African Leadership Excellence Academy
Open in Telegram
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ በንድፈ-ኃ
Show more2 789
Subscribers
No data24 hours
+177 days
+10130 days
Posts Archive
የአሻራ እና ሃላፊነትን የመወጣት ሃይል እና የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ትግል ትልቅ ትርጉም እና ፋይዳ
በዛዲግ አብርሃ
👉የምትኖሩት ለራሳችሁ ብቻ ሳይሆን ላልተወለደው ትውልድም ጭምር ነው 1
👍አሻራ በአያቶች እና በልጅ ልጆች መካከል ያለ ድልድይ🌉 ነው
🇪🇹የኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ትግል ለመኖር እንጂ ለማደግ አልነበረም! ይህ ትውልድ ግን ዛሬን ከመኖር አልፎ ለመጪው ጊዜም የሚሆን ጥንካሬ መገንባት አለበት! ካለፉት ትውልዶች የተለየ የሚሆነው እንደዛ ማድረግ ሲችል ብቻ ነው ❗️
ኢትዮጵያ 🇪🇹 በ2100 ዓ.ም ምን ትሆናለች❓
የዛሬ ኢትዮጵያውያን ምን አይነት አሻራ ማኖር አለብን ❓🤔 የሚለው ጥያቄ የተመለሰበት ገለጻ
Facebook: https://web.facebook.com/@aflexacademy.gov.et
YouTube: http://www.youtube.com/@AfricanLeadershipExcellenceAca
TikTok: https://shorturl.at/xxN9x
X (Twitter): https://x.com/Afleexacademy?s=09
LinkedIn: https://shorturl.at/VEGEx
Website: https://aflexacademy.gov.et
Telegram: https://t.me/afleexac
#AFLEXLeadershipChallenge #AFLEXDigitalAmbassador #LeadWithAFLEX
"ኢትዮጵያን ከድህነት አውጥተን ወደ ብልፅግና ለማሸጋገር በምናደርገው ሂደት ውስጥ የመንገድ እና ድልድይ ስራን ከሀገራችን የአንድነትና የማህበራዊ ንቅናቄ ስረ-መሰረት ጋር እያገናኘን በስትራቴጂያዊ እይታ መመልከት አለብን" የሚሉት አቶ ዛዲግ የመንገድ መሰረተ ልማት በባህርይው የሀገር እና የህዝቦች ስልጣኔ የሚፀነስበት ፣ የሚወለድበት እና የሚያድግበት በመሆኑ እድልና ተስፋን በአንድነት የምናገኝበት ዘርፍ እንደሆነም አብራርተዋል::
የመንገድ መሰረተ ልማት የጂኦ-ፖለቲካ መሳሪያ ብቻ ሳይሆን የፍትሀዊነት ማረጋገጫና የእድገት ማሳለጫ እንደሆነና ይህንን የተረዱ እንደ ቻይና እና ሲንጋፖር ያሉ ሀገራት መንገድን እንደ 'ኢምፓየር' እንደገነቡት ያስታወሱት አቶ ዛዲግ "የመንገድ ፖሊሲ የብሄራዊ ስትራቴጂ አካል ፣ መሀንዲሶቹ ደግሞ ብሄራዊ ኩራት ተደርገው ሊወሰዱ ይገባል" ብለዋል::
"የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ማንሰራራት እውን የሚሆነው የሥነምግባር ከፍታ ባላቸው ፣ አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብ በሚያመነጩ እና ስትራቴጂያዊ መሀንዲሶች አማካይነት ነው" ያሉት አቶ ዛዲግ መሀንዲሶች ሀገር ሲገነቡ ህፃናት ወደ ትምህርት ቤት ይሄዳሉ ፣ ምርት ለገበያ ይቀርባል፣ እናቶች ወደ ሆስፒታል ያመራሉ፣ ግንኙነት ይሳለጣል በድምሩ የብሄረ መንግስት እና የሀገረ መንግስት ግንባታ እውን እንደሚሆን በስልጠናው ላይ ተብራርቷል::
አንዲት ሀገር ህልሟ ላይ እንድትደርስና ራሷን ፈልጋ እንድታገኝ መሀንዲሶች ምክንያቶች እንደሚሆኑ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ፣ መንገድ የሚሰራ መሀንዲስ ከሚሰራው መንገድ ባሻገር የሚሊየኖች ሀገር እንዳለች ታሳቢ አድርጎ ማህበራዊ ምስቅልቅሎቻችንን እና መንፈራቀቆቻችንን የሚፈታ ድልድይ እየገነባ መሆኑን ማመን እና መረዳት አለበት ብለዋል::
