en
Feedback
የቀሲስ ታምራት ውቤ ትምህርቶች

የቀሲስ ታምራት ውቤ ትምህርቶች

Open in Telegram

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን! ይህ ቻናል ቀሲስ ታምራት ውቤ በተለያዩ መንፈሳዊ ጉባያት ያስተማሯቸው ትምህርቶች እየተቀረጹ የሚቀርብበት ነው:: yeneta.info

Show more
902
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+1130 days
Posts Archive
"እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ። ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ። አሮጊቶችዋን እጅግ እባርካለሁ፥ ድሆችዋንም እን
"እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ። ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ። አሮጊቶችዋን እጅግ እባርካለሁ፥ ድሆችዋንም እንጀራ አጠግባለሁ። ካህናቶችዋንም ደኅንነትን አለብሳቸዋለሁ፥ ቅዱሳኖችዋም እጅግ ደስ ይላቸዋል።" መዝ. 131፥13  "ሰሎሞንም፡የእግዚአብሔርን፡ቃል፡ኪዳን፡ታቦት፡ከዳዊት፡ከተማ፡ከጽዮን፡ያወጡ፡ዘንድ፡የእስራኤልን፡ሽማግሌዎችና፡የነገድ፡አለቃዎችን፡ዅሉ፥የእስራኤልን፡ልጆች፡የአባቶቻቸውን፡ቤቶች፡መሳፍንት፥ንጉሡ፡ ሰሎሞን፡ወዳለበት፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ሰበሰባቸው። " 1ኛ ነገ. 8 ፥1

በጾመ ነቢያት ያሉ ሳምንታት ስያሜ እና ትርጓሜ በቤተክርስቲያን እይታ :- አስተምህሮ (አስተምሕሮ) ወቅቱ/ጊዜው፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዘመን አከፋፈል መሠረት ከኅዳር 6 ጀም
በጾመ ነቢያት ያሉ ሳምንታት ስያሜ እና ትርጓሜ በቤተክርስቲያን እይታ :- አስተምህሮ (አስተምሕሮ) ወቅቱ/ጊዜው፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዘመን አከፋፈል መሠረት ከኅዳር 6 ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ 7 ወይም 13 ቀን ድረስ ያለው ወቅት ዘመነ አስተምሕሮ (አስተምህሮ) ይባላል፡፡ አስተምህሮ፡ ቃሉ በሃሌታው “ሀ” (“አስተምህሮ” ተብሎ) ሲጻፍ የቃለ እግዚአብሔር ማስተማሪያ (የትምህርተ ወንጌል) ዘመን ማለት ነው፡፡ ሥርወ ቃሉም “መሀረ – አስተማረ፤ ለመምህር ሰጠ፤ መራ፤ አሳየ፤ መከረ፤ አለመደ” ወይም “ተምህረ – ተማረ፤ ለመደ” የሚለው የግእዝ ግስ ሲሆን፣ ይኸውም የእግዚአብሔር ቸርነቱ፣ ርኅራኄው፣ ትዕግሥቱና የማዳን ሥራው በቤተክርስቲያን በስፋት የሚሰበክበት ጊዜ ነው፡፡ አስተምሕሮ፡ ቃሉ በሐመሩ “ሐ” (“አስተምሕሮ” ተብሎ) ሲጻፍ ደግሞ የምሕረት፣ የይቅርታ ዘመን ማለት ነው፡፡ ሥርወ ቃሉም “መሐረ – ይቅር አለ፣ ዕዳ በደልን ተወ” ወይም “አምሐረ – አስማረ፤ ይቅር አሰኘ፤ አራራ፤ አሳዘነ” የሚለው የግእዝ ግስ ነው፡፡ ዘመነ አስተምሕሮ ስለ እግዚአብሔር ቸርነትና ርኅራኄ፤ እርሱ በደላችንን ሁሉ ይቅር እንደሚለን እኛ ምእመናንም እርስ በእርስ ይቅር መባባል እንደሚገባን ትምህርት የሚሰጥበት ወቅት ነው፡፡ ዘመነ አስተምህ(ሕ)ሮ፡ ዘመነ አስተምሕሮ ስለ እግዚአብሔር ቸርነትና ርኅራኄ፤ እርሱ በደላችንን ሁሉ ይቅር እንደሚለን እኛ ምእመናንም እርስ በእርስ ይቅር መባባል እንደሚገባን ትምህርት የሚሰጥበት ጊዜ ነው፡፡ ይህ ዘመነ አስተምሕሮ ቤተ ክርስቲያን ስለ ልጆቿ ይቅርታ የምትጠይቅበት፤ ምእመናንንም ስለ በደላቸው ይቅርታ የሚጠይቁበት፤ ስለዚህም በስፋት ትምህርት የሚሰጥበት ዘመን ነው፡፡

