en
Feedback
etrade.gov.et

etrade.gov.et

Open in Telegram

ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS.

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel etrade.gov.et

Channel etrade.gov.et (@etrade_gov_et) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 16 715 subscribers, ranking 6 225 in the Business category and 1 835 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 16 715 subscribers.

According to the latest data from 23 July, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 73 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 July, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Business category.

16 715
Subscribers
No data24 hours
+367 days
+7330 days
Posts Archive
ውድ ደንበኞቻችን የክፍያ ሥርዓታችን ላይ አሁን የቴክኒካል ችግር ተፈትቶልናል። ስለሆነም ክፍያ የተቸገራችሁ ደንበኞቻችን አሁን አገልግሎት ክፍየዎትን በቴሌብር ወይም በንግድ ባንክ ባሉት አማራጮች መጠቀም መክፈል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻልን። እናመሰግናለን። +++ =================================== +++ ‼️ Short Notice‼️ Dear customers, we were experiencing a technical problem with our payment system. But the problem is solved now. Thank You! +++ ================================ +++ ለጠቅላላ መረጃ :- https://t.me/+XJLYynaaOrk3ZGI8

‼️ማስታወቂያ‼️ ውድ ደንበኞቻችን ከ29/02/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለንግዱ ሕብረተሰብ ደህንነት ሲባል "ከመግባትዎ በፊት ማንነትዎን ማረጋገጥ አለብን። በመግቢያ ገጹ ላይ የሚከተለውን ኮድ ያስገቡ" የሚል መልዕክት በስልክዎ ይደርሶታል። በመሆኑም የደረስዎትን ኮድ በማስገባት አግልገሎት ከፖርታላችን ላይ ማግኘት ይችላሉ። መልዕክቱ ካልደረስዎት ወደ አቅራቢያዎት ንግድ ጽ/ቤት እገዛ ማግኘት ይችላሉ። እናመሰግናለን። +++ =================================== +++ ‼️ Short Notice‼️ Dear customers, for the safety of the business community since Nov 08/2024, you have received a message on your phone saying "Before you sign in, we need to verify your identity. Enter the following code on the sign-in page." Therefore, you can request the services from our portal by entering the code you received. If you do not receive the message, you can contact your nearest Trade office for assistance. Thank You! ለጠቅላላ መረጃ :- https://t.me/+XJLYynaaOrk3ZGI8

ውድ ደንበኞቻችን የክፍያ ሥርዓታችን ላይ አሁን የቴክኒካል ችግር ተፈትቶልናል። ስለሆነም ክፍያ የተቸገራችሁ ደንበኞቻችን አሁን አገልግሎት ክፍየዎትን በቴሌብር ወይም በንግድ ባንክ ባሉት አማራጮች መጠቀም መክፈል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻልን። እናመሰግናለን። +++ =================================== +++ ‼️ Short Notice‼️ Dear customers, we were experiencing a technical problem with our payment system. But the problem is solved now. Thank You! +++ ================================ +++ ለጠቅላላ መረጃ :- https://t.me/+XJLYynaaOrk3ZGI8

‼️ ማስታወቂያ‼️ ውድ ደንበኞቻችን የክፍያ ሥርዓታችን ላይ አሁን የቴክኒካል ችግር ገጥሞናል። ስለሆነም የሚመለከታቸው መ/ቤቶች መፍትሔ እንደሚሰጡን በመተማመን በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን። እናመሰግናለን። +++ =================================== +++ ‼️ Short Notice‼️ Dear customers, we are currently experiencing a technical problem with our payment system. Therefore, we ask you to wait patiently, trusting that the concerned organization will give us a solution. Thank You! +++ ================================ +++ ለድጋፍ (for support) @motriHelpBot ወይም ለጠቅላላ መረጃ :- https://t.me/+XJLYynaaOrk3ZGI8

‼️ ማስታወቂያ ‼️ ውድ ደንበኞቻችን የአገልግሎት መስጫ የውስጥ ፖርታላችን በኔትወርክ መቆረጥ ምክንያት ከጠዋት 04፡10 ሰዓት እሰከ 8፡30 ድረስ አገልግሎት እየሰጠን አልነበረም። አሁን ግን ችግሩ የተፈታልን መሆኑን እንገልፃል። ለበለጠ መረጃ for more Info: -https://t.me/EthioEoDB