መሐንዲሶች መከራና ችግርን ተቋቁመው ፣ ሀገርን ባለመንገድ አድርገው ፣ ርዕይን ወደ እውነት መንዝረው ፣ ሚሊዮኖችን ያገናኛሉ" ዛዲግ አብርሃ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 13 ቀን 2017 (አፍሌክስ):- የሀገራችን መሐንዲሶች ባልተመቻቸ ሁኔታ ውስጥ ሆነው በሚከውኗቸው ሙያዊ ተግባራት ፣ መከራና ችግር እንደሚያጋጥማቸውና ይህንኑ ተቋቁመው ሀገራችውን ባለመንገድ እና ድልድይ እያደረጉ የሀገርን ርዕይን በተግባር የሚመነዝሩ እና ሚሊዮኖችን የሚያገናኙ የሀገር ባለውለታዎች መሆናችው ተገለጸ::
የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ፣ የዲስትሪክት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች 'መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት' በሚል ርዕስ እየሰጡ ባለው ስልጠና ላይ እንደገለፁት የኢትዮጵያ መሐንዲሶች አስቸጋሪውን መልክዐ ምድርና የአየር ጠባይ ተቋቁመው ተራሮችን እየቦረቦሩና አለቶችን እየሰነጠቁ ሀገርን ባለመንገድ እና ድልድይ ህዝቡን ደግሞ ባለሀገር እያደረጉት እንደሆነ ተናግረዋል::
የሚዲያው ዘርፍ እንችላለን የሚለው ቃል እና አመለካከት እንደ ወረርሽኝ እንዲስፋፋ መስራት እንደሚጠበቅበት እና ለዚህም እንደ ህዳሴ ግድብ ያሉ ቋሚ ምስክሮቻችንን አጉልቶ ማስተዋወቅ እና ማጋራት እንደሚገባም ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል::
ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ሲጠቃለል የኢዜአ ተወካይ አቶ ተፈራ በሰጡት አስተያየት ስልጠናው ለተቋሙ አመራሮች እና ባለሙያዎች መሰረታዊ ለውጥ እንደሚያመጣ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል::
በማጠቃለያው ስልጠና ላይ የሙያ ፍቅርን ጨምሮ የትዕግስትን ኃይል እና የታጋሾችን የድል አክሊል የሚያሳዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ታሪኮች በማሳያነት ቀርበው ሰፊ ውይይቶች ተደርገዋል::
+3
"ተስፋ ማድረግ ይጎዳል ፣ ተስፋ መቁረጥ ይገድላል" ዛዲግ አብርሃ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 10 ቀን 2017 (አፍሌክስ):- ተስፋ ማድረግ እንደሚጎዳ ፣ ተስፋ መቁረጥ ግን እንደሚገድል የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) አመራሮች እና ጋዜጠኞች በሰጡት ስልጠና ላይ እንደገለጹት ተስፋ የሚያስቆርጡ ነገሮች ሲያጋጥሙ የአዕምሮን የማገገም ችሎታ በመጠቀም ተስፋ ማድረግን መለማመድ አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመው ፣ የሙያ ፍቅርን እንደ ዓላማ ማስፈፀሚያ መሳሪያ በመጠቀም ተስፋ ተሟጦ እንዳያልቅና እንዳይጠፋ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል::
"የሙያ ፍቅር ከዓላማ ፣ ከስቃይ እና ከፅናት ማህፀን ይወለዳል" የሚሉት አቶ ዛዲግ የሚዲያ አመራሮች እና ባለሙያዎች የሙያ ፍቅርን ወደ መቃብር ከሚያወርዱ ተግባራት መራቅ እንደሚገባቸው አስታውሰው ፣ ቅጥ አልባ መዘግየት ፣ ግብረ መልስ አልባ ተግባር ፣ ትችት እና ራስን ከሌላ ጋር ባልተገባ መልኩ ማወዳደር ፣ ድካምና መሰልቸት ፣ የተደበቀ እና ያመረቀዘ ቁስል እንዲሁም የማይመች የስራ አካባቢ የሙያ ፍቅርን እና ተስፋን የሚገድሉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል::
የሙያ ፍቅር እንደ እሳት እንደሆነና በቂ እንክብካቤ እና ክትትል ካልተደረገለት በንፋስ እንደሚወሰድ ያስታወሱት አቶ ዛዲግ ፣ ጋዜጠኞች የህይወት ጥሪያቸውን እና ህልማቸውን ከዓላማቸው ጋር አስተሳስረው በትክክለኛው መስመር ከተጏዙ አትራፊ ይሆናሉ ብለዋል::
