en
Feedback
etrade.gov.et

etrade.gov.et

Open in Telegram

ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS.

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel etrade.gov.et

Channel etrade.gov.et (@etrade_gov_et) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 16 715 subscribers, ranking 6 225 in the Business category and 1 835 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 16 715 subscribers.

According to the latest data from 23 July, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 73 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 July, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Business category.

16 715
Subscribers
No data24 hours
+367 days
+7330 days
Posts Archive
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኢ-ሰርቪስ አገልግሎት በኦንላይን የንግድ ፍቃድ አሰጣጥን ተግባራዊ በማድረጉ በስትራይድ ሽልማት(stride Award) ተሸላሚ ሆነ:: ==================== አዲስ አበባ 21/09/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) ሳይንስ በር ይከፍታል፤ቴክኖሎጂ ያስተሳስራል ፈጠራ ወደ ፊት ያራምዳል በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ስትራይድ ኢትዮጵያ ኤክስፖ (STRIDE Ethiopia 2024 Expo) ማጠቃለያ መድረክ ላይ የተሻለ የዲጂታል አሰራር የተገበሩ ተቋማት የስትራይድ ሽልማት(Stride Award) ተሸልመዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ የመንግስት ተቋማቱ የዲጂታል ኢትዮጵያን ግንባታ እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በብቃት በመስራትና ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት በመዘርጋት ይህ ሽልማት እንደተበረከተላቸው ተናግረዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኢ-ሰርቪስ አገልግሎት በኦንላይን የንግድ ፍቃድ አሰጣጥን ተግባራዊ በማድረግ (Automate Trade License Process) ይህ የዲጂታል አሰራርን የተገበረ ስትራይድ ሽልማት ተሸላሚ ሆኗል። የመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር የኤሌክትሮኒክ ግዥ አሰተዳዳር(ኢጂፒ)ን ተግባራዊ በማድረግ በአጭር ጊዜ ውስጥ የዲጂታል አሰራርን በመተግበር ላሳየው ውጤት በስትራይድ ሽልማት(Stride Award) ዲጂታል አሰራር በተገበሩ ተቋማት ሽልማት ዘርፍ ተሸላሚ ሆኗል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የኮንስትራክሽንን ፍቃድ በኢ-ሰርቪስ በመስጠት የደንበኞቹን እንግልት በመቀነስ እና የዲጂታል አሰራርን በፍጥነት በመተግበር ተሸላሚ ሆኗል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዘንድሮ ባዘጋጀው የስትራይድ ሽልማት ላይ ሶስት ተቋማት ተሸላሚ ሆነዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:-https://www.facebook.com Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

ለኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር መፋጠን የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ነጋዴዎች መረጃ በዲጂታል ቋት ተደራጅቷል =================== አዲስ አበባ 19/09/2016(ንቀትሚ) ለኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር መፋጠን እስካሁን የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ነጋዴዎች መረጃ በዲጂታል ቋት መደራጀቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር አቶ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ። ኢትዮጵያ በ2025 ሀገራዊ አቅሞችን በመጠቀም ፈጠራ የታከለበትና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ዲጂታል ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ስትራቴጂ ቀርፃ እየተገበረች ነው። ስትራቴጂው ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ፣ የአሥር ዓመት የልማት ዕቅድ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ ጋር የተሳሰረ ነው፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር አቶ ገብረመስቀል ጫላ፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ የግልና የመንግሥትን ዘርፎች በማስተሳሰር የዲጂታል ኢኮኖሚ ጉዞን ለማሳለጥ ከሚተገበርባቸው ዘርፎች ውስጥ አንዱ የንግዱ መስክ መሆኑን ገልፀዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ ትግበራ የንግዱን ዘርፍ የዲጂታል ሽግግሩ ዋና ባለቤት ለማድረግ ምቹ ምህዳር እየተፈጠረ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ለዚህም ለረዥም ዓመታት ሲያገለግል የቆየው የኢትዮጵያ የንግድ ሕግ ከሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ጋር ተቃኝቶ መሻሻሉን ተናግረዋል። የንግዱ ማኅበረሰብ የንግድ ፈቃድ ምዝገባን ጨምሮ 16 አገልግሎቶችን በበይነ-መረብ አማካኝነት ባለበት ሆኖ በተቀላጠፈ መልኩ የሚገለገልበት የዲጂታል ቋት ተገንብቶ ወደ ሥራ መግባቱን አክለዋል። ኢትዮጵያም በዲጂታል ዘርፉ በዓለም ተወዳዳሪና ተጠቃሚ ለመሆን የኢ-ኮሜርስ ረቂቅ ስትራቴጂ ማዘጋጀቷን ጠቅሰው፤ በቅርቡ ጸድቆ ወደ ሥራ እንደሚገባም ጠቁመዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሀገራዊ የዲጂታል ሽግግሩን ለማፋጠን በተሰጠው ተልዕኮ መሠረት የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ነጋዴዎችን መረጃ ወደ ዲጂታል ማህደር መመዝገቡን ተናግረዋል። ይህንን ግዙፍ መረጃ ደኅንነቱ በተጠበቀ መልኩ በማከማቸትና በመተንተን ለሀገር ጥቅም ለማዋል በኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ የተገነቡ የዳታ ማዕከላት ሚና ጉልህ ስለመሆኑም አንስተዋል። ፓርኩ በርካታ ወጣቶች ሥራ የሚያገኙበት እና የቢዝነስ ሽግግር አድርገው ኩባንያ የሚፈጥሩበት ማዕከል በመሆኑ ከንግዱ ዘርፍ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው ብለዋል። የንግዱን ዘርፍ ዲጂታል ሽግግርን ከማፋጠን አኳያ የባለሙያዎችና የኅብረተሰቡን የዲጂታል ክህሎት ማሳደግ ላይ እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል። የኔትዎርክ ትስስር መቆራረጥ ሲያጋጥምም ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር እየተሠራ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል ሲል ኢዚአ ዘግቧል ። ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:-https://www.facebook.com Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

የተቀናጀ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ለመፍጠር የሚያስችል የጋራ ስምምነት ተፈረመ። ===================== አዲስ አበባ 07/09/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የተቀናጀ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ለመፍጠር የሚያስችለውን የጋራ ስምምነት ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት ጋር ተፈራረመ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር አቶ ገብረመስቀል ጫላ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሀገሪቷን የንግድ ስራ አመችነት ለማሻሻል ባከናወናቸው በርካታ የሪፎም ስራዎች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው በ2013 ዓ.ም የተጀመረው ኦን ላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ አድጎ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ከ 1.9 ሚሊዮን በላይ አገልግሎቶች ለነጋዴው ህብረተሰብ በኦንላይን መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡ ዛሬ የተፈረመው የጋራ ስምምነት የንግድ መለያ ቁጥር፣ የግብር ደረሰኝ፣ የብቃት ማረጋገጫ የምስክረ ወረቀት፣ ብሔራዊ መታወቂያ እና ሌሎችም ሰነዶችን አውቶሜት በማድረግ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025ን እውን ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑንም ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡ በሚኒስቴር መ/ቤቱ የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ስራ አስፈፃሚ አቶ ጸጋው በለጠ ከኦንላይን የንግድ መዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ጀምሮ ዲጂታላይዜሽን ላይ ተቋሙ እየሰራ ያለው ስራ ኢትዮጵያ ለንግድ ስራ ያላትን አመችነት በከፍተኛ ደረጃ ያሻሽለዋል ያሉ ሲሆን በተደረገው ስምምነት መሰረት ስራዎች በቅንጅት ተሰርተው አውቶሜት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ የንግድ ፈቃድ በአማካኝ በአንድ ቀን ማውጣት ይቻላል ብለዋል፡፡ ስምምነቱ ከፈረሙ ተቋማት ውስጥ የገቢዎች ሚኒስቴር፣የሰነዶች ማረጋገጫ፣ ብሄራዊ መታወቂያ፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ይገኙበታል፡፡

photo content

‼️ ማስታወቂያ‼️ የንድ ፈቃዳችሁን ያላደሱ የአማራ ክልል የሚገኙ ነጋዴዎች በሙሉ፣ የንግድ ፈቃድ ማደሻ ጊዜ እስከ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም የተራዘመ ስለሆነ የሚጠበቅባችሁን የግብር ክሊራንስ በማቅረብ ያለቅጣት የንግድ ፈቃዳችሁን ማደስ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። +++++++++++++++++++++++++ ‼️ NOTICE‼️ To all traders in the Amhara region who have not renewed your business license, we would like to inform you that you can renew your business license without penalty by providing the required tax clearance as the business license renewal period has been extended until SENE 30/2016 E.C. ============================ መጀመሪያው ወር የቅጣት እድሳት ሊያበቃ 6 ቀን ብቻ እንደቀረው ያውቃሉ? ለተጨማሪ ቅጣት ከመዳረጎ በፊት የንግድ ፍቃድዎን እንዲያድሱ እናሳስባለን። ለተጨማሪ መረጃ፡- https://t.me/EthioEoDB/9