በ2017 በጀት ዓመት ባለፋት ሶስት ወራት በሀገር አቀፍ ጀረጃ በኦን ላይን 915,098 የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች ተሠጥተዋል፡፡፡ ================ አዲስ አበባ 07/02/2017 ዓ.ም (ንቀትሚ) በ2017 በጀት ዓመት ባለፋት ሶስት ወራት በሀገር አቀፍ ጀረጃ በኦን ላይን 1,000,265 (አንድ ሚሊዮን ሁለትመቶ ስልሳ አምስት) የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን ለመስጠት ታቅዶ 915,098 (ዘጠኝ መቶ አስራ አምስት ሺህ ዘጠና ስምንት) የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን ለመስጠት ተችሏል፡፡ አፈፃፀሙ በሶስት ወራት ከተያዘው እቅድ አንፃር 91.4% መሆኑን የገለፁት የላይሠንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ መስከረም ባህሩ በ2016 በጀት ዓመት ሶስት ወራት ከተሠጠው 464 ሺህ 845 አገልግሎት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን አስረድተዋል፡፡ ሚኒስቴር መ/ቤቱ በስኬት ካከናወናቸው ሥራዎች መካከል አንዱ የሆነው የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት የጊዜና የሀብት ብክነትን በመቀነስ እንዲሁም የተገልጋዮችን እንግልት በማስቀረት ለንግዱ ማህበረሰብ የተቀላጠፈ አገልግሎትን ለመስጠት ያስቻለ ነው፡፡ እንደ መሪ ስራ አስፈፃሚዋ ገለፃ በ2017 በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ጀረጃ በ13 የተለያዮ የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ዘርፎች 2,857,907 (ሁለት ሚሊየን ስምንት መቶ ሃምሳ ሠባት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሠባት) የኦን ላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን ለመስጠት እቅድ ተይዟል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ሽፋንን በ2016 ከነበረበት 89 በመቶ በ2017 በጀት አመት ወደ 100% ለማሳደግ ታቀዶ እየተሠራ እንደሚገኝ መሪ ስራ አስፈፃሚዋ ወ/ሮ መስከረም ባህሩ ገልፀዋል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ t.me/EthioEoDB

በ2017 በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ጀረጃ በኦን ላይን ከ2.8 ሚሊየን በላይ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን ለመስጠት ታቅዷል፡፡ ============== አዲስ አበባ 10/01/2016 ዓ.ም (ንቀትሚ) በ2017 በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ጀረጃ በ13 የተለያዮ የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ዘርፎች 2,857,907 (ሁለት ሚሊየን ስምንት መቶ ሃምሳ ሠባት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሠባት) የኦን ላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን ለመስጠት እቅድ ተይዟል፡፡ ሚኒስቴር መ/ቤታችን በስኬት ካከናወናቸው ሥራዎች መካከል የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት በማዘመን እና ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የንግዱን ማህበረሰብ የጊዜና ሀብት ብክነት እና የተገልጋዮች እንግልት በማስቀረት የተቀላጠፈ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር በተሰራዉ ስራ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ2016 በጀት አመት አፈፃፀም 2,601,711 (ሁለት ሚሊየን ስድስት መቶ አንድ ሺህ ሰባት መቶ አስራ አንድ) የኦንላይን አገልግሎቶች ተሰጥተዋል፡፡ በ2016 በጀት አመት በሀገር አቀፍ ደረጃ የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ሽፋን 89 በመቶ ማድረስ የተቻለ ሲሆን ይህ ውጤት በ2015 በጀት አመት ከነበረበት 57 በመቶ ሽፋን ጋር ሲወዳደር ከፍተኛ ውጤት የተገኘበት መሆኑን የላይሠንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጅራታ ነመራ ገልፀዋል፡፡ እንደ መሪ ስራ አስፈፃሚው ገለፃ በ2017 በጀት አመት በሀገር አቀፍ ደረጃ የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ሽፋንን ወደ 100% ለማሳደግ ታቀዶ እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:-https://www.facebook.com Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/Ethiopian Ministry of Trade& Regional Integration Facebook (https://www.facebook.com/)

