2 790
Subscribers
-324 hours
+87 days
+9530 days
Posts Archive
ሰላም ሰላም ዉድ የዩኒቨርስቲያችን ተማሪዎች በሙሉ በያዝነው ዓመት የሚጀምረው የመዉጫ ፈተና በየትምህርት ክፍላችን የሚካተቱና ትኩረት ማድረግ የሚገቡን የትምህርት አይነቶች ስለታወቁ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድናደርግ እናሳስባለን። ከመዉጫ ፈተናው ጋር በተያያዘ በዩኒቨርስቲዉና በተማሪ ህብረት የሚሰጡና የሚሰሩ ስራዎች ስላሉ ሁላችንም ተባባሪ እንድንሆንና በየትምህርት ክፍላችንም የተጠቀሱትን የትምህርት አይነቶች በጋራ እየተረዳዳንና እየተማማማርን እንድንቀጥል እንዲሁም መምህራን ለሚሰጡት ምክረሃሳቦችና የቲቶሪያል ክላሶች ተገቢውን ትኩረት በመስጠት እንድንከታተል እናሳስባለን።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያልን ከመነሀሪያ ጀምሮ ግቢ የሚያደርስ ሰርቪስ (የትራንስፖርት አገልግሎት) የተዘጋጀ መሆኑን እየገለፅን የተማሪዎች ህብረት አመራርም እናንተን ለመቀበል ዝግጅታችን ጨርሰናል።
እንኳን ደህና መጣችሁ!
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያልን ከመነሀሪያ ጀምሮ ግቢ የሚያደርስ ሰርቪስ (የትራንስፖርት አገልግሎት) የተዘጋጀ መሆኑን እየገለፅን የተማሪዎች ህብረት አመራርም እናንተን ለመቀበል ዝግጅታችን ጨርሰናል።
እንኳን ደህና መጣችሁ!
ለወቅታዊ መረጃዎች https://t.me/IUSU1
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያልን
ከመነሀሪያ ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው በተዘጋጀው ሰርቪስ የትራንስፖርት አገልግሎት የተዘጋጀ መሆኑን እንገልጻለን።
እንኳን ደህና መጣችሁ!
አዲናስ!
በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተፈታኝ ተማሪዎች የመኝታ ዶርማችሁን ከታች በተገለጹት አድራሻዎች ማግኘት ትችላላችሁ።
መልካም የፈተና ጊዜ
ለሦስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የመጀመሪያው ዙር ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ፡፡
---------
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የማኅበራዊ ዘርፍ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂ ፈተና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዛሬ መጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ፈተናውን የወሰዱት ከ9ሺ በላይ ተማሪዎች ሲሆኑ ቀድሞ በተደረገላቸው ገለፃ እና አቅጣጫ ስድስቱንም ፈተና በሰላም አጠናቀዋል፡፡
ዶ/ር ጋርዳቸው አያይዘው እንደገለጹት የፈተና ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የፈተና ግብረ ኃይል ኮሚቴዎች፣ ከትምህርት ሚኒስቴር የተላኩ ፈተና አስፈጻሚዎች እና የፀጥታ ኃይሎች በጋራ የመሥራት ውጤት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ፈተናቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ጥቅምት 2 እና 3/2015 ዓ.ም መኪና ተዘጋጅቶላቸው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተሸኙ ሲሆን ጥቅምት 4/2015 ዓ.ም የሚገቡትን የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ተቀብሎ ለማስፈተን ዩኒቨርሲቲው ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቁንም አክለው ገልጸዋል፡፡
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለሁሉም ለተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም ውጤት ይመኛል!