ጋዜጠኞች የአንድ ሀገር የመጀመሪያዎቹ የታሪክ ፀሀፊዎች መሆናቸውን ተረድተው ሀገራዊ ትርክትን በሚሻገር መልኩ መቅረፅ ፣ ማከማቸት እና ማሰራጨት ከቻሉ እንደ ታሪክ ባለሙያ ሲዘከሩ እና ሲታወሱ እንደሚኖሩ ያመላከቱት አቶ ዛዲግ ፣ የሚሰሩ ዘገባዎች እና ዜናዎች በሀቅ ላይ የተመሰረቱ እና ዜጎች በተስፋ እንዲኖሩ የሚያግዙ እንዲሁም ቅቡልነት ፣ ግልፅነት እና አካታችነት ያላቸው ተቋማት እንዲገነቡ መሰረት የሚጥሉ መሆን አለባቸው ብለዋል::
ሚዲያው በህዝብ እና መንግስት መካከል መተማመን እንዲዳብር ፣ ተቋማት እንዳይበላሹና እንዳይላሽቁ ፣ የእውነት መሰረተ ልማት እንዲስፋፋ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት በስልጠናው ላይ ተነስቷል::
+3
"ክብራቸውን ጠብቀው ፣ ወኔን ታጥቀው ፣ ለህዝብ ዓላማ ቅድሚያ ሰጥተው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች ሀገር ገንቢዎች ናቸው" ዛዲግ አብርሃ የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 09 ቀን 2017 (አፍሌክስ): ክብራቸውን ጠብቀው ፣ ወኔን ታጥቀው ፣ ለህዝብ ዓላማ ቅድሚያ ሰጥተው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች የሀገር ገንቢዎች እንደሆኑ ተገለፀ::
የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) አመራሮች እና ጋዜጠኞች እየሰጡት ባለው ስልጠና ላይ እንደጠቀሱት በሀገረ መንግሥት እና ውጤታማ ተቋማት ግንባታ ሂደት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰው ፣ ዘርፉ የሚያስፈልገውን የሙያ ክብር ጠብቀውና ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለህዝብ ዓላማ ቅድሚያ ሰጥተው ከሰሩ በሀገር ግንባታ ውስጥ የማይተካ ሚና ይኖራቸዋል ብለዋል::
የሚዲያ ባለሙያዎች ሀገርን እና ሰውነትን ካስቀደሙ ድልድይ ገንቢዎች ሆነው አንድነትን ያዋልዳሉ ፣ የጋራ ትርክት መሀንዲስ ሆነው ፅንፈኝነትን ይታገላሉ የሚሉት አቶ ዛዲግ ፣ ሚዲያው ዜጎች ራሳቸውን ከተሳሳተ እና ከተዛባ መረጃ እንዲጠብቁ በማድረግ ብሄራዊ ማንነት የሚገነባበትን ጡብ ማቀበል እንዳለበት ተናግረዋል::
ያልተሟላ እና ሁሉን አቀፍ የሚዲያ ስርዓት ሲጏደል ፅንፈኝነት እንደሚነግስ ፣ ፍራቻ እንደሚስፋፋ፣ ጥላቻ ነብስ እንደሚዘራ ፣ ፍትህ ጥያቄ ውስጥ እንደሚገባ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ፣ የሚዲያ አመራር እና ባለሙያው ለብሔራዊ ጥቅም ቀጣይነት እና ዘላቂነት ትኩረት ሰጥተው ከሰሩ መጪውን ጊዜ እንደ ዕድል ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ ተናግረዋል::
ብሔራዊ ትርክትን ከህዝብ ጥቅም አንፃር ለመበየን ከፍተኛ ሚና ካላቸው ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አንዱ መሆኑን የጠቅሱት አቶ ዛዲግ ፣ እንደ ኢዜአ ያሉ ተቋማት የመረጃ ምንጭ ብቻ ሳይሆኑ የመረጃ ሉዓላዊነትን እንደሚያስጠብቁ ፣ የሀገራችን ምስል በዓለም አቀፍ ደረጃ ቅርፅ እንዲይዝ እንደሚያደርጉ እና የቀውስ ጊዜ አይበገሬ የሽግግር አጀንዳ ቀራጭ ናቸው ብለዋል::
ስልጠናው የሀገራችንን ነባራዊ እውነታ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ጋር ባጣጣመ መልኩ ለሁለተኛ ቀን ቀጥሎ የዋለ ሲሆን ሰልጣኞች በቡድን ውይይት ሀሳብ ተለዋውጠዋል::
+6
"መጪውን ጊዜ ከሚዲያ እና ጋዜጠኝነት ሙያ አንፃር ስናየው ያልተፃፈ ዘመን ነው ፣ ከዚህ በፊት ያልተከሰተ ስጋትና አጋጥሞ የማያውቅ ዕድልን ይዞ እየመጣ ነው" አቶ ዛዲግ አብርሃ የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 08 ቀን 2017 (አፍሌክስ): መጪው ጊዜ ከሚዲያ እና ጋዜጠኝነት ሙያ አንፃር ሲታይ ያልተፃፈ ዘመን እንደሆነና ከዚህ በፊት ያልተከሰተ ስጋትና አጋጥሞ የማያውቅ ዕድልን ይዞ እየመጣ እንደሆነ የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለፁ::
