en
Feedback
Injibara University Student Union

Injibara University Student Union

Open in Telegram
2 790
Subscribers
-324 hours
+87 days
+9530 days
Posts Archive
የሀዘን መግለጫ😭 ============ ተማሪ ተሾመ በሪሁን መኩሪያው የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዓመት የህግ ተማሪ የነበረ ሲሆን ቤተሰቦቹ ጋር በሄደበት ባደረበት ህመም ምክንያት ሚያዚያ 21/20
+1
የሀዘን መግለጫ😭 ============ ተማሪ ተሾመ በሪሁን መኩሪያው የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዓመት የህግ ተማሪ የነበረ ሲሆን ቤተሰቦቹ ጋር በሄደበት ባደረበት ህመም ምክንያት ሚያዚያ 21/2015 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል። እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት በተማሪ ተሾመ በሪሁን ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ፣ ለጓደኞቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ይመኛል። ነፍስህ በአፀደ ገነት ትረፍ!!!

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት በዚህ አመት ሊሰጥ በታሰበው የመውጫ ፈተና ዙርያ በስሙ የተሰራጨው መረጃ ህብረቱን የማይወክል መሆኑንን አስታወቀ። *********************************** የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት በቅርቡ በስሙ በተሰራጨው መረጃ ዙርያ በትላንናው እለት መጋቢት 09/2015 ዓ.ም መግለጫ አውጥቷል። የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናን በተመለከተ በአስፈላጊነቱ ዙርያ ሁሉም ያመነበት ነው ሲል የገለፀው መግለጫው ፈተናው ስለሚሰጥበት ጊዜና ሁኔታ ላይ የተለያዩ ሀሳቦች ሲሰነዘሩ መቆየቱን አውስቶ ፈተናው ተማሪዎችን ባማከለ መልኩ በዚህ አመት እንዲስጥ የተወሰነ በመሆኑ ተማሪዎች በሚያነሷቸው ስጋቶች እና ቅሬታዎች ላይ ከትምህርት ሚኒስተር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መጠነ ሰፊ ውይይቶች መደረጋቸውን እንዲሁም ወደፊትም እንደሚደረጉ ተገልጿል። በውይይቶቹ የተነሱ ሀሳቦች ገሚሶቹ ምላሽ ያገኙ ቢሆንም በቀጣይም በውይይት ዳብረው የሚስተካከሉ መረጃዎችን የሚያሳወቅ መሆኑንን የገለፀው ህብረቱ፤ ፈተናው የተማሪዎችን ብቃት የሚመዝን እና የተነሱ ጥያቄዎችን ያገናዘበ እንዲሆን ብሎም የሀገሪቱን የትምህርት ጥራት ሊያስጠብቅ በሚችልበት ሁኔታ ላይ አሁንም በጋራ እየሰራ መሆኑን አስታውሷል። ተማሪዎች በፈተናው እና በተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ሀሳብ በግቢያቸው ላለው የተማሪዎች ህብረት እያቀረቡ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት በኩል ከትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያየት ምላሽ የሚሰጥበት መሆኑንም ተገልጿል። በቅርቡ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ስም የተሰራጨው መረጃ ፈፅሞ ህብረቱን የማይወክልና ተቀባይነት የሌለው መሆኑን የተገለፀ ሲሆን በህብረቱ በኩል የተጠራ ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፍ ባለመኖሩ፤ ተማሪዎች በተለይም የዚህ አመት ተመራቂዎች በተረጋጋ መንፈስ በቅርብ በተሰራጨው የፈተናው ንድፈ ማሳያ(Blueprint) እና የተመረጡ የትምህርት አይነቶች ያሉበት ቁልፍ የብቃት መለኪያ (Core Competencies) መሰረት በማድረግ፤ በተቋሞቻቸውና በህብረቶቻቸው በኩል የሚሰጡ የድጋፍ ትምህርቶችን በመከታተልእርስ በእርስ በመተጋገዝ እንዲሁም በተናጥል በማንበብ ብሎም ከሀሰተኛ መረጃዎች በመጠበቅ በዩንቨርሲቲዎቻቸው ካሉ ህብረቶች፣ ከመምህራን እና ከበላይ አመራሮች ብቻ ትክክለኛውን መረጃ በመውሰድ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ህብረቱ ጥሪ አቀርቧል። በመጨረሻም ህብረቱ የተዛባ መረጃ በማሰራጨት ተማሪዎችን የሚያዘናጉ እና አላስፈላጊ ለሆነ ነገር የሚያነሳሱ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በጥብቅ አሳስቧል። #መረጃው_የኢትዮጲያ_ከፍተኛ_ትምህርት_ተቋማት_ተማሪዎ_ህብረ_የመረጃና_አለም_አቀፍ_ግንኙነት_ዘርፍ ነው