መስከረም 2/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በመጪው 2015 ዓ/ም መጨረሻ ላይ የመውጫ ፈተና መሰጠት ይጀምራል‼️
በ2015 ዓ.ም መጨረሻ መተግበር በሚጀምረው የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዙሪያ ከሰሞኑን የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለአዲስ ዘመን ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።
ሚኒስትር ዴኤታው ካነሳሷቸው ሃሳቦች መካከል ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው
የመውጫ ፈተና ምዘና የሚሰጠው ለመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ብቻ ነው።
በግልም ሆነ በመንግስት የትምህርት ተቋም የሚማር ተማሪ ዲግሪውን የሚያገኘው ምዘናውን ሲያልፍ ብቻ ነው፡፡
የመውጫ ፈተናው የሚዘጋጅበት፣ የሚያዝበት እና የሚሰራጭበት ስርዓት ከሰው ንክኪ ነጻ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
በየዓመቱ ከ150 እስከ 180 ሺህ በመጀመሪያ ዲግሪ የሚመረቁ ተማሪዎችን ምዘና ለመስጠት የሚያስችል አቅም አለ፡፡
የሙያ ማኅበራት አቅማቸው ሲጎለብት የሙያ ፈተና ይሰጣሉ፤ የመውጫ ፈተና ሥራን ከመንግስት ይረከባሉ።
ፈተናውን የሚያሰናዱ ተቋማትና መምህራን ዝግጅት ሥራዎች እስከ ግንቦት 2015 ዓ.ም ይሰራሉ፡፡
የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ግልጸኝነቱ የተጠበቀ ለማድረግ እየተሰራበት ነው።
ለተለያዩ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎች https://telegram.me/IUSU12 join አርጉ።
የSTEM የአሌክትሮኒክስ ቤተ-ሙከራዎች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ፡፡
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ STEM Power ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውሥጥ ለሳይንስ፣ቴክኖሎጅ፣ኢንጅነሪንግ እና ሂሳብ ትምህሮቶች የሚያገለግሉ የቬርቹዋል እና ኤሌክትሮኒክስ ሁለት ቤተ-ሙከራዎችን ስራ አስጀምሯል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አዕምሮ ታደሰ (ዶ/ር) ያደጉ ሀገራት አሁን ያሉበት ደረጃ የደረሱት በሳይንስ ዘርፍ ከፍተኛ ስራ በመስራታቸው መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲው ለዚህ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የኤሌክትሮኒክስ ቤተ-ሙከራዎች ከ STEM Power ጋር በመተባበር ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም በዩኒቨርሲቲው በኩል የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ስለተሟሉ ተማሪዎች በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
የእንጅባራዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝዳንት ወሀቤ ብርሃን(ዶ/ር) ይህ ፕሮግራም እንዲሣካ ከፍተኛ ጥረት ላደረጉ ለተፈጥሮ እና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ እና ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሩክቶሬትን አመስግነው STEM ቤተ-ሙከራዎች ንድፈ ሃሳብን በተግባር ለመስራት የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የSTEM ኦፕሬሽን ማኔጀር የሆኑት አቶ አንተነህ ፍስሃ በበኩላቸው ድርጅቱ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ቤተ-ሙከራዎችን መስራት እና ስለ ቤተ-ሙከራዎቹ አስፈላጊውን ስልጠና በመስጠት ለተለያዩ ተቋማት እንደሚያስረክብ ተናግረው “Inside every child is A scientist'' በሚል መሪ ቃል በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ፣ኢንጅነሪንግ እና ሂሳብ ዘርፎች አተኩሮ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ሐምሌ 25/2014ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
ለተለያዩ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎች https://telegram.me/IUSU12 join አርጉ።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 12/2014 ዓ.ም ዲሽቃ ለሰራው የቀድሞው የዳንግላ ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ትምህርት ቤት ተማሪ ሀብታሙ ጫኔ ዘመናዊ ላፕቶብ ሽልማት አበርክቶለታል፡፡
ሽልማቱን የሰጡት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አዕምሮ ታደሰ( ዶ/ር) እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን( ዶ/ር) ናቸው፡፡
ተማሪ ሀብታሙ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባደረገለት የላፕቶፕ ሽልማት በጣም መደሰቱን ተናግሮ በቀጣይም በአዲስ ፈጠራ ስራ እንደሚሰራ ተናግሯል፡፡ ተማሪው በአሁኑ ሰዓት ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በመማር ላይ ነው፡፡
ለ2014 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎች ገለፃ ተደረገ::
ግንቦት 12/2014፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በ2014 ዓ.ም ወደ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ስላሉ ህግና ደንቦች ላ ያተኮረ ገለፃ ተደርጓል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ዲን የሆኑት ጌታየ ሙሉጌታ እንደገለጹት ገለፃው ዩኒቨርስቲው በዚህ ዓመት ለተቀበላቸው አዲስ ተማሪዎች መሆኑን ጠቅሰው ትምህርት ከመጀመራቸው በፊት ስለ ተማሪዎች ምግብ እና መኝታ አጠቃቀም፣ ስለ ሬጅስትራር እና የቤተ መጽሐፍት አገልግሎት እንዲሁም የመጀመሪያ ዓመት ትምህርት ፕሮግራሞችን የተመለከተ ሲሆን በአጠቃላይ በግቢ ቆይታቸው ስለሚኖራቸው እንቅስቃሴ ያተኮረ ገለፃ መሰጠቱን አስረድተዋል፡፡
ዲኑ አያይዘውም ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ በስኬት እንዲያጠናቅቁ እና የዩኒቨርሲቲውን ህግ ደንብ በማክበርና መብትና ግዴታቸውን እንዲወጡ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
#እንጅባራ_ዩኒቨርሲቲ