አቶ ዛዲግ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)
አመራሮች እና ጋዜጠኞች ስልጠና ሲሰጡ እንደተናገሩት መጪው ዘመን ለሚዲያ ኢንዱስትሪው ፈተና እና ስጋትን አጣምሮ ይዞ እንደሚመጣ አመላክተው ፣ ለአዳዲስ የሰው ሰራሽ አስተውሎቶች እና ፈጠራዎች ባይተዋር ባለመሆን የድህረ እውነትን ዘመን መሻገር እንደሚገባ ጠቁመዋል::
በድህረ እውነት ዘመን እውነት የሚፎካከረው ከውሸት ጋር ብቻ ሳይሆን ከስሜት ጋር ነው ያሉት አቶ ዛዲግ ፣ በስሜት ማዕበል የሚናጠውን የማህበራዊ ሚዲያ ኢንዱስትሪ በተሟላ እና ሁሉን አቀፍ በሆነ የሚዲያ ስርዓት በመተካት መጪውን ዘመን መዋጀት ይገባል ብለዋል::
+5
“ የብሔራዊ ማንነት ትርክትን የሚመሩ እና የሚቆጣጠሩ የሚዲያ አመራሮች ታሪክ እንዲቀየር ምክንያት ይሆናሉ" አቶ ዛዲግ አብርሃ የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 07 ቀን 2017 (አፍሌክስ):- የብሔራዊ ማንነትን ትርክት የሚመሩ እና የሚቆጣጠሩ የሚዲያ አመራሮች ታሪክ እንዲቀየር ምክንያት እንደሚሆኑ የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለፁ::
ፕሬዚደንቱ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) አመራሮች እና ጋዜጠኞች ስለ ትርክት ሀይል ስልጠና ሲሰጡ እንደገለፁት የሚዲያ አመራሮች ገዥ ትርክትን ሲመሩ እና ሲቆጣጠሩ በታሪክ ምዕራፍ ላይ የራሳቸውን በጎ አሻራ እያሳረፉ መሆኑን ጠቅሰው ሚዲያው ገዥ ትርክቶችን በስጋ እና ደም በማዋቀር መፃኢው ጊዜ በተስፋ እንዲሞላ የማድረግ ሀላፊነቱን እንዲወጣ አስታውሰዋል::
ሀገር ከድህነት ወደ ብልፅግና እንድትሸጋገር የሚዲያ አመራሩ እና ጋዜጠኛው የጋራ አሻራ በማበጀት ገዥ ትርክትን ወደ አዲስ አድማስ በመውሰድ የሚኖራቸውን ሚና የጠቆሙት አቶ ዛዲግ አመራሩ እና ባለሙያው አሁን ያለውን ትርክት ማዳመጥ በእውነታዎች መካከል ያለውን ተቃርኖ መረዳት አዲስ ትርክት ማዋቀር የተዋቀረውን ገዥ ትርክት በተከታታይ እና ቀጣይነት ባለው መልኩ ማቅረብ እንዲሁም አካታች በሆነ መልኩ ሌሎችን በመጋበዝ የትርክቱ አካል እንዲሆኑ መስራት ይገባቸዋል ብለዋል::
ዋልታ ረገጥ አስተሳሰብ እና አመለካከት በናኘበት በዚህ ዘመን የሚዲያ አመራሩ እና ባለሙያው የትርክት መሳሪያውን በአግባቡ መረዳት ይኖርባቸዋል የሚሉት አቶ ዛዲግ ገዥ ትርክትን ከጠላት ለመጠበቅ እና ለመከላከል ስትራቴጂ ነድፎ መስራት ተገቢ እንደሆነና የራሳቸውን ትርክት ከጥቃት ያልተከላከሉ እና በአግባቡ ያልሸጡ ሀገራት በሌላው የሀሰት ትርክት ለመኖር እንደሚገደዱም አቶ ዛዲግ ገልጸዋል::
የኔዘርላንድ መልቲ ፓርቲ ዴሞክራሲ ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ተወካይ ይነበብ ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥በኢትዮጵያ ጠንካራ የመድብለ-ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ የቴክኒክና የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል።