በጾመ ነቢያት ያሉ ሳምንታት ስያሜ እና ትርጓሜ በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ከኅዳር 13- 19 ያለው ሳምንት ቅድስት በመባል ይታወቃል፡፡ ( ሰንበትን ለቀደሰ ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ማቅረብ እንደ
በጾመ ነቢያት ያሉ ሳምንታት ስያሜ እና ትርጓሜ በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ከኅዳር 13- 19 ያለው ሳምንት ቅድስት በመባል ይታወቃል፡፡ ( ሰንበትን ለቀደሰ ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ማቅረብ እንደሚገባ የሚነገርበት ሳምንት ነው።) ይባላል ወንጌሉ ዮሐንስ ሲሆን ቅዳሴው ኦትናቴዎስ ነው። 1. በሰማይና፡በምድር፡በባሕርና፡በጥልቆች፡ዅሉ፥እግዚአብሔር፡የወደደውን፡ዅሉ፡አደረገ መዝ. 134፥6 2. ስለዚህም፡በሰንበት፡ይህን፡ስላደረገ፡አይሁድ፡ኢየሱስን፡ያሳድዱት፡ነበር፡ሊገድሉትም፡ይፈልጉ፡ነበር። ዮሐ . 5፥16-21

እግዚአብሔር የእስራኤልን ሕዝብ በሙሴ አማካይነት ከፈርዖን የባርነት አገዛዝና ከምድረ ግብፅ የሥቃይ ኑሮ ነጻ አውጥቶ መዓልቱን በደመና ሌሊቱንም በእሳት ዓምድ ከልሎ በአምላካቸው ቸርነት ይደረግላቸው
እግዚአብሔር የእስራኤልን ሕዝብ በሙሴ አማካይነት ከፈርዖን የባርነት አገዛዝና ከምድረ ግብፅ የሥቃይ ኑሮ ነጻ አውጥቶ መዓልቱን በደመና ሌሊቱንም በእሳት ዓምድ ከልሎ በአምላካቸው ቸርነት ይደረግላቸው የነበረውን ያን ኹሉ የተራዳኢነት ተልእኮ ይፈጽምላቸው የነበረዉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነበር። "እግዚአብሔርም፡ሙሴን፡እንዲህ፡ብሎ፡ተናገረው፦ኺድ፥ለአብርሃምና፡ለይሥሐቅ፡ለያዕቆብም፦ለዘርኽ ፡እሰጣታለኹ፡ብዬ፡ወደማልኹባት፡ምድር፥ወተትና፡ማርም፡ወደምታፈስሰው፡ምድር፡አንተ፡ከግብጽ፡ምድር፡ካወጣኸው፡ሕዝብ፡ጋራ፡ከዚህም፡ውጣ። አንገተ፡ደንዳና፡ሕዝብ፡ስለ፡ኾንኽ፡በመንገድ፡ላይ፡እንዳላጠፋኽ፡እኔ፡ ባንተ፡መካከል፡አልወጣምና፡በፊትኽ፡መልአክ፡እሰዳ፟ለኹ። " ዘጸ. 33፥ 1-3