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል። ==================== አዲስ አበባ 27/07/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ መጋቢት ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። በዚህም መሰረት ከመጋቢት 28/07/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በስራ ላይ በነበረበት ዋጋ እንዲቀጥል ተወስኗል። ተጨማሪ መረጃዎችን:-- https://t.me/EthioEoDB

የሸማጮች መብትና የነጋዴው ግዴታ ለተጨማሪ መረጃ፡- https://t.me/EthioEoDB

photo content
+2

!! ማስታወቅያ !! አዲስ አበባ 22/06/2016ዓ.ም (የንቀትሚ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በገብያ ቦታ በመገኝት በሰራው የገብያ ክትትልና ቁጥጥር ስራ ምንጩ የማይታወቅ እንዲሁም የጥራት ደረጃቸውን ያላሟሉ አስር ምርቶችን በገብያ ውስጥ ያገኝ በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው አሳሰበ፡፡ በመሆኑም እነዚህን ምርቶች በገበያ ቦታ ማንኛውም ነጋዴ ሆነ ግለሰብ ሲሸጥ ከተገኙ ለክልሎችና ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮዎች እንዲሁም ለሚመለከታቸው የፍትህ አካላት ጥቆማ እንድታደረጉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- https://t.me/EthioEoDB/33

‼️‼️------------------- በዛሬው ይዘታችን ላይ የግል ድርጅትን(sole proprietorship) ማዋቀር ምን ጥቅም እና ጉዳት እንዳለው እንዳስሳለን። ‼️‼️------------------- ተጨማሪ መረጃ :https://t.me/EthioEoDB

የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጠና ስምምነት ትግበራ ማፋጠን ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ነው ================== አዲስ አበባ 12/06/2016 (ንቀትሚ)የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጠና ስምምነት ትግበራን ማፋጠን እና የአፍሪካ የንግድ እና የኢኮኖሚ ትስስርን ማሳደግ በሚል መሪ ሃሳብ ለአምባሳደሮች እና ለዲፕሎማቶች ስልጠና እየተሰጠ ነው። በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መስሪያ ቤት ውስጥ እየተሰጠ ባለው ስልጠና አምባሳደሮች፣ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ዛዲግ አብርሃ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ስልጠናው በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረገውን የግብይት መጠን እና የንግድ ትስስር ለማሳደግ ያለመ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት እንደሚሰጥ ተመላክቷል ሲል ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል፡፡ ተጨማሪ :https://t.me/EthioEoDB

ኦን ላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ሽፋን 89.8 በመቶ ደርሷል። =================== አዲስ አበባ 05/06/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) ባለፉት ስድስት ወራት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና ተደራሽ ለማድረግ በልዩ ትኩረት በተሰራው ስራ ኦን ላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ሽፋን 89.8 በመቶ መድረሱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር አቶ ገብረመስቀል ጫላ ተናግረዋል፡፡ በሀገራችን የንግድ ስራን ለመጀመር የነበረውን አስቸጋሪነት ለመፍታት የተጀመረው ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግት ሽፋን ባለፈው በጀት ዓመት ከነበረበት 57 በመቶ ባለፉት 6 ወራት ወደ 89.8 በመቶ ማድረስ መቻሉን ያስረዱት ሚኒስትሩ ይህም የንግድ ማህበረሰቡ የነበረበትን እንግልት፣ ወጪ እና የጊዜ ብክነት በማስቀረት  የደንበኛ እርካታን ማሳደጉን ገልጸዋል፡፡ በሌላ መልኩ የድህረ ፈቃድ ክትትለና ቁጥጥር ስራው የተሟላ ባለመሆኑና የሚወሰደው እርምጃ የተጠናከረ ባለመሆኑ ፈቃድ ሳይኖራቸው የሚነግዱ፣ ፈቃድ ሳያሳድሱ እንዲሁም  ከዘርፍ ውጪ የሚነግዱ በመኖራቸው በቀጣይ ክትትልና ቁጥጥሩን በማጠናከር አስተማሪ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በግማሽ በጀት ዓመቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ 1,381,938 አገልግለቶች በኦንላይ የተሰጡ ሲሆን ይህ አፈፃጸም ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት አፈፃጸም ጋር ሲነፃጸር የ69 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et fakebook:-https://www.facebook.com/people/Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