በመድብለ ፓርቲ ስርዓት ውስጥ እየተገነባ ላለው ዴሞክራሲ ስርዓት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፥ከልህቀት አካዳሚው ጋርም በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በዛሬው ዕለት መፈራረማቸውን ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ጠንካራ የመድበለ-ፓርቲ ሥርዓት በመገንባት ሂደት በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብረሃ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በዚህ ረገድ ተቋማቱ በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ-ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የተፈራረሙትን ስምምነት ውጤታማ ለማድረግ አቅማቸውን አሟጠው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
+4
በኢትዮጵያ የዳበረ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን አቅም ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቷል
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (አፍሌክስ)፦በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም ማጎልበት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣የአፍሪካ አመራር ልዕቀት አካዳሚና የኔዘርላንድስ መልቲ ፓርቲ ዴሞክራሲ ኢንስቲትዩት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የሦስትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በመግባቢያ ስምምነቱ ሥነ-ሥርዓት ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለማዳበር በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አመራርና አባላት አቅም መገንባት ያስፈልጋል።
ለዚህ ደግሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራር አባላትን አቅም ማጎልበት የሚያስችሉ ሥልጠናዎች ማዘጋጀት ወሳኝ ነው ብለዋል።
ምክር ቤቱ ከዚህ አኳያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋርም መስራቱ በዕውቀት የሚመራ አመራር ለመገንባት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዳበረ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ የልህቀት አካዳሚው ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል።
ለዚህ ደግሞ አካዳሚው በአገር በቀል ዕውቀት የታገዘ የፖለቲካ ፓርቲዎች የስልጠና መመሪያና የአመራር ልማት ግንባታ እቅድና ስትራቴጂ ማዘጋጀቱንም ገልጸዋል።
+3
ሠራዊቱ በየጊዜው በሚከፍለው መልከ ብዙ መስዋዕትነት ሀገርን ማፅናት ችሏል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ
ዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ሀምሌ 04 ቀን 2017 ዓ.ም
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በማዕከላዊ ዕዝ ጊቤ ማሠልጠኛ ማዕከል ተገኝተው ለሠልጣኝ ታክቲካል አመራሮች የአመራርነት ስልጠና ሰጥተዋል።
ሠራዊቱ በየጊዜው በሚከፍለው መልከ ብዙ መስዋዕትነት ሀገርን ማፅናት ችሏል ያሉት ባለ ስልጣኑ አመራርነት ሳይንስን ከተሞክሮ ጋር አጣምሮ መስራትን የሚሻ በመሆኑ በስልጠና የምታገኙትን የአመራርነት ትምህርት ከተሞክሯችሁ ጋር በማዳመር ልትጠቀሙበት ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
አቶ ዛዲግ ጨምረውም ማዕከላዊ ዕዝ የበሳልና ቆራጥ አመራሮች መገኛ መሆኑን አውስተው ይሄንኑ በማስቀጠል እንደ ዕዝ የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት የተጀመረውን ትጋትና እንቅስቃሴ አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።
