Ethiopia Protestant Mezmur
Open in Telegram
2 ዜና 20 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ❝²¹ ከሕዝቡም ጋር ተማክሮ በሠራዊቱ ፊት የሚሄዱትን፦ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ የሚሉትንም፥ ጌጠኛ ልብስም ለብሰው የሚያመሰግኑትን፥ #ለእግዚአብሔርም_የሚዘምሩትን_መዘምራን_አቆመ። ²² #ዝማሬውንና_ምስጋናውንም_በጀመሩ_ጊዜ_ይሁዳን_ሊወጉ_በመጡት_በአሞንና_በሞዓብ_ልጆች_በሴይርም_ተራራ_ሰዎች_ላይ_እግዚአብሔር_ድብቅ_ጦርን_አመጣባቸው_እነርሱም_ተመቱ።❞
Show more953
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
አልንደላቀቅም - ፀጋን ስትሰጠኝ - ጊዜን አልነሳህም።
አፍታ እንደ ቀረው ሰው - ጉድ ጉድ እላለሁ።
አገልግለኝ ካልከኝ - ዕድሉን ካገኘሁ።
ተንሰፍስፌ ነው - ማገለግልህ.....
😭😭🙌🙌🙌🙌⛈ አድምጡት ይህን መዝሙር 🙌🙌🙌
⭕️ @desyalew_yizemir ⭕️
ኑሮዎን የሚያቀሉ, የህጻናት,የማዕድ ቤት,የውበት፣
የስፖርት,የመኪና,ኤሌክትሮኒክስ ..ደረጃቸውን
የጠበቁ አቃዎቺን ከDillaAmazonMarket ያገኛሉ. አድራሻችን
👇
:- Dilla Noc ህንፃ ግራውንድ ለይ
👉0926877902
✔️ስለ ዕቃወቹ መረጃ እና ቪዲዮዎች ለማየት ቴሌግራማንን ይቀላቀሉ
👉Telegram: https://t.me/dillaamazon
https://t.me/dillaamazon
AdsCash is the #1 marketing network.You can easily earn ETB10000 a day just by working on your phone for 1-2 hours, AdsCash lets regular users make money with social media and friends! https://adscashqmw.buzz/35431194566703/?s=tg
https://open.spotify.com/user/31x5uwejmivwxcxiipdmhziorxsi?si=C0Vq-8FKSlO4FCWz-IP0WA
በspotify መዝሙር ይፈልጋሉ እንግዳውስ ሊንኩል ይንኩና ወደ ውስጥ ይግቡ እናመሰግናለን!
Aman Tesfaye has invited you to join a Blend on Spotify. Join on the Spotify mobile app. https://open.spotify.com/blend/taste-match/5a9134819762d29d?si=XPiwThbFRQS6NPtngzRfNg&fallback=getapp
Aman Tesfaye has invited you to join a Blend on Spotify. Join on the Spotify mobile app. https://open.spotify.com/blend/taste-match/468001a2064c7089?si=dNoRa9U5Q76aAD2vSNGEpw&fallback=getapp
7_Bereket_Tesfaye_ክብር_አለ_Kiber_Ale_በረከት_ተስፋዬ720p_20230601_100943.mp35.10 MB
8_Bereket_Tesfaye_ይወደኛል_Yewedegnal_በረከት_ተስፋዬ720p_20230601_100935.mp37.15 MB
ማንኛውም አካላዊ ከፍታ የሚጠበቀው መንፈሳዊ ከፍታን በማስጠበቅ ነው።እርግጠኛ ሁኑ መንፈሳዊ ከፍታችሁን ማስጠበቅ የማትችሉ ከሆነ የትኛውንም ምድራዊ ከፍታ ልታስጠብቁ አትችሉም።
መንፈሳዊ የሆነውን ሁሉ ከሁሉ በፊት አድርጉት ከሁሉ በፊት ጠብቁት ከሁሉ በፊትህ አሳድጉት።
የእግዚአብሔር ሰው ቃልአብ ታደሰ.
