en
Feedback
EPS Grade-2

EPS Grade-2

Open in Telegram

EPS Grade 2 Resource Center

Show more
504
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
photo content

photo content

ማስታወቂያ ለገርጂ፣ ጉለሌና ጉርድ ሾላ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤቶች የተማሪ ወላጆች በሙሉ የ2014 ዓ.ም የሁለተኛው ኳርተር የትምህርት አገልግሎት ክፍያ የሚከናወነው ከህዳር 27 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 11 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ መሆኑን አውቃችሁ ክፍያውን በወቅቱ እንድትከፍሉ እናሳስባለን፡፡ ኆኅተ ጥበብ አ.ማ (ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት )

ማስታወቂያ በገርጂና በጉለሌ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤቶች በ5ኛ፣6ኛ፣7ኛ፣9ኛ፣10ኛ እና 11ኛ ክፍል ልጆቻችሁን በማስተማር ላይ ለምትገኙ ወላጆች በሙሉ በዚህ በያዝነው ዓመት ከዚህ ቀደም እንሰጥ የነበረውን ነገር ግን ለጥቂት አመታት ተቋርጦ የነበረውን የቅዳሜ ማጠናከሪያ ትምህርት ለመጀመር እቅድ ይዘናል፡፡ ይሄንኑ አስመልክቶ በት/ቤቶቹ በኩል ልጆቻችሁን ለማስተማር የምትፈልጉ ወላጆች ፍላጐታችሁን እንድታሳውቁን በሚል በልጆቻችሁ በኩል ደብዳቤ ልከን ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት በተለያዩ የክፍል ደረጃዎች ልጆች ያላቸው ወላጆች ለማስተማር ፈቃደኝነታቸውን አሳውቀውናል፡፡ ይሁን እንጂ አሁንም ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ወላጆች ፍላጐታቸውን ያልገለፁልን ስለሆነ ልጆቻችሁን በማጠናከሪያ ትምህርቱ እንዲሳተፉ የምትፈልጉ ከሆነ ከህዳር 6 - ህዳር 9 ቀን 2014 ዓ.ም በየት/ቤቶቹ በመቅረብ ማረጋገጫ እንድትሰጡ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ ኆኀተ ጥበብ አክሲዮን ማህበር (ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት)

photo content

ማስታወቂያ በኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት (ገርጂ ቅርንጫፍ) ለ2014 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ከመዋዕለ ህፃናት እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡፡ የ2014 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ሰኞ ጥቅምት 1 ቀን 2014 ዓ.ም የሚጀመር ስለሆነ አስፈላጊውን የኮቪድ ፕሮቶኮል እና የትምህርት ቤቱን የተማሪዎች የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) በማሟላት በዕለቱ ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ በት/ቤት በመገኘት ትምህርታችሁን እንድትጀምሩ እናስታውቃለን። ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት(ገርጂ ቅርንጫፍ)

photo content

ማስታወቂያ በኢትዮ-ፓረንትስ ገርጂ፣ጉለሌናሐዋሳ ቅርንጫፍ ት/ቤቶች ነባር ተማሪዎች ወላጆች የሆናችሁ ለ2014 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ልጆቻችሁን እስካሁን ላላስመዘገባችሁ ወላጆች በሙሉ ለአዲሱ ትምህርት ዘመን የነባር ተማሪዎችንምዝገባ በተመለከተ በቂ የመመዝገቢያ ጊዜ የሰጠን ቢሆንም እስካሁን ድረስ ልጆቻችሁን እንዳላስመዘገባችሁ ከየት/ቤቶቹ ካሠባስብነው መረጃ ለመረዳት ችለናል፡፡ በዚሁ መሠረት በተለያዩ ምክንያቶች ምዝገባውን ሳታከናውኑት ቆያላችሁ የሚለውን ሃሳብ ከግምት ውስጥ በማስገባት የነባር ተማሪዎችን ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29 ቀን 2013 ዓ.ም ያራዘምን ስለሆነ የተሰጠውን ጊዜ ተጠቅማችሁ እንድታስመዘግቡ እያሳስብን በተጠቀሱት ቀናት ልጆቻችሁን ሳታስመዘግቡ ቀርታችሁ ቦታው በአዲስ ተመዝጋቢ ተማሪዎች ቢያዝ ሃላፊነቱን የምትወስዱ መሆኑን በአፅንኦት ማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ኆኅተ ጥ.አ.ማ

ቀን፡-19/12/2013 ዓ.ም. ማስታወቂያ በኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት (ገርጂ ቅርንጫፍ) የ2014 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 11 - 21/2013 ዓ.ም (የ9ኛ ክፍል ከነሀሴ 14 - 24, 2013ዓ.ም) ድረስ ባሉት ቀናት እየተካሄደ ስለሆነ የት/ቤት ክፍያ ትከፍሉ በነበረበት ባንክ እየከፈላችሁ ልጆቻችሁን በወቅቱ እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን። ት/ቤቱ

photo content

ቀን፡-17/12/2013ዓ.ም ማስታወቂያ በኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት (ገርጂ ቅርንጫፍ) የ2014ዓ.ም የትምህርት ዘመን የነባር 9ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 14 - 24/2013 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት እየተካሄደ ስለሆነ የት/ቤት ክፍያ ትከፍሉ በነበረበት ባንክ እየከፈላችሁ ልጆቻችሁን በወቅቱ እንድታስመዘግቡ እያሳሰብን የክፍያው ዝርዝር ከዚህ በታች ተያይዞ ቀርቧል። ት/ቤቱ