አባትን ደስ ማሰኘት የሚቻለው ፈቃዱን በመፈጸም ነው:: "እወደዋለሁ " በማለት ብቻ ደስ ማሰኘት አይቻልም። ጌታችን አባቱን ደስ ማሰኘት የቻለው የአባቱን ፈቃድ በመፈጸም ነው:: ዮሐ. 4፥34 ጥያቄው
አባትን ደስ ማሰኘት የሚቻለው ፈቃዱን በመፈጸም ነው:: "እወደዋለሁ " በማለት ብቻ ደስ ማሰኘት አይቻልም። ጌታችን አባቱን ደስ ማሰኘት የቻለው የአባቱን ፈቃድ በመፈጸም ነው:: ዮሐ. 4፥34 ጥያቄው የእኛስ ፈቃድ ምንን መፈጸም ነው? ልጆቹ ተብለን ምን ፈጽመናል ? ሰዎች እና እግዚአብሔር በእኛ ምን ያህል ደስተኞች ናቸው? የሚለው ነው። ምላሹም ለእያንዳንዳችን የተተወ ነው።

አንድ ሰው እንዲህ አለ፦ ሴቶች የተቀበሉትን ነገር ለውጠው አብዝተው እንጂ የሰጠሃቸውን እንዳለ መመለስ ተፈጥሯቸው አይፈቅድም። ሴት ዘር ስትሰጣት ልጅ ትሰጥሃለች፤ ቤት ብትሰጣት ኑሮ ትሰጥሃለች፤ አስቤዛ ብትሰጣት ምግብ ትሰጥሃለች፤ ነገር (ጭቅጭቅ) ከሰጠሃት ደግሞ . . . "If you don't like what you are getting, change what you are giving" መምረጥ የእያንዳንዱ ፈንታ ነው።

ሎጎስ በማህበራዊ ጉዳዮች የማማከር አገልግሎት በቅድመ ትዳር፣ በድኀረ ትዳር እና የልጆች አስተዳደግ የትምህርትና የምክክር ፕሮግራም ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል። መሳተፍ የምትፈልጉ ከላይ በተዘ
+2
ሎጎስ በማህበራዊ ጉዳዮች የማማከር አገልግሎት በቅድመ ትዳር፣ በድኀረ ትዳር እና የልጆች አስተዳደግ የትምህርትና የምክክር ፕሮግራም ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል። መሳተፍ የምትፈልጉ ከላይ በተዘረዘሩት አማራጮች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን

ሎጎስ በማህበራዊ ጉዳዮች የማማከር አገልግሎት በቅድመ ትዳር፣ በድኀረ ትዳር እና የልጆች አስተዳደግ የትምህርትና የምክክር ፕሮግራም ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል። መሳተፍ የምትፈልጉ ከላይ በተዘ
+1
ሎጎስ በማህበራዊ ጉዳዮች የማማከር አገልግሎት በቅድመ ትዳር፣ በድኀረ ትዳር እና የልጆች አስተዳደግ የትምህርትና የምክክር ፕሮግራም ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል። መሳተፍ የምትፈልጉ ከላይ በተዘረዘሩት አማራጮች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን

ዔሊ | ጃንደረባው ሚድያ | ጥቅምት 2016 ዓ.ም.| ✍🏽 ቀሲስ ታምራት ውቤ እንደጻፉት ከጌታ እግዚአብሔር ጋር የተዋሐዶ ሕይወትን መኖር የሚፈልግ ስብከት ከመስማት፣ መጽሐፍ ቅዱስና አዋልድ መጻሕፍ
ዔሊ | ጃንደረባው ሚድያ | ጥቅምት 2016 ዓ.ም.| ✍🏽 ቀሲስ ታምራት ውቤ እንደጻፉት ከጌታ እግዚአብሔር ጋር የተዋሐዶ ሕይወትን መኖር የሚፈልግ ስብከት ከመስማት፣ መጽሐፍ ቅዱስና አዋልድ መጻሕፍትን ከማንበብ በማያንስ ደረጃ ማንበብ ያለበት ሌላ ትልቅ መጽሐፍ አለ፤ ፍጥረት! የተሰጣቸው ግዕዛን ከጌታ እግዚአብሔር ጋር ደረጃው ከፍ ያለ ግንኙነት ላጎናፀፋቸው መላእክትና ሰው ጌታ እግዚአብሔር በፍጥረት ጭምር ሀልዎቱንና ባሕርይውን ከእነርሱም ምን እንደሚጠብቅ ይተርክላቸዋል፡፡ ሰው ፍጥረትን በአምስቱ የአፍአና በአምስቱ የውስጥ ሕዋሳት የመረዳት፣ የመተርጎምና የመተረክ ጸጋ ተሰጥቶታል። በዚህ ጸጋችን ተመርተን ከላይ ስሟ በተጠቀሰ እንስሳ የተቀመጠልንን ምሳሌ እንመርምር። አንድ መጽሐፍ ስመለከት የምድር ፍጥረት በአጠቃላይ ዔሊ ከምድር ገጽ እንድትጠፋ አድማ ያደርጋሉ። ስብሰባው ሲበተን ከመካከላቸው አንዱ ሀገር አማን ብላ ሣር የምትግጠዋን ዔሊን ያገኛትና እርሷን ለማጥፋት ውሳኔ ከተላለፈበት ስብሰባ መምጣቱን ይነግራታል፡፡ ዔሊ ምንም ጥፋት ሳይኖርባት ይህ በመወሰኑ በመገረም "ለመሆኑ ስብሰባው ላይ ማን ማን ነበረ?" ስትል ትጠይቃለች። ወሬ ነጋሪውም ማንም የቀረ እንዳልነበርና ውሳኔውም በሙሉ ድምፅ መጽደቁን ያረዳታል (አይ ድምፅi ከድምፅ አልፈው ቃል ጋር መድረስ ያልቻሉ መገለጫቸው ይህ ነው፤ ሀሳብ አልቦ ድምፅ ብቻ መሆን፤ ያለ ቃል ማሰብ አይቻልም፤ ያለ ቃል ሀሳብ አይገለጥም)። ዔሊ ትንሽ ከተከዘች በኋላ "ለመሆኑ ስብሰባው ላይ የፍጥረታት ባለቤት እግዚአብሔር ነበር?" ስትል ያልጠበቀውን ጥያቄ ለወሬ ነጋሪው አቀረበች። እርሱም ሳያመነታ "አይ እርሱስ የለም፤ አልተገኘም፤ አላየሁትም " በማለት በርግጠኝነት ሲመልስ ዔሊ "እንግዲያውስ ተዋቸው!" ብላ ሣር ወደ መጋጧ ተመለሰች። ሙሉውን ያንብቡ

Repost from Janderebaw Media
+ ገበያው + | ጃንደረባው ሚዲያ | መስከረም 2016 ዓ.ም.| ✍🏽 ቀሲስ ታምራት ውቤ እንደጻፉት ብዙዎች ኪራዩን በማይደፍሩት በታላቁ ገበያ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ዋጋ የከፈለ አንድ ሰው እጅግ የ
+ ገበያው + | ጃንደረባው ሚዲያ | መስከረም 2016 ዓ.ም.| ✍🏽 ቀሲስ ታምራት ውቤ እንደጻፉት ብዙዎች ኪራዩን በማይደፍሩት በታላቁ ገበያ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ዋጋ የከፈለ አንድ ሰው እጅግ የከበሩ የሥጦታ ዕቃዎችን ይዞ ተቀምጧል፡፡ ሽማቹ ለሚበላና ለሚጠጣ፣ ለልብስና ለጌጣጌጥ፣ ለተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ቴክኖሎጂ ውጤቶችና ከወደረኞቻቸው ልቀው ለሚታዩባቸው ነገሮች ጊዜያቸውን፣ የመምረጥ ዕድላቸውን፣ ሀሳባቸውን፣ ክብራቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ወዘተ . . . ይሠዋሉ። ለኪሳራ ገበያ ይውላሉ። ጥቂት ብልሆች ግን ዕውቀትን፣ ማስተዋልን፣ ጥበብን ገዝተው ይገባሉ። በአፀደ ሥጋም ሆነ በአፀደ ነፍስ ካሉ ጠቢባን የሕይወት ዘመን ድካማቸውን ይሸምታሉ። ከግሪክ አሰላሳዮች ጥበብን፣ ከሮም ግንበኞች ሥነ ሕንፃን፣ ከአክሱም ደባትር ዜማን፣ ከቪየና ቀማሪያን ረቂቅ ሙዚቃን፣ ከግዮን እስከ ዳኑብ ዥረቶች አቋርጠው ቅኔን ይገዛሉ። ሳያተርፉ ይመለሳሉ። ሙሉውን ያንብቡ