Repost from OLD PROTESTANT SONGS 🇪🇹
❤#ክርስቶስ_ዘላለማዊ_የእግዚአብሔር_ልጅ
==================================
❤"#መገለጥ_የሚጠይቅ_እውነት" ❤
📌""እምቅድመ አለም ከአብ ያለእናት የባህርይ ልጁ የሆነ ድህረ አለም ከድንግል ማርያም ያለአባት በሥጋ የተገለጠ""
📌#ክርስቶስ ከአለም ፍጥረት በፊት ከዘለዓለም ያለ እናት ከአብ የተወለደ (#እግዚአብሔር )
#ኢየሱስ አለም ከተፈጠረ በኃላ የዛሬ 2000 አመት ያለ አባት ከሴት (ከማርያም) የተወለደ (#ሰው) ክርስቶስ ኢየሱስ (God-Man) ነው።
"ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እነደሆነ ይሉታል"?
✍️ስለ ናዝሬቱ ኢየሱስ ማንነት እዉነታው ያለው ከሰው ዘንድ አይደለም። ኢየሱስ ማን እንደሆነ የመግለጥና የማስረዳት ስልጣን ያለው ራሱ ኢየሱስ፥ አብና መንፈስ ቅዱስ ብቻ ናቸው። ጌታ ራሱ ከሰው ምስክርነት አልቀበልም ብሏል። ስለ እርሱ የሚመሰክሩ አብና መንፈስ ቅዱስ ናቸው።
✍️መጽሐፍ ቅዱስ ልጆችሽ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ እንደሚል፥ የጌታ ሐዋርያትም ለዚህ ነገር እኛ ምስክሮች ነን እንዳሉ እኛም ከመንፈስ ቅዱስም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የተማርነውንና የሰማነውን እውነት እንናገራለን እንመሰክራለን።
ማቴዎስ 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ እርሱም፦ እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
¹⁶ ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ።
“ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። እነርሱም። አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት። እርሱም። እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ። #አንተ_ክርስቶስ_የሕያው #እግዚአብሔር_ልጅ_ነህ አለ ። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ ። ” ማቴ 16፡13-)።
✍️ለመሆኑ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ሲባል ምን ማለት ነው ?
ብዙዎች እንደሚያስቡት በሰው ልጆች እንዳለ አባትነት እና ልጅነት አባት ቀዳሚ ልጅ ተከታይ በሚለው ሰዋዊ ስሌት ሳይሆን በመልክ የሚመስለው በባህሪ የሚስተካከለው ማለታችን ነው ዮሐ 1፡1-3 ፤ ዮሐ 10 ፡30 ፤ዮሐ 14፡8-10 ‹‹እኔና አብ አንድ ነን እኔን ያየ አብን አይቷል››፡፡ ልጅነቱም የባህሪ ልጅነት ነው ማለትም ከማንም ያልተቀበለው ማንም የማይወስድበት ዘላለማዊ ልጅነት ነው፡፡
✍️ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአብ ልጅ እንደሆነ ከአብ ጋር አንድ እንደሆነ እና አብ የሚያደርገውን ሁሉ እንደሚያደርግ ለአይሁድ ሲነግራቸው ድንጋይ አንስተው ሊወግሩት በማሰባቸው ጌታችን ስለምን ትወግሩኛላቻሁ ባላቸው ጊዜ ስለመልካም ስራህ አንወግርህም ስለስድብህ ነው ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለማድረግህ ነው ማለታቸው በወንጌል ተመዝግቧል እንግዲህ አይሁድ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ማለቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ገብቷቸዋል ማለት ነው ዮሐ 10፡25-38 ፡፡
ከዚህ ጥቅስ እንደምንረዳው ጌታችን ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ ብሎ መጥራቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ነው/ ሙሉውን የአይሁድ እና የጌታን ንግግር አንብቡት/፡፡
✍️እንደዚሁ በዮሐንስ ወንጌል 5:18 አይሁድ ጌታ ኢየሱስን የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎ ራሱን መጥራቱን ተቃውመው ሊገሉት እንደነበር የእግዚአብሄር ልጅ ነኝ ማለቱ ደግሞ እግዚአብሔር ነኝ ማለቱ እንደሆነ ተረድተውት ሊገሉት እንደሚፈልጉ ተገልጧል ‹‹እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ። እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር።››ዮሐ 5፡18
✍️ስናጠቃልለው ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሎ መጠራቱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተመለከትነው አምላክ/እግዚአብሔር መሆኑን የሚገልጥልን ልጅነቱም ከማንም ያልተቀበለው የባህሪ ልጅነት እንደሆነ እግዚአብሄርንም የሚስተካከልበት ልጅነት በመልክ ሚመስልበት ልጅነት እንደሆነ ልንረዳ ያስፈልጋል፡፡
✍️ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ወይስ ጌታ? ሀይማኖተኞች ያልመለሱት ጥያቄ
ማቴዎስ 22 (Matthew)
41-42፤ ፈሪሳውያንም ተሰብስበው ሳሉ፥ ኢየሱስ፡— ስለ ክርስቶስ ምን ይመስላችኋል? የማንስ ልጅ ነው? ብሎ ጠየቃቸው። የዳዊት ልጅ ነው፡ አሉት።
43-44፤ እርሱም፡— እንኪያስ ዳዊት፡— ጌታ ጌታዬን፡— ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው፡ ሲል እንዴት በመንፈስ ጌታ ብሎ ይጠራዋል?