ማስታወቂያ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የጫት ላኪነት የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸውን ላኪዎችም ሆነ አዲስ የጫት ላኪነት የንግድ ስራ ፈቃድ ፈላጊዎችን አስመልክቶ በተዘጋጀው የጫት ላኪነት የንግድ ስራ ቅድመ ፈቃድ ብቃት ማረጋገጫ መስፈርት መሰረት ከመስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ ፈቃድ ማውጣት፣የነባር ንግድ ስራ ፈቃድ ዕድሳት እና የማሻሻል አገልግሎቶችን መስጠት ይጀምራል፡፡ በዚሁ መሰረት ላኪዎች አዲስ አበባ ጉርድ ሾላ ሴንቸሪ ሞል አጠገብ ከሚገኘው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የወጪ ንግድ ግብይት የስራ ክፍል በግንባር በመገኘት የተዘጋጀውን መስፈርት በማሟላት አዲስ የቅድመ ፈቃድ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት በማውጣት፣ ነባሩን በማደስ ወይም ማሻሻያ በማድረግ የንግድ ስራ ፈቃዳቸውንም በተመሳሳይ በግንባር በመቅረብ እሰከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲያወጡ፣ እንዲያድሱ ወይም እንዲያሻሽሉ እያሳሰብን ከህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለነባርም ሆነ አዲስ የጫት ላኪነት ንግድ ስራ ፈቃድ ጠያቂዎች የቅድመ ፈቃድ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የመስጠት አገልግሎት የሚቆም መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ማሳሰቢያ ፡የጫት ላኪነት የቅድመ ፈቀድ ብቃት ማረጋገጫ የወሰዱ ላኪዎች የንግድ ስራ ፈቃድ ማውጣት፣ማደስ እና ማሻሻል የሚችሉት የብቃት ማረጋገጫውን ከወሰዱበት ቀን አንስቶ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ብቻ ነው፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር!

ማስታወቂያ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የጫት ላኪነት የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸውን ላኪዎችም ሆነ አዲስ የጫት ላኪነት የንግድ ስራ ፈቃድ ፈላጊዎችን አስመልክቶ በተዘጋጀው የጫት ላኪነት የንግድ ስራ ቅድመ ፈቃድ ብቃት ማረጋገጫ መስፈርት መሰረት ከመስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ ፈቃድ ማውጣት፣የነባር ንግድ ስራ ፈቃድ ዕድሳት እና የማሻሻል አገልግሎቶችን መስጠት ይጀምራል፡፡ በዚሁ መሰረት ላኪዎች አዲስ አበባ ጉርድ ሾላ ሴንቸሪ ሞል አጠገብ ከሚገኘው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የወጪ ንግድ ግብይት የስራ ክፍል በግንባር በመገኘት የተዘጋጀውን መስፈርት በማሟላት አዲስ የቅድመ ፈቃድ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት በማውጣት፣ ነባሩን በማደስ ወይም ማሻሻያ በማድረግ የንግድ ስራ ፈቃዳቸውንም በተመሳሳይ በግንባር በመቅረብ እሰከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲያወጡ፣ እንዲያድሱ ወይም እንዲያሻሽሉ እያሳሰብን ከህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለነባርም ሆነ አዲስ የጫት ላኪነት ንግድ ስራ ፈቃድ ጠያቂዎች የቅድመ ፈቃድ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የመስጠት አገልግሎት የሚቆም መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ማሳሰቢያ ፡የጫት ላኪነት የቅድመ ፈቀድ ብቃት ማረጋገጫ የወሰዱ ላኪዎች የንግድ ስራ ፈቃድ ማውጣት፣ማደስ እና ማሻሻል የሚችሉት የብቃት ማረጋገጫውን ከወሰዱበት ቀን አንስቶ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ብቻ ነው፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር!

‼️ ማስታወቂያ ‼️ የኔትወርክ ችገራች ተፈቶልናል መፍትሔ የሰጠንን መ/ቤት እናመሰግናለን። ውድ ደንበኞቻችን በትግስት ስለጠበቃችሁን አያመሰገንን፣ ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ አገልግሎት መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

‼️ ማስታወቂያ ‼️ ውድ ደንበኞቻችን የአገልግሎት መስጫ ፖርታላችን በኔትወርክ መቆረጥ ምክንያት ከትናንት 3፡00 ሰዓት ጅመሮ አገልግሎት እየሰጠን አይደለም። የውጪና የውስጥ የEtrade ደንበኞቻችን የሚመለከተው መ/ቤት እስኪያስተካክልልን ድረስ በትግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን። ‼️ Notice ‼️ Dear Customers, our E-trade portal has been down since 3:00 local time yesterday due to a network outage. We ask you to wait patiently until the concerned office maintain our Network. for more Info: -https://t.me/EthioEoDB

