cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

✿ ቅዱሳት አንስት ✿

"የቅዱሳንን ዜናቸውን ለመናገር ፍቅር ያስገድደኛል::" ---አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ . . . . ༺ፀሎታቸው በረከታቸው አይለየን!༻

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
189Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

📯ቃለ እግዚአብሔርን ከልጅነታቸው ጀምረው እየተመገቡ የክርስቶስ ፍቅር ያደረባቸው እማሆይ እነሆ 👑👑👑👑👑👑👑👑👑👑👑👑👑👉 በደብረ ዲማ ቅዱስ ጊዎርጊስ ቅኔ ተምረው አስመስክረዋል 👉በባህርዳር የአብነት ትምህርትቤት የአቋቋም ትምህርት ተምረዋል 👉በዘመናዊ ትምህርት የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ተመርቀዋል 👉አሁን በ 2014 በማዕረግ ማስተርሳቸውን ያዙ አሁን በቅስት ስላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ በማስተማር ላይ ይገኛሉ እኛ ማናቃቸው ስንት አሉ መሰላችሁ እንደዚ አይነት እንቁዎች ❤በእድሜ በፀጋ ያቆይልን👏👏👏
Show all...
እመቤታችንን ንጽሕት፣ ጽንዕት፣ ክብርት፣ ልዩ ትባላለች። ይህም፡- "ንጽሕት" ስንል፡- ሌሎች ሰዎች (ቅዱሳን) ቢነጹ ከገቢር፣ ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም፡፡ እርሷ ግን ከነቢብ፣ ከገቢር፣ ከኃልዮ ንጽሕት ናት፡፡ "ለመኑ ተውኅቦ ተደንግሎ ኅሊና ለመላእክትሂ ኢተክህሎሙ" ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም" እንዲል፡፡ (ተአምረ ማርያም) "ጽንዕት" ስንል:- ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በኋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው:: እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ ጊዜ ጸኒስ ድኅረ ጸኒስ ቅድመ ወሊድ ጊዜ ወሊድ ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና:: "ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት ቅዱስ ያሬድ "ወትረ ድንግል ማርያም" ማርያም ዘለዓለማዊት ድንግል ናት" እንዳለ፡፡ (መጽሐፈ ቅዳሴ) "ክብርት" ስንል፡- ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው እመቤታችንን ግን የምናከብራት "የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና፡፡ "ልዩ" ስንል፡- ከእርሷ በቀር እናት ሆና ድንግል እመቤት ሆና አገልጋይ የሆነች በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና፡፡ በዚህም እመቤታችንን ንጽሕት፣ ጽንዕት፣ ክብርት፣ ልዩ እንላታለን፡፡
Show all...
Show all...
በፍጥረት ረቡዕ ቀን ምን ተደረገልኝ? ለእመቤታችን ምሳሌነቱ || ሊቀ ማእምራን መምህር ዘበነ ለማ

Show all...
በፍጥረት ማክሰኞ ቀን ምን ተደረገልኝ? ሊቀ ማእምራን መምህር ዘበነ ለማ

Show all...
በፍጥረት ሰኞ ቀን ምን ተደረገልኝ? ሊቀ ማእምራን መምህር ዘበነ ለማ

ከእመቤታችን የዘመናችን ድንቅ ተአምራት አንዱ (በፈረንጆች ጥር/2014 የተደረገ ድንቅ ተዓምር) ቅልጥ ያለ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ባለባት ሶርያ ውስጥ አንድ የሴቶች ገዳም አለ። አክራረሪዎች ገዳሙን ለማውደም ሮኬቶችን ተኮሱ። የተኩስ ንውጽውጽታም ገዳማውያኑን ለሞት እንደተቃረቡ አረዳ። ነገር ግን ከፍርሃት ሰቀቀን ባይላቀቁም ምንም ሳይሆኑ ቀሩ። ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ምን እንደሆኑ ለማየት የመጣው አንድ መኮንን መነኮሳያቱን ደኅና ማግኘቱ አስደንቆት ሲጠይቃቸው የሆነውን አስረዱት። እርሱም ተኩሱን አይቶ ስለነበር ተዘዋውሮ ሲመለከት ሮኬቱ ሳይፈነዳ መቀመጡን አይቶ ደነገጠ። ገዳማውያቱ እናቶችም አይተው ደነገጡ፤ ፈሩም። በዚያው ቅጽበት ግን አንድ ነገር ድንገት ታየ። ሰማያዊ ቀሚስ የለበሰች፣ ግርማዋ የሚያስደንቅ ሴት ከሰማይ ወረደች እና ሁሉም እያዩ ተተኩሶና ገዳሙ ላይ ወድቆ ያልፈነዳውን የሮኬት ጥይት አንስታ ወሰደችው። መኮንኑ ተደነቀና ማን ነች ሲል መናኞቹን ጠየቃቸው። ከእመቤታችን ውጭ ሌላ ሴት ልትሆን እንደማትችል መለሱለት። እመቤታችን ሆይ በእኛ ሀገርም ደራሽ ለሌቸው ሁሉ ድረሽላቸው። ጌታችን ሆይ ከእናትህ ጋር ስለመሰደድህ ብለህ ስደቱንና መከራውን መቋቋም ለሚያቅታቸው ራራላቸው፤ የጨካኞችን ልቡና መልሰህ ሕዝቡ በፍቅር እንዲኖር እርዳን፤ አሜን። (ከዲያቆን ብርሃኑ አድማስ አንለይ የተወሰደ) Source: (http://www.pravoslavie.ru/english/67980.htm)
Show all...
Miracle of Holy Theotokos in the Christian town of Saidnaya

The Miraculous incident took place last month when a rebel group fired rockets at one of the monasteries.

Show all...
የአጋንንት ሓይማኖት / ሊቀ ሊቃውንት ሥሙር አላምረው

ሊቀ ሊቃውንት ሥሙር አላምረው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ስብከት ethiopian orthodox tewahedo sibket, orthodox sibket orthodox mezmur orthodox new mezmur ኦርቶዶክስ ስብከት ኦርቶዶክስ Deacon henok ...