In her presentation, she elaborates on the essence of public diplomacy, its defining characteristics, and strategies for effectively managing soft power in diplomatic efforts.
Additionally, Mr. Roger Tirazona from the Malta Ministry for Education, Sport, Youth, Research and Innovation provides valuable insights into ethics, sharing Malta's journey in ethics education.
His discussion emphasizes the role of ethics in diplomacy and the necessity of fostering ethical standards in international relations.
The event is designed to be interactive, featuring engaging question-and-answer sessions that encourage participants to delve deeper into the topics presented.
This format allows for lively discussions, enabling attendees to explore the nuances of public diplomacy and ethics in a collaborative environment.
Overall, the lecture serves as a significant platform for knowledge exchange, reinforcing the importance of public diplomacy and ethical considerations in the field of international relations.
The collaboration between AFLEX, the Embassy of Malta, and the EU delegation contributes to a richer understanding of these crucial topics among attendees.
+4
AFLEX Hosts Engaging Lecture on Public Diplomacy and Ethics
Sululta - 9 June, 2025 (AFLE) - AFLEX conducted a pivotal training session, focusing on the themes of public diplomacy and ethics.
The event is organized in collaboration with the Embassy of Malta to Ethiopia and the EU delegation to Ethiopia, highlighting the significance of international cooperation in diplomatic education.
The lecture attracts a diverse audience, including AFLEX staff, H.E. Mr. Ronald Micallef, the Ambassador of Malta to Ethiopia, H.E. Mrs. Sofie From-Emmesberger, the Ambassador of the European Union to Ethiopia, and delegates from the Mediterranean Academy of Diplomatic Studies (MEDAC).
Their presence underscores the importance of the topics being discussed and the collaborative efforts in fostering diplomatic skills.
Ms. Lourdes Pullicino, Senior Academician of Diplomatic Studies at MEDAC, delivers an informative lecture titled "Public Diplomacy: Increasing Influence with Limited Resources."