በ2015 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ እያልን ጽዱ፣ ውብ፣ በትምህርት ጥራት ተመራጭ፣ ፍጹም ሰላማዊ የሆነውን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲን የመጀመሪያ ምርጫችሁ አድርጋችሁ እንድትመርጡን እየጋበዝን፣ በዩኒቨርሲቲው የሚስጡ ኮሌጆች፣ 1) ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 2) ግብርና፣ ምግብ እና አየር ንብረት ሳይንስ ኮሌጅ 3) ቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ 4) ቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ 5) ተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ 6) ማህበራዊ እና ሰባዊ ኮሌጅ 7) ትምህርትና ስነ-ባህሪ ኮሌጅ እና 8 የህግ ትምህርት ቤት ናችው፣ ውድ ተማሪዎች ለውሳኔ እንዲረዳችሁ ካላይ በተጠቀሱት ኮሌጆች ስር በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጡትን ዝርዝር ፕሮግራሞች እና ትምህርት ክፍሎችን ከዚህ በታች ማየት ትችላላችሁ፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ምርጫችሁ አድርጉ፡፡ https://www.inu.edu.et/postgraduate-programs https://www.inu.edu.et/undergraduate-programs የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ እና እንግዳ ተቀባይ የእንጅባራ ህዝብ አዲናስ ለማለት ቅድመ-ዝግጀት አጠናቀው ይጠብቋችኃል!!

tew engi bakih...neber nw yemibalew...

ሰላም ሰላም ዉድ የዩኒቨርስቲው የ2ኛ ዓመት የክላስ አካዳሚክ ተወካይና የክላስ ተወካይ የሆናችሁ የተማሪ ተወካዮች አሁን 5:30 ላይ ከአካዳሚክ ካላንደር ጋር በተያያዘ ዉይይት ስለሚደረግ ሴሚናር አዳራሽ እንድትገኙ ስንል በአክብሮት እናሳስባለን።

ሰላም ዉድ የዩኒቨርስቲያችን ተማሪዎች በሙሉ የመማር ማስተማር ስራ ዛሬ ከሰዓት ማለትም ከ28/03/15ዓ.ም ጀምሮ ስለሚጀምር ሁላችሁም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ የከሰዓት ክላስ ያላችሁ ተማሪዎቻችን ወደየክፍ
ሰላም ዉድ የዩኒቨርስቲያችን ተማሪዎች በሙሉ የመማር ማስተማር ስራ ዛሬ ከሰዓት ማለትም ከ28/03/15ዓ.ም ጀምሮ ስለሚጀምር ሁላችሁም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ የከሰዓት ክላስ ያላችሁ ተማሪዎቻችን ወደየክፍላችሁ በመሄድ እንድትገኙ ስንል በአክብሮት እናሳዉቃለን።

@IUSU12 ወደ ሊንኩ ሁሉም ተማሪዎች እንዲቀላቀሉ foreword እናድርግ።

+2
PSIR.pdf1.12 MB

+6
Adult Edu. & Community Devlopment OR in BED.pdf1.38 MB

Validated Competencies for Band VI (Social Science and Humanities)

+6
Accounting_&_Finance,_Identified_Competencies_and_Courses_Copy.pdf1.38 MB

Validated Competencies for Band V (Business and Economics)

+9
Agrbusiness Exit Exam .pdf9.73 KB

Validated Competencies for Band IV (Agriculture)

+8
Biology BSc Exit Exam.pdf1.20 MB

Validated Competencies for Band II (Natural and Computational Science)

+4
Mechanical Engineering.pdf8.86 KB

+9
Architecture.pdf1.01 MB