ኦን ላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ሽፋን 89.8 በመቶ ደርሷል። =================== አዲስ አበባ 05/06/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) ባለፉት ስድስት ወራት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና ተደራሽ ለማድረግ በልዩ ትኩረት በተሰራው ስራ ኦን ላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ሽፋን 89.8 በመቶ መድረሱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር አቶ ገብረመስቀል ጫላ ተናግረዋል፡፡ በሀገራችን የንግድ ስራን ለመጀመር የነበረውን አስቸጋሪነት ለመፍታት የተጀመረው ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግት ሽፋን ባለፈው በጀት ዓመት ከነበረበት 57 በመቶ ባለፉት 6 ወራት ወደ 89.8 በመቶ ማድረስ መቻሉን ያስረዱት ሚኒስትሩ ይህም የንግድ ማህበረሰቡ የነበረበትን እንግልት፣ ወጪ እና የጊዜ ብክነት በማስቀረት የደንበኛ እርካታን ማሳደጉን ገልጸዋል፡፡ በሌላ መልኩ የድህረ ፈቃድ ክትትለና ቁጥጥር ስራው የተሟላ ባለመሆኑና የሚወሰደው እርምጃ የተጠናከረ ባለመሆኑ ፈቃድ ሳይኖራቸው የሚነግዱ፣ ፈቃድ ሳያሳድሱ እንዲሁም ከዘርፍ ውጪ የሚነግዱ በመኖራቸው በቀጣይ ክትትልና ቁጥጥሩን በማጠናከር አስተማሪ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በግማሽ በጀት ዓመቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ 1,381,938 አገልግለቶች በኦንላይ የተሰጡ ሲሆን ይህ አፈፃጸም ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት አፈፃጸም ጋር ሲነፃጸር የ69 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et fakebook:-https://www.facebook.com/people/Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

https://t.me/EthioEoDB/28 Telegram EoDB (Ease of Doing Business) ‼️‼️------------------- በንግድ ስም እና በድርጅት ስም ምሃከል ያለውን ልዩነት ያውቃሉ? ‼️‼️------------------- ድርጅቶ የሚጠሩበት ስም ለድርጅትዎ ስኬት ወይም ውድቀት ምክያት ሊሆን ይችላል። እርግጥ ነው፣ ድርጅትዎ ስኬታም እንዲሆን ሚና የሚጫወቱ ብዙ ነገሮች አሉ ከነሱም ውስጥ አንዱና ዋነኛው ግን የንግድዎ ስም ነው። የንግድ/የድርጅት ስምዎት የአገልግሎቶት/የምርቶት ተጠቃሚዎች ስለ ድርጅቶት ከሚያስተውሏቸው የመጀመሪያ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነው።

በንግድ ስም እና በንግድ ምልክት መሃከል ያለውን ልዩነት ያውቃሉ? ለተጨማሪ መረጃ፡- https://t.me/EthioEoDB/9

የመጀመሪያው ወር የቅጣት እድሳት ሊያበቃ 1 ቀን ብቻ እንደቀረው ያውቃሉ?  ለተጨማሪ ቅጣት ከመዳረጎ በፊት የንግድ ፍቃድዎን እንዲያድሱ እናሳስባለን። ለተጨማሪ መረጃ፡- https://t.me/EthioEoDB/9 +++==================================================== +++ This is a polite reminder that only 1 day remain till the first month of penalty renewal for the Ethiopian fiscal year expires. If you haven't done, we strongly advise you to renew your business license today to prevent incurring excessive fines and penalties. for more Info :- https://t.me/EthioEoDB/9

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል። ===================== አዲስ አበባ 27/05/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። በዚህም መሰረት ከጥር 28/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በስራ ላይ በነበረበት ዋጋ እንዲቀጥል ተወስኗል። ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et fakebook:-https://www.facebook.com/people/Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade For more info:-