+3
አፍሌክስ የጥናታዊ ጽሁፎች ዎርክሾፕ አካሄደ
ሱሉልታ/ ሐምሌ 1/2017 ዓ.ም/ (አፍሌክስ) – የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (አፍሌክስ) የውስጥ ግምገማ ሂደቱ አካል የሆነውን የጥናታዊ ጽሁፎች ማረጋገጫ ዎርክሾፕ ዛሬ አካሂዷል።
በዎርክሾፑ የጥናትና ምርምር፣ የአመራር ልማት ስልጠና፣ የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት እና የአይዲዬሽን ዲፓርትመንቶችን ጨምሮ ከተለያዩ የስራ ክፍሎች የተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።
የዎርክሾፑ ዋና ትኩረት በአፍሌክስ ተመራማሪዎች የተካሄዱ 12 ጥናታዊ ጽሁፎችን ተመልክቶ የህትመት ማረጋገጫ መስጠት ነበር።
ይህ የአቻ ግምገማ ሂደት የምርምር ጽሁፎቹ በአጥኚዎቹ የቀረቡበትን እና የጥያቄና መልስ ክፍለ ጊዜን ያካተተ ሲሆን፣ ገንቢ አስተያየቶች የተሰጡበትን ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
የጥናቶቹ ጭብጥ በዋናነት በፖሊሲ አጀንዳዎች ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን፣ ይህም አፍሌክስ ጠቃሚና ተፅዕኖ ፈጣሪ ምርምርን እንደ ዋና ተግባር ለማካሄድ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያንፀባርቅ ነው።
አፍሌክስ የውስጥ ባለድርሻ አካላትን በዚህ ሂደት በማሳተፍ የምርምር ጥረቶቹን ጥራት እና ተግባራዊነት ለማሳደግ ያለመ ሲሆን፣ ይህም በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ለተሻሉ የአመራር ልምዶች አስተዋፅኦ ያደርጋል።
🇪🇹 የሀገር ፍቅር ተራሮችን ያንቀጠቅጣል መጪውን ጊዜ ይገነባል:: ያለፈውን መጥፎ ጊዜ እንድንረሳ ያደርጋል
🇪🇹 ለሀገር መስዋእት ስንሆን ከመረሳት ይልቅ ለዘለዓለም እንታወሳለን
🇪🇹 በሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ መስመር የለቀቀ ነገር ካለ እንዲስተካከል መጠየቅ የሀገር ፍቅር መገለጫ ነው
🇪🇹 ራሳቸውን ለሀገራቸው ሲሉ መስዋዕት ያደረጉ ሰዎች ደም ዘር ነው ይዘራል ፍሬም አለው ያፈራል::
🇪🇹 የሀገር መሰረታዊ እመርታ መስዋዕት ለመክፈል በተዘጋጁ ትውልዶች የሚረጋገጥ ነው
🇪🇹 ፍቅር ፅናት እና አይበገሬነት አንዱ የሌለውን ሌላው እያሟላ እና እየተጋገዙ የሀገር ፍቅርን ከፍታ ያሰምራሉ
🇪🇹 የሀገር ፍቅር የወለደው ፅናት ሲኖር ዜጎች በአንድ እጃቸው መሳሪያ በሌላ እጃቸው ሞፈር ይጨብጣሉ
የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን አመራሮች እና ባለሙያዎች በአድዋ መታሰቢያ ሙዝየም ውስጥ እየሰጡ ባለው የአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ ስለ #ሀገር_ፍቅር ካነሷቸው ሀሳቦች :-
🇪🇹 በሀገር ግንባታ እና በብሔረ መንግስት ግንባታ ሂደት የሀገር ፍቅር ቁልፍ ሚና አለው
🇪🇹 ለሀገር ህልውና እና ማበብ ፍቅር አስፈላጊው ነገር ነው
🇪🇹 የሀገር ፍቅር ከአድናቆት የተሻገረ ራስን እና አንድያ ህይወትን ለሀገር ጥቅም እስከ መስጠት የሚዘልቅ ነው
🇪🇹 ለሀገር ጥቅም ሲባል የግል ምቾትን ሀብትን ስልጣንን እና ደህነትን መተው የሀገር ፍቅር ማሳያ ነው