ቀን፡-17/12/2013ዓ.ም የነባር የጉለሌ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ወላጆች የ2014ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ 9ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 17 - 27/2013 ዓ.ም ድረስ ለማካሄድ ፕሮግራም ተይዟል፡፡በዚሁ መሰረት በተጠቀሱት ቀናት በአዋሽ ባንክ አለምፀሐይ ድልድይ ቅርንጫፍ ክፍያችሁን እንድታጠናቅቁ እናስታውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ፡-የትምህርት ዘመኑ የክፍያ ዝርዝር ከዚህ ቻናል ላይ ይመልከቱ፡፡ ት/ቤቱ

photo content

ማስታወቂያ በኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት (ገርጂ ቅርንጫፍ) ልጆቻችሁን ከ K.G - 12 ክፍል ድረስ እያስተማራችሁ ለምትገኙ ወላጆች በሙሉ የ 2014 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ነሐሴ 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ድረስ ሥለሚካሄድ ይህንን አውቃችሁ የት/ቤት ክፍያ ትከፍሉ በነበረበት ባንክ እየከፈላችሁ ልጆቻችሁን በወቅቱ እንድታስመዘግቡ እያሳሰብን የክፍያው ዝርዝር ከዚህ በታች ተያይዞ ቀርቧል። ት/ቤቱ

ማስታወቂያ በገርጂ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ከ1ኛ - 4ኛ ክፍል ልጆቻችሁን በማስተማር ላይ ለምትገኙ ወላጆች በሙሉ ድርጅታችን ለ2014 ዓ.ም ትምህርት ዘመን በጉርድ ሾላ አካባቢ በሻሌ ሆቴል ጀርባ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ጉርድ ሾላ ካምፓስ በሚል ከ1ኛ - 4ኛ ክፍል ድረስ ለማስተማር አዲስ ት/ቤት የከፈተ ስለሆነ በገርጂ ት/ቤት ከ1ኛ - 4ኛ ክፍሎች ድረስ ልጆቻችሁን በማስተማር ላይ የምትገኙ ወላጆች አዲስ የከፈትነው ት/ቤት በሁሉም ሁኔታ ከገርጂ ት/ቤት ጋር በተመሳሳይ የትምህርት ጥራት ደረጃ እና በነባር መምህራን እንዲሁም በጥሩ ሁኔታ በትምህርት ግብአት ተሟልቶለት የተከፈተ ት/ቤት ሲሆን አዲስ ተማሪዎችን በመመዝገብ ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ት/ቤቱ አቅራቢያችሁ ለሆኑ ከ1ኛ - 4ኛ ክፍል ድረስ ላሉ ወላጆች ልጆቻቸውን አዛውረው ማስተማር እንዲችሉ ዕድሉን አመቻችተናል፡፡ ስለሆነም ከትራንስፖርትም አንፃር ይቀርበናል አመቺ ነው የምትሉ ወላጆች ት/ቤቱ አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ቦታ ከመሙላቱ በፊት በእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እናሳስባለን፡፡ ኆኅተ ጥ.አ.ማ

5/12/2013 ዓ.ም ለጉለሌ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ወለጆች በ2014ዓ.ም የትምህርት ዘመን ልጆቻችሁን ከ7ኛ-12ኛ ክፍል ለማስተማር የምትፈልጉ ቦታ የለን 7ኛ,8ኛ እና 11ኛ ላይ ብቻ በመሆኑ አዲስና ነባር ወላጆች ምዝገባ ሐሙስ ነሐሴ 06/12/2013ዓ.ም እና ዓርብ 07/12/2013ዓ.ም ከቀኑ 6:30 ሰዓት ድረስ እንድታስመዝገቡ እናስታውቃለን፡፡ የት/ቤቱ አስተደደር

CamScanner 08-09-2021 15.33 - Page 2.pdf

ቀን፡-03/12/13ዓ.ም የነባር የጉለሌ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ወላጆች የ2014ዓ.ም የትምህርት ዘመን የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 5 - 15/2013 ዓ.ም ድረስ ለማካሄድ ፕሮግራም ተይዟል፡፡በዚሁ መሰረት በተጠቀሱት ቀናት በአዋሽ ባንክ አለምፀሐይ ድልድይ ቅርንጫፍ ክፍያችሁን እንድታጠናቅቁ እናስታውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ የትምህርት ዘመኑ የክፍያ ዝርዝር ከዚህ በታች የተዘረዘረ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ት/ቤቱ

ቀን፡-03/12/13ዓ.ም ለጉለሌ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ወላጆች በ2014ዓ.ም የት/ት ዘመን ልጆቻችሁን በት/ቤቱ ከኬጂ እስከ 6ኛ ክፍል (ከ3ኛ ክፍል በስተቀር) ለማስተማር የምትፈልጉ ነባርም ሆነ አዲስ ገቢ ምዝገባ ከነሀሴ 3 እስከ 5/2013ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ድረስ እንድታስመዘግቡ እናሳውቃለን፡፡ የት/ቤቱ አስተዳደር ጉለሌ

03/12/2013ዓ.ም ለጉለሌ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት ወላጆች በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ልጆቻችሁን በአፀደ ህፃናት (Pre-KG) ለማስተማር የምትፈልጉ ነባር ወላጆች ምዝገባ ከዛሬ ነሐሴ 3-5/2013ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት ድረስ እንድታስመዘግቡ እናስታውቃለን። የት/ቤቱ አስተዳደር