45፤ ዳዊትስ ጌታ ብሎ ከጠራው፥ እንዴት ልጁ ይሆናል? አላቸው።
📌ሐዋርያው ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈበትን አላማ በመጀመሪያው ምዕራፍ እና በመጨረሻው ምዕራፍ ሲገልጽልን፦
ኢየሱስ በአባቱ እቅፍ ያለ አምላክ የሆነ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ እንደሆነ መጽሐፍ ይነግረናል
👉 ዮሐንስ 1፥18 (አዲሱ መ.ት)
“ከቶውንም እግዚአብሔርን ያየ ማንም የለም፤ ነገር ግን በአብ እቅፍ ያለው አንድያ ልጁ የሆነው አምላክ እርሱ ገለጠው።”
ቀጥሎም...
👉 ዮሐንስ 20 (John)
31፤ ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።
📌ሐዋርያው ዮሐንስ ከወንጌሉ በመቀጠልም በመልእክቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ከአባቱ ዘንድ ተልኮ የመጣ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በተደጋጋሚ ይነግረናል የተላከና የመጣ ካልን ተልኮ ከመምጣቱ በፊትም የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በግልጽ ያስረዳናል
👉1 ዮሐንስ 4 (1 John)
9፤..... #እግዚአብሔር_አንድ #ልጁን_ወደ_ዓለም_ልኮታልና።
👉1 ዮሐንስ 4 (1 John)
10፤ #እግዚአብሔር......
#ልጁን_እንደ_ላከ
👉1 ዮሐንስ 5 (1 John)
20፤ #የእግዚአብሔርም_ልጅ_እንደ #መጣ
ሐዋርያው ጳውሎስም ከሐዋርያው ዮሐንስ ጋር የሚስማማ እውነት ይነግረናል ፦
👉 ገላትያ 4፡4 (ሕያው ቃል)
ነገር ግን እግዚአብሔር የወሰነው ጊዜ ሲደርስ #ልጁን_ልኮ የአይሁድ ወገን ከምትሆን ሴት እንዲወለድ አደረገ
📌ኢየሱስ ክርስቶስ አባቱ አለማትን የፈጠረበት ልጁ እንደሆነ እና እኛንም የተናገረን በእርሱ እንደሆነ እርሱ ኢየሱስ ደግሞ በባህርዩ አባቱን እንደሚመስል ቃሉ ይመሰክርልናል
👉 ዕብራውያን 1 (Hebrews)
2፤ ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም #ዓለማትን_በፈጠረበት_በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤
3፤ እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤
📌ምሳሌ መጽሐፍም ስለ አባትና ልጅ አንዳች ነገር ይጠቁመናል
👉 ምሳሌ 30 (Proverbs)
4፤ ወደ ሰማይ የወጣ የወረደስ ማን ነው? ነፋስንስ በእጁ የጨበጠ ማን ነው? ውኃንስ በልብሱ የቋጠረ ማን ነው? የምድርን ዳርቻ ሁሉ ያጸና ማን ነው? ይህን ታውቅ እንደ ሆንህ፥ #ስሙ_ማን_የልጁስ_ስም_ማን_ ነው?
✍ይሁዳ 1 (Jude)
17፤ እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ቀድሞ የተነገረውን ቃል አስቡ፤
✍2 ቆሮንቶስ 13 (2 Corinthians)
14፤ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።