🇪🇹 የሀገራችንን አርበኞች ጨምሮ እነ መሀተመ ጋንዲ ኔልሰን ማንዴላ አብርሀም ሊንከን በሀገራቸው ጥልቅ ፍቅር ወድቀው በብሔራዊ ፍቅር ተመርተው ሀገራቸውን ነፃ አውጥተዋል
🇪🇹 ሀገራችን በነብሳቸው ተወራርደው ደማቸውን ያፈሰሱ አጥንታቸውን የከሰከሱ አርበኞች ሀገር ናት
🇪🇹 የሰው ልጅ ከራሱ በላይ ለሆነ ነገር መኖርን እና አሻራውን ትቶ ማለፍ ካሻው የሀገር ፍቅር ያስፈልገዋል
🇪🇹 የሀገር ፍቅር ያላቸው ሰዎች ሀገራቸውን ሲወዱ በመውደዳቸው ምክንያት የሚደርስባቸውን ስቃይ ተቋቁመው ላፈቀሩት ነገር ቅድሚያ ይሰጣሉ
🇪🇹 ሀገራት እንደ ሀገር ሳይፈርሱ የሚቆዩት ዜጎቻቸው ለጋራ ዓላማ ባላቸው ፍቅር እና ራሳቸውን ባስገዙበት የፍቅር ልክ ነው
🇪🇹 የሀገር ፍቅር የስሜት ማዕበል የሚንጠው ሳይሆን የህይወት ዘመን ፍቅር ነው
🇪🇹 ለሀገር የሚኖር ፍቅር ደካማና ልፍስፍስ አይደለም:: ለረጅም ጊዜ የሚቆይና አንድነትን የማምጣት ሀይሉ ከፍተኛ ነው
🇪🇹 የሀገር ፍቅር ካለ የማይተዋወቁ ሰዎች በዓላማ ተሳስረው ለጋራ ግብ ስኬት ይሰለፋሉ:: ለቆሙለት ዓላማም ይሰዋሉ
+9
የአፍሌክስ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በአፋር ክልል ተገኝተው ለክልሉ የመንግስት እና የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጡት የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ::
አፋር ሰመራ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ):- በአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ክቡር ሀጂ አወል አርባ በይፋ የተጀመረውና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ተጠናቋል::
በስልጠናው ላይ በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ አቶ መሐመድ ሁሴንን ጨምሮ የክልሉ የመንግስት እና የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በስድስት የተለያዩ ርዕሶች ላይ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሰልጥነዋል::
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ክቡር ሀጂ አወል አርባ የተገኙ ሲሆን አቶ ዛዲግ አብርሃ ለሰጡት የአመራር ልማት ስልጠና አመስግነው የአፍሌክስ እና የክልሉ መንግስት ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል:: አቶ ዛዲግ ላበረከቱት አስተዋጽዖም ልዩ ሽልማት አበርክተዋል::
የአፍሌክስ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ አፍሌክስ የተቋቋመበትን ዓላማ ለማሳካት እየሰሩ እንደሆነ አስታውስው እስካሁንም በዲላ በሀረር በድሬዳዋ በሱማሌ በሲዳማ በአዲስ አበባ በአማራ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ለሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል::
አፍሌክስ የጀመረውን የስልጠና መርሃግብር በሌሎችም ክልሎች እና ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚቀጥል የጠቀሱት አቶ ዛዲግ የሁሉንም ፍላጎት ለማስተናገድ በስፋት ዝግጅት እንደተደረገም አስታውሰዋል::