‼️ ማስታወቂያ ‼️ ውድ ደንበኞቻችን የአገልግሎት መስጫ ፖርታላችን በኔትወርክ መቆረጥ ምክንያት ከትናንት 10፡00 ሰዓት ጅመሮ አገልግሎት እየሰጠን አይደለም። የውጪና የውስጥ የEtrade ደንበኞቻችን የሚመለከተው መ/ቤት እስኪያስተካክልልን ድረስ በትግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን። ‼️ Notice ‼️ Dear Customers, our E-trade portal has been down since 10:00 yesterday due to a network outage. We ask you to wait patiently until the concerned office maintain our Network. for more Info: -https://t.me/EthioEoDB

‼️ ማስታወቂያ ‼️ ውድ ድንበኞቻችን የመልዕክት መላኪያችን ላይ በዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ መዘግየቶች ምክንያት የተወሰኑ አገልግሎቶች ላይ መስተጓጎል የገጠመ ቢሆነም አሁን ችግሩ የተፈታ መሆኑን እናሳውቃለን። ‼️ Notice ‼️ Dear customers, Due to delays in our short Message delivery service for the past two days, some services have been disrupted, but the problem has now been resolved. for more Info: -https://t.me/EthioEoDB

ለ431 የአይሲቲና ዲጂታል ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ ተሰጥቷል ተባለ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ለ431 የአይሲቲ እና ዲጂታል የንግድ ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ መሰጠቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች የ2016 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም እና በ2017 በጀት አመት ዕቅድ ላይ ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)÷ ኢትዮጵያን የዕድገት ጉዞ ለማስቀጠል ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ድርሻ አለው ብለዋል፡፡ ስትራይድ ኢትዮጵያን አጠናክሮ በማስቀጠል ወጣቶች አቅማቸውን እንዲያወጡ መስራት እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል፡፡ በ2016 በጀት አመት የተሰሩ የስታርትአፕና የምርምር ድጋፍ ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ሳይሆን ቴክኖሎጂ አምራች ሀይልም መፍጠር ይጠበቅብናል ነው ያሉት። ከኮርያ መንግስት ጋር በመተባበር በኢኖቤዝ ኬ ኢትዮጵያ በስታርትአፕ ዙርያ ለወጣቶች የተሰጠው ስልጠናና የሚደረገው ድጋፍ እንደ ሀገር በዘርፉ ውጤት ማስመዝገብ የቻለ ነው ተብሏል፡፡ 95 የምርመር ተቋማት ተለይተው በተለያዩ ዘርፍ የሚደረጉ ሀገራዊ ምርምሮችን የመደገፍ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም መገለጹን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡ ስትራይድ ኢትዮጵያ ኤክስፖ 2024፣ ስታርትአፕ ኢትዮጵያ ሀገራዊ መድረኮችን በማዘጋጀት ወጣቶች የመደገፍና የማበረታታት ስራ መሰራቱም ተነስቷል። በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመንግስትና የንግድ አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ከሚሰሩ ስራዎች አንዱ የሆነው የመንግስት የቢዝነስ ፖርታል ላይ በአራት ከተሞች መተግበሩ ለ431 የአይሲቲ እና ዲጂታል የንግድ ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ መሰጠቱ በመድረኩ ተጠቅሷል። Source official page of MiNT

የንግድ ፈቃድዎን በወቅቱ ባሉበት ሆነው በኦንላይን ያድሱ አይዘናጉ!! ================== ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.e
የንግድ ፈቃድዎን በወቅቱ ባሉበት ሆነው በኦንላይን ያድሱ አይዘናጉ!! ================== ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:-https://www.facebook.com Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et

‼️ ማስታወቂያ ‼️ በኢትዮጵያ በጀት ዓመት የምትጠቀሙ የአማራ ክልል ውድ ደንበኞቻችን፣ የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት ጠይቃችሁ እና አገልግሎት ክፍያ በቅጣት የሚያሳያችሁ ድበኞች ቅጣቱ የተነሳ መሆኑን እየገለጽን ክፍያችሁን ዛሬውኑ በንግድ ባንክ ወይም በቴሌብር እንድትከፍሉ እንጠይቃለን። እናመሰግናለን። +++======================================== +++ ‼️ Notice ‼️ Dear customers of the Amhara region who are using the Ethiopian fiscal year, if you have asked for business license renewal service and are showing you the service fee as a penalty, we ask you to pay your payment today without Penalty through a commercial bank or telebirr. Thank you!

