎሯ ላይ ካሉት ሻወር ቤቶች መካከል አንደኛዉን መርጣ ገባች..የሻወሩን ቁልፍ እስከ መጨረሻዉ አዞረችዉ...ዉሃዉ ሿ..ሿ..ሿ እያለ ከፀጉሯ ጀምሮ በእርቃን ገላዋ ላይ ይፈስ ጀመር...ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም ለመታጠብ... ገላዋን በሳሙና ለመምታት የምታደርገዉም ጥረት የለም...ብቻ ዉሃዉ በገላዋ ላይ ኮለል ክብልል እያለ ይወርዳል...የዉሃዉ ጠብታ ዳሌዋ ላይ እየነጠረ ጭኖቿን እያዳረሰ ቁልቁል ይምዘገዘጋል። ረዘም ላሉ ደቂቃዎች ከዉሃዉ ሳትወጣ ከሀሳቧ ጋር እየሞገተች አሳለፈች...በመጨረሻም ከዉሃዉ ወጥታ ብርዱ እያንዘፈዘፋት ወደ ዶርሟ አመራች...ሰዉነቷን አደራርቃ የምትወደዉን ሽቶ በአፍንጫዋ ማገችዉ...መአዛዉ በአፍንጫዋ ገብቶ ዉስጧን ሲያረሰርሰዉ ተሰማት..ሽቶ ደስታዋ ነዉ...ስትጨነቅም ሆነ ስትደሰት ሽቶ አይለያትም..ዛር እና ዉቃቢ እንዳለባት አሮጊት ሽቶን ታፈቅራለች።... በአንገቷና በደረቷ ሽቶዉን አርከፈከፈችዉና ተጠቅልላ በጎኗ ጋደም አለች...አሁን ትንሽ ቀለል ብሏታል...ቅዝቃዜዉ እያንቀጠቀጣት ቢሆንም የዛለዉ ጉልበቷ ሀይል አግኝቷል...በጭንቀት የተወጠረዉ አእምሮዋም ረገብ ብሏል...ክፍሏን ቃኘት አደረገችዉ...በሚገባ አፅድተዋለች..የተዘበራረቁትን ነገሮች አስተካክላ ሰዉ የሚኖርበት አስመስላዋለች... "እነዚህ ልጆች መች ይሆን የሚመጡት..?" እራሷን ጠየቀች ብቻዋን እንደሆነች እያሰበች "ምናልባት ዛሬ ማታ ይገቡ ይሆናል...ለእራሷ ጥያቄ እራሷዉ መላሽ ሆነች... "አለምነህ ግን ምን ሆኖ ይሆን የጠፋዉ..?" በድጋሜ ጠየቀች የሚመልስላት ያለ ይመስል... "አልመቸዉ ብሎ ይሆናል...እንደዉም ዛሬ ተራዉ አይደለም ማለት ነዉ"...ከጭንቀቴ ይገላግለኛል ያለችዉን መላምት አስቀመጠች...ዙሪያዋን በግድግዳ እና ተደራራቢ አልጋዎች ተከባ እንዲህ ብቻዋን ከራሷ ጋር እየተነጋገረች እንቅልፍ ሸለብ አደረጋት።... ትእግስት ትላንት ላወቀችዉ ሰዉ እንዲህ አጥብቃ መጨነቋ ለምን ይሆን..? ሰዋዊነቱ ዉስጧ ዘልቆ ገብቶ ሰብአዊ ጎኗን ነካት..? ወይስ ወዳዉ ይሆን..? አሁን ላይ እሷንም ብጠይቋት መልሱን አታዉቀዉም...እኔም የማዉቀዉ ነገር የለም ብቻ ግን ጊዜ ይፈታዋል...ጊዜ የማያነግሰዉ የማይሽረዉ...
Show all...