504
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
504
ለገርጂና ጉለሌ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ተማሪዎች በሙሉ
በኮቪድ - 19 ወረርሽኝ ምክንያት የመደበኛ የመማር ማስተማሩ ሥራ መቋረጡ የሚታወስ ነው፡፡ ትምህርቱ ከተቋረጠበት ጊዜ አንስቶ ተማሪዎቻችን በየቤታችሁ ሆናችሁ ትምህርቱን በኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ስም በከፈትነው የቴሌግራም ቻናላችን ኖቶች፣ አሳይመንቶች፣ ወርክሽቶች ወዘተ እንዲደርሳችሁ ማድረጋችን ይታወቃል፡፡
በተያዘው ዓመት 2013 ዓ.ም ተማሪዎች በየክፍል ደረጃቸው በቴሌግራም ቻናላችን በኩል ልዩ ልዩ የትምህርት ይዘቶችን አዘጋጅተን በመላክ ላይ እንገኛለን በመሆኑም ሁሉም ተማሪዎቻችን ይህንን በማወቅ እንደሚላክላችሁ የትምህርት ይዘት መመሪያ መሠረት ማለትም ኖት ከሆነ በየደብተሮቻችሁ መገልበጥን የቤት ሥራዎችን በየደብተሮቻችሁ ላይ መገልበጥና በትጋት መሥራት የሚገባችሁ መሆኑን ማሳሰብ እንወዳለን፡፡
የተማሪዎች ወላጆችም ተማሪ ልጆቻችሁ በቴሌግራም የምንልክላቸውን የትምህርት ይዘቶች በሚሰጣቸው ትዕዛዝ መሠረት ትኩረት ሰጥተው በየደብተሮቻቸው ላይ እንዲሠሩ እንድታበረታቱዋቸው አበክረን ልናሳስባችሁ እንወዳለን፡፡
ኆኀተ ጥበብ አክሲዮን ማህበር
ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤ
504
ለኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ወላጆች በሙሉ ት/ቤታችን በጥቅምት 30/2013ዓ.ም ይከፈታል ተብሎ እንደነበር ይታወሣል፡፡ሆኖም የመክፈቻው ጊዜ በመራዘሙ ትምህርት በተለያየ የኤሌክትሮኒክስ ዘዴ መስጠት እንዳለት ታምኗል፡፡ በመሆኑም ለአሁኑ በቴለግራም ቻናላችን በየክፍል ደረጃዎችየት/ት ማስታወሻና መልመጃዎች የሚተላለፍ በመሆኑ ልጆችትምህርቱን እንድከታተሉና እንድያነቡመልመጃዎችን እንድሠሩ ክትትልና እገዛ እንድታደርጉላቸው እናሳስባለን፡፡ ት/ቤቱ