በጠረፍ ንግድ አሰራር ዙሪያ ለጠረፍ ነጋዴዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ። ======================= አዲስ አበባ 25/10/2016ዓ.ም (የንቀትሚ) በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች በጂቡቲ በኩል የጠረፍ ንግድ ስራ ለመጀመር በጠረፍ ንግድ አሰራር እና የጉምሩክ የአሰራር ስርዓት ዙሪያ ለጠረፍ ነጋዴዎች እና ባለድርሻ አካላት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል፡፡ በአፋር ክልል ከኤልዳአር፣ አፋምቦ፣ አሳይታ እና ገረኔ ወረዳዎች የጠረፍ ንግድ እንዲነግዱ በአካባቢው ማህበረሰብ ለተመረጡ የጠረፍ ነጋዴዎች ሰመራ ላይ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን በሶማሌ ክልል ደግሞ ከአይሻ፣ ገብለሎ እና አዲጋላ ወረዳዎች ለተመረጡ የጠረፍ ነጋዴዎች ድሬዳዋ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ከስልጠናው ጎን ለጎን ለጠረፍ ነገዴዎቹ የጠረፍ ንግድ ፈቃድ በኦንላይ የመስጠት ስራም ተሰርቷል። ስልጠናው ከTrade Mark Africa/TMA/” ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን በቀጣይም ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለንን የጠረፍ ንግድ ለማሳለጥ በትብብር የሚሰራ ይሆናል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:-https://www.facebook.com Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጠረፍ ንግድ ፈቃድ በኦንላይን መሰጠት ተጀመረ። ======================= አዲስ አበባ 21/10/2016ዓ.ም (የንቀትሚ) በአፋር ክልል ከጁቡቲ ድንበር በ50 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ የሚገኙ የድንበር አካባቢ ነዋሪዎችን በጠረፍ ንግድ ተጠቃሚ ለማድረግ ከ ሰኔ 21 ቀን 2016 ዓ.ም የጠረፍ ንግድ ፈቃድ በኦንላይን ለመጀመሪያ ጊዜ መስጠት ተጀምሯል፡፡ በጠረፍ ንግድ ፈቃድ አሰጣጥ እና የጉምሩክ የአሰራር ስርዓት ዙሪያ ለጠረፍ ነገዴዎች እና ባለድርሻ አካላት ከሰኔ 20-21 ቀን 2016 ዓ.ም በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን ከስልጠናው ጎን ለጎን በንግድ ምዝገባ፣ ፈቃድ እና ድህረ ፈቃድ ኢንስፔክሽን መመሪያ ቁጥር 935/2015 መሰረት መስፈርቱን ለሚያሟሉ የጠረፍ ነጋዴዎች የጠረፍ ንግድ ፈቃድ በኦንላይን እየተሰጠ ይገኛል፡፡ የጠረፍ ንግድ ፈቃድ በኦንላይን የተሰጣቸው በአፋር ክልል ከጂቡቲ ድንበር በ50 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ከሚገኙ የድንበር አካባቢዎች ማለትም ከኤልዳአር፣ አፋምቦ፣ አሳይታ እና ገረኔ ወራዳዎች የጠረፍ ንግድ እንዲነግዱ በአካባቢው ማህበረሰብ ተሳትፎ የተመረጡ ነጋዴዎች ናቸው፡፡ በሶማሌ ክልል ከአይሻ፣ ገብለሎ እና አዲጋላ ወረዳዎች የጠረፍ ንግድ እንዲንግዱ በማህበረሰቡ ተሳትፎ ለተለዩት ነጋዴዎችም ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የጠረፍ ንግድ ፈቃድ በኦንላይን የሚሰጥ ይሆናል፡፡

‼️ ማስታወቂያ‼️ ውድ ድንበኞቻችን ለ1፡30 ያህል ተቋርጦ የነበረው የ 'www.etrade.gov.et' አሁን አገልግሎት መጀመሩን እናሳውቃለን። +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ ‼️ Short Notice‼️ Dear customers, we would like to inform you that the service of 'www.etrade.gov.et', which was interrupted for about 1:30